በሃገራችን ውስጥ እየተከሰተ ያለው የሰብኣዊ መብት ጥሰት እኛ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን የአለም ህዝብ ትኩረት በመሳብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በገሃድ እየታየ ነው:: ይህ የሰብኣዊ መብት ጥሰት የሚፈጸመው ቁልፍ ባለስልጣናት የፖሊስ መኮንኖችን በመጠቀም የህዝብን ሰላም ማደፍረስ እና ሽብር መንዛት የእለት ተግባራቸው አድርገው ተያይዘውታል::

ብልሃት በሌለው መልካም አስተዳደር የፖሊስ ባለስልጣናት የሚፈጽሙት ኢሰብኣዊ ተግባራት የህዝብን የመኖር ሁኔታ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከቶታል::ከጥያቄ ምልክትም አልፎ ከባባድ ወንጀሎች በህዝብ የእለት ተለት ሂደት ውስጥ ራሱን መንግስት ያሰኛው ሕወሓት እየፈጸመ ነው::የኢትዮጵያ ህዝቦች ሃይማኖት እና የፖለቲካ አስተሳሰብ ሳይለያቸው በጋራ የሚያቀርቡትን ጥያቄ
ላይ መልስ መስጠት እየተቻለ በጉልበት እና በማስፈራራት በመግደል እና በማሰር የሚመጣ ለውጥ የለም:; የህዝቦች ትግል በየፈርጁ እየቀጠለ ይሄዳል::ማንኛውም ህዝብ ለለውጥ እስከተነሳ ድረስ የሚሞትለት አላማ እንዳለውም ማሰብ ያስፈልጋል::

ባለስልጣናት ህጋዊ የሆኑ ዜጎች እንዲታሰሩ እንዲገላቱ የሚያደርጉት ከተጠያቂነት አያድናቸውም:; ህገመንግስታዊ መብቶችን በመጣስ ዜጎችን በአገራቸው እና ህጋዊ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማዋከብ ስልጣን ላይ ያለው ጁንታ ህግን እንደማያከብር ፍንትው አድርጎ ያሳየበት ህገወጥ ተግባር በተደጋጋሚ እያየን ነው:: ራሳቹህ ያወጣችሁትን ህግ ያላከበራችሁ እኛ እንዴት እናክብርላችሁ?? መጀመሪያ አንድ መንግስት ባለስልጣኖቹ ህግን አክብረው ለህዝቡ አርኣያ መሆን አለባቸው:: እያየን ያለነው ግን ሕግ አውጪው እና አስፈጻሚው አካል ህግን እየጣሰ መሆኑን ነው:: ስለዚህ ብልሃት አልባ ዲሞክራሲ በሞላባቸው እና የሰውን ልጅ መብት ትርጉም በማያቁ ባለስልጣናት ከመመራት ሞትን መርጦ መታገል አማራጭ እየሆነ ያለበት ዘመን ላይ ደርሰናል::

ከማናችንም ኢትዮጵያውያን በፊት ባለስልጣናት ህግ አውጪዎች ህግ አስፈጻሚዎች እና የጸጥታ ሃይሎች ለህግ ተገዢ ይሁኑልን::ለእኛም አርኣያ ይሁኑ::በጉልበት እና በሃይል በብልሃት አልባ ዲሞክራሲ ሽብር እየነዙ ሃገር አይመራም!!!ምንሊክ ሳልሳዊ

በወያኔ ዘርኝነት፤ ጎጠኝነትና ወደር የለሽ ጭቆና ከሁለት አስርተ አመታት በላይ ጀርባዉ የጎበጠዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ሁለት ወራት ዉስጥ በሁለት እጅግ አስቀያሚና ዘግናኝ በሆኑ የታሪክ ምዕራፎች ዉስጥ አልፏል። ለወትሮዉ በወርሃ ህዳርና ታህሳስ፤ ህዳር ሚካኤልንና የገና በዐልን እያከበረ አጆቹን ወደ ፈጣሪዉ የሚዘረጋዉ የኢትዮጵያ ህዝብ፤ ዘንድሮ ከእነዚህ ሁለት የቆዩ ባህሎቹና ወጎቹ ፈቀቅ ብሎ በሁለት ክብሩን ባዋረዱና ማንነቱን ጥያቄ ዉስጥ በከተቱ ከስተቶች ልቡ ቆስሎ ከራሱ ጋር ሲነታረክ ሰንብቷል። የፈጠረዉን አምላክ መለምን እንጂ በፈጣሪዉ አማርሮ የማያዉቀዉ የኢትዮጵያ ህዝብ . . . የሚያስብልኝ መንግስት እንደለሌለኝ አዉቃለሁ፤ አምላኬ ግን በፍጹም አይረሳኝም። ምነዉ ቅዱስ ሚካኤል አንተና ሰይፍህ እያላችሁ እንዴት እንዲህ ይደረጋል አንዴ . . . እያለ በምድራዊዉም በሰማያዊዉም መንግስታት ላይ የመረረ ጩኸቱን አሰምቷል።
በህዳር 2006 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ አገራቸዉ ዉስጥ የስራ ዕድል ተነፍገዉ ስራ ፍለጋ ወደ ሳዑዲ የተሰደዱ ወገኖቹ በሳዑዲ ፖሊስና ህዝብ ከፍተኛ በደል ሲፈጸምባቸዉ ተመልክቶ በኃዘንና በቁጭት ልቡ በግኗል። በተለይ ወንዶች ልጆቹ ፈለጊ እንደሌለዉ እንስሳ በየአደባባዩ ሲረገጡና ሲደበደቡ፤ ሴቶች ልጆቹ ደግሞ በየማጀቱ ሲደፈሩ ተመልክቶ ለህዝብና ለአገር ለሚያስቡ አስተዋይና ጨዋ መሪዎች ባለመታደሉ በባዕድ አገር ዉስጥ በደረሰበት ዉርደትና መከራ በአለም አቀፍ ደረጃ ጩኸቱን አሰምቷል።በዚሁ በ2006 ዓም በታህሳሰ ወር አጋማሽ ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ብርድ ልብስ ተጠቅልሎ የተጣለ የሰዉ ልጅ አጽም ቀርቶ በስመአብ ተብሎ የታረደ በሬ ስጋም ማየት በማይፈልግበት በገና ፆም ወቅት የገዛ ወገኖቹ አጽም በመንገድ ቆፋሪዎች ከመሬት ዉስጥ እየተጎተተ ሲወጣ አይቶ በቆሰለ ልብና በነደደ አንደበት “እባክህ ፈጠሪ ወይ ዉረድ ወይ ፍረድ” እያለ ከወያኔ ጋር ከመኖር የፈጣሪን ፍርዱን አለዚያም ዳግም ምጽአቱን ተመኝቷል።
ባለፉት ሁለት ወራት ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ድፍን ህዳርንና ታህሳስን በአለም ዙሪያ በአራቱም ማዕዘን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንን ያሰባሰበ፤ ያነጋገረ፤ ያበሳጨ፤ ያስቆጨና አንጀት ያሳረረ ጉዳይ ነበር። አዎ የ2006 ህዳርና ታህሳስ አገር ዉስጥም ካገር ዉጭም ለምን መጡ የሚያሰኙ የቀን ጎደሎዎች ነበሩ። የወገኖቹ በባዕድ አገር አላግባብ መታሰር፤መደብደብና መገደል ያበሳጨዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ ሀዘኑና ብስጭቱ ሳይላቀቅ ነበር ባለፈዉ ታህሳስ 18ትና 19 ቀን ሌላ አሳዛኝና አስደንጋጭ ዜና የጭንቅና የመከራ ጓዳ የሆነችዉን መዲናችን ከአዲስ አበባን አንደ ሐምሌ ጨለማ የከበባት። ደርግን አሸንፈዉ ስልጣን ሲይዙ ደርግ ገድሎ የቀበረዉን አስከሬን መቃብር እየቆፈሩ ያወጡት የወያኔ መሪዎች እነሱም በተራቸዉ በጅምላ ገድለዉ በብርድ ልብስ እየጠቀለሉ የቀበሯቸዉን ኢትዮጵያዉያን አስከሬን ዬት እንደቀበሩት እንኳን ሰለማያዉቁ እነሱ እራሳቸዉ እየቆፈሩ አዉጥተዉ ወንድሞቹና እህቶቹ እንደወጡ የቀሩበትን የኢትዮጵያን ህዝብ አንጀት እንደገና አቁስለዋል።
እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም ሊያሳስበንና ሊያስጨንቀን የሚገባ ነገር ቢኖር ባለፈዉ ሳምንት ከስድት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የጃንሜዳ ጦር ካምፕ አካባቢ በብርድ ልብስ እንደተጠቀለለ የተገኘዉ የ6 ሰዎች አጽም ሊገኝ የቻለዉ ሆን ተብሎ የጅምላ መቃብር ለማግኘት በተደረገ ቁፋሮ ሳይሆን በአጋጣሚ ነዉ። ይህ የሚያሳየን አዲስ አበባን ጨምሮ በብዙ የአገራችን አካባቢዎች ዉስጥ መረጃ የተሰበሰባበቸዉንና የሚጠረጠሩ ቦታዎችን የኢትዮጵያ ህዝብ ከአለም አቀፉ ህብረተሰብ ጋር ተባብሮ እየቆፈረ መፈተሽ ቢጀምር ወያኔ ጭካኔዉን ሊያሳየን ከሞከረዉ ከደርግ ስርዐት ጋር ምንም የማይለያይ ጨካኝና አረመኔ ስርዐት ለመሆኑ ማንም ማስተባበል የማይችለዉ ተጨባጭ ማስረጃ ይገኛል ብለን እናምናለን።
የወያኔ ዘረኞች አዲስ አበባን በተቆጣጠሩ ማግስት ስራችን ብለዉ የጀመሩት ደርግ የሰለበዉን የኢትዮጵያን ህዝብ ሞራል ማደስ ወይም በሶሻሊዝም ስም የደቀቀዉን የአገራችንን ኤኮኖሚ መገንባት አልነበረም። የደርግ ሰርዐት አንደ ገለባ ሲበተን አብሮት የተበተነዉ የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያሰራዊትም ቢሆን እንደጠላት የሚመለከቱት ኃይል ስለነበር ይህ ለእናት አገሩ ዳር ድንበር መከበር ደሙን ያፈሰሰ ሰራዊት የሚበላና የሚቀመስ አጥቶ ወደ መንገድ ላይ ለማኝነት ሲቀየር ሌላ ቢቀር ጡረታዉን እንኳን ለማስከበር ያደረጉለት ምንም ነገር አልነበረም። ወያኔዎች ስልጣን እንደጨበጡ የደረጉት አቢይ ነገር ቢኖር ከክፍለ ሀገር ክፍለ ሀገረ እየዞሩ ደርግ በቀይ ሽብርና በሌላም ሌላ ግዜ ገድሎ የቀበራቸዉን ሰዎች መቃብር እየቆፈሩ አጽም መሰብሰብ ነበር። በወቅቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተከታታይ እንደተመለከትነዉ የወያኔ ጉድጓድ ቆፋሪዎች የሰነበተ መቃብር እየከፈቱና አጽም እየሰበሰቡ ደርግ ምን አይነት ጨካኝ ነብሰ ገዳይ እንደሆነ ለአመታት የምናዉቀዉን እዉነት እንደገና እንድናዉቀዉ አድርገዉናል። በዚህ ከአንድ አመት ከመንፈቅ በላይ በዘለቀዉ የወያኔ መቃብር ቁፋሮ ወያኔ የቀድሞዉን ንጉስ የቀዳማዊ ኃ/ስላሤን ጨምሮ የብዙ ሰዎችን የመቃብር ቦታ እየቆፈረ እሱ ለፖለቲካ ፍጆታዉ የሚፈልጋቸዉንና በተለይ ደግሞ የኔ ናቸዉ የሚላቸዉን ሰዎች አጽም እየለቀመ አንደገና በክብር እንዲቀበሩ ሲያደርግ ሌሎቹን የደርግ ሰለባዎች ደግሞ ምሶ ያወጣዉን አፈር አንደገና መልሶባቸዋል። እንደዚህ አይነት ጉድ የተመለከትነዉ ከሃያ ሁለት አመታት በፊት ወያኔ ኢትየጵያን ሲቆጣጠር ነበር።
ባለፈዉ ሳምንት አዲስ አበባ ዉስጥ መንገድ የሚሰሩ ሰዎች ለራሳቸዉ ጉዳይ መሬት ሲቆፍሩ ከተጠቀለሉበት የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስ ዉስጥ እየዘለሉ ወጥተዉ “የፍትህ ያለህ” እያሉ ሲጮኹ የሰማናቸዉ አጽሞች ወያኔ በእኔ ዘመነ መንግስት ሰዉ በሰዉነቱ ይከበራል እንጂ እየተጎተተ አየገደልም ብሎ ከማለ በኋላ በራሱ በወያኔ በግፍ እየተጎተቱ ተገድለዉ የተጣሉ ዜጎች አጽም ነዉ። ይህንን በታሪካችን ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ጉድ በስፍራዉ ተገኝተዉ የተመለከቱ የአይን ምስክሮች እንደተናገሩት ቦታዉ ዘመናዊ የመቆፈሪያ ማሽኖች በመቆፈር ላይ እያለ በመጀመሪያ አራት አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተንከባለዉ ወደላይ ሲወጡ የታዩ ሲሆን፤ በሁኔታዉ የተደናገጡት ቆፋሪዎች ስራቸዉን አቋርጠዉ ወደ ቤታቸዉ ከሄዱ በኋላ በነጋታው ረፋዱ ላይ በሌላ አቅጣጫ ሌላ ቁፋሮ ሲያደርጉ አሁንም እንደገና በተመሳሳይ ሁኔታ በብርድ ልብስ የተጠቀለሉ ስድስት አስከሬኖች አግኝተዋል።
አንድ አስከሬኖቹ በተገኙበት አካባቢ በብዛት ተገኝቶ ሁኔታዉን ይመለከት የነበረዉን ህዝብ ለማባረር ወታደሮቹን አስከትሎ የመጣ ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንን “ይህ ግቢ ሶስት ስርዓቶችን ያገለገለ በመሆኑ የማናቸው እንደሆነ ለማወቅ አይቻልም፤ ሆኖም ሰዎች በመሆናቸው ክቡር ናቸውና አፈር አልብሷቸው” በማለት የዘረኞቹን የወያኔ መሪዎች አይን ያወጣ ወንጀል ለመደበቅ ሲሞክር ተደምጧል። ሆኖም ሁኔታዉን በቅርብ ሆኖ የተከታተለዉም ሆነ በርቀት ሆኖ በምስል የተመለከተ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወንጀሉ የሌሎቹ መንግስታት ሳይሆን የወያኔ መሆኑን ለመገንዘብ ግዜ አልወሰደበትም። አስከሬኖቹ በጅምላ የተጠቀለሉበት የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስም ቢሆን እንኳን መሬት ዉስጥ ተቀብሮ ምስጥ፤ እርጥበትና ዘመን ተፈራርቀዉበት፤ አልጋ ላይ ህያዉ ሰዉ ለብሶትም ቢሆን ሃያ አመት ቀርቶ አምስት አመትም የሚቆየዉ የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ለብሰዉት አንደመጡት ቁምጣ በመርፌ ከተጠቋቆመ ብቻ ነዉ። ባለፈዉ ሳምንት አርብና ቅዳሜ አስር አስከሬኖችን እንዳቀፈ ከመሬት ዉስጥ ሲወጣ ያየነነዉ ብርድል ልብስ የሚያሳየን ነገር ቢኖር ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ኢትዮጵያዉያንን በሚስጢር እየገደለ እንደ ቆሻሻ ዕቃ ዬትም ቦታ መጣሉን እንዳማያቆም ነዉ።
የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ለሀይማኖት የሚሰጠዉ ቦታ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። በእስልምናዉ፤ በክርስትናዉም ሆነ በአይሁድ ሀይማኖቶች አስተምህሮ በሀይማኖት ዉስጥ ሁለቱ ዋና ዋና አካሎች እግዚአብሄርና ሰዉ ናቸዉ፤ ይህ የሚያሳየን ሰዉ ክቡር ፍጡር መሆኑን ነዉ። ወደዚህ አለም ሲመጣም ሆነ ይህችን አለም ሲለይ በከብር መጥቶ በክብር የሚሸኝ የሰዉ ልጅ ብቻ ነዉ። የኢትዮጵያ ክርስትና እምነት መሰረት ከሆነችዉ ከትግራይ ክልል የመጡት የዛሬዎቹ የኢትዮጵያ መሪዎች ግን ክርስትናዉን ብቻ ሳይሆን የራሳቸዉንም ሰዉ መሆን የረሱ ይመስላል። ሰዉን የመሰለ ክቡር ፍጡር በጅምላ ተገድሎ፤ በጅምላ ከተቀበረበት ቦታ በኮንስትራክሺን ሠራተኞች ከመሬት ዉስጥ እየተጎተተ መዉጣቱን የሰሙ የወያኔ መሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ አንድም ትንፍሽ ያሉት ቃል የለም። እነሱ ብቻ ሳይሆኑ በእነሱ ቁጥጥር ስር ያሉት የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥንም እነማን እንደሆኑ፤ መቼ እንደሞቱና ማን እንደገደላቸዉ የማይታወቅ ሰዎች አስከሬን በብርድልብስ ተጠቅልሎ ሲገኝ ያንን ለስድብና ህዝብን ለመኮነን ቀኑን ሙሉ የሚከፍቱትን አፋቹዉን መክፈት አልፈለጉም። የሚገርመዉ እንደ አለባሌ ነገር ከተጣሉበት ቦታ ተጎትተዉ የወጡት አስከሬኖች ሁኔታና የተጠቀለሉበት ብርድልብስ ሙሉ በሙሉ ወንጀሉን ወያኔ ላይ ስለሚያመለክት ነዉ እንጂ የእነሱ እጅ የሌለበት ወንጀል ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሳምንት ሙሉ ሌላ ዜና አይሰማም ነበር።
አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ አገሮች የሚኖረዉ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ባለፈዉ ሳምንት እንደ ዋዛ ከመሬት ዉስጥ እየተጎተቱ የወጡ ወገኖቹን አስከሬን ጉዳይ በቀላሉ መመልከት የለበትም። ወያኔ ስልጣን እጁ ከገባ ጀምሮ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያንን እያፈነ በየማጎሪያ ቤቱ አጉሯቸዋል። ከሰሞኑ ጃንሜዳ አካባቢ ያየነዉ ዘግናኝ ክስተት ስለእነዚህ ወያኔ በየድብቅ አስር ቤቶች አስሮ አድራሻቸዉ ስለጠፋ ዜጎቻችን ብዙ የሚለዉ ነገር ያለ ይመስለናል። እኛ ነን አድራሻቸዉ የጠፋ ሰዎች እያልን የምንጨነቀዉ እንጂ እነዚህ ወያኔ አስሯቸዉ አድራሻቸዉ የጠፋ ሰዎች ዬት እንዳሉ ጃንሜዳ አፉን ከፍቶ ነግሮናል። አዲስ አበባና በየከተማዉ የሚኖረዉ ህዝብ ስለወያኔ የጅምላ ግድያ የሚያዉቀዉ ብዙ ሚስጢር ይኖራል፤ በጅምላ ተገድለዉ በጅምላ የሚቀበሩ ሰዎችንም ጉዳይ በተመለከተ ማንም ሰዉ ሳያየዉና ሳያዉቀዉ የሚፈጸም ነገር አይመስለንምና ከአሁን በኋላ ጥረታቻን ሁሉ የወያኔ የጅምላ ግድያዎች በብሄራዊና በአለም አቀፍ አካላት እንዲመረመሩና ወንጀለኞቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ መሆን አለበት። በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃ ያላቸዉ ዜጎች መረጃዎቻቸዉን ማሰባሰብ፤ማደራጀትና ለሚመለከተቸዉ አካላት መስጠት ይኖርባቸዋል። ዬት እንደደረሱ ሳናዉቅ ባለፈዉ ሳምንት ሳይተሳብ በደብረህርሃን ብርድ ልብስ እንደተጠቀለሉ ከመሬት ዉስጥ የወጡ ዜጎቻችን ፍትህ ሳያገኙ ማንም ኢትዮጵያዊ እንቅልፍ ሊወስደዉ አይገባም።

ካለመታደል ሀገራችን ዛሬም ሰላም ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት በልማትና በእድገት ጎዳና የምትራመድ ሀገር አልሆነችም። ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም እንደ ዓቢይ ምክንያት ተደርጎ የሚቀርበው የህዝብን ይሁንታን ያገኘ፡ ህዝብን በእኩልነት የሚዳኝ፡ ህዝባዊና ዲሞክራሲያዊ የሆነ መንግሥት አለመመስረቱ፡ አገርና ህዝብ የሚተዳደሩበት ዲሞክራሲያዊ ህገ መንግሥት አለመኖሩ ነው።

እስከዛሬ በተጨባጭ እንደታየው በ ኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተፈራረቁበት ገዥዎቹ በየበኩላቸው አንዱ ከሌላው የሚለዩባቸው ባህርያት ቢኖራቸውም ሁሉንም ግን አንድ የሚያስመስሏቸው ባህርያትም አሏቸው። እነሱም ሁሉም በኃይል ሥልጣን መያዛቸው፡ አምባገነንነታቸው፡ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ማራመዳቸው፡ በህዝብ መካከል የጋራ መተማመንና ከበሬታን ለመፍጠር፡ ሁሉም ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን በሀገሪቱ ለማስፈን አለመቻላቸው ደግሞ ዛሬ ለሁሉም በግልጥ እየታየ ያለ ነው። በዚህም የተነሳ በሀገራችን ለብሔራዊ ክብርና ነፃነት፡ ለዲሞክራሲ፡ ለማህበራዊ ፍትህ፡ ለሰላምና ለእኩልነት የሚታገሉ ኃይሎች የሰላማዊ ለውጥ በሮች ስለተዘጉባቸው የአ መፅን ጎዳና እንዲከተሉ የሚጋብዝ በር ተቀዶ ይገኛል።

በሌላ በኩል ደግሞ በሀገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ መረጋጋት ንእዲፈጠር፡ ሕዝቡም አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ አግኝቶ ያለስጋት ለመኖር እንዲችል፡ የዳኝነት ተቋሞች ነፃ ሆነው የሚሠሩበት፡ የህግ የበላይነት የተረጋገጠበት ሁኔታ እንዲፈጠርና፡ ህዝቡም በህግና ሥርዓት መኖር ላይ እምነት እንዲያድርበት ለማድረግ እንዲቻል፡ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊ ተቃዋሚ ኃይሎች በተናጠልም ሆነ በኅብረት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል። ሆኖም እስከዛሬ የተደረጉት ጥረቶችን ሁሉ በማምከን ወያኔ የሰላምና የእርቅ መሰናከል ከመሆኑም ባሻገር በንፁሃን ዜጎች ደም ሰላምን አጠልሽቶታል። ወያኔ ስለ ሰላምና እርቅ ሊሰማም ሊነጋገርም እማይችልበት የደም ስካር ላይ ደርሷል።

ብአዴን ቢመጣ ኦህዴድ ቢመጣ ደህዴን ቢመጣ የሚለወጥ ነገር አይኖርም። ጠንከር ያለ ለለውጥ የተዘጋጀ – አስከ ሞት የቆረጠ -ጠቅላይ ሚኒስተር ስልጣን አገኘ ማለት የህወሃት የበላይነት እና ፈላጭ ቆራጭነት ፍላጎት ፈተና ይገጥመዋል ማለት ስለሆነ! ህወህት የበላይነቱን ለማሰጠበቅ የፈጠራቸው የመንግስት ስልጣን አደረጃጀት አና ተቋማት ዛሬም በሙሉ ሃይላቸው አሉ። የህወሃት ፈላጭ ቆራጭነት ሳይዳከም ለውጥ አይመጣም። የህወሃት ፈላጭ ቆራጭነት መሰረቱ ደሞ ከምንም በላይ ወታደራዊ ሃይሉ ላይ የተመሰረተ አንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው። በደህነንት ቢሮ ያሉትን የህወሃት አመራሮች ከታች ያሉት ማዳክም የሚችሉበትን አጋጣሚ አና ሁኔታ ተጠቅመው አስካላዳከሙት ደረስ የህወሃት የስልጣን የበላይነት ትርጉም ባለው ሁኔታ እክል ሊገጥመው አይችልም።

ሌላ ሌላውን ትተን መሰረታዊ የሆነ ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ ያስፈልጋል፣ የፍትህ ስርዕቱ የፍትህ ስርእት መመስልም መሆንም አለበት፣ የነጻው ፕሬስና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ህዳሴ አንመራለን አየተባለ በመካከለኛው ዘመን አና ከዛ በፊት ከነበረው አንደነበረው በሰይፍ አና በሰደፍ መያዝ የለበትም። አነኚህ ወሳኝ ርምጃዎች በአዝጋሚ ለውጥ ይመጣሉ ብየ አላስብም። የአዝጋሚ ለውጥ ዲስኩር (ፍላጎት ካለ ፍላጎትም) ጭራሽ ወደማይቀልበስ የባርነት ዓለም አና ዘመን የመውሰጃ ከፓለቲካ ዘዴ ሊሆን ይችላል። ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓለቲካ መሪዎች ዘብጥያ ሲጣሉ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፈጠሩትን ዓይነት ጫና መፍጠር ስላልተቻለ አንኳን መሰረታዊ የፕሬስ ነጻነት አና በነጻነት ያለገደብ የመደራጀት መብት የሚከበርበት ፍንጭ ሊገኝ ቀርቶ የታሰሩትን ጋዜጠኞች አና የፓለቲካ መሪዎች ማስፈታት አንኳን አልተቻለም። ጭራሽ መብታቸው ተረግጦ ያላግባብ አስር ቤት የተጣሉ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ድረስ “አሸባሪ” አየተባሉ አየተፌዘባቸው ነው ያለው። አቶ ኃይለማርያምም ፌዙን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ አያስተጋቡት ነው።

ከበቀለበት የተጋጋበት አንዲሉ የ”በሳሉ መሪ ራዕይ” ዜማ ከህወሃት አባላት በእህት ድርጂቶች የፓለቲካ አላዋቂዎች አና መሪዎች ይበልጥ ተዜመ! በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝም ተሰማ። ችግሩ የለውጥ ጥያቄ ማድበስበሻ ሆኖ ለረዢም ጊዜ ሊቆይ አይችልም። በውሽት ላይ የተመሰረተ ፐሮፓጋንዳ ስር ሊይዝ አይችልም።አንዴት ይሄን ማየት አቃታቸው?!የሕዝባችን መከራና ሰቆቃ እየከፋ ሄደ። የተጨቆነዉ ሕዝብ ተነሳስቶ ለመብቱ ሲታገል ጨቋኝ መንግሥታት ለዉጥ እንዲያደርጉ ይገደዳሉ፤ ካለዚያ በተባበረዉ የሕዝብ ኃይል ተንኮታኩተዉ ይወድቃሉ። የታገለዉ ለዉጥ ያመጣል፤ ያልታገለዉ ቁጭ ብሎ በባርነት ሲገዛ ይኖራል፤ ቁጭም ባለበት ይሞታል ማለት ነው። የለዉጥ ባለቤት ሁሌ ሕዝብ መሆን አለበት። ህዝቡ ትግሉን በሚገባ እንዲያቀናጅ የትግል መሪ ይፈልጋል።

ስለዚህ የተቃዋሚ የፖሊቲካ መሪዎች ታላቅ ኃላፊነት ይጠበቅባቸዋል። ያገራችንን ጭብጥ ሁኔታ ስንመረምር ግን በሁለቱም በኩል ታላላቅና ተደጋጋሚ ድክመቶች ታይተዋል። አምባገነን መንግሥታት ለዘለዓለም ካልገዛን ሲሉ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኅብረታቸዉን ማጠናከር ስላልቻሉ የጨቋኝ መንግሥታትን ዘመናት ሲያራዝሙ ቆይተዋል።ወያኔ/ኢሕአደግ ለዘለዓለም ሊገዛ አይችልም፤ ለሁሉም ጊዜ አለዉና።ትግሉ ይበልጥ መፋፋም፡ ይበልጥ መጨስ፡ መጋጋም፡ መንደድ ይጠበቅበታል። ትግሉን ለማፈንና አቅጣጫውን ለማሳት የወያኔ መንጋ እየተሯሯጠ ነው። በውጭ ያለውንም የሕዝብና የድርጅቶችን ተቃውሞ ቢቻለው ለማዳፈን፡ ካልሆነለት ደግሞ ለማዳከም፡ በአሁኑ ወቅት የወያኔ ከፋፋይ ቡድን በየቦታው በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ እያየን ነው። ይህ ቡድንም፡ ምሁር ነን፡ አስታራቂ ነን፡ ሽማግሌ ነን ወይም ታጋይ ነን በሚሉ መሰሪዎችም እየተደገፈ ነው።

የሕዝብ ክንድ ይላላ፡ ይደክም ዘንድ፡ በከፋፋይ ሴራ የተሰማሩትን ነቅቶ መጠበቅ፡ ትግሉን መከላከል ብቻ ሳይሆን ወያኔ ለባሾችን፡ ሰላዮችን ሳንፈራ እየመነጠርን ማጋለጥ ይኖርብናል። ዘረኛው ቡድንና ጭፍሮቹ የሕዝቡን ትግል ለመከፋፈል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየጣሩ ናቸውና። ሕዝብ አንድነቱን ጠብቆ፡ የወያኔን ቡድን ለአንዴም ለሁሌም ለማስወገድ አስፈላጊውን መስዋእ ትነት እየከፈለ ባለበት ወቅት የፖለቲካ ድርጅቶችን እገዛና አመራር ይጠይቃል። የሕዝብ አሸናፊነት አጠራጣሪ ባይሆንም፡ አሸናፊ ለመሆን ግን መታገል መቅደም እንዳለበት ምን ጊዜም መረሳት የለበትም። ለዚህ መሠረቱ ግን ከራስ ጋር እየታረቁ፡ ከወገን ጋር እየተስማሙ በጋራ ዓላማና ብሔራዊ እጅንዳ ዙሪያ ተሰባስቦ በጋራ መታገል ብቻ ነው።

በዓለም ታላቅ ዝና ያተረፉት የግ/ቀ/ኃ/ሥና በአፍሪቃ አህጉር መሬትን ያንቀጠቀጠዉ የደርግ መንግሥት ቀናቸዉ ሲደርስ እንዴት እንደመነመኑና እንደከሰሙ መዘርዘር አይኖርብኝም፤ በታሪክ ፊት ተቀምጧልና። በሩቁም በእነ አሜሪካ ለረዥም ዓመታት ሲረዱና ሲደገፉ በነበሩት በእነ ሞቡቱ፤ የሻህ ንጉሥ፤ ሆስኒ ሙባረክ፤ ወዘተ ላይ በመጨረሻ የደረሰዉን ዉርደት መገንዘብ ያስፈልጋል። ተቃዋሚ የፖሊቲካ ድርጅቶች ነን የሚሉትና በተግባር ግን የጭቆናን ዘመን የሚያራዝሙ በሙሉ ካለፉት ስህተቶች ገና ሊማሩ አልቻሉም፤ ・ድር ቢያብር እንበሳ ያስር・ የተባለዉን ቅዱስ አሳብ ደጋግመዉ መናቃቸዉ ያስተዛዝባል። ቁርጥ ያለ አቋም ያስፈልጋል፤ ከዛፍ ዛፍ መዝለል ዬትም አያደርስም። ለጊዜያዊ ጥቅማ ጥቅሞች በርካሽ መገዛትና አገርን መሸጥ በሰማይም በምድርም ያስጠይቃል። ቀኑ ሲደርስ ራቆታችንን ወደምድር እነደመጣን ሁሉ ራቆታችንን ወደዚያዉ እነደምንመለስ አንርሳ!!!

ነገርግን በህብረት ለሀገር ታሪክ ሰርቶ ማለፍ ዘላለማዊ የትዉልድና የሀገር ክብር ነዉ!!!

ከጎልጉል የተወሰደ

ኢትዮጵያዊነት የሚለው ቃል እኮ የኢያንዳንዳችን መከበሪያ እና መኩሪያ እንጂ ማፈሪያ አይደለም::ለአመታት ታገልን የሚሉ ከወያኔ ጎን እየፈሉም ያሉ እና የከሰሙ የብሄር ድርጅቶች በታገሉባቸው አመታቶች ከወሬ ውጭ ለሃገሪቱም ይሁን ለሚጠሩት ብሄር ምንም የፈየዱት ነገር የለም:: ያመጡትም ነጻነት የለም ይብሱኑ እርስ በእርስ ከማጨፋጨፍ ውጪ እና ህዝብን ለእልቂት ከመዳረክ ውጪ ምንም ያመጡት ውጤት የለም:: በብሄር ስም መታገል እና ዘረኝነት ማራመድ ለብሄራዊ ጭቆና በር መክፈት ነው :: ገዢው ፓርቲን ሕወሓትን እንኳን ብትመለከቱት ለትግራይ ህዝብ የፈጠረው አዲስ ነገር የለም:: የትግራይ ህዝብ በዘመናዊ ጭቆና ፍዳውን እያየ ነው::

እኛ በጋራ እስካልታገልን ድረስ ለውጥ አይመጣም:: ከሃገር ሲወጡ የወያኔን ጽዋ ጠጥተው እዚህ ከመጡ በኋላ የሚከረበቱ አስመሳይ ተለጣፊ ፖለቲከኞችን ማስወገድ ግዴታችን ነው:: ኢትዮጵያዊነት የሚለው ቃል እኮ የኢያንዳንዳችን መከበሪያ እና መኩሪያ እንጂ ማፈሪያ አይደለም:: ከሌላው አለም የምንወስደው ትምህርት ምንድን ነው??ሌላው ዜጋ ሃገሩን እና ሌላውን ወገኑን እንዴት ነው የሚወደው?? የዘር እና የቀለም ልዩነት እየተወገደ በሚሄድበት በዚህ በሰለጠነው አለም ላይ ትላንትን እያሰብን የምንኖር ሰዎች ግንዛቤያችንን ማስፋት ይጠበቅብናል::

ኢትዮጵያ ምን አደረገችልኝ የሚል አነጋገር የሚናገሩ ጠባብ ብሄርተኞች አላማቸው የት ላይ እንደሚያርፍ ራሳቸው አያውቁትም::ኢትዮጵያ እኮ አንዲት ግኡዝ አካል ነች :: ተንቀሳቅሳ ላንተ ላንቺ እና ለእናንተ የምትፈይደው ነገር የለም ምድሯን እየረገጥን እየተማርን እየኖርን ያለነው እኛ ነን ::የእኛ ስራ ደሞ አገርን ከክፉ ገዢዎች አድነን ራሳችንን ነጻ በማውጣት የወገንን እምባ ማበስ እንጂ በወገን እንባ እና ደም መነገድ አላስፈላጊ ኪሳራ ያስከትልብናል ለኢትዮጵያ ምን ሰራሁላት ለወገኔ ምን አደረኩለት ብለህ ጠይቅ እንጂ እንደ ከብት አታጓራ:: በህዝብ ጥያቄ ስም ተደብቆ ጠባብነትን ማራመድ ክሽፈትን ያመጣል እና እንጠንቀቅ:: በየትኛውም አገር ያለን ኢትዮጵያውያን በጡት ነካሾች የታሰበውን ጸረ ኢትዮጵያ ዘመቻ ልንቃወም ይገባል::ምንሊክ ሳልሳዊ

አምስተኛው ዙር አገር አቀፍ ‹‹ምርጫ›› እንደወትሮው ሁሉ በቀጣዩ ዓመት ሊደረግ በዕቅድ ተይዟል፤ ወሬውም ከወዲሁ ለፖለቲካ ፍጆታነት እየዋለ ነው፤ ኢህአዴግም በበኩሉ ‹አውራ ፓርቲ›ነቱን ከቀደመው በበለጠ አጠናክሮ የሚቀጥልበትን ሴራ ፈትሎ በመግመድ ውሎ ማደሩን ገና በማለዳ እያቀላጠፈው መሆኑን እየታዘብን ነው፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ (ከልቡ ባይሆንም) በ1996 ዓ.ም ወርሃ ሐምሌ ላይ በተደረገ የግንባሩ ጉባኤ ‹‹የሚቀጥለው ምርጫ እንከን-አልባ ይሆናል›› ሲል ‹ቃል› ገብቶ የነበር ቢሆንም፣ ከስድስት ዓመት በኋላ በተካሄደው አራተኛው ዙር ‹‹ምርጫ›› በግላጭ ‹እንከን-አልባ ድል› በሚል ሲቀይረው ቅንጣት ታህል ሀፍረት

አልተሰማውም ነበር፡፡ ግና! ‹አንድ ለእናቱ› እንዲል አቤ ጎበኛ፣ የተቃውሞውን ስብስብ የምትወክል አንዲት ወንበር ሾልካ ወደ ምክር ቤቱ በመግባቷ፣ ፓርቲው ዛሬም ድረስ እንደ እግር እሳት እያንገበገበችው መሆኑን በተለያየ መንገድ እያሳየን ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ኢህአዴግ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ በሚቀጥለው ዓመት በሚደረግው ‹‹ምርጫ›› እንዲህ አይነት ‹እንዝህላልነትን› ለማረም በከፍተኛ ዝግጅት መጠመዱን የሚጠቁሙ መረጃዎች እያፈተለኩ ነው፡፡ መቼም የጉዳዩ እውነትነት ከተረጋገጠ፣ ምናልባትም በ2012 ዓ.ም ልክ እንደ ኤርትራ ወይም እንደ ቻይና ‹ልማታዊ መንግስት እንጂ ምርጫ የሚባል ነገር አያስፈልግም! የምርጫ ፖለቲካ የኒዎ-ሊበራሊስቶች አጀንዳ ነውና!!› ከማለት የሚመለስ አይመስለኝም፡፡ ማን ያውቃል? …እንዲህ እንደዛሬው የሶስት ሺ ዓመት ታሪክ ያላትን እና የዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ አገርን ፍርሃት በመንዛት አሸንፎ ከቆየ የምናየው ይሆናል፡፡

ከዚህ ባለፈ ቀጣዩን ‹‹ምርጫ›› በፍፁማዊ ጠቅላይነት ለመጨረስ እያደረገ ያለው መሰናዶ በሶስት የተከፈለ ነው፤ የመጀመሪያው ለመላው የድርጅቱ አባላት (የመንግስታዊ ተቋማት ኃላፊዎችን ጨምሮ) የተዘጋጀው ፓኬጅ ነው (ሰሞኑን በተለያዩ ከተሞች ስለ ‹አውራ ፓርቲ› አስፈላጊነት እና የ‹ልማታዊ መንግስት›ን ጠቀሜታ በተመለከተ እየተሰጠ ያለው ሥልጠናም የዚሁ አካል እንደሆነ ሰምቻለሁ)፤ ሁለተኛው መራጩ ሕዝብ ላይ በተናጥል አተኩሮ ለመተግበር እየተሞከረ ካለው ቀመር ጋር የሚያያዝ ሲሆን፤ ይህም እንደ ቀድሞው ሁሉ ለአቅመ-ምርጫ የደረሰውን ህዝብ በኮንዶሚንየም፣ በመልካም አስተዳደር እና በማይጨበጡ የተስፋ ፕሮፓጋንዳዎች ማማለልን የሚያካትት ነው፤ የመጨረሻው ደግሞ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና የግሉ የህትመት ሚዲያ ላይ ያነጣጥራል፤ በዚህ ፅሁፍም አጀንዳ የምናደርገው አገዛዙ በዚህኛው ግንባር ከሚያስወነጭፋቸው የ‹ጦር መሳሪያዎች› በዋነኛነት በዘጋቢ ወይም በዶክመንተሪ መልክ የሚያዘጋጃቸው ፊልሞችን የተመለከተ ነው፡፡

ስውሩ አጀንዳ…
በርግጥ ይህ አይነቱ አሰራር ዛሬ የተጀመረ አይደለም፤ ባለፉት ሃያ ዓመታት በሙሉ ሲተገበር የነበረ ነው፡፡ በተለይ ሕዝባዊ ተቃውሞን

የመሰለ ለሥልጣን የሚያሰጋ ድንገቴ አጋጣሚ ሲከሰት የሚመረቱት ፊልሞች ቁጥርም እንዲሁ ይጨምራል፤ እንደ ምሳሌም የ1993ቱን የህወሓት ክፍፍልን ተከትሎ በየአካባቢው የሕዝብ ማጉረምረም በበረታበት ወቅት፣ የሰሜን አፍሪካ አብዮት በጋመበት ማግስት እና የእስልምና እምነት ተከታዮች ሕገ-መንግስታዊው የኃይማኖት ነፃነት እንዲከበርላቸው በአደባባይ በጠየቁባቸው ጊዜያት በ‹‹ዘጋቢ ትዕይንት›› ስም የተሰራጩትን ብቻ መመልከቱ በቂ ነው ብዬ አስባለሁ (በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት ጭብጥ ያላቸው ፊልሞች ደራሲያን፣ የስርዓቱ ዋነኞች ‹ኤጲስ-ቆጶሳት› እንጂ ተቋሙ የሰበሰባቸው ብላቴና ልማታውያን ጋዜጠኞች አይደሉም)

ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የመረጃ ምንጮቼ እንዳረጋገጥኩት ‹ዶክመንተሪ ፊልሞች› የሚዘጋጁት በሁለት መንገድ ነው፤ የመጀመሪያው በኢቲቪ ባልደረቦች ሃሳብ አመንጪነት በፕሮፓጋንዳ ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣ በሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ይሁንታን ሲያገኝ እንዲተላለፍ የሚደረግ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ፣ በጉምቱ የፓርቲው መሪዎች የጭብጥ አሰናጅነት ሙሉ ድራማው አልቆለት በቀጥታ አየር ላይ እንዲውል ወደ ጣቢያው የሚላከው ነው፡፡ በዚህ ዘውግ የሚመደቡት አብዛኛዎቹ ፊልሞች ተቃዋሚ ፓርቲዎችን፣ በግል ሚዲያ ላይ የተሰማሩ ጋዜጠኞችን፣ የኃይማኖት መሪዎችን እና ዓለም-አቀፍ ተቋማትን በመወንጀልና በመዝለፍ ላይ የሚያውጠነጥኑ ናቸው (የቅርቦቹን እንኳ ለማስታውስ ያህል ብንጠቅሳቸው ይህንኑ ያስረግጣሉ፡- ‹አዲስ አበባን እንደ ባግዳድ›፣ ‹አኬልዳማ›፣ ‹ጀሀዳዊ ሀረካት›፣ ‹ሽብርተኝነት በኢትዮጵያ› እና የመሳሰሉት)

በጥቅሉ እስከ 2004 ዓ.ም መገባደጃ ድረስ የእነዚህ ፊልሞች ደራሲ አቶ መለስ ዜናዊ የነበረ ሲሆን፤ ከእርሱ ህልፈት በኋላ የኮሚኒኬሽን መ/ቤት (ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር አማካሪዎች) በደህንነት እና ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል ስም

እንደሚያዘጋጁት ውስጥ-አወቅ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ኢቲቪ በእንዲህ አይነት ጭብጥ ዙሪያ በሚያውጠነጥኑ ፊልሞች ላይ ምንም አይነት ተሳትፎ አያደርግም፤ ሳይቀንስና ሳይጨምር ለሕዝብ ማስተላለፍ አማራጭ ያልተተወለት ብቸኛ ግዴታው ነው፤ የህወሓቱ ሰው ገራገሩ የተቋሙ ስራ አስኪያጅ ዘርዓይ አስግዶምም ቢሆን ይህ ኃላፊነት ሲሰጠው ትጉህ አገልጋይነቱ ለማን እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቀዋልና፣

በፍፁም ፈቃደኝነት ሥራውን ከማሳለጥ በቀር የሚቃወምበት ወይም የኤዲቶሪያል ነፃነቴን አላስገፋም ብሎ የሚቀብጥበት አንዳች ምክንያት የለውም፡፡ በግልባጩ ውዳሴ መለስ፣ ስደት፣ የአባይ ቁጭት፣ የኮንዶሚንየም ቤቶችንና መሰል ጉዳዮችን በተመለከተ ደግሞ ሩቅ አላሚዎቹ ‹‹ልማታዊ ጋዜጠኞች››፣ እንቅልፍ አጥተው የሚጨነቁበትና እርስ በእርስ ለመቀዳደም የሚተጉበት አጀንዳ ስለመሆኑ ራሱ በረከት ስምዖንም ገና ድሮ የገባው ይመስለኛል (በነገራችን ላይ በየጊዜው ጥቂት የጣቢያው የተለያዩ ፕሮግራም አዘጋጆች እና የዘጋቢ ፊልም ባለሙያዎች የቻይናን የሚዲያ ተሞክሮ አጥንተው እንዲመጡ እንደሚደረግ ይታወቃል)

ለዚህ ፅሁፍም እንደ ማሳያ የምጠቅሰው፣ ባለፈው ሳምንት ‹‹ሽብርተኝነት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ ለተመልካች የቀረበው ዘጋቢ ፊልም፣ ሙሉ በሙሉ በብሔራዊ መረጃ መ/ቤት ስም የተዘጋጀ ሲሆን፣ በንባብ የተሳተፉት ሁለቱ ‹‹ጋዜጠኞች››ም የኢቲቪ መደበኛ

ባልደረቦች እንዳልሆኑ ከምንጮቼ አረጋግጫለሁ፡፡ ምንም እንኳ የፊልሙ ‹ባለቤት› የሆነው የደህንነት ቢሮ በሽብርተኝነት ዙሪያ የሚያውጠነጥን ነው ቢለንም፣ እንዲተላለፍ የተፈለገው ዋነኛ መልዕክት በቀጥታ ከቀጣዩ ምርጫ ጋር የተያየዘ ነው ወደሚል ጠርዝ የሚገፉንን ማሳያዎች መምዘዝ የሚቻል ይመስለኛል፡፡ እንዴት ሆኖ? የሚለውን ጥያቄ በአዲስ ርዕስ ሥር እናፍታታው፡፡

ከፍርሃት ጋር ወደፊት!

በዚህ ፊልም ላይ ዋነኛ አጋፋሪ ሆነው የቀረቡት ሶስት ሰዎች ናቸው፤ የኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ ሽመልስ ከማል (ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በእንዲህ አይነት ፊልሞች ላይ የመሪ-ተዋናይነትን ገፀ-ባህሪ ወክሎ መጫወቱን እየተካነው እንደሆነ እኔም ራሴ እመሰክርለታለሁ¡)፣ የፌደራሉ ዋና ዓቃቢ-ሕግ ብርሃኑ ወንድማገኝ እና አቶ ዘሪሁን ተሾመ (ይህ ሰው ደግሞ አሉባልታና ጠቀሜታቸው ረብ-የለሽ የሆነ ወሬዎችን በማቅረብ የሚታወቀው የ‹ዛሚ-90.7› ሬዲዮ ባለቤት ሚሚ ስብሃቱ የትዳር አጋር ነው) ከትዕይንቱ መካከል የሚታወሱ ፊቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ድራማው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ተሰፍሮ የተሰጣቸውንና በፈጠራ ታሪክ የተሞላውን ‹ስክሪፕት› ቃል-በቃል ሸምድደው መምጣታቸውን በግልፅ በሚያሳይ መልኩ ሲያነበንቡ ላስተዋላቸው ተመልካች ‹‹ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች›› የጣሉባቸውን ግዴታ በቁርጠኝነት ለማስፈፀም ‹ቀራኒዮ› ድረስ የሚጓዙ ሊመስለው ቢችል አይፈረድበትም¡ መቼም አገዛዙ ዓለማዊ ፍላጎታቸውን እስካሟላላቸው ድረስ ሀገር፣ ሕገ-መንግስት፣ ሕሊና… ደንታ ሳይሰጧቸው ሕዝብን በማሸበር የስርዓቱ ዕድሜ ይረዝም ዘንድ ‹ከፍርሃት ጋር ወደፊት!!› ለማለት የማያመነቱ ሰዎችን በዙሪያው የኮለኮለው ለእንዲህ አይነቱ ጊዜ ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ፊልሙ ከቀድሞዎቹ አንፃር እንኳ ሲመዘን የወረደና አሰልቺ ቢሆንም፣ ያን ያህል ከተደሰኮረለት የ‹‹ሽብርተኝነት ጉዳይ›› ባሻገር ሁለት ያደፈጡ ስውር ዓላማዎች ያሉት ይመስለኛልና፣ እነርሱን ነጣጥለን እንመልከት፡፡

የቀደሙ ልምዶችን ተንተርሰን ስናብሰለስለው፣ የዘጋቢ ትዕይንቱ ድብቅ ዓላማ ተደርጎ ሊጠቀስ የሚችለው የመጀመሪያው የቢሆን ሃሳብ፣ ኢህአዴግ ከምርጫው መዳረሻ በፊት በተቃውሞ ፖለቲካው ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ ያሉ የተወሰኑ የአመራር አባላትን እና ጥቂት ጋዜጠኞችን እንደተለመደው ከግንቦት 7 ጋር አቆራኝቶ ለማሰር እየተዘጋጀ ነው የሚል ይሆናል፡፡ በርግጥም ይህንን መከራከሪያ ከመቀበል ሌላ አማራጭ የሚያሳጡ ሁለት ገፊ ምክንያቶች አሉ፤ አንዱ ፓርቲው ቀጣዩን ምርጫ ከትግል ዘመኑ ጀምሮ ይመራው ከነበረው ጉልበታሙ አቶ መለስ ውጪ የሚያደርገው መሆኑ ያሳደረበት ስጋት ወደ ጭፍን አምባገነንት እንዲቀየር ከማስገደድ አልፎ፣ ይህንኑ የሰውየውን ህልፈት ተከትሎ የተከሰተው የኃይል መከፋፈል ያነበረው የመሳሳት ተፅእኖ ይመስለኛል፤ እነዚህ ኩነቶችም ስርዓቱ ህልውናውን ካፀናበት አምባገነናዊ ባህሪው አኳያ ድንገቴ እርምጃ እንዲወስድ መግፋታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ካደረ ተሞክሮው የሚነሳ ነው፤ ይኸውም በ2002ቱ ምርጫ ዋዜማ በተልካሻ ምክንያት የአንድነት ለፍትሕና ዴሞክራሲ ሊቀ-መንበር የነበረችውን ብርቱካን ሚደቅሳን እስር ቤት በመክተት ፓርቲውን እና የተቃውሞ ደጋፊ ኃይሉን እስረኛ በማስፈታት አጀንዳ እንዲጠመድ ያደረገበት ስልት እና ሁነቱ የፈጠረው ማሕበረሰባዊ የፍርሃት ድባብ ያስገኘለት ጠቀሜታን ሊከልሰው መሞከሩ አይቀሬ መሆኑ ነው፡፡ በአናቱም በወቅቱ ከፍተኛ ተነባቢነት የነበራትን የ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ አዘጋጆች ምርጫው አራት ወር ብቻ ሲቀረው በግልፅና ስውር ጫና ጋዜጣውን ዘግተው ከሀገር እንዲሰደዱ ያደረገበት መንገድም የዚሁ አፈና ጉትያ እንደነበረ አለመዘንጋቱ፣ በቅርብ ከሚፈጠሩ ተመሳሳይ ክስተቶች ጋር ለማያያዝ ያስችላል፡፡

ሌላኛው የዘጋቢ ፊልሙ ዓላማ በቀጣዩ ምርጫ ለውጥ ፈላጊውን የህብረተሰብ ክፍል ወደ ተቃውሞ ጎራ ሊያሰባስብና መነቃቃት ሊፈጥር ይችላል የሚል ብርቱ ጥርጣሬ ያሳደረበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጣቢያን በመርገም (በሽመልስ ከማል አነጋገር ‹‹ውጉዝ ከመአርዮስ›› በማለት) የተቀናቃኝ ድምፆች በተከበበላቸው ሞገድ ብቻ እንዲሰሙ ማስገደድ ነው፡፡ ይህ ሁናቴ አገር ውስጥ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እና ጋዜጠኞች ለጣቢያው ቃለ-ምልልስ እንዳይሰጡ በፍርሃት ቆፈን መሸበብንም ያከተተ ነው፡፡ አስደንጋጩ ጉዳይ ደግሞ መከራከሪያ ሆኖ የቀረበው ሕገ-መንግስታዊው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ሳይሆን፣ ለሚዲያ ተቋሙ የብሶት መግለጫዎችን መስጠትም ሆነ ኢ-ፍትሀዊ አሰራርን ማጋለጥ በሽብርተኝነት እንደሚያስከስስ የሚተርክ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም››

መሆኑ ነው፡፡ በርግጥ ለዚህ ማስፈራሪያ እንደ መደገፊያ የተጠቀሙት ፀረ-ሽብር ሕጉ በግብረ-አበርነት ተጠያቂ የሚያደርግበትን የተለጣጭነት ባህሪውን አፅንኦት በመስጠት እንደነበረ ታዝበናል፡፡

በፊልሙ ላይ አቶ ዘሪሁን ምሬት በዋጠው ድምፅ ‹‹ኢሳት የግንቦት 7 ወፍጮ ነው!›› የሚል መፈክር ሲያሰማ፣ ሽመልስ ከማል ደግሞ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ከዚህ ቀደም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ‹አሸባሪ› ተብለው ከተፈረጁት ድርጅቶች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳይኖር ለማድረግ እንደሆነ ምሎ-እየተገዘተ ተመልካቹን በፍርሃት ለማንበድበድ ሲሞክር ተስተውሏል፡፡ ይሁንና የአቶ
ሽመልስን እርግጠኛነት ለማመን አመክንዮ መጠቀም የግድ ይሆናል፤ እናም ኢሳት የእነዚህ ድርጅቶች ዓላማ አራማጅ መሆኑን ለማሳየት ምን ተጨባጭ ማስረጃ አቀረባችሁ? ለሚለው ጥያቄ እየነገሩን ካለው እንቶ-ፈንቶ ባለፈ በማስረጃ የተደገፈ መልስ መስጠት የሚኖርባቸው ይመስለኛል፡፡ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የኤርትራ መንግስት ከሰጠው አምስት መቶ ሺህ ዶላር ውስጥ ሁለት መቶ ሺውን ለኢሳት ሥራ ማኪያሄጃ እንዲውል መወሰኑን በስልክ ሲናገር ከማሰማት በዘለለ ማለቴ ነው፡፡

እግረ-መንገድ ለመጥቀስ ያህል የዚህ ፅሁፍ ዓላማ ኢሳትን መንግስት ለምን ወነጀለው በሚል ግብረ-መልስ መስጠት አለመሆኑን ማስገንዘቡ አስፈላጊ ይመስለኛል፤ መነሻ ምክንያቴ እንደ ሚዲያ ተቋምነቱ ከእኔ ሞያ ጋር በቀጥታ መገናኘቱ ሲሆን፤ ለምን ይህ ሆነ? ያልኩበት ተጠየቅም የሕግ የበላይነት ጉዳይ ብቻ በመሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም የተመለከትነው ፕሮግራም ኢሳት እስከ ዛሬ ባሰራጨው ዘገባ ላይ ‹አሸባሪ› ሊያስብለው የሚያስችል ትዕዛዝ ያስተላለፈበትን ወይም ንፁሃን ኢትዮጵያውያንን በተጠመደ ፈንጂ ዶግ-አምድ እንዲሆኑ መቀስቀሱን የሚያጋልጥ ሳይሆን፣ በሰላማዊም ሆነ በትጥቅ ትግል ከተደራጁ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት ጋር ያደረገውን ቃለ- መጠይቅ ብቻ በመደጋገም ነው፡፡ ለዚህም ይመስለኛል የዘጋቢ ፊልሙ ድብቅ ዓላማ ስርዓቱ በሀገር ውስጥ ያሉትን ጥቂት የግል የሕትመት ሚዲያዎች በፈርጣማ የፖለቲካና ቢሮክራሲ ክንዱ ደቁሶ ካኮሰመነ በኋላ፣ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ድምፅ ላጡት ድምፅ መሆን እየቻለ የመጣውን እና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች አማራጭ የሚዲያ ምህዳር የፈጠረውን የቴሌቪዥን ጣቢያ ከተለመደው የአፈና መንገድ /ጃሚንግ/ በተለየ ስልት ከጨዋታ ውጪ ለማድረግና በቀጣዩ ምርጫ ‹አውራ ፓርቲ›ነቱን ለማስጠበቅ የሚያደርገው ዝግጅት ነው እንድንል የተገደድነው፡፡

ከዚህ ቀደም እነ እስክንድር ነጋ በግንቦታ 7 አባልነት ተወንጅለው በታሰሩበት ወቅት አቶ መለስ ዜናዊ ለፓርላማው ‹‹ክምር ማስረጃ አለን›› ቢልም፣ ጉዳዩ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ግን በጨበጣ እንደገባበት ማየታችን አደባባይ የወጣ ሀቅ ነበር፤ በርግጥም ማስረጃ ሆኖ የተቆጠረው ራሱ ያዘጋጀው ‹‹አኬልዳማ›› የሚል ‹‹ዘገቢ ፊልም›› እንደነበረ ስንመለከት፣ ይህ ስርዓት አስቀድሞ የተናገረበት ጉዳይ ስህተት መሆኑ እንዳይጋለጥ ምንም ነገር ከማድረግ እንደማይመለስ እንታዘባለን (በነገራችን ላይ በወቅቱ በፍትህ ጋዜጣ ‹‹አኬልዳማው! የአይሁድ ወይስ የኢህአዴግ?›› በሚል ርዕስ የዘገባውን ፈጠራነት በተጠናከረ ማስረጃ ለማጋለጥ ከተሞከረ በኋላ እንዲህ የሚል ምክር አዘል ቁም-ነገር ተላልፎ እንደ ነበር አይዘነጋም፡-

‹‹ሆሊውድ የሚሰሩ አስፈሪ (ሆረር) ፊልሞች እንኳ ቢያንስ ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች እንዳያዩአቸው የሚከለክል ሕግ አለ፣ ኢቲቪ ግን የተበጠሰ አንገት፣ የተገነጠለ ክንድ፣ የተቆረጠ እጅ፣ የተፈረከሰ ጭንቅላት… እያሳየ፣ ‹13 ዓመት የሞላው ሕፃን በሙሉ ሊያየው ይችላል› ማለቱ ኃላፊነት የጎደለው አሰራር ነው››

ባለፈው ሳምንት በቀረበው ፊልም ላይ ቢያንስ ይህ ሁኔታ ታርሞ ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች ሊያዩት እንደማይገባ ከሚያስጠነቅቅ መልዕክት ጋር መተላለፉ ስርዓቱ ምክር መስማት ጀመረ እንዴ? እንድንል የሚያጭር ነው፡፡ በርግጥም በሌሎች ጉዳዮችም እንዲህ ቢያዳምጡን ኖሮ፣ እየዋጣቸው ካለው ጥልቅ ጨለማ ራሳቸውን መታደግ የሚችሉበት በርካታ ዕድል ነበር፡፡)

የሆነው ሆኖ በዚህና መሰል ፊልሞች ላይ የሚነሳው ሌላው ለትዝብት የሚያጋልጠው ጉዳይ የደህንነት ተቋሙ ሁሉንም ዜጋ አብጠርጥሬ አውቃለሁ የሚለው ማንአህሎኝነቱ ነው፡፡ አስቂኙ ጉዳይ ግን በአዋጅ የተቋቋሙት የመረጃው መስሪያ ቤት እና የፀረ-ሽብር ግብረ-ኃይል፣ ያሻቸውን ዜጋ ቤት (በስውርም በግልፅም) መበርበር፣ ስልክ መጥለፍ፣ የኢ-ሜል እና የማሕበራዊ ሚዲያዎችን አካውንት ‹የሚስጥር ቁልፍ ቃላት› ሰብሮ መፈተሽ… ከሚያስችል ያልተገደበ ሥልጣን ጋር የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፣ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እንደ አዋጭ መፍትሄ የወሰዱት ‹ዶክመንተሪ ፊልም›ን እስኪመስል ድረስ በሳምንት አንዴ መመልከቱ የተለመደ መሆኑ ነው፡፡ ርግጥ እንዲህ አይነት ትዕይንቶች ተጨማሪ ስርዓታዊ ጠቀሜታቸው ማህበራዊ ተቀባይነታቸው የጎላ ዜጎችን በስቅየት (ቶርቸር) እያንበረከኩ በቴሌቭዥን መስኮት አንገት አስደፍተው በማቅረብ ትውልዱ ተጠራጣሪና ድንጉጥ እንዲሆን ያላቸው አስተዋፆኦ አንዱ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ይህው ቃል በሚከሰሱት ንፁሀን ላይ ተመልሶ እንደ ማስረጃ ተቆጥሮ፣ ከአስር ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ የሚደርስ ቅጣት በ‹ካንጋሮው› ፍርድ ቤት እንዲጣልባቸው የሚያደርገው ግፈኝነት ነው፡፡ ለዚህም ቅጥ ያጣ አምባገነንነት አይደፈሬ ሥልጣኑ የሰጠውና ገና ሲረቅቅ ጀምሮ ጠንካራ ተቃውሞ ሲቀርብበት የነበረውን የፀረ-ሽብር አዋጅን የሕጋዊነት ከለላ አድርጎ እየተባባሰ በመጣ መልኩ መጠቀሙን መቀጠሉ ነው፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የታተመው ‹‹ኒውስ ዊክ›› መፅሄት ‹‹Ethiopia declares war on [deleted] men›› በሚል ርዕስ ባስነበበው አደገኛ መጣጥፍ አዋጁን ያብጠለጠለበት ሀረግ የትችቶቹን ሙሉ መንፈስ የሚጠቀልል ይመስለኛልና እዚህ ጋር ልጥቀሰው፡-

‹‹የፀረ-ሽብር ሕጉ መንግስት ሽብርተኝነት ብሎ የሚያስበውን ጉዳይ በ‹መፃፍ፣ ማቀናበር፣ ማተም ወይም ማሰራጨት› የሚከሰውን ዜጋ በሃያ ዓመታት እስር እንዲቀጣ ፈቅዶለታል፡፡››

እነዚህን ነገሮች ጠቅልለን ስንመለከት ገዥው ፓርቲ ለሀገሪቱ ስጋት እንደሆነ የሚነግረንን ሽብርተኝነት ራሱ ባዘጋጀው ሕገ-መንግስት ሳይሆን፣ በዶክመንተሪ ፊልም ጎርፍ ለመግታት ነው የተዘጋጀው ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ በርግጥ የፓርቲው አላማ ሥልጣኑን መጠበቅ ነውና ሕገ-መንግስቱን ወዲያ ጥሎ ዘጋቢ ፊልሞች ላይ ቢንጠለጠል እንዴት ልንገረም እንችላለን?!

ወደ የፍርሃት ‹ሪፐብሊክ›

ይህች መከረኛ ሀገር በደርግና በኢህአዴግ ከተሠጣት ቅጥያዎች አንዱ ‹‹ሪፐብሊክ›› የሚል እንደሆነ ይታወቃል (የደርጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሲል፤ ይህኛው ደግሞ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ነች ይለናል)፡፡ ዝርዝር ሃተታውን

ትተን ከዚህ ፅሁፍ አውድ አንፃር የሪፐብሊክን ብያኔ ሕዝባዊ መንግስትነት የሚል ትርጓሜ ሰጥተን ማለፍ ይበቃል፡፡ ይሁንና የተሻገርናቸው ሁለት አስርታት የሚያስረግጡት ብቸኛ እውነት ቢኖር ሀገሪቱ ከዚህ የተጠያቂ መንግስት ምስረታ ተፃራሪ የሆነውን መንገድ መምረጧን ነው፡፡ ከላይ ለማሳያነት የጠቀስኩት ዶክመንተሪ ፊልምም ሆነ ተያያዥ አፋኝ ሕጎቹ እና ፖለቲካዊ አተገባበራቸው በፍርሃት የሚርድ ማሕበረሰብ በመፍጠር፣ ቀጣይ አስርታቱን ካለአንዳች መደነቃቀፍ ረግጦ መግዛትን ዋነኛ ግብ ያደረጉ ናቸው፡፡ ይህን ተቋማዊነትን ተደግፎ የሚካሄደው መንግስታዊ ሽብር፣ በአንዳች ክስተት ብርክ በሚያናውጣቸው ዜጎች ማሕበረሰቡ እየተሞላ እንደሚሄድ ግልፅ ነው፤ ከፌደራላዊ ወደ ፍርሃት ሪፐብሊክ እየተደረገ ባለው በዚህ ጉዞ፣ ሀገሪቱን ከዝግመታዊ ሞት ለመታደግ የበረቱ መዳረሻቸውን ስርዓቱ አዘጋጅቷል፡፡ እናም ዋጋው ምንም ቢሆንም በአደባባዩ ላይ የሚደረግ የተቃውሞን እንቅስቃሴ፣ ኢህአዴግን ከሥልጣን የማውረድ ብቻ ከመሆን መታለፉን በሚገባ ልናስብበት እንደምንገደድ ይሰማኛል፡፡ እነርሱ ከሚቀጥለው ምርጫ በፊትም ሆነ በኋላ ሕዝባዊ ምህዳሩን ምንም አይነት የተቃውሞ ድምፅ የማይሰማበት ምድረ-በዳ ለማድረግ ይህን ያህል ርቀት መጓዛቸውን ስንመለከት ምርጫችን ሁለት ብቻ ይሆናል፡፡ ቀጣዩን ትውልድ በፍርሃት ሪፐብሊክ ውስጥ ትቶ ማለፍ፣ አሊያም አደባባዩን በጨኸት መሙላት፡፡

ኢትዮሚድያ

ይሄ አደጋ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ የግዲያ ሙከራ ይሁን አሊያም በአጋጣሚ የተፈጠረ የእሳት ቃጠሎ ይሁን ማወቅ አልተቻለም።

የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት እና የዓረና ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የውብማር አስፋው ጋር በመሆን በመኪና እየሄዱ እያለ ድንገት መኪናቸው በእሳት መያያዟን የተመለከቱ ሰዎች ባደረጉላቸው ጥቆማና ርብርብ ከእሳቱ ቃጠሎ ለጥቂት መትረፋቸውን ማወቅ ተችሏል። በመኪናዋን ግን እዚያ የነበረው ሰው ሁሉ ብዙ ርብርብ ቢያደርግም ከቃጠለው ማተረፍ አልተቻለም። በእውነቱ ይህን መረጃ እንደደረሰኝ አላመንኩም ነበር፤

በመሆኑም ወዲያው ወደ አቶ ገብሩ አስራት ስልክ ደውዬ እውነት መሆኑን ማረጋገጥ ችያለሁ። ነገር ግን የአቶ ገብሩ ባለቤት ወ/ሮ የውብማር አስፋው ህወሃት ባካሄደው የትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም ሚና ከነበራቸው ጥቂት ሴት ታጋዮች ውስጥ የሚመደቡ እና “ፊኒክስዋ ሞታም ተነሳለች፥ ያልተቋጨው የትግራይ ሴቶች ትግል” የሚለውን መፅሐፍ የፃፉ ናቸው።
ለማነኛውም ለአቶ ገብሩ አስራት እና ለባለቤታቸው ወ/ሮ የውብማር አስፋው እንኳን በህይወት አተረፋችሁ ለማለት እፈልጋለሁ።

ግርማይ ገብሩ የቀድሞ የህወሓት ታጋይና የአሁን የቪኦኤ (VOA) ዘጋቢና ደራሲ ነው። ዓላማዬ ስለ ግርማይ ገብሩ ለመፃፍ አይደለም፤ ግርማይ በፌስቡክ ገፁ ስላሰፈረው መረጃ ለመዋስ እንጂ። መረጃው ከዚህ በፊትም አውቀው ነበር። ግን ለማስረጃ ያህል ግርማይን ልጥቀስ: ምክንያቱም ግርማይ የህወሓት ታጋይ ነበርና።

ግርማይ በ1969 ዓም የህወሓት (ተሓህት) ሦስቱ መፈክሮች ሲጠቅስ የመጀመርያውና ዋነኛው አድርጎ የፃፈው “አፄነት፣ መስፍንነትና የአማራ የበላይነት ይወድማሉ” ይላል።
በትግርኛ “ካብ ጭርሖታት ህወሓት 1969 ዓም: ሃፀይነት፣ መስፍንነትን ናይ አምሓራ ዕብለላን ዓነውቲ እዮም!” ይላል። ግርማይ ገብሩ አልተሳሳተም። ከህወሓቶች ጋር የማልስማማበት ግን ነጥብ አለኝ።

እርግጥ ነው። እኔም አፄነትና መስፍንነትን እንደ ስርዓት አልቀበልም። ምክንያቱም አፄነትና መስፍንነት (እንደ ስርዓት) ላሁኗ ኢትዮጵያ አይመጥኑም። የአፄነትና መስፍንነት ስርዓት በኢትዮጵያ ታሪክ እዚ ግባ የሚባል ለውጥ አላመጣም። ስለዚህ እኛ የሚያስፈልገን ዘመናዊ (ከዘመኑ ንቃተ ህሊናችን ጋር አብሮ የሚሄድ) የህዝብ አስተዳደር (ዴሞክራሲ) እንጂ ንጉስነት (የሰው ገዢነት) አይደለም። የምንፈልገው የሕግ የበላይነት እንጂ የንጉስ የበላይነት አይደለም።

ግን አፄነትና መስፍንነት እንደ ስርዓት ባልቀበለውም የንጉሳውያን ቤተሰቦችና መሳፍንቶች መጥፋት አለባቸው ብዬ ግን አላምንም። እኔ ብሆን እነኚህ የንጉስ ቤተሰቦችና መሳፍንት ቁልፍ የመንግስት ስልጣን አልሰጣቸውም ነበር። በሀገራቸው በሰላም እንዲኖሩ ግን እፈቅድላቸው ነበር። ምክንያቱም እንደማንኛውም ሰው ዜጎች ናቸው፤ ለሀገራቸው በተቻላቸው መጠን አስትዋፅዖ አድርገዋል። ስለዚህ ንጉሳዊ ቤተሰብና መሳፍንት ስለሆኑ ብቻ መጥፋት አለባቸው ብዬ አልፈርድም። እንደ ጠላትም አላያቸውም፣ እንደ ዜጎች እንጂ።

ህወሓት ግን በመፈክር ደረጃ በጠላትነት ፈረጃቸው። በተግባርም አጠፋቸው፣ ገደላቸው። በንጉሳዊ ቤተሰብና መስፍንነት ዝንባሌዎች ሰበብ ብዙ የተምቤን፣ ዓጋመ፣ እንደርታ፣ ዓድዋ፣ ሽረ፣ አክሱም ወዘተ መሳፍንቶች እንዲጠፉ ተደረገ። ‘ትግራይ ከመሳፍንቶች ነፃ ወጣች’ ተባለ። እውነታው ግን ‘ትግራይ ተገደለች’ መባል ነበረበት። መሳፍንቶች ከስልጣን ማውረድ እየተቻለ መግደል ምን አመጣው (ህወሓቶች ከስልጣን ማውረድ እየተቻለ መግደል ለምን ያስፈልጋል)?

ባጠቃላይ መሳፍንቶቹ ሲወድሙ ትግራይ ወደመች። አሁን በትግራይ የተቃውሞ መንፈሱ የተዳከመው በመስፍንነት ሰበብ ብዙ ብቁ ሰው ስለተፈጀብን ነው የሚል እምነት አለኝ። በህወሓት የተገደሉብንን ያህን በሌላ ስርዓት አልተገደሉብንም። ስለዚህ መሳፍንቶች ከስልጣን በማውረድ (መሳፍንቶችን ሳይሆን መስፍናዊ ስርዓቱ) ከህወሓቶች ጋር እስማማለሁ። መስፍናዊ ስርዓቱ ለማጥፋት መሳፍንቶቹ ማጥፋት ከሚል የህወሓት መፈክር ወይ መርህ ግን አልስማማም።

ሌላውና መሰረታዊ የህወሓት ችግር “የአማራ የበላይነት ይውደም!” የሚል መፈክር ነው። እኔም ብሆን የማንም ሰው ወይ ብሄር ወይ ሌላ አካል የበላይነት አልቀበለም። የቴድሮስ ወይ ዮሃንስ ወይ ምኒሊክ ወይ ኃይለስላሴ ወይ መንግስቱ ወይ መለስ ወይ ኃይለማርያም ወይ አማራ ህዝብ ወይ ትግራይ ህዝብ ወይ ኦሮሞ ህዝብ ወይ ሌላ … የበላይነት አልቀበልም። እኔ የምቀበለው የበላይነት ‘የሕግ የበላይነት’ ብቻ ነው። የሌላ የማንም የበላይነት አልቀበልም።

እንደ ፖለቲካ ድርጅት አንድን ህዝብ ዒላማ አድርጎ መነሳት ግን ስህተት ብቻ ሳይሆን በሽታ ነው። ህወሓት (ተሓህት) የአማራን ህዝብ ዒላማ አድርጎ ሲነሳ፣ ሌሎች የህወሓት ተቃዋሚዎች ደግሞ በህወሓት ምክንያት የትግራይን ህዝብ ዒላማ ሲያደርጉ ዉጤቱ ምን ይሆናል? አንድን ህዝብ ከሌላ ህዝብ ጋር የማጣላት ስትራተጂ የፖለቲካ ዕብደት ነው። ህዝብና ገዢው መደብ አለመለያየት (አንድ እንደሆኑ አድርጎ ማሰብ) የፖለቲካ እውቀት ማነስ ዉጤት ነው። ስርዓቱ መቃወምና መታገል እየተቻለ ህዝብን ዒላማ አድርጎ በህዝቦች ላይ መተማመን እንዳይኖር መትጋትና በህዝቦች መካከል ጥላቻ እንዲነግስ መስራት ጠባብነት ነው።

አንድን ህዝብ የበላይነት ሊይዝ አይችልም። አንድን ቡድን ግን በአንድን ህዝብ ስም በመነገድ ሌሎችን ሊበድል ይችላል። የሰው የበላይነት (በህዝቦች ላይ) ሊተገብር ይችላል። ህዝብ እንደ ህዝብ ግን ሌላውን ህዝብ ሊበድል አይችልም። ህወሓት የትግራይን ህዝብ እንደሚወክል ይነግረናል። የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ እያለ ሌሎች ህዝቦች (የትግራይን ጨምሮ) ይበድላል። ሌሎች ህዝቦች (የትግራይ ዉጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን) ደግሞ በህወሓት ስርዓት ሲበደሉ በትግራይ ህዝብ የተበደሉ አድርገው ያስባሉ። ግን ስህተት ነው። መታረም አለበት። የትግራይ ህዝብ ለራሱ በህወሓት አገዛዝ የሚበደል ነውና።

“የአማራ የበላይነት” የሚባለው የህወሓት በሽታ እስካሁን ፈውስ አላገኘም። በመርህ ደረጃ ህዝብን ዒላማ አድርጎ ህዝብን ለመታገል መነሳት ስህተት ነው ብያለሁ። በፖለቲካ ህዝብን ዒላማ አይደረግም። ምክንያቱም የፖለቲካ ዓላማ ህዝብን ማገልገል እንጂ ህዝብን መጨቆን አይደለም። ስለዚህ ህዝብን የመበደል ዓላማ መያዝም መተግበርም የህሊና ወንጀል ነው። ህወሓቶች ይህን በሽታ (“የአማራ የበላይነት” መፈክር) አልተዋቸውም። አሁንም “ፀረ አማራ” እንቅስቃሴዎች አሉ። የህወሓት የአሁኑ ስትራተጂ “እኛ ከስልጣን የምንወርድ ከሆነ ከአማራ ጋር አብረን አንቀጥልም” የሚል ገንጣይ አስተሳሰብ እያራመዱ ይገኛሉ። “እኔ ከሌለሁ ሠርዶ አይብቀል …” ዓይነት ስትራተጂ መሆኑ ነው። በጣም የሚገርመው ነገር ፀረ ብአዴንም መነሳታቸው ነው። ለነሱ ከስልጣን ከሚወርዱ ኢትዮጵያ ብትበታተንና ትግራይን አስገንጥለው ትግራይን እየጨቆኑ ቢገዙ ይመርጣሉ።

ግን ይህን “አማራ” የሚባል ህዝብ መቼ ይሆን የበላይነት ይዞ ሌሎች ህዝቦችን የበደለው? አንድን ህዝብ እንዴት ሌላውን ህዝብ ይበድላል? ህዝብ ህዝብን ሊበድል አይችልም። ምክንያቱም አንድን ህዝብ ሌላውን ህዝብ መበደል ከጀመረ (ከቻለ) ህዝብ መሆኑ ቀርቶ ገዢ መደብ (elite) ሁነዋል ማለት ነው። ገዢ መደብ ከሆነ ደግሞ ህዝብ አይደለም። ገዢ መደብ ስርዓት ነው። ህዝብና ስርዓት ደግሞ ይለያያሉ።

ምናልባት የህዝብ የበላይነት አለ የምንለው ህዝብን የሚያስተዳደር (የሚገዛ) ስርዓት ከህዝቡ የወጣ ሲሆን ይሆን? ይህም አሳማኝ አይደለም። ምክንያቱም ገዢ ሁሌ ከህዝቡ ነው የሚወጣው (የቅኝ ግዛት ካልሆነ በስተቀየር)፤ ገዢ ከህዝቡ እንጂ ከማርስ አይመጣም። የኢትዮጵያ መሪ ከኢትዮጵያ ህዝብ ይወጣል። በኢትዮጵያ ብዙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሉ። ስርዓቱ ከሁሉም ህዝቦች ሰዎች ይኖሩታል። መሪ ግን አንድ ነው የሚሆነው። ያ አንድ ሰው (መሪው) ከአንድ ብሄር ሊሆን ይችላል። ያ አንድ ሰው ስልጣኑ ተጠቅሞ ሌሎች ህዝቦችን ሊበደል (ወይ ሊጠቅም) ይችላል። ሰውየው የፈጠረው ስርዓት ለህዝቡ ቢጎዳም ቢጠምም ከስርዓቱ ይገናኛል እንጂ መሪው ከመጣበት ብሄር ጋር አይገናኝም። ስለዚህ ገዢዎች የሚወክሉት የፈጠሩትን ስርዓት እንጂ የመጡበትን ብሄር አይደለም።

የደርግ ስርዓት ሲበድለን፣ “አማራ በድሎናል” ይሉናል። የኃይለስላሴ ስርዓት ሲበድለን “አማራ በድሎናል” ይሉናል። የምኒሊክ ስርዓት ሲበድለን “አማራ በድሎናል” አሉን። የህወሓት ስርዓት ሲበድለንስ ማን በደለን ሊሉን ነው? የትግራይ ህዝብ? አይሆንም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ የትግራይን ህዝብ ይበድላል? አንድን ህዝብ ራሱን ይበድላል? በደል ሁሉ ወደ አማራ ህዝብ ለምን? ስርዓትና ህዝብ ማገናኘት የፖለቲካ ኪሳራ ያስከትላል።

ግን እስቲ ይሁን፤ መሪዎች የመጡበትን ብሄር ይወክላሉ እንበል (ስህተት ቢሆንም)። እነሱ (መሪዎቹ) ሲበድሉ የመጡበት ብሄር በበዳይነት ተፈርጆ እንደ ጠላት ይቆጠር እንበል። የአማራ ህዝብ መቼ ይሆን በመሪዎቹ አድርጎ ሌሎች ህዝቦችን የገዛ (የበደለ)? ያለፉ ጨቋኝ ስርዓቶች አማራ ነበሩ ያለው ማነው? አማርኛ የተናገረ ሁሉ አማራ አይደለም። እስቲ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ መሪዎች እንመልከት።

ብዙ ግዜ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ የሚጀምረው ከአፄ ቴድሮስ ነው (ወይም ከዚሁ እንጀምር! ምክንያቱም ከአፄ ቴድሮስ በፊት ኢትዮጵያ በመሳፍንቶች ነበር የምትተዳደረው። በዘመነ መሳፍንት መሳፍንቶች የራሳቸውን ህዝብ (ብሄር) ይገዙና ይበድሉ ነበር)። “አማራ” ተብሎ ከተሰየመው አከባቢ የሚወለድ ገዢ ቴድሮስ ነው። አፄ ቴድሮስ ኢትዮጵያ አንድ ለማድረግ በዛን ግዜ የነበሩ መሳፍንቶች ተዋጉ። አፄ ቴድሮስ ዉግያው የጀመሩት በአማራ መሳፍንቶች (የጎጃም፣ ወሎና ጎንደር) ነበር። ቴድሮስ “ከአማራ ስለመጣሁ፣ አማራ ስለምወክል፣ የአማራ መሳፍንቶች ማጥፋት የለብኝም” አላሉም። (ህወሓት ለትግራይ መሳፍንቶች እንዳደረገው ሁሉ)። ስለዚህ አፄ ቴድሮስ አማራን ወክለው ሌላው ኢትዮጵያዊ አልበደሉም (ከበደሉም ለሁሉም ነው)። ስለዚህ “በአማራ ህዝብ ተገዛን” የሚለው ክስ “በአፄ ቴድሮስ ተገዛን” የሚል እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ።

የአማራ ተወላጅ የሆነ የኢትዮጵያ ገዢ ቴድሮስ ብቻ ነው ብዬ አስባለሁ (ጉዳዩ ለታሪክ ተመራማሪዎች ልተወው እንዳልሳሳት፤ ከተሳሳትኩ እታረማለሁ)። ዮሃንስ አማራ አልነበረም፣ ምኒሊክ አማራ አልነበረም፣ ኃይለስላሴ አማራ አልነበረም፣ መንግስቱ አማራ አልነበረም፣ መለስ አማራ አልነበረም፣ ኃይለማርያም አማራ አይደለም። ማነው አማራ?

ምናልባት “የአማራ ገዢዎች” የምንለው ግለሰቦቹ (ንጉሶቹና መሪዎቹ) ሳይሆን ስርዓቱ ነው ካልን ያው ስርዓቱማ ከሁሉም ህዝቦች ተወካዮች አሉበት። አማራ ለብቻው ገዥ ነበር ማለት አንችልም። ምናልባት ገዢዎቹ አማርኛ ስለሚናገሩ ነው ካልን ደግሞ አማርኛ የተናገረ ሁሉ አማራ አይደለም። አቶ መለስም አማርኛ ይናገር ነበር። አፄ ዮሃንስም አማርኛ ይናገሩ ነበር (አማርኛ የኢትዮጵያ ኦፊሽየላዊ የስራ ቋንቋ እንዲሆን የወሰኑት አፄ ዮሃንስ ናቸው የሚል መረጃ አለኝ፤ ‘መረጃ’ እንጂ ‘ማስረጃ’ አላልኩም)።

የአማራ ህዝብ እንደ ማንኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በኢትዮጵያ ገዢዎች ሲሰቃይ የነበረ ነው። ባልበላበት በልተሃል፣ ባልገዛበት ገዝተሃል ሲባል ይገርማል፤ ልክ እንደ ትግራይ ህዝብ። የትግራይ ህዝብ ሳይበላ በልተሃል፣ ሳይገዛ ገዝተሃል ይባላል፤ ህወሓት በበላው፣ ህወሓት በገዛው። ህወሓት ትግርኛ ተናጋሪ ስለሆነ ከትግራይ ህዝብ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም (በፖለቲካ መልኩ)። ያለፉ ገዢዎች አማርኛ ስለሚናገሩ ከአማራ ህዝብ ጋር የሚያገናኛቸው ነገር የለም። ህዝብ ሌላ ገዢ ሌላ።

ባጭሩ ፀረ ህዝብ አቋም መያዝ ተገቢ አይደለም (ለማንኛውም ህዝብ)። ሰው የፈለገውን የፖለቲካ አመለካከት መያዝ ይችላል። “የቀድሞ ስርዓት አባላት …” ምናምን እያልን አንፈርጅ። የህወሓት አባላት ለሌሎች ሰዎች የቀድሞ ስርዓት አባላት፣ ናፋቂዎች ወዘተ እያላቹ ስትፈርጁ እናንተም ራሳችሁ ከህወሓት ስርዓት በኋላ “የቀድሞ ስርዓት አባላት ..” ምናምን እየተባላቹ ስማቹ ይጠፋል፣ የፈለጋችሁን የፖለቲካ ፓርቲ አባል የመሆን መብታቹ ይገደባል። አሁን በሌሎች ላይ የምትፈፅሙትን ስም የማጥፋት ተግባር በናንተ (በራሳቹ) ይፈፀማል።

ስለዚህ እናስተውል። ከጥላቻ ፍቅር ይሻለናል። ጥላቻ ይውደም። አሜን!

It is so!!!

ምንሊክ ሳልሳዊ:-የትርፍ ሰአት ፖለቲካ በህዝብ ላይ የሚሴር ያልታወቀ እና ያልተነቃበት ሴራ ነው::ይህ ማለት ፖለቲከኞቹ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በሃሊዮ ወላ በገቢር የህዝብን የመኖር ደህንነት አደፍርሰዋል ::ራሳቸውንም ኢእውቀታዊ ወደሆነ የፖለቲካ ኪሳራ አዘቅት ልከውታል:: ታዲያ ለእነዚህ የትርፍ ሰኣት ፖለቲከኞች ወይም ሴረኞች እንበላቸው ጸረ ህዝብ እና ጸረ ሰላም የሚል ታርጋ ይነሳቸው = ወያኔን አሸባሪ ማፊያ አድፍጦ ገዳይ አፋኝ ወዘተ ስንለው እነዚህን ታቃዋሚ እና ታማኝ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ሂደታቸው ላይ ያልነቁ ደበኞች ብንላቸው ሲያንሳቸው ነው::

ተቃዋሚ ፖለቲከኝነት በብዛት የትርፍ ሰአት ስራ የሆነባት ኢትዮጵያ አንድም ከወያኔ ቅጥረኝነት ሌላም ከፖለቲካ ከሚገኘው ጥቅም የተትረፈረፈ የህይወት ስኬት ለማግኘት የሚደረግ ሩጫ አስመስሎታል::ያለፉት 22 አመታት መለስ ብለን ስናስበው የሽግግር ወቅት እንዲመሰረት ወያኔ ከፈጠራቸው የአናሳ ድርጅቶች እና በኋላም በተቃዋሚ ስም እንዲንቀሳቀሱ ተደርገው የምክር ቤት ወንበር እስከመያዝ የደረሱት ፖለቲከኞች አንድም የዩንቨርስቲ መምህር ናቸው አሊያም የግል ስራቸውን የሚያሯሩጡ እና በትርፍ ሰኣታቸው ገንዘብ ላለማጥፋት ወደ ፖለቲካው ያዘነበሉ አሊያም ከገዢው ፓርቲ ዳጎስ ያለ ጉርሻ አግኝተው የሚኖሩ ግለሰቦች ናቸው::

የትርፍ ሰአት ፖለቲካ የሚመነጨው ከግለኝነት ስለሆነ በሃገር ላይ የሚደረጉ ህዝባዊ አብዮቶችን እና ለውጦችን በምናገባኝነት ስሜት(አስመሳይነት) እንዲመለከቱት ያደርጋል;ፕሮፓጋንዳን ብቻ ለፖልቲካ ፍጆታነት የመጠቀም ስልት ማለትም ነው::ግለኝነት ስንል ፖለቲከኛው በፖለቲካው ረገድ መጫወት ያለበትን ሚና ረስቶ ከፖለቲካው ከሚገኘው ጥቅም ላይ ስለሚያተኩር ሲሆን ህዝባዊነትን ገደል ይከተዋል:: ወያኔዎች እያንዳንዳቸው ፖለቲካውን ስራዬ ብለው ስለያዙት በፖለቲካው መስክ ያላቸው ስኬት በዲሞክራሲ ስም ወደ አምባገነንነት አድጓል::

የትርፍ ስራ ፖለቲካ ሌላ ያዋጣቸው ለታማኝ ተቃዋሚዎች ነው::ታማኝ ተቃዋሚዎች ከተቃሚነት ሌላ የፖለቲካ ስለላ ያካሂዳሉ:: የፈለጉትን የትምህርት ዘርፍ ይማራሉ::አስፈላጊው የውስጥ እና የቅርብ ርቀት ጥበቃ ይደረግላቸዋል::በዚህ ላይ በስልጣን እርከን እንደመምሪያ ሃላፊ የመሳሰሉትን ስልጣኖች ይሰጣቸዋል:: ከዛም ስልጣን ሰበብ ለማስመሰል ይባረራሉ::አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የህዝብ ጥያቄ ሲነሳ ከትርፍ ስራ ተቃዋሚነት ወደ ቋሚ ፖለቲከኝነት በጊዜያዊነት ተመሳስለው ገብተው እንዲያከሽፉት ይደረጋል:: አቤት ታማኝ ተቃዋሚዎች የመንግስትን ወንበር ከያዙት ይልቅ እኮ እነሱ የተመቻቸው ናቸው::

የትርፍ ሰአት ፖለቲካ እያራመዱ ሃገርን እና ህዝብን የፖለቲካ ኪሳራ ላይ የጣሉ የ22 አመታት የፈጠራቸው ተቃዋሚ ፖለቲከኞች አሁን አሁንማ የኪሳራቸው ውጤት ስድብ ብቻ ሆነ::የትም ላይደርሱ እየተፈራገጡ:: ባለፉት 22 አመታት ጫካ ገብተው ቢሆን እስካሁን የመንግስትን ስልጣን ይዘው ባናፉብን ነበር::በጎረሩብን ነበር:: እኛም ወያኔ ጭራቁን አስወገዱ ብለን ባከበርናቸው ነበር:: እነ ሽማግሌዎቹ ጡረተኛ ፖለቲከኞችም ቢሆኑ በቋሚነት ስላለባቸው ደምብዛት እና ሰኳር ማስታመም ጋዜጣ ማንበብ እና መጻፍ በትርፍ ሰኣታቸው ህዝቡ ትዝ ሲላቸው ተነስተው ይህችኑ ፖለቲካቸውን ይተነፍሱብናል::

ገና በጠዋቱ “ዓሰብን ማስመለስ አለብን የምትለው እንዴት ነው? ወደ አላስፈላጊ ጦርነትና ደም ማፋሰስ ልታስገቡን ፈለጋቹ?” የሚል አስተያየት አዘል ጥያቄ አገኘሁ።

መጀመርያ ወደ ጭንቅላታችን መምጣት ያለበት ጉዳይ ‘የዓሰብ ወደብ የማነው?’ የሚል ነው። ዓሰብ የኢትዮጵያ ልአላዊ ግዛት (ንብረት) ስለመሆኑ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ሕጋዊ (በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት) ማረጋገጫዎች አሉን። ዓሰብ የኛ ስለመሆኑ የሚያጠራጥር ምንም ምክንያት የለም። ማስረጃዎቹ (ማረጋገጫዎቹ) እዚሁ ፌስቡክ ላይ ባልፅፋቸውም በወደቡ ባለቤትነታችን ጥርጣሬ አይግባቹ። ስለዚህ ጥያቂያችን ፍትሐብሄር ነው።
ሁለተኛ ጉዳይ ዓሰብ የኛ ቢሆንም አሁን ያለው ግን በኤርትራ ቁጥጥር ስር ነው። ንብረት ሃብታችን ተነጥቀናል ማለት ነው። ጥያቄው መሆን ያለበት ‘ዓሰብ ወደብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል?’ የሚል ነው። መልሱ: ‘አዎ! ያስፈልጋታል’ ነው። የባህር በሯን የተነጠቀች ብቸኛዋ ትልቅ ሀገር ኢትዮጵያ ናት። በአሁኑ ግዜ የባህር በር የአንድ ሀገር የህልውና በር ነው። የህልውና በሩ መዘጋት የለበትም። ስለዚህ ኢትዮጵያ ንብረቷ (ወደቧ) የማስመለስ መብትም ታሪካዊ ግዴታም አለባት።

ሦስተኛ ‘እንዴት ነው ወደቡን ማስመለስ የምንችለው?’ የሚል ጥያቄ ማየት ተገቢ ነው። ምክንያቱም ዓሰብ የኢትዮጵያ ቢሆንም በመሪዎቻችን ሐላፊነት የጎደለው ዉሳኔ ምክንያት ለኤርትራ ተሰጥቶ ይገኛል። ‘ወደባችን አለ አግባብ ለኤርትራ በመሰጠቱ ምክንያት ዓሰብን የማስመለስ ጉዳይ ከባድ ሊያደርገው ይችላል’ የሚል ሐሳብ ቢነሳ አግባብነት አለው። ጦርነትም ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ሊቀቅ ይችላል።
ግን ማትኮር ያለብን ስለ ጦርነት አይደለም፤ ስለ ዓሰብ ንብረትነት እንጂ። ዓሰብ የኛ መሆኑ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ማረጋገጥ (ማሳመን) ይኖርብናል። በዓሰብ ጉዳይ ፅኑ አቋም ይዘን የኢትዮጵያም የኤርትራም ህዝብ እንዲገነዘበው መጣር አለብን። የዓለም ህዝብ ይሁን መንግስትታት ይደግፉናል። ምክንያቱም የባለቤትነት መከራከርያ ነጥባችን ጠንካራ ነው። የዓለም አቀፍ ሕግም ይደግፈናል። ዓሰብ የኢትዮጵያ ስለ መሆኑ የሚመሰክግሩ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ ስምምነቶችም አሉ።
አራተኛ ዓሰብ የኛ መሆኑ ቢናረጋግጥና ለዓለም መንግስታትና ማህበረሰብ ቢናሳውቅ እንኳ እንዴት ዓሰብን መመለስ እንችላለን? የኤርትራ መንግስትኮ ፍቃደኛ አይሆንም፣ ጦርነት ሊነሳ ይችላል … ወዘተ የሚሉ ጉዳዮች መነሳታቸው አይቀርም። ግን ችግር የለውም። ዓሰብ የኛ መሆኑ ካረጋገጥን ‘ንብረታችን መልስልን’ ብለን የመጠየቅ መብት አለን። የኤርትራ መንግስት ፍቃደኛ ላይሆን ይችላል። ጦርነትም ሊከፍት ይችላል።
እኛ ጦርነት አንፈልግም። ሕጋዊ ንብረታችን (ወደባችን) በሰለማዊ መንገድ እንዲሰጠን ነው የምንጠይቀው። አዎ! ጦርነት አንፈልግም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ግን ጦርነት ከፍተን በሃይል የሌላ ሀገርና ህዝብ ንብረት አንወርም ማለት እንጂ ጦርነት ፈርተን ልአላዊ ግዛታችን (ሃብታችን) ለሌሎች ሃይሎች አሳልፈን እንሰጣለን ማለት አይደለም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ጦርነት እንፈራለን ማለት አይደለም። አዎ! ጦርነት ስለማንፈልግ ሌሎች ህዝቦችን አንወርም። ጦርነት ፈርተን ግን እናት ሀገራችን አናስደፍርም።
ጦርነት ስለማንፈልግ ዓሰብን በሰለማዊ መንገድ የምንረከብበት መንገድ እናመቻቻለን። የኤርትራ መንግስት ጦርነት ሊከፍትብን ይችላል ብለን ግን ሃብት ንብረታችን ከመጠየቅ ወደኋላ አንልም። ጦርነት ተፈርቶኮ የሀገር ግዛት አሳልፎ አይሰጥም። ጦርነት ተፈርቶኮ ልአላዊ ግዛትን ከማስከበር ወደኋላ አይባልም። በባድመ ጉዳይ ጦርነት ዉስጥ የገባነው ጦርነት ስለምንፈልግ ሳይሆን ልአላዊ ግዛታችን የማስከበር፣ ሀገራችን ከወራሪዎች የመከላከል ሀገራዊ ግዴታ ስላለብን ነው። ጦርነት ፈርተን እጃችንና እግራችን አጣጥፈን የባድመን መሬት ለሻዕቢያ ወራሪዎች አሳልፈን አልሰጠንም።
(በኋላ በፖለቲካዊ ዉሳኔ፣ በመሪዎቻችን ግድየለሽነት ምክንያት ባድመን መስዋእት ከፍለን በደም አስመልሰን ሲናበቃ በእስክርቢቶ ለወራሪዎች ተላልፎ ተሰጠ እንጂ። በጦርነት የተመለሰ ንብረት በድርድር ሲከሽፍ በታሪክ ለመጀመርያ ግዜ ነው። የባድመ ጉዳይ …!)
ምንም እንኳ ጦርነት ባንፈልግም ሃብት ንብረታችን ግን አሳልፈን አንሰጥም። ጦርነት መስዋእት ይጠይቃል። ግን ለሀገራችን መስዋእት ብንከፍል ችግሩ ምንድነው? ለሀገራችንኮ መሞት አለብን። በምንክያት መስዋእት መሆን እንቻላለን። ደግሞኮ ኢህአዴጎች የዓሰብን ጉዳይ ስናነሳባቸው ‘ጦርነት ናፋቂዎች’ ይሉናል። እኔ ግን ለሀገር መስዋእት ብንከፍል ጉዳት የለውም ባይ ነኝ። እንኳንም ለሀገራችን ኢትዮጵያ ለሶማሊያም እየሞትን ነው። ይቅርታ ለሶማሊያም እየሞትን አይደለንም። ምክንያቱ ላልታወቀ ጉዳይ ነው በሶማሊያ እየሞትን ያለነው። ወታደሮቻችን በሀገረ ሶማሊያ እየሞቱ ያሉ ለምን ዓላማ ነው? ዜጎቻችን ዓላማው ለማይታወቅ ጉዳይ በሶማሊያ ከሚሞቱ ለሀገራችን ቢሞቱ አይሻልም ነበር? ኢህአዴጎች ‘ጦርነት ጥሩ አይደለም’ ይሉናል። ጦርነት ጥሩ አለመሆኑ ቢያውቁ ኑሮ ለምን በሶማሊያ ያሉ ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው አያስገቡም?
አዎ! ጦርነት ጥሩ አይደለም። በተቻለ መጠን ጦርነትን ማስወገድ አለብን። ጦርነት ፈርተን ግን ሀገራችንን አሳልፈን አንሰጥም።
አሜን!

Image

በአሁኑ ጊዜ ወያኔ ሰውን እያፈረሰ፣ ማህበረሰብን እያፈረሰ ሰማይ-ጠቀስ ሕንጻዎችን በሚሠራበት ጊዜ፣ ከትናንት ወዲያ የሰዎችን ቤቶች አፍርሶ ትናንት የመኪና መንገድ ከሠራ በኋላ ዛሬ መንገዱን አፍርሶ የባቡር መንገድ እየተሠራ አዲስ አበባ በትራፊክ መጨናነቅ መኪና መንዳት አደገኛ በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ባለሥልጣኖች የሚሠሩት ጠፍቶአቸው የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ የሚባለውን በአማካሪዎች ከሞሉት በኋላ ለሚኒስትሮችም አማካሪ መሾም በተጀመረበት ጊዜ፣ ዛሬ በሳኡዲ አረብያ ኢትዮጵያውያን እንደአደገኛ አውሬ እየታደኑ በሚደበደቡበት፣ በሚታሰሩበት፣ በሚደፈሩበትና በሚገደሉበት ጊዜ፣ ዛሬ በኬንያና በዩጋንዳ እንዲሁም በእሥራኤል ኢትዮጵያውያንን የማንገላታት ዝንባሌዎች በሚታዩበት ጊዜ፣ ዛሬ ኢትዮጵያውያን ከስዊድን እስከአውስትራልያ እየተሰበሰቡ በመጮህ ለማይሰሟቸው ሁሉ አቤቱታቸውን በሚያቀርቡበት ጊዜ፣ ዛሬ በተለያዩ አገሮች በኢትዮጵያውያን ላይ በሚፈጸመው ጥቃትና በደል፣ አለሁላችሁ የሚል መንግሥት በሌለበት ጊዜ —- ዛሬ ታሪካዊትዋ ኢትዮጵያ፣ ራሳቸውን የሚያከብሩና ኩራት ራታችን የሚሉት ኢትዮጵያውያን አልቀው ለሆድ በየሰው አገር መሰደድ ባህል በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ዶር. በድሉ ዋቅጅራ ስለኢትዮጵያና ስለኢትዮጵያውያን ውርደት ደጋግሞ የነፍሱን ኡኡታ ባሰማበት ጊዜ በድንገት አንገታችንን ቀና አድርጎ ኩራታችንን ሊያስጎነጨን የሞከረ ሰው ተገኘ! ኢትዮጵያ ሁሌም የተአምር አገር ነች።
በታላቁ ሰው በኔልሰን ማንዴላ እረፍት ምክንያት አንድ ተደብቆ የኖረ ክቡር ኢትዮጵያዊ ብቅ አለ፤ ማንዴላ ለሥልጠና በኢትዮጵያ በነበረበት ጊዜ ምናልባትም እንግሊዞች ማንዴላን ሊያስገድሉ ከጠባቂዎቹ አንዱ የነበረውን ወታደር በገንዘብ ገዝተው ዓላማቸውን ለመፈጸም አቅደው ነበር፤ ወታደሩ ገንዘቡን ከተቀበለ በኋላ ሀሳቡን ለውጦ ገንዘቡን ለአለቃው ሰጠ፤ ማንዴላ ከሞት ተረፈ፤ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊ ራሱንና አገሩን የሚያስከብር ሥራ ሲሠራ የሚኮሰኩሳቸው ባለሥልጣኖች ለእነሱ የማይተላለፍ ክብር በመሆኑ ተዳፍኖ እንዲኖር አደረጉት፤ እነሱ ሞተው ወይም ተሰድደው ሲያልቁ የተዳፈነው ምሥጢር ብቅ አለ፤ ባለሥልጣኖቹ ሸልመውት ይሆናል፤ ግን አላከበሩትም፤ ሻምበል ጉታን ያከበረው የማንዴላ ሞት ነው፤ የሚያሳዝነው ማንዴላ ይህንን የሱን ሕይወት ለማትረፍ ሁለት ሺህ ፓውንድ ያጣውን ኢትዮጵያዊ ወታደር ሳያውቀው መሞቱ ነው።
የኢትዮጵያ አርበኞች ታሪካቸው ተቀብሮ የቀረው እንዲህ እየሆነ ነው፤ ታዴዎስ ታንቱ ሥራዬ ብሎ የተረሱ አርበኞችን ከመቃብር እያወጣ ያስተዋውቀናል፤ በሌሎች አገሮች እንደዚህ ለአገር ትልቅ ፋይዳ ያለው ሥራ በአንድ ሰው በበጎ ፈቃድ የሚሠራ ሳይሆን ዋና የመንግሥት ተግባር ነው።
ሻምበል ጉታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ባይሆንም ራሱን ችሎ ለኔልሰን ማንዴላ መቃብር ደርሶአል፤ በአገር ደረጃ በሥልጣን ወንበሮቹ ላይ ለአገር የሚያስቡ ሰዎች አለመኖራቸውን ለማወቅ ግሩም ማስረጃ ነው፤ ለቀብር የሄደው ባለሥልጣን ሻምበል ጉታን ይዞ ቢሄድ ኖሮ ለራሱም ሆነ ለአገሩ ክብርና ጌጥ ይሆንለት ነበር፤ ለደቡብ አፍሪካ ሕዝብም ሆነ ለዓለም በመላ አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር አልሸጥም-አልለወጥም ብሎ የኔልሰን ማንዴላን ሕይወት ማትረፉን በማስታወቅ አገሪቱን ያስከብር ነበር፤ የታፈነው ታሪክ አፈትልኮ ሲወጣ ከስደተኞች ጋር ተያይዞ መሆኑ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የአደባባይ መክሸፍ የሚያሳይ ነው፤ ባለቤት ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳ ተቀበለው፤ መንግሥት ያፈነውን ክብር ስደተኞች አጌጡበት!
ለእኔ አሁን አንድ ጥያቄ ይቀራል፤ ሻምበል ጉታ የአገሩን ክብር ከራሱ ጥቅም በላይ በማድረጉ፣ የተቀበለውን አደራ በመጠበቁ ቢያንስ ሁለት ሺህ ፓውንድ አጥቷል፤ እንዳጣ ሊቀር ነው? ቢያንስ የከፈለውን ሁለት ሺህ ፓውንድ ወይስ ያንን አሥር እጥፍ አድርገን እንከፍለዋለን? ሻምበል ጉታን የምናመሰግነው በርጥቡ ነው በደረቁ? እኛ ያለጥርጥር ኮርተንበታል፤ ሁላችንም በኢትዮጵያዊነታችን የሱን ክብር በመጋራት ራሳችንን አክብረናል፤ ሻምበል ጉታም በእኛ እንዲኮራና በእኛ እንዲከበር ማድረግ ያለብን ይመስለኛል፤ ስለዚህ ምን እናድርግ? ለራሱ ክብር፣ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ክብር ሲል የከፈለውን እስቲ ከወሬ ያለፈ ነገር እናስብና ለዚህ ጀግና የምንችለውን አድርገንለት እግዚአብሔር ዕድሜ ይስጥህ እንበለው።

ሕወሓት መራሹ ገዢ መደብ ኢሕኣዴግ በድርጅቱ ውስጥ ባደረገው ውስጣዊ ጥናት እና ግምገማ መሰረት ከተቃዋሚው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ቁርኝት አላቸው ግንኙነት ፈጥረዋል ለዲሞክራሲያዊ ስርኣቱ እንቅፋት ሆነዋል የድርጅቱን መረጃ አቀብለዋል ያላቸውን አባሎቹን ሊያባርር መሆኑን ከአዲስ አበባ የኢሕኣዴግ ጽ/ቤት የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል::

በዚሁም መሰረት የተደረገው ውስጣዊ ጥናት እና ግምገማ እንዲሁም ከብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ቢሮ የተገኘ ማስረጃን መሰረት በማድረግ የሚባረሩትን አባላት እና ከተባረሩ በኋላ ሊወሰድባቸው የሚገባ እርምጃ እየተጠና መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ጦር ሰራዊቱ የከፍተኛ መኮንኖች ግምገማ ሊያደርግ መሆኑ ታውቋል::ከሻለቃ ማእረግ ጀምሮ ወደላይ እስከ ጄኔራሎች ድረስ የሚደረገው ግምገማ አጀንዳው ሙስናን ያጠቃል/አያጠቃል ባይታወቅም በዚህ ሰሞን በሕወሓቱ ጄኔራል ሳሞራ ቢሮ የተሰበሰቡት ጄኔራሎች በከፍተኛ መኮንኖች ላይ ግምገማ እንዲደረግ መወሰናቸው ሲታወቅ በግምገማው ላይ የሚገመገሙ መኮንኖች ስም ዝርዝር እንዲዘጋጅ ለወታደራዊ ደህንነት ክፍል ትእዛዝ የተሰጠ ሲሆን ስም ዝርዝራቸው ያልተጠቀሱ መኮንኖች እንደማይገመገሙ ሆኖም እንደሚገመግሙ ታውቋል::ምኒልክ ሳልሳዊ

የሰሜን ጎንደር የማረሚያ ቤት ሀላፊ ኮማንደር መተከል አያልሰዉ እርምጃተወሰደበት::
አርምጃዉ የተወሰደዉ ትናት ማታ ሰባት ሰአት ሲሆን በተደጋጋሚ ከግፍ ስራዉ እንዲቆጠብ መልክት ቢደረሰዉ አሻፈረኝ በማለቱ ተገሎአል :: አወጋን

ኢትዮጵያን ለረጅም ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩትና ሰፊ ስልጣን የነበራቸው መለስ ዜናዊ በነሃሴ ወር በድንገት መሞት በሃገር ውስጥም ሆነ በኢትዮጵያ ዓለማቀፍ አጋሮች ዘንድ የሀገሪቱን ፖለቲካዊ ሽግግር የሚመለከቱ ጥያቄዎችንና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን አስነስቶ ነበር።በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተለይ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እየከፋ ሄዷል።አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በመስከረም ወር ስልጣኑን የተረከቡ ቢሆንም መንግስት በርሳቸው አመራር ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ ለውጦች ያደርግ ወይስ አያደርግ እንደሆነ ገና የሚታይ ነው።

እ.ኤ.አ በ2013ም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት መሰረታዊ የሆኑትን ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብቶች በጥብቅ መገደባቸውን ቀጥለዋል።ለኣሻሚ ትርጉሞች በተጋለጠውና በ2002 ዓ.ም በወጣው የሀገሪቱ የጸረ ሽብርተኝነት ሕግ 30 ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።በዋና ከተማዪቱ አዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል የእስልምና እምነት ተከታዮች ላካሄዷቸው የተቃውሞ ሰልፎች የጸጥታ ሃይሎች የሰጡት ምላሽ የዘፈቀደ አፈሳ፣ እስር እና ድብደባ ነበር።

የኢትዮጵያ መንግስት በአምስት ክልሎች የሚኖሩ የገጠር ነዋሪዎችን የተሻለ የመሰረታዊ ግልጋሎቶች አቅርቦት ሊያገኙ ወደሚችሉባቸው አካባቢዎች ለመውሰድ በሚል ምክንያት 1.5 ሚሊዮን የገጠር ነዋሪዎችን መልሶ ለማስፈር የሚያካሂደውን የሰፈራ ፕሮግራም ቀጥሎበታል።በጋምቤላ ክልል የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች ከፍላጎታቸው ውጭ በሃይል እንዲፈናቀሉ በመደረጋቸው ለከፍተኛ ችግሮች ተጋልጠዋል። ከዚህ በተጨማሪም መንግስት ለሚያካሂደው ሰፊ የስኳር ልማት መሬት ለማስለቀቅ ሲባል በኢትዮጵያ የታችኛው ኦሞ ሸለቆ ነዋሪ የሆኑትን አርብቶ አደር ማህበረሰቦች ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው።

ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣የመደራጀት እና የመሰብሰብ መብቶች

መንግስታዊ ያልሆኑ ደርጅቶችን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር የበጎ አድራጎት ደርጅቶች እና ማህበራት አዋጅ እንዲሁም የጸረ ሽብርተኝነት ሕግ በ2002 ዓ.ም ከታወጁ ወዲህ በኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ከፍተኛ ገደብ ተጥሎባቸዋል። እነዚህ ሁለት ሕጎች መንግስት በሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች፣በጋዜጠኞች እና በሌሎችም የመንግስትን ፖሊሲ በሚተቹና መንግስት እንዲነሱ በማይፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ሃሳባቸውን በሚገልጹ ሰዎች ላይ ካካሄደው ሰፊ እና የማያቋርጥ ማዋከብ፣ዛቻ እና ማስፈራራት ጋር ተዳምሮ ያስከተሉት ውጤት የከፋ ነው።

ኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ የጎላ እንቅስቃሴ ያደርጉ የነበሩ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች እንቅስቃሴዎቻቸውን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀንሱ ወይም ሰብአዊ መብቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ከስራ ዝርዝራቸው ውስጥ እንዲያወጡ የተገደዱ ሲሆን ቁጥራቸው ያልታወቀ ድርጅቶችም ጭራሹኑ ተዘግተዋል። በደረሰባቸው ማስፈራሪያ ምክንያት ሰፊ ልምድና መልካም ስም የነበራቸው ብዙ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ሃገሪቱን ለቀው ሄደዋል። አሁን ሰፍኖ የሚገኘው ሁኔታ ለነጻ ፕሬስ እንቅስቃሴም እንዲሁ የተመቸ አይደለም።ባለፉት አስር ዓመታት በደረሰባቸው ዛቻ እና ማስፈራራት ሳቢያ ሃገራቸውን ለመልቀቅ በተገደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር በዓለም ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ ናት። የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች የሆነው ድርጅት ሲፒጄ እንደሚገልጸው ቢያንስ 79 ጋዜጠኞች ሃገራቸውን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል።

የጸረ ሽብርተኝነት አዋጁ፣ ተቃዋሚ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ሰዎችን ዒላማ ለማድረግ፣ተቃውሞን ለማፈን እና ጋዜጠኞችን ዝም ለማሰኘት ስራ ላይ እየዋለ ነው። እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም 30 የፖለቲካ መሪዎች፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እንዲሁም ጋዜጠኞች በግልጽ ባልተብራሩ የሽብርተኝነት ወንጀሎች ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።ከ2011 ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ 11 ጋዜጠኞች በዚሁ ሕግ ተከሰው ተፈርዶባቸዋል።

ጥር 17 ቀን 2004 ዓ.ም አሁን የተዘጋው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ምክትል አዘጋጅ በነበረው ውብሸት ታዬ እና የጋዜጣው ዓምደኛ በነበረችው ርዕዮት ዓለሙ ላይ በአዲስ አበባ የሚገኝ ፍርድ ቤት የ 14 ዓመታት እስር ፈርዶባቸዋል።የርዕዮት ዓለሙ ፍርድ በኋላ በይግባኝ ወደ አምስት ዓመታት የተቀነሰ ሲሆን ከቀረቡባት ክሶች ውስጥም አብዛኞቹ ተሰርዘዋል።

ከፍተኛ ክብር ያለውን የፔን አሜሪካ ፍሪደም ቱ ራይት ሽልማት በሚያዝያ ወር 2004 ዓ.ም ያሸነፈው አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ብሎገር እስክንድር ነጋ ሐምሌ 6 ቀን 2004 ዓ.ም ከሌሎች ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ጋር በቀረበበት ክስ የ 18 ዓመታት እስራት ተፈርዶበታል። በስደት ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች አብይ ተክለማርያም እና መስፍን ነጋሽም እስካሁን ድረስ ጋዜጠኞች ላይ ብቻ ተግባራዊ በተደረገው የጸረ ሽብርተኝነት ሕጉ አንቀጽ መሰረት ጥፋተኛ ተብለው እያንዳንዳቸው የ 8 ዓመታት እስራት ተፈርዶባቸዋል። በይፋ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀሰው ተቃዋሚ ፓርቲ አንድነት ለፍትሕ እና ለዲሞክራሲ አባል የሆነው አንዷለም አራጌ በስለላ፣ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በመናድ እንዲሁም የሽብር ተግባር ለመፈጸም ምልመላ እና ስልጠና በማካሄድ ወንጀሎች ጥፋተኛ ተብሎ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል።

በመስከረም ወር 2004 ዓ.ም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእስክንድር ነጋ እና በስደት ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ አበበ በለው እንዲሁም የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባሉ አንዷለም አራጌ ንብረቶች እንዲወረሱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፍትሕ ጋዜጣ የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚያካሂዱትን ተቃውሞ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን የጤንነት ሁኔታ አስመልክቶ ያዘጋጃቸው ዘገባዎች የሃገሪቱን ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ናቸው በማለት መንግስት ሀምሌ 20 ቀን ጋዜጣው እንዳይሰራጭ አግዷል። ነሃሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ በቁጥጥር ስር ውሎ ዋስትና ተከልክሏል። ተመስገን ነሃሴ 24 ቀን ከእስር የተለቀቀ ሲሆን ተጨማሪ ምርመራ እስኪካሄድ ድረስ ሁሉም ክሶች ተነስተውለት ነበር።

ሀምሌ 13 ቀን 2004 ዓ.ም ‘የሙስሊሞች ጉዳይ’ የተሰኘው ተወዳጅ የሙስሊሞች መጽሄት ዋና አዘጋጅ የሆነው የሱፍ ጌታቸው ቤት በፖሊሶች የተፈተሸ ሲሆን በዚያው ዕለት ምሽትም የሱፍ በቁጥጥር ስር ውሏል። መፅሄቱ ከዚያ በኋላ መታተም ያቆመ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከሚዘጋጅበት ጊዜም የሱፍ በቁጥጥር ስር ይገኛል።

በሕገ ወጥነት ከተፈረጀው አማጺው የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ጋር በምስራቃዊ ኢትዮጵያ ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር የዋሉት ማርቲን ሺብዬ እና ዮሃን ፒርሰን የተባሉ ሁለት ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ለሽብርተኛ ድርጅት ድጋፍ በመስጠት ወንጀል ታህሳስ 17 ቀን 2004 ዓ.ም የጥፋተኝነት ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል። በተጨማሪም በሕገ ወጥ መንገድ ወደሃገሪቱ በመግባት ጥፋተኞች ተብለዋል።ፍርድ ቤቱም በ 11 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ወስኗል። ሁለቱ ጋዜጠኞች አዲሱን ዓመት በማስመልክት በየዓመቱ ለእስረኞች በሚሰጠው ምህረት ከሌሎች 1950 በላይ ከሚሆኑ እስረኞች ጋር ምህረት ተደርጎላቸው ጳጉሜ 5 ቀን 2004 ዓ.ም ከእስር ተለቀዋል።

መንግስት በሃገሪቱ የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ጉዳዮች ምክር ቤት ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት በመቃወም ለታቃውሞ የወጡ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ለመበተን በሐምሌ ወር 2004 በተለያዩ ቀናት የፌደራል ፖሊስ ድብደባን ጨምሮ ከልክ ያለፈ ሃይል ተጠቅሟል።ሀምሌ 6 ቀን አዲስ አበባ ወደሚገኘው የአወሊያ መስጊድ በሃይል በመግባት ፖሊሶች መስኮቶችን የሰባበሩ ሲሆን በመስጊዱ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ ተኩሰዋል። ሐምሌ 14ም በመስጊዱ ለተቃውሞ ተቀምጠው የነበሩ ሰዎችን ሃይል በመጠቀም እንዲበተኑ አድርገዋል። ከሐምሌ 12 እስከ 14 በነበሩት ቀናትም በርካታ ሰዎች የታፈሱ ሲሆን 17 ከፍተኛ የእምነቱ መሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ክስ ሳይመሰረትባቸው ከአንድ ሳምንት በላይ በእስር ቆይተዋል።ብዙዎቹ ታሳሪዎች በእስር ላይ እያሉ ማንገላታት እንደተፈጸመባቸው ገልጸዋል።

ተገዶ መፈናቀል

ሰፈራ በሚባለው ፕሮግራሙ የኢትዮጵያ መንግስት በአምስት ቆላማ ክልሎች ማለትም በጋምቤላ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣በአፋር፣ በደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች እና ሕዝቦች እንዲሁም በሶማሌ ክልሎች የሚኖሩ 1.5 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎችን የተሻለ የመሰረታዊ አገልግሎቶች አቅርቦት ወደሚያገኙባቸው አካባቢዎች ለማዛወር በሚል ወደሌሎች ቦታዎች ወስዶ ለማስፈር እቅድ አለው።

በጋምቤላ እና በደቡብ ኦሞ ሸለቆ ከነዋሪዎች ጋር በቂ የቅድሚያ ምክክር ሳይደረግ እና የካሳ ክፍያ ሳይፈጸም አስገድዶ የማፈናቀል ተግባር እየተፈጸመ ነው።ሂዩማን ራይትስ ዎች እንዳረጋገጠው በተለይ በጋምቤላ ወደሌሎች አካባቢዎች አዛውሮ የማስፈሩ ሂደት የሚከናወነው ብዙ ጊዜ ነዋሪዎቹን ለም የሆኑ መሬቶቻቸውን በማስለቀቅ አነስ ያለ ለምነት ወዳላቸው መሬቶች በማስፈር ነው።ወደ አዳዲሶቹ መንደሮች እንዲሰፍሩ የሚላኩት ሰፋሪዎች አብዛኛውን ጊዜ መሬታቸውን መመንጠር እና ጎጆዎቻቸውን መስራት ያለባቸው ሲሆን ይህንንም በወታደሮች ተቆጣጣሪነት ያከናውናሉ።ቃል የተገቡላቸው አገልግሎቶች ማለትም ትምህርት ቤቶች፣ክሊኒኮች እና የውሃ ፓምፖች የተሟሉ አይደሉም።

በደቡብ ኦሞ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ ሺህ የሚደርስ ተወላጅ ሕዝቦች መንግስት ለሚያካሂደው የስኳር ልማት ቦታ ለማስለቀቅ ሲባል መሬታቸው ተወርሶ ወደሌሎች አካባቢዎች እንዲሰፍሩ እየተደረገ ነው። ነዋሪዎቹ ከመሬቶቻቸው ላይ በሃይል እነደሚነሱ፣የግጦሽ መሬቶቻቸው በጎርፍ እንዲጥለቀለቁ እንደሚደረግ፣ ማሳዎቻቸው እንደሚገለበጡ እንዲሁም ለህልውናቸው እና ለአኗኗር ዘይቤአቸው እጅግ አስፈላጊ የሆነውን የኦሞ ወንዝ ውሃ እንዳያገኙ እንደሚከለከሉ ተናግረዋል።

ሕገ ወጥ ግድያ፣ማሰቃየት እና በቁጥጥር ስር ባሉ ሰዎች ላይ የተፈጸሙ ጥሰቶች

በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጋሸሞ ወረዳ ራቅዳ በተባለች መንደር ከነዋሪዎች ጋር የተፈጠረን ግጭት ተከትሎ ‘ልዩ ሃይል’ በሚል ስያሜ የሚታወቅ፣ በኢትዮጵያ መንግስት የሚደገፍ ታጣቂ ቡድን በቁጥጥሩ ስር የነበሩ 10 ሰዎችን እና ሌሎች 9 የመንደሩ ነዋሪዎችን የገደለው መጋቢት 7 እና 8 ቀን 2004 ዓ.ም ነበር።

በሚያዝያ ወር 2004 ዓ.ም ማንነታቸው ያልታወቀ መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች በጋምቤላ ክልል በሚገኝ እና ባለቤትነቱ የሳውዲ ስታር ኩባንያ በሆነ ሰፊ እርሻ ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል። ይህ የእርሻ ልማት በክልሉ የሰፈራ ሂደት በተካሄደበት ወቅት የከፋ የመብቶች ጥሰቶችና ማንገላታት ከተፈጸመባቸው አካባቢዎች በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው። ለዚህ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት የኢትዮጵያ ወታደሮች ቤት ለቤት በመዞር ድርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን የፈለጉ ሲሆን የአካባቢውን ነዋሪዎችም ‘አማጺያኑ’ የሚገኙበትን ቦታ አጋልጡ በማለት ሲያስፈራሯቸው ነበር። ወታደሮቹ በርካታ ወጣት ወንዶችን በዘፈቀደ ከማሰራቸውም በላይ ስለ ጥቃቱ መረጃ ለማግኘት ባደረጉት ሙከራ ማሰቃየት፣አስገድዶ መድፈር እንዲሁም ሌሎች ጥሰቶችን በብዙ ነዋሪዎች ላይ ፈጽመዋል።

ሂዩማን ራይትስ ዎች በአዲስ አበባ ማዕከላዊ በመባል በሚታወቀው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጣቢያ እና በክልሎች በሚገኙ የእስር ቦታዎች እንደዚሁም በሶማሌ፣ በኦሮሚያ እና በጋምቤላ ክልሎች በሚገኙ ወታደራዊ ካምፖች ውስጥ የሚፈጸሙ የማሰቃየት ድርጊቶችን የሚመለከቱ መረጃዎችን ማሰባሰቡን ቀጥሏል። በእነዚህ የእስር ጣቢያዎች ከፖለቲካ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተያዙ ታሳሪዎች ከጠበቆቻቸው ጋር የሚገናኙበት እድል በጣም የመነመነ ሲሆን በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች ከፍርድ ሂደት በፊት እና በፍርድ ሂደት ወቅት ሊከበሩላቸው የሚገቡ መብቶችን ለማክበር ያለው ፍላጎትም በጣም አናሳ ነው። ይህም ታሳሪዎቹን ለከፉ ጥሰቶች ያጋልጣቸዋል።

የስደተኛ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች አያያዝ

በሊባኖስ የቤት ሰራተኛ የነበረቸው ኢትዮጵያዊት ዓለም ደቻሳ ደሲሳ ድብደባ ሲፈጸምባት የሚያሳየው ቪዲዮ ከተሰራጨና ይህነኑ ተከትሎም ዓለም መጋቢት 5 ቀን 2004 ዓ.ም ሕይቷን ካጠፋች በኋላ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት በመካከለኛው ምስራቅ ሃገራት በቤት ሰራተኝነት የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የሚደርስባቸው መከራ የተጠናከረ ትኩረት አግኝቶ ነበር። ብዙ በስደት የሚሰሩ የቤት ሰራተኞች ወደ ውጭ ሃገራት ሄደው ከመቀጠራቸው በፊት ከባድ የገንዘብ ዕዳ ውስጥ ይገባሉ፤ እንዲሁም ከቅጥር ሂደቱ ጋር የተያያዙ ሌሎች ማንገላታቶች ይፈጸሙባቸዋል።ውጭ ሀገር ሄደው ስራ ከጀመሩም በኋላ ለረጅም ሰዓታት ከመስራት በተጨማሪ ባርነት በሚመስሉ የስራ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሰሩ ይደረጋሉ፣ እንዲሁም ሌሎች መጠነ ሰፊ ጥቃቶች ይደርሱባቸዋል።(የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ሳኡዲ አረቢያ እና ሊባኖስን የሚመለከቱትን ምዕራፎች ይመልከቱ)።

ዋና ዋና ዓለማቀፍ አጋሮች

በመለስ ዜናዊ አመራር ኢትዮጵያ በአካባቢ ጉዳዮች ላይ የጎላ ሚና ትጫወት ነበር።ወደ አወዛጋቢው የሱዳን አቢዬ ክልል በተባበሩት መንግስታት ስር የሰላም አስከባሪ ሃይሎችን አሰማርታለች፣በሱዳን እና በደቡብ ሱዳን መካከል የነበረውን አለመግባባት ሸምግላለች እንዲሁም አል ሸባብን ለመውጋት የተደረገውን ዓለማቀፍ ጥረት ለማገዝ ሰራዊቷን ወደሶማሊያ ልካለች። እ.ኤ.አ ከ 1998-2000 ድረስ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተካሄደውን ከፍተኛ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ተከትሎ ኢትዮጵያ ከጎረቤቷ ኤርትራ ጋር ያላት ግንኙነት መልካም አይደለም። ኤርትራ ለግጭቱ መነሻ የነበሩ ቦታዎች ለኤርትራ እንደሚገቡ የወሰነውን የድንበር ኮሚሽን ውሳኔ የተቀበለች ሲሆን ኢትዮጵያ ግን ውሳኔውን አልተቀበለችም።

ኢትዮጵያ ለምዕራብ መንግስታት ጠቃሚ ስትራተጂያዊና የደህንነት አጋር ስትሆን ከእነዚህ መንግስታት በአፍሪካ ከፍተኛውን የልማት እርዳታ የምታገኝ ሀገርም ናት።በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በዓመት ወደ 3.5 ሚሊዮን የሚደርስ የአሜሪካን ዶላር በረጅም ጊዜ የልማት እርዳታ መልክ ታገኛለች።የለጋሽ ሃገራት ፖሊሲዎች በሀገሪቱ እየከፋ ከሄደው የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጋር በተያያዘ ብዙም የተለወጡ አይመስሉም።

እ.ኤ.አ በመስከረም ወር 2012 የዓለም ባንክ ራሱ እና ሌሎችም የልማት ተቋማት ዘለቄታ ላለው ልማት እጅግ አስፈላጊ ናቸው የሚሏቸውን የሰብአዊ መብቶች እና የመልካም አስተዳደር መርሆች ብዙም ከግምት ውስጥ ያላስገባ አዲስ ብሔራዊ የጋራ ሰትራተጂ ባንኩ አጽድቋል።ባንኩ በተጨማሪም ሦስተኛውን ዙር የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥበቃ ፕሮግራም (ፒቢኤስ 3)ያለፈቃድ የሚደረግ ሰፈራን የሚከለክሉ እና ለተወላጅ ሕዝቦች ጥበቃዎችን የሚያደርጉ ድንጋጌዎችን ሳያካትት አጽድቋል።

HRW
Image

የሕወሓት አትኩሮት ስልጣን በማስረዘም ላይ ነው እንጂ በዜጎች ደህንነት ላይ አይደለም ::
Minilik Salsawi
ዜጎች በየትኛውን የውጭም ይሁን የአገር ውስጥ በባለስልጣናት የሚደርስባቸው መከራና ግፍ መንግስት የለም ወይ ያሰኛል:: እኛ እየተናገርን ያለነው ስለ ፖለቲከ ተቃዋሚዎች ሳይሆን ስለዜጎች ነው:: ስለፖለቲካ ተቃዋሚዎች ራሳቸው እየደሰኮሩት ነው ዜጎች ግን የመኖር የመስራት የማምለክ መብታቸው ሊከበር ይገባል:: ህግ ሲከበር ስልጣን ይረዝማል:: ህግ ሲከበር ዜጎች ሰላም ያገኛሉ:: ኢኮኖሚው ቢዋዥቅ እንኳን ሰላም ካለ ብልሃቱ አይጠፋም::

ሕወሃት መራሹ ኢህኣዴግ ስልጣኑን ለማስረዘም የሚጠቀምበት ስልት የተበላበት እና ያረጀ መሆኑ እሙን ነው::ዜጎች በሃገራቸው መኖር ካልቻሉ ለመኖር ሲሉ የሚፈጥሩት ፍትጊያ ባለስልጣናቱን ከጨዋታ ውጪ አድርጎ በህዝብ እንዲበሉ ያደርጋቸዋል::ዜጎች በገዛ አገራቸው ዛሬም እየተፈናቀሉ ነው::በአለም ላይ ታይቶ የማይታወቅ የፌዴራሊዝም ከፋፍለህ ግዛው ፖሊሲ በዚህ በሰለጠነ ዘመን ተቀባይነት የሌለው እና ለራስ ጦስ የሚሆን እንደሆነ ወያኔዎች ሊረዱት ይገባል:: እንደጫካ የተለመደው ማፊያዊ መሹለኩለክ የትም የማያደርስ አደጋ የሚያስከትል መሆኑን ሊታወቅ ይገባል::
ሕወሓት ስሟንም ሙዷንም ትቀይርልን::በቃ ነቅተናል!!! ከሕወሓት ውጭ ማንም ወንጀለኛ የለም::
ትላንት ዛሬም ነገም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በህገወጥ መንገድ ቢሞት ቢገደል ቢታነቅ ቢታፈን ቢታሰር እና ከነዚህ ነገሮች ጋር በተያያዘ ከሕወሃት ውጭ ማንም ይህን የሚፈጽም የለም :: ይህንን ደሞ እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንቅቆ አውቆታል:: በቃ ነቅተናል!! ከህወሃት ውጭ ማንም ወንጀለኛ የለም::

በአለማቀፍ ደረጃ ከአሸባሪ ድርጅቶች እኩል ስሟ ሰፍሮ የሚገኘው ሕወሓት በኢትዮጵያ እና በዜጎቿ ላይ በግልጽ እና በድብቅ የተለያዩ ማፊያዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው::ሕወሓት በተለያዩ የደህንነት መዋቅሯ አማካኝነት ራሷ ከፈጠረቻቸው ከፍተኛ ባለስልጣኖች ጀምሮ እስከ ተራ ዜጎች ድረስ በስውር እጆቿ በልታቸዋለች:: በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ከተሞች በተለያየ ጊዜ ቦምቦችን በማፈንዳት በተቃዋሚዎች ላይ ሰበብ ለመፍጠር ሞክራለች:: በእነዚህ ፍንዳታዎች ያለቁትን ዜጎች አስቧቸው:: ……..ኦነግ ሻእቢያ አልሸባብ ቅንጅት አክራሪ …ምናምን ቢባል ማንም የሚያምን የለም ::አሁንም ያልተነቃ የሚመስላቸው እነዚህ ሰው በላዎች የጫካ ማፊያዊ ድርጊታቸውን እየፈጸሙ ይገኛሉ..በቃ ነቅተናል!!! ከሕወሓት ውጭ ማንም ወንጀለኛ የለም::

ስለዚህ በቃ ነቅተናል ልንል ይገባል:: ሁላችንም በያለንበት የሕወሓትን ስውር እጆች ልናጋልጥ ይገባል:: ሕወሓትን የምንመክረው ግን አመድ ከመሆንሽ በፊት ስምሽን እና ሙድሽን ቀይሪልን ነው::
በቃ ነቅተናል!!! ከሕወሓት ውጭ ማንም ወንጀለኛ የለም::


“አንጥረኛ” ቤተሰብና ታላላቅ ሥራዎቻቸው

Image

አያታችን የአፄ ምኒልክን፣ አባታችን የአፄ ኃይለስላሴን ዘውድ ሰርተዋል
ወንድሜን ሙያውን ጀርመን አገር ያስተማሩት ንጉሱ ናቸው
የአክሱምና ላሊበላ መስቀሎችን ዲዛይን አሻሽሎ የሰራው አባቴ ነው
ወላጆቻቸው የአንኮበር ተወላጆች ናቸው። አባታቸው ከአንኮበር ጀምሮ በአዲስ አበባ ቤተመንግሥትም የወርቅና ብር

ጌጣጌጦች ባለሙያ ነበሩ፡፡ ከታላቅ ወንድማቸው ጋር በመሆን የአባታቸውን ሙያ ከልጅነት ዕድሜያቸው ጀምሮ

የቀሰሙት አቶ ይሔይስ ደጀኔ፤ በጀርመን አገርም ተጨማሪ ዕውቀት ገብይተዋል፡፡ ደምበል ሕንፃ ላይ “ይሔይስ ደጀኔ

የወርቅና ብር ሠሪ” የሚል መደብር ያላቸው አቶ ይሔይስ፤ “አባታችን በሙያው የነበረውን ዕውቀት ዛሬ በ76ተኛ

ዓመቴም አልደረስኩበትም” ይላሉ፡፡ በወርቅና በብር ከሚሰሩ ጌጣ ጌጦች ጋር በተያያዘ የቤተሰባቸውን ታሪክና ተያያዥ

ጉዳዮችን አውግተውናል።
ከትውልድዎና አስተዳደግዎ ይጀምሩልኝ…
በአዲስ አበባ ከተማ ጐላ ሠፈር በ1930 ዓ.ም ነው የተወለድኩት፡፡ በልጅነቴ ያመኝ ስለነበር፤ ከጐንደር የመጡ መምሬ

ቅሩብ የሚባሉ ቄስ ተቀጥረውልኝ ቤት ውስጥ ነበር ትምህርቴን የተከታተልኩት፡፡ ሌሎችም የጐላ ሠፈር ልጆች እየመጡ

እንማርበት የነበረው ቤት የእናቴ ወንድም ነበር፡፡ የቤተመንግሥት ካባ ሰፊና ሙካሽ ጠላፊ ባለሙያ የነበሩት አጐቴ፤

አቶ አድማሱ ኃይለማርያም ይባላሉ፡፡ የቄስ ትምህርቴን ፊደል ከመቁጠር ጀምሬ፣ ዳዊት በመድገም፣ በወንጌል ንባብ

ካዳበርኩ በኋላ፤ በመርካቶው ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን እንድቀድስ ተጠይቄ ነበረ፡፡ እኔ ግን ዘመናዊ ትምህርት

የመማር ፍላጐት ስለነበረኝ፣ በ1944 ዓ.ም ኮከበ ጽባሕ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ትምህርት ቤት ገባሁ፡፡
የትምህርት ቤታችን ርዕሰ መምህር ካርል ማይክል የሚባሉ አሜሪካዊ ነበሩ፡፡ 12ተኛ ክፍልን ካጠናቀቅኩ በኋላ

ለተጨማሪ ትምህርት ወደ ጀርመን አገር እንድሄድ ነገሮችን ያመቻቸልኝ ታላቅ ወንድሜ አቶ ክበርዬ ደጀኔ ነበር፡፡
ይህንን ያደረገበት ምክንያት ደግሞ፤ ቤተሰባችን ለተሰማራበት የአንጥረኝነት ሙያ እኔ ከፍተኛ ፍላጐት እንዳለኝ

በማስተዋሉ ነው፡፡ ታላቅ ወንድሜም ጀርመን አገር ድረስ ሄዶ ሙያውን ተምሮ ስለነበር፣ እኔም ወደዚያ እንድሄድ

ያመቻቸልኝ፤ በጀርመን አገር የሚያውቃቸውን ሰዎች በማነጋገር ነበር፡፡
እስቲ ወደኋላ መለስ ብለው የእናንተ ቤተሰብ ከአንጥረኝነት ሙያ ጋር በተያያዘ ያለው ታሪክ ምን እንደሚመስል

ይንገሩኝ…
የአባቴ አባት አቶ በላይነህ ዓለምነህ እና የእናቴ አባት አቶ ደገፉ ጋሼ፤ በአንኮበር ቤተመንግሥት በአንጥረኝነት ሙያ

ይሰሩ ነበር፡፡ በዚያ ወቅት መስቀልና የቤተክህነት ዕቃዎችን ሠርተዋል፡፡ አፄ ምኒልክ ሲነግሱ የተጠቀሙበትን ዘውድ

አርመናዊው ዲክራን አቢያን ሲሰራ፣ አያቴና ወንድሙ በሥራው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ አፄ ኃይለሥላሴ ሲነግሱ

የተገለገሉበትን ዘውድ በመስራትም አባቴ ሙያዊ ዕውቀቱን አዋጥቷል፡፡ ከዚያም በኋላ ብዙ ነገር ሠርቷል፡፡
ጥንታዊውን የአክሱምና የላሊበላ መስቀሎችን ዲዛይን አሻሽሎ የሰራው አባቴ ነው፡፡ አሁን በአራት ኪሎ ቤተመንግሥት

አጥር ላይ የሚታየውና የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን ሥም ምህፃረ ቃል በድርብ ዲዛይን የቀረፀውም እሱ ነው፡፡ የጃንሆይ

የክብር አልባሳት ቁልፎችንም ሠርቷል፡፡ የአፄ ኃይለሥላሴ የልብስ ቁልፍ በመጀመሪያ ተሰርቶ የመጣው ከእንግሊዝ

ነበር፡፡ ንጉሡ ከለንደን የመጣውን ዲዛይን ስላልወደዱት አባቴ አሻሽሎ እንዲሰራላቸው ጠይቀውት፣ የልብስ

ቁልፎቻቸውን በ21 ካራት ወርቅ ሠርቶላቸዋል፡፡
የንጉሡ የልብስ ቁልፎች ላይ ምን ዲዛይን ነበረ?
የአፄ ኃይለሥላሴ ልብስ የወርቅ ቁልፎች በተለያየ ዲዛይን ነበር የተሰራው፡፡ መሐሉ ላይ የቅዱስ ጊዮርጊስ አርማ ያለበት

አለ፡፡ ግራና ቀኝ የተጠላለፉ ሻምላዎችን አርማ የያዙም ቁልፎች ነበሩ፡፡ በክብ ቅርጽ የተሰሩት የልብስ ቁልፎች

በዙሪያቸው የዘንባባ ዲዛይን የተሰራላቸው ሲሆን ጫፋቸው ላይ ደግሞ የዘውድ አርማ አላቸው፡፡
አባትዎ በየትኛው ቤተመንግሥት ውስጥ ነበር እነዚህን ሥራዎች የሚሠሩት?
ከቤተመንግሥት ቅጥር ሠራተኞች አንዱ ሆኖ በአንጥረኝነት ሙያ ያገለገለው፤ በጃንሆይ ልዩ ግምጃ ቤት ውስጥ ነበር፡፡

ግምጃ ቤቱ በገንዘብ ሚኒስቴር ስር የሚተዳደር ሲሆን፤ ቦታውም አሁን 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ በሆነው ገነተ ልዑል

ቤተመንግሥት ውስጥ፤ ከማርቆስ ቤተክርስቲያን በስተጀርባ ነበር። ከአባቴ ጋር የሚሰሩ በጅሮንድ ማንደፍሮ የሚባሉ

ሌላ ኢትዮጵያዊም ነበሩ፡፡
በሙያው ላይ የተሰማሩ የውጭ አገር ሰዎችስ አልነበሩም?
የአንጥረኝነት ሙያ በአገራችን በሁለት መንገድ ተስፋፍቶ ነው ለዛሬ የደረሰው፡፡ አንደኛው፤ ከጥንት አክሱማዊያን አንስቶ

ትውልዶች እየተቀባበሉ እዚህ ያደረሱት ሲሆን፤ ሁለተኛው ከአፄ ምኒልክ ጊዜ አንስቶ ልዩ ልዩ ዕውቀት ያላቸው የተለያዩ

አገራት ባለሙያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ሲደረግ ከገቡት መሐል አርመኖችም ስለነበሩበት፣ እነሱ በአገራችን

የአንጥረኝነት ሙያ እንዲያድግና እንዲስፋፋ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
አባታችን በንጉሠ ነገሥቱ ግምጃ ቤት በሚሰሩበት ዘመን፣ ፒያሳ ላይ የወርቅና ብር መስሪያና መሸጫ ያለው ሳቫጂያን

የሚባል አርመናዊ ነበር፡፡ በነገራችን ላይ የንጉሡ ግምጃ ቤት “ብር መኪና ቤት”ም ተብሎ ይጠራ ነበር። አባታችን

እንደነገረን፣ በ”ብር መኪና ቤት” ገንዘብ የማተም ሥራ፣ የወርቅና ብር ሥራ ብቻ ሳይሆን ከረሜላ ሁሉ ይመረትበት

ነበር፡፡
አባትዎ የሰሯቸው ሌሎች ሥራዎች ካሉ ቢነግሩኝ…
ለአፄ ኃይለሥላሴና ለቤተመንግሥት ብዙ ነገር ሠርቷል፡፡ የጃንሆይን የልብስ ቁልፎች ከአባቴ ውጭ ማንም

አልሰማራም፡፡ የሲጃራ መያዣ ሣጥን፣ የሴት ቦርሳ ጌጦች፣ የተለያዩ አገራት እንግዶች ሲመጡ፤ ጃንሆይ በሽልማትነት

የሚሰጧቸው ኒሻንና ሜዳሊያዎች፣ የወታደራዊ የማዕረግ ምልክቶች፣ የሸሚዝ እጅጌ ማስያዣ ቁልፎች (ከፊሊንግ)፣ የአበባ

ማስቀመጫዎችና የተለያዩ የሳሎን ጌጣጌጦች፤ በወርቅ፣ በብር፣ በዝሆን ጥርስና በአልማዝ ጭምር ሠርቷል፡፡
አርመናዊው ሳቫጂያንም ለቤተ መንግሥት ብዙ ነገሮችን ሠርቷል፡፡ ማህተም ይቀርጽ ነበር። ለወታደራዊ አገልግሎት

የሚውሉ ጌጣ ጌጦች፣ የማዕረግ ምልክቶችና የልብስ ቁልፎችን ይሰራ ነበር፡፡ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጥይት ፋብሪካም

በተመሳሳይ መልኩ በብዙ ሥራዎች ላይ ተሳትፏል፡፡
ከአፄ ኃይለሥላሴ ውጭ የልብስ ቁልፎችን በወርቅ ያሰራ ሌላ ማን አለ?
አንደኛ ሥራው በሚስጢር ነው የሚሰራው፡፡ ሁለተኛ የዲዛይን ሥራው የዳበረ ዕውቀትና ልምድ ስለሚጠይቅ፤ አሰራሩም

ጊዜ ስለሚወስድ ብዙ ሰው የልብስ ቁልፎችን ከወርቅ ሊያሰራ አይችልም። የማሰሪያ ዋጋውም ቢሆን ውድ ነው፡፡ ልዑል

ራስ አስራተ ካሳ ግን ከወርቅ የተሰራ የልብስ ቁልፎች ነበሯቸው፡፡
ታላቅ ወንድምዎ የወርቅና ብር ሥራን ለመማር ወደ ጀርመን መሄዳቸውን ገልፀውልኛል፡፡ እስቲ ስለ ወንድምዎ

ይንገሩኝ…
አቶ ክብርዬ ደጀኔ ታላቅ ወንድሜ ነው፡፡ አያታችን በአፄ ምኒልክ ዘውድ፣ አባታችን በአፄ ኃይለሥላሴ ዘውድ ሥራ ላይ

እንደመሳተፋቸው ሁሉ፤ አቶ ክብርዬም የሥላሴ ካቴድራልና የአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያናትን መንበር በብርና በወርቅ

በመሥራት ባለታሪክ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ አባታችን ወደሚሰራበት ቤተመንግሥት እየሄደ በመለማመድ ነበር ሙያውን

ያዳበረው፡፡ በየዓመቱ ለገና በዓል የአበባ ማስቀመጫ ከብር እየሰራ ለንጉሠ ነገሥቱ ያበረክትላቸው ነበር፡፡ ይህንን

ፍላጎቱን ያዩት አፄ ኃይለሥላሴ፤ ሙሉ ወጪውን ችለው ጀርመን አገር ሄዶ ሙያውን እንዲማር ረዱት፡፡ ከጀርመን

ሲመለስ ፒያሳ ከማህሙድ ሙዚቃ ቤት በታች፣ ሱቅ ከፍቶ በወርቅና ብር ሥራ ላይ ተሰማራ፡፡
እርስዎስ ለትምህርት ጀርመን የሄዱት እንዴት ነበር?
ታላቅ ወንድሜ ጀርመን በሄደበት ወቅት፣ ትምህርት በማይኖረኝ ጊዜ፤ ቤተመንግሥት እየሄድኩ አባታችንን በሥራ እረዳ

ነበር፡፡ ወንድሜ የፒያሳውን ሱቅ በ1954 ዓ.ም. ከከፈተም በኋላ በተመሳሳይ መልኩ በሥራው ላይ እሳተፍ ስለነበር፣

ለሙያው ያለኝን ፍቅርና ችሎታ ያየው ወንድሜ፤ ጀርመን ሄጄ እንድማር ሁኔታዎችን አመቻችቶ ሲልከኝ፣ የትራንስፖርት

ወጪዬን የሸፈኑልኝ ንጉሥ ኃይለሥላሴ ነበሩ፡፡
አባታችሁ በሙያቸው እያገለገሉ በቤተመንግሥት ሠራተኛነት የቆዩት ለምን ያህል ጊዜ ነው?
ጃንሆይ የጡረታ ዕድሜውን እያራዘሙለት ብዙ ቆይቷል፡፡ ንጉሡ ወርደው ደርግ የመንግሥት ስልጣን ሲይዝ፤ ኮሎኔል

መንግሥቱ ኃይለማርያም “እናውቃለን፤ ብዙ አገልግለዋል፤ ምንም የተሻለ ነገር ስላላገኙ ባለዎት ደሞዝ ጡረታ

እንዲወጡ ፈቅጃለሁ” ብሎት የቤተ መንግሥት ሠራተኛነት ሲያበቃ፤ ፒያሳ ወንድሜ በከፈተው ሱቅ ለብዙ ጊዜ

ሠርቷል፡፡ አሁን አባቴም ወንድሜም በሕይወት የሉም፡፡ እኔ ሙያውን ያስተማርኩት ታናሽ ወንድሜ ተመስገን ደጀኔ፤

በፒያሳ ወርቅ ቤት እየሰራ ነው፡፡ በውጭ አገር የሚኖሩ ወንድምና እህትም አሉን፡፡
እስቲ ስለ ጀርመን ትምህርትዎ ያጫውቱኝ…
የገባሁበት ትምህርት ቤት 26 ሠራተኞችና 150 ተማሪዎች ነበሩበት፡፡ 149ኙ ተማሪዎች ጀርመናዊያን ነበሩ፡፡ መጀመሪያ

ላይ ቋንቋቸው ቢያስቸግረኝም 6 ዓመት የሚፈጀውን ስልጠና በ3 ዓመት አጠናቅቄ ነው ዲፕሎማዬን ይዤ የመጣሁት፡፡

በብርና ወርቅ ሥራ ዲዛይን በማውጣትም ሆነ ያንን በትክክል ወደ ተግባር በመለወጥ ከልጅነቴ ጀምሮ የዳበረ ዕውቀት

ስለነበረኝ፤ ትምህርቱን በቶሎ ለማጠናቀቅ አስችሎኛል፡፡ ትምህርቱ የሙያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ታሪክና ጠቅላላ

ዕውቀትንም ያካተተ ነበር፡፡ በዚህም በኩል ቢሆን አጥጋቢ ውጤት ነበር ያመጣሁት፡፡ በአገር ውስጥ ተማሪ እያለሁ

በሒሳብ ትምህርት ጎበዝ ነበርኩ፡፡ ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ነገር ባናውቅም የዓለምን ታሪክ በስፋት ነበር የምንማረው፡፡

ይሄ የጀርመኑን ትምህርት ቀላል አድርጐልኛል፡፡
ከጀርመን ከመጡ በኋላ ሥራ የት ጀመሩ?
ወንድሜ አቶ ክብርዬ፤ ከፒያሳውም በተጨማሪ በጊዮንና በሒልተን ሆቴሎች ተጨማሪ ሱቆችን ከፍቶ ስለነበር፣

ከጀርመን እንደመጣሁ ሥራ የጀመርኩት እሱ ጋር ነበር፡፡ በወቅቱ አባታችንም በቤተመንግሥት ይሰራ ስለነበር፣ ሦስታችን

በመተባበር ብዙ ሥራዎችን ሠርተናል፡፡ የአፄ ኃይለሥላሴ 80ኛ ዓመት የልደት በዓል ሲከበር ምድር ጦር፣ ፖሊስ

ሠራዊት፣ ፓርላማ፣ የሐረር ሕዝብ፣ የባሌ ሕዝብ … ትዕዛዝ እየሰጡን ልዩ ልዩ የስጦታ ዕቃዎችን፤ ከወርቅ ከብር፣

ከአልማዝ፣ ከከርከሮ ጥርስ … ሠርተናል። በዲዛይን ሥራዎቹ ላይ ሎሬት አፈወርቅ ተክሌም የተሳተፉባቸው ነበሩ።
እራስዎን ችለው መሥራት የጀመሩት መቼ ነው?
በ1968 ዓ.ም ጥቁር አንበሳ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት “ይሔይስ ደጀኔ ወርቅና ብር ሠሪ” የሚል መደብር ከፈትኩ፡፡
ከዚያ በኋላ ለአገር ውስጥና ለውጭ ብዙ ታላላቅ ሰዎች በርካታ ጌጣጌጦችን ሠርቻለሁ፡፡ አልችልም ብዬ የምመልሰው

ሥራ የለም፡፡ እንዲህም ሆኖ በሙያው ላይ አባታችን የነበረውን ዕውቀት አሁን በ76ኛ ዓመቴም አልደረስኩበትም

እላለሁ፡፡
ለእኛ ዕውቀት መሠረት አባታችን እንደሆነው ሁሉ፣ እኔም ሙያውን ለሌሎች ኢትዮጵያዊያን በማስተማሬ ደስተኛ ነኝ፡፡

የወንድሜና የእኔም ልጆች የቤተሰባችንን ሙያ ማስቀጠል የሚያስችል ዕውቀት አላቸው፤ ሥራውንም በደንብ እየሰሩት

ነው፡፡
በመጨረሻ በአገራችን የወርቅና ብር ሥራ ያለበትን ደረጃ ቢነግሩኝ…
በወርቅና ብር ሥራ የላቀ ችሎታ ያላቸው ኢትዮጵያዊያን በየቦታው አሉ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሉ የሚባሉት የከበሩ

ማዕድናትም ብዙዎቹ በአገራችን ይገኛሉ፡፡ እነዚህን ለመፈለግና ለመስራት ግን አንተጋም። የመስራት ስንፍና አለብን፡፡

ድሆች ተብለን የምንጠራው ለዚህ ነው፡፡ መንግሥትና ሕዝብ ከተባበሩ ይህ ችግር ይቀረፋል ብዬ አምናለሁ። ተባብረንና

ተከባብረን እንስራ የሚል መልዕክት ባስተላልፍ ደስ ይለኛል፡፡

በበደኖ አርባጉጉ አሰቦት አበምሳ እና በቀሪው የኦሮሚያ ክልል የተጨፈጨፉ ዜጎች የማን ትእዛዝ ነበር?
“ለረጅም ግዜ ኣብረን የኖርን እና የተዋለድን ስለሆን አንፈርምም :የአማራ ህዝብ አይመታም መመታት ያለበት ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ነው::” ሀጅ ቃሲም (ኣርባጉጉ)
ምንሊክ ሳልሳዊ
የፕ/ር ዓስራት ወልደየስ የመአሕድ ፕሬዝደንት ሰኔ 1ቀን 1984ዓ.ም ቁጥር መአሕድ /48/84 ለኢትዮጵያ የሽግግር መንግስት ተወካዮች ም/ቤት በአማራ ህዝብ ላይ የደረሰዉን ጭፍጨፋ እንዲያቆሙ የጻፉት ደብዳቤ ኦሕዴድ እን ኦነግ በጋራ የፈጸሙትን ወንጀል የሚያጋልጥ ታሪካዊ ማስረጃ ነው::
አንድ መቶ አመት ወደኋላ ተመልሰን ዛሬም አእምሮኣችንን እርቃኑን ከማስቀረት ከ100 አመት በፊት ከነበሩ ያልተማሩ መሪዎች ያነሰ የሚያስቡ ባዶዎች በዚህ በሰለጠነ ዘመን የፈጸሙት ወንጀል በትውልዳችን መጠየቅ ሊኖርበት ነው ብንል ባያስኬድም ለሁሉ የሚበጀው ግን መልካሙን ይዞ ማደግ ተመራጭ ነው::

በኣርባጉጉ የአውራጃ የኦህዴድ ተወካይ አቶ ዲማ ጉርሜሳ ግንቦት 26/1984 በአበምሳ ከተማና በኣካባቢው የሚኖሩትን የኦሮሞ ተወላጆችን ስብሰባ ከጠሩ በሆላ “ኣሼ :ኦዴ:ዒመና :ኣቡሌ በሚባሉ መንደሮች የሚኖሩ አማሮች ይገደሉ ብላችሁ ፈርሙ ” በማለት ትዕዛዝ ይሰጣሉ ከተሰበሰቡት የኦሮሞ ተወላጅ መካከል ሀጅ ቃሲም የተባሉ እጃቼውን ኣውጥተው
“ለረጅም ግዜ ኣብረን የኖርን እና የተዋለድን ስለሆን አንፈርምም :የአማራ ህዝብ አይመታም መመታት ያለበት ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጭ ነው ” የሚል አስተያየት በማቅረባቼው
የኦህዴዱ ተወካይ በመናደዱ ሽጉጡን ኣውጥቶ “የነፍጠኛ እረዳት ነህ በማለት ማስፈራራት ሲጀምሩ ስብሰባው የሀጅ ቃሲምን ሀሳብ በመከተል ተበተነ ::
ይህንን ባለ 6 ገጽ የፕሮፌሰር አስራትን ፊርማ የያዘ ደብዳቤ ይመልከቱ::
Image

Image

Image

Image

Image

Image

#MinilikSalsawi

Image

ያኔ እንዲህ ሳይምታታበት ጃዋር ኦህዴድን ኦሮሞን የሚያስገዙ አዲሶቹ ‹‹ጎበናዎች›› ብሎ ይተች እንደነበር ይታወቃል፡፡ ያኔ ‹‹ከጎበናዎቹ›› ይልቅ ከእነ አንድነት ጋር በመስራት የበኩሉን አስተዋጽኦም አድርጓል፡፡ እያቆየ ግን ጃዋር ከኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች እየሸሸ አሁን አብሯቸው እየሰራ ከሚገኘው ኢህአዴጎች ጎን መሸጎጥ ጀምሯል፡፡ ጃዋር ‹‹እኔ መጀመሪያ ኦሮሞ ነኝ›› ከሚለው አንስቶ ከህወሓት ጋር እንዲተባበር ያስገደዱት የተለያዩ ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አንዱና የመጀመሪያው እሱ ‹‹ቀኝ ጽንፍ›› ብሎ የሚጠራቸው ፓርቲዎች ከሌሎቹ የተሻለ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ነው፡፡ ጃዋርና አቶ ቡልቻ ይበልጡን መጥበብ የጀመሩት አንድነት አብሮት መሄድ ካልቻለው መድረክ ይልቅ ከሌሎች ህብረ ብሄራዊ ፓርቲዎች ጋር ትብብር ለመፍጠር ፍላጎት እንዳለው በተነገረበት ማግስት ነው፡፡ ሰማያዊና አንድነት በሰላማዊ ሰልፍና በሌሎች መንገዶች ጠንከር ያለ የፖለቲካ እንቅስቀሴ ሲያደርጉ ደግሞ እነ ጃዋር ‹‹የጠላቴ ጠላት›› ብልሹ ፖለቲካ ውስጥ ገቡ፡፡

ዶ/ር መረራ ጉዲያ በአዲሱ መጽሃፋቸው እንደሚገልጹት 97 ላይ ቅንጅት ጠንካራ እንቅስቀሴ ሲያደርግ ህወሓትም ሆነ ኦህዴድ ‹‹የጸረ ነፍጠኛ›› ግንባር ለቋቋም ጥሪ አድርገውላቸው ነበር፡፡ ዶክተሩ ‹‹አልፈልግም!›› ብለው ባይመልሷቸው እሳቸውም በነ ጃዋር ‹‹አዲስ ጎበና›› ሆነውት አርፈው ነበር፡፡ ይህ ለደ/ር መረራ የቀረበ ጥሪ አንድነትና ሰማያዊ ሲጠናከሩ፣ አሊያም ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ኦህዴድ እራሱን ሊያጠናክር፣ ወይንም የዲያስፖራውን ጫና ለመቀነስ ጃዋርና የእነ ለንጮው ኦነግም ‹የጸረ ነፍጠኛው›› ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡ ይህን ተከትሎም የእነ ለንጮ ለታው ኦነግ በ2007 ዓ/ም ምርጫ ለመድረስ እየተሰናዳ እንደሆነ እየተወራ ነው፡፡ ኦነግ ለ‹‹ጸረ ነፍጠኛ›› ትግሉ ያመቸው ዘንድ አገር ውስጥ የራሱን ጠባብ ሚዲያዎች ማቋቋም ጀምሯል፡፡ ለአብነት ያህል ከወራት በፊት ‹‹ሰፉ›› የተባለች በኦሮምኛና አማርኛ የምትታተም መጽሄት ገበያ ላይ አውሏል፡፡ ለዚህም የተደራዳሪዎቹ የኦህዴድም ሆነ ህወሓት ይሁንታ እንደሚያስፈልግ አጠያያቂ አይደለም፡፡ የመጽሄቷ ዋና አላማም ስለ አሁኑ ዘመን ጭቆናም ሆነ በደል ሳይሆን ‹‹አማራ በኦሮሞ ህዝብ ላይ ያደረሰውን በደል ማጋለጥ ነው››፡፡ ይህ እንግዲህ የድርድሩም ሆነ የኦነግ ስልት አንዱ አካል መሆኑ ነው፡፡ ህወሓትና ኦነግ የሚስማሙበት አላማ!

በእርግጥ ወደ አገር ውስጥ የሚመለሱት የኦነግ አመራሮች ብቻ አይደሉም፡፡ ጃዋር ሊመለስ እንደሚችልም አንዳንድ ጭምጭምታዎች እየተሰሙ ነው፡፡ ኢህአዴግ ከሌሎቹ ተቀናቃኞቹ ይልቅ ለጃዋር ርህራሄ ማሰየቱን ማሳየቱ አንድ ፍንጭ ነው፡፡ እነ አቡበክር፣ እስክንድር፣ ርዕዮት…. በእጃቸው ምንም ሳይገኝ፣ በፍጹም ሰላማዊነታቸው ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ሲፈረድባቸውና ፊልም ሲሰራባቸው የሜንጫ ጀብድን ሲያስተምር የታየው ጃዋር ምንም አልተባለም፡፡ ከእሱ ይልቅ ኮፈሌ ውስጥ ለበቅ የያዙ ወጣቶችን ከቦኮሃራም፣ ከታሊባንና አልቃይዳ ጋር እያመሳሰሉ ‹‹አሸባሪዎች›› ብለው ፊልም ሰርተውባቸዋል፡፡ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ደግሞ ኤሊያስ ክፍሌ ስለ ኤሌክትሪክ ገመድ ማቋረጥ ያወራው ‹‹የአሸባሪዎች ማንነት ማሳያ!›› ተደርጎ ሊቀርብ ነው፡፡ በምን መመዘኛ የኤሌክትሪክ መስመር መቁረጥ የሰው አንገት በሜንጫ ከመቁረጥ በልጦ ‹‹ሽብር›› ሊሆን ይችላል? የጃዋርን ‹‹ጀብድ›› እነ ዶ/ር መረራ፣ ዶ/ር ብርሃኑ፣ የኢሳት ጋዜጠኞች፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዱዓለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ….አውርተውት ቢሆን ኖሮ ስንት ፊልም ይሰራበት ነበር? ኢህአዴግ ይህንን የጃዋር ጀብድ አሁን ባይጠቀምበትም መቼም አይጠቀምበትም ማለት አይደለም፡፡ ሌሎች እሱ ከእኛ በላይ የሚያውቃቸውንም ሚስጥሮች እንደተደራደረባቸው ሁሉ ወደ አብሯቸው እየሰራ እንዳያፈነግጥም በልጓምነት ይጠቀሙበታል፡፡ እግረ መንገዱን በርካታ ‹‹ፋኦሎችን›› ያሰሩታል፡፡

በእርግጥ ጃዋር በፖለቲካው ከስሮ ወደ አገር ቤት የገባ የመጀመሪያው ሰው አይደለም፡፡ በርካቶቹ ከእሱ በላይ ‹‹ጀግና›› ተብለው ከህወሓት/ኢህአዴግ ብብት ተሸጉጠዋል፡፡ እነ ሰለሞን ተካልኝ ኤርትራ በርሃ ድረስ ሄደው ‹‹በለው!›› እንዳላሉ ተመልሰው ‹‹ይቀጥል!›› ብለዋል፡፡ ሙዚቀኞች፣ ጋዜጠኞች ፖለቲከኞች፣ የእምነት ‹‹አባቶች›› ብቻ በርካቶች እየከሰሩ ተመልሰዋል፡፡ ሲወናበድ የኖረው ጃዋር ተደራድሮ ቢመለስ የሚገርም አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ ለጃዋር አገሩ ናትና መመለሱን የሚጠላ የለም፡፡ ችግሩ በዚህ ስርዓት ምርጫ እንደሌለ ሲናገር እንዳልቆየ ለምርጫ ሊመለስ መሆኑ መነገሩ ነው፡፡ ለኦሮሞ ህዝብ ባለመቆማቸው ኦህዴዶችን ‹‹ጎበናዎች›› እንዳላለ ከህወሓት፣ ብአዴንና ደኢህዴን ስር የሴቶች፣ የትራንስፖርት……ሚኒስቴር ስር ለመስራት ከፈቀደ ነው፡፡#MinilikSalsawi

Image

ባህር ከማል

የአንድ ወጣት እድሜ አስቆጥሯል፤ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው ቡድን ህወሃት/ኢህአዴግ መግዛት ከጀመረ። በብሄርና በሃይማኖት እኩልነት ስም ህብረተሰቡን በመከፋፈል ለሃያ ሶስት አመታት ስልጣኑ ላይ ከመቆየቱም በላይ፤ ጥቂቶቹ የቡድኑ አባላትና ደጋፊቆቻቸው በጉቦ በዘረፋና ለም መሬት በመሽጠት ጭምር ሲከብሩ፤ ብዙሃኑ ሕዝብ ግን ኑሮው ከእለት እለት እያሽቆለቆለበት ሲሄድ፤ አገዛዙ ግን በአሥራ ምናምን ከመቶ አድገሃል እያለ ሕዝቡን ሊያታልለው ይሞክራልል።

በአሳ መበላት፤ በዘራፉዎች መደብደብና መዘረፍ ከዚያም አልፎ ተገድሎ የሆድ እቃው መቸብቸብ እንዳለ እያወቀ ባለሁበት ሁኜ ከሚሞት እድሌን ልሞክር በማለት ክፍት በሆነለት መንገድ ከአጋሪቷ የሚሸሸው ህዝብ ቁጥር ከፍተኛ ነው ። ከዚህ ሁሉ መከራና ስቃይ ተርፈው ወደ “ተፈለገበት አገር” የሚደርሱ ወገኖቻችን እዚያም ከደረሱ በኋላ የሚደርስባቸው ስቃይና እንግልት ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም። ለዚህም በአለም ደቻሳ በሊባኖስ፤ በሸዋዬ ሞላ በሊቢያ፤ እንዲሁም ካሜራና የድምጽ መቅረጫ ያላገኛቸው በሺዎች በሚቆጠሩ፡ ወገኖቻችን የደረሰባቸውና ዛሬም በሳውዲና እንዲሁም በደቡብሱዳ እየደረስባቸው ያለው መከራና ስቃይ በቂ ምስክርነው። በእንቅርት ላይ ጆሮደግፍ እንዲሉ ሊወክላቸው የሚገባው መንግስት ህገወጥ ስደተኖች ናቸው ብሎ ተሳልቆባቸዋል።

ከላይ እንደገለጽኩት የገዢው ቡድን ህብረተሰቡን በመከፋፈልና ያለውን ሃይል በመጠቀም ጭምር እስካሁን ስልጣን ላይ ለመቆየት በቅቶአል፡:

የዛሬው ሁኔታ ባለ መልኩ ለዘላልም ስለማይቆይ ሁሉም ነገር ያልፋልና እነሱ ሲያልፉ (በጡረታም ሆነ በደከመን ወይም በዘረፋው በቃን ሲገለሉ) ልጆቻቸውን ለመተካት ሽርጉዱ ከተጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። መተካካት ይሉታል በነሱ ቋንቋ ።

የመተካካቱ ጉዳይ ተግባራዊ ለማድረግ የመጀመሪያ እርምጃ ተተኪዎችን በአምሳያቸው ማሰልጠን ስለሆነ ለዝህም ለጆቻቸውን በውጭ ሃገር በጥሩ ትምህርት ቤቶች (በአብዛኛው ለዚሁ ጉዳይ) አስተምረዋል እያስተማሩም ነው:: በአንድ ውቅት ይህንኑ የታዘበው ጋዜጠኛ ተመስግን ደሳልኝ እንድህ ብሎ ጽፎ ነበር፡

“በእርግጥ እናንተ ሲደክማችሁ ብላቴና ልጆቻችሁን ለመተካት አስባችሁ ከሆነ የክፍለ ዘመኑ አስቂኝ ቀልድ ነው። ያውም እንዲህ የሚል..ብሶት ከወለዳቸው ወደ ደም የወለዳቸው የሚደረግ መተካካት…በሰም እና አጥንት ቆጠራ ለስልጣን መብቃት ወይም በአባት እግር ልጅን መተካት። ይህ ከሆነ መቼም በነካ እጃችሁ የመሬት ፖሊሲያችሁንም ወደ … ርስተ ጉልት … ሲስተም መቀየር የሚኖርባችሁ የመስለኛል።”

ገዢው ቡድን እንኳንስ ለሚያስቅ ለሚያስለቅስ ያውም የደም እምባ ተግባር ግድ የለለው መሆኑን ላለፉት ሁለት አስርት አመታት ሲያሳየን የሰነበተ በመሆኑ ከተሳካለት ለሳቃችን ብዙም ደንታ የለውም። የመሬት ስሪቱንም በተመለከተ ዛሬም የመሪት ባለቤት ማን ሆኖ ነው።የገዢው ቡድን ነው ገንዘብ ሲያጥረው በእንቨስትመንት ስም መሬቶችን እየቸበቸበ ያለው።ያውም ነዋሪዎችን ከቄዬያቸው በማፈናቅል።

ሃገርን የሚያህል ነገር ለማስተዳደር አነሰም በዛ በተመሳሳይ ሁኔታ በተግባር መፈተንን የግድ ይላል። ይህንን ስል መልካም አስተዳድርን ማለቴ ሳይሆን በስልጣን ላይ እንዳለው ቡድን ለራስ በሚያመች ሁኔታ መግዛትና ህዝቡን መቆጣጠር መቻል ማለቴ ነው። የህወሃት አባላት ይህንን በረሃ በነበሩበት ወቅት ተለማምድው ነው ቤተ-መንግስቱን የተቆጣጠሩት። ስለዚህም ለተተኪዎቻቸው የሙከራ ሜዳ ማስፈለጉ አልቀረም:: አገር ውስጥ መዋቅሩን እነሱ ስለዘረጉት ተተኪዎቻቸውን (ወራሾቹን) ለማሰልጠን ላያስችግር ይችላል። በዝህ የስለላ መዋቅራቸው (አንድ ለአምስት) ህዝቡን ለግዜውም ቢሆን ጠፍሮ ስለያዙት ስጋታቸው ሌላ ቦታ ነው። ለገዢው ቡድን የራስ ምታት የሆነውና ለወደፊትም ለወራሾቻቸው (ለማውረስ ከበቁ) ጭምር መሆኑ የሚቀጥለው የዳያስፖራው ክፍል ስለሆነ፤ ይህንን ክፍል ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ቀጥሎ፤ ዛሬ ወራሾቻቸው ከሆኑ ዳያስፖራውን መቆጣጠር ከቻሉ የተሳካ ውርስ ሊሆንላቸው ስለሚችል ይህንኑ የተያያዙ ይመስላል። ለዚህም ያለፈው ሰሞን የሳውዲ ተቃውሞ ሰልፍ ሁኔታና የነሱ ቀደም ቀደም ማለት በቂ ምስክር ነው።

ተመስገን ጽሁፉን በመቀጠል

“ከአባት አመራርም ወደ ልጆች አመራር ልታሸጋግሩን መዘጋጀታችሁም ምን አልባት የምትመሩትን ህዝብ አለማወቅ እንዳይመስልባችሁ ብትጠነቀቁ መልካም ነው። ምን አልባት የምትነጥፍው ጥገት ታልባ የተገኘውን ማውረስ እንጂ ሃገርና ህዝብን ለማውረስ መሞከር የመጨረሻ መጀመሪያ ሊሆን ይችላል ።” ብሎ ነበር

እነርሱ ለምክር የሚሆን ጆሮ ያላቸው አይመስልም። ስልጣናቸውን ተጠቅመው ሀብት አፍርተዋል። የቀራቸው ለስም መጠሪያ የሚያገለግል ዶክቶሬት መሸመት ስለሆነ ይህንኑን ከሰሞኑን የአለም ረከርድ ባሻሻለ ሁኔታ ተያይዘውታል። ስልጣኑን ለልጆቻቸው ካወረሱ በኋላ በጡረተኛ ኑሯቸው ዶክተር እገለ ተባብለው ኑሯቸውን ለመግፋት።

ዳያስፖራው

የተቃዋሚው/የአማራጩ ክፍል ግን ገዚው ቡድን ካጠመደለት የክፍፍል ወጥመድ ብዙም ያመለጠ ሳይመስል 23 አመት አስቆጠረ::

የሃገር ቤቱን የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴን በተመለከተ በዘርም ሆነ በብሄራዊ ደረጃ የተደራጁ ፓርቲዎች እንደ አሸን የፈሉበ ወቅት ከመሆኑ ባሻገር ሀዝቡን በማሳተፍም ሆነ ጫና በመፍጠር ገዢውን ቡድን በህዝባዊ ምርጫ ለመለወጥ አለመቻላቸው እንዳለ ሆኖ ብዙዎቹ በሰላማዊም ሆነ በሌላ አማራጭ ለሥርዓት ለውጥ ትግላቸውን ቀጥለዋል:: ለትግሉ እስካሁን ውጤታማ አለመሆን ምክንያታዊ ሃተታውን ግን ሃገር ቤት ላሉት ገምጋሚዎች ብተው መልካም ነው።

የዳያስፖራው ተሳትፎ ግን ልዩ መልክና ሚና አለው:: በተለያዩ ምክንያቶች ከነበረበት አገር ለቆ ወደ ሌላ አገር ለተወሰነም ሆነ ላልተወሰነ ጊዜ እየኖረ ያለ ሰው/ማኅበረሰብ ቀድሞ ለነበረበት አገር ሰዎች ‹ዳያስፖራ› ይባላል (dispersed; Diaspora /የፈለሰ፤ ፈላሻ ፡፡ ባጭሩ ይህ የዳያስፖራ ትርጉም ሲሆን ይህ የህብረተሰብ ክፍል ለትውልድ አገሩ (Home land) በፖለቲካው በኢኮኖሚውና በማህበራዊ ኑሮ ረገድ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው።

አፋኝ የሆኑ አምባገነናዊ መንግስታት ባሉባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉት ሃገሮች ሚዲያ በገዢዎች ቁጥጥር ስር ሆኖ ለነሱ ፕሮፖጋንዳ መሳሪያነት ብቻ በሚያገልግልበት ዳያስፖራው የራሱን ዘዴ በመጠቀም መሬት ላይ ያለውን ተጨባጭ መረጃዎችን ለህዝብ ለማድረስ አቅም አለው። በተለይም በአሁን የመረጃ ቴክኖሎጂ ክፍለ-ዘመን፤ ማህበራዊ የመረጃ ልውውጦሽ በተስፋፋበት ስራውን ያቃልለታል። ሀገር ውስጥ ያለውን እንቅስቃሴ በገንዘብ በመደጎም አንጻርም የተሻለ አቅም ያለው ማህበረሰብ ነው።በ እንግድነትም ሆነ በቋሚነት በሚኖርበት ሁለተኛ አገሩ ባሉት መግስታት አማካይነት በትውልድ አገሩ አገዛዝ ላይ ጫና በማስፈጠርም ሚና ይጫወታል። ለዝህም ሃገራችንን በተመለከተ ምርጫ 97ትን አስከትሎ ገዚው ቡድን በህዝብ ስም የሚሰበስበውን እርዳታ በተመለከተና የ2006 የኢትዮጵያ ዴሞክራሲና ተጠያቂነት ድንጋጌ ህገ-ረቂቅ (H.R.5680 (Bill) known as The Ethiopia Freedom, Democracy and Human Rights Advancement Act of 2006) በምሳሌነት የሚጠቀስነው። ለቅንጅትም ስኬታማነት ዳያስፖራው ጉልህ ሚና ተጫውቷል። በተሟላ የ97 አይነቱ መንፈስ ጥንካሬ ባይሆንም የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ለትግሉ ወደፊት መራምድ ተጽ እኖ ማሳደሩን እንደቀጠለ ነው። በጥቅሉ ዳያስፖራው ለትውልድ ሃገሩ (Home land ) ለሚደረገው ለውጥ የሚጫወተው ሚና የጎላ ቢሆንም፤ ወሳኝነት የለውም፡፡ ወሳኙ ህዝቡ ነው፤ ችግሩንና ብሶቱን እየኖረ ያለው እሱ ነውና።

በአንጻሩም ሁሉም የዳያስፖራው ማህበረ ሰብ አባል ለትውልድ አገሩ እኩል ይቆረቆራል ወይም ይሳተፋል ማለት አይደልም።ሁሉም ከህወሃት/ኢህአዴግ ከከፋፍለህ ግዛ ዘይቤ የጸዳ ነው ማለትም አይደለም። እንዲያም ከሀገር ውስጥ ይልቅ መከፋፈል በጉልህ የሚታይበትና የሚተገበርበት በዳያስፖራው ሳይሆን አይቀርም። በዘር በሃይማኖት እንዳለ ሆኖ አልፎ አልፎ በተመሣሣይ እምነትና ዘር መንደርን ጨምሮ ክፍፍል ይንጸባረቃል። የክፍፍል ወረርሺኝ ባህር ተሻግሮ እዚህ ካለንበት ሲያተራምሰን ማየቱ እጅግ ያሳዝናል:: ይህም በበኩሉ ከመተማመን መጠራጠርን፡ ከመከባበር መናናቅን፡ ከጋራነት ግለኝነትን ካንድነት መከፋፈልን አስፍኗል። አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ይህንን የሚያራምዱ ጥቂት የማይባሉ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ በበኩሉ ትግሉን ያከብደዋል ያራዝመዋልም።

በርግጥ በግል አነሳሽነት ብዙ መስራት ቢቻልም ለአስትማማኝና ዘላቂ ውጤት ግን በጋራ መስራት አማራጭ የለውም። ለዚህም ነው የድርጅትና የመሪዎች አስፈላጊነትና ወሳኝነት። ከላይ በጠቀስኩት ምክንያት አብሮ መስራት በማይቻልበት ወቅት ሰዎች የራሳቸውን ድርጅት ለመመስረት ይወስናሉ::

በርግጥ ይህ ለትግሉ ቀጣይነት አማራጭ ከመፈልግ የመነጨ ቢሆንም የድርጅት ጋጋታ ለብቻው መፍትሄ ልሆን አይችልም። ትግላችን የሚለካው ሃገር ውስጥም ሆነ ውጭ ባሉት የድርጅቶች ብዛት ቢሆን ኖሮ ለህዝባችን ያሰብነውን መልካም አስተዳደር እውን ባደረግን ነበር።

የድርጅት መብዛት ውድድሩን ያሰፋና የተወሰኑት ጠንክረው አሸናፊ ሆነው የወጣሉ ብለው የሚከራከሩ አልጠፉም። በሃገራችን የተፈጠሩት ድርጅቶች ግልጽ በሆነ የፖለቲካ ስርአት ላይ ሳይሆን ብሄርን መስረት ያደረጉ በመሆኑ ለፉክክር የማያመቹ ናቸው ያ ከሌለ ፉክክር ደግሞ አንዱ አሸናፊ ሆኖ መውጣቱ አይኖርም ማለት ነው። ስለዝህም መሬት ላይ ያለው እውነታ የሚያሳየው በሚያመቸው መልኩ የድርጅቶች አብሮ መስራት የግድ ይላል። የሰው ሃይልና ሃብት/ገንዘብ አንድ ላይ በማምጣት ያሉት ድርጅቶች እንዲጎለብቱና ትግሉን በዘላቂነት እንዲቀጥሉ ይረዳል።

ብዙዎች የዲያስፖራው ማህበርሰብ አባላት፤ አቶ ሃይለማርያም የገዚው ቡድን መሪ ሆኖ ሲተኩ ከቅን አመለካከት የተነሳ፤ መሰረታዊ ባይሆንም ለውጥ ይኖራል፡ በይቅር መባባል ህዝባችንን ወደ ተሻለ አቅጣጫ መምራት ይቻላልና ጊዜ እንስጣቸው ብለው ነበር ። ያ ሳይሆን ቀረ። አሁንም ተስፋ ባለመቁረጥ ምንም እንኳን የተለወጠ ነገር ባይኖርም የማንዴላን ህልፈት በማስታከክ ለእውነትና ለእርቅ (truth and reconciliation) በድጋሜ ጥሪ እየቀረበ ነው።

የበደልንን ይቅር ብሎ አብሮ ለመስራት መፍትሄ መፈለግ ለሁሉም ይበጃል። ተበዳዩ ህዝብ ነውና እሱኑ ይቅርታ ጠይቆ እሱኑ ለማገልገል አብሮ መስራት ብልህነት ነው። የቂም ፖለቲካ የትም አያደርስምና። ችግሩ ግን እርቅ የሁሉንም በጎገ ፍቃደኝነት ይጠይቃል። በምኞት ብቻ የሚሆን አይደለም። ከምኞትም አልፎ አስገዳጅ ሆኔታዎች መፈጠር የግድ ይላል። የደቡብ አፍሪካን ስንመለከትም የአለም አቀፍ መንግስታት ጫና፣ መገለልና አለም አቀፍ ፖለቲካ አሰላለፍ በመለወጡ ጭምር እንጂ ዘረኛው የነጮች መግስት ከምንም ተነስቶ አይደለም ማንዴላንና ፓርቲያቸውን የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስን ነጻ ያደረጋቸው።

ህወሃት/ኢህአዴግ ከጥንስሡ ጀምሮ እያካሄደ ያለው የቂም ፖለቲካ ነው። ብዙ አመታት ወደኋላ ሄዶ እንድህ ነበርን/ነበራችሁ፡ ተደረግን/ተደረጋችሁ እያለ ለስልጣን መቆያ ከመጠቀም ባሻገር እየተጓዘበት ያለው መንገድ የትም እንደማያድርስ አውቆ፤ አንዴም ቆምብሎ አስቦ አብሮ የመድራትን ፍንጭ ያሳየበት ወቅት የለም።

የተቃዋሚው ክፍል ጫና ማሳደር ካልቻለ እርቅ ምኞት ሆኖ የቀራል። በርግጥ ገዢዎቻችን ቢያውቁበት ኖሮ፤ ፕ/ት ኦባማ እንዳሉት በፍቃደኝነት ህዝቡን ነጻ ቢያወጡ፤ እነሱ ጭምር ነበር ነጻ የሚወጡት:: ጊዜያቸው ሲደርስ መውደቃቸው ላይቀር። ያኔ ግን ለይቅርታ ጊዜው የመሸ ይሆናል።

ከዳያስፖራውም ክፍል ለሆዱ ያደረና ከህዝቡ ይልቅ ህገር ቤት የቀለሰ ጎጆ የሚያሳስበው፤ ቤተሰቡን ሰብስቦ ለቀሪው ዘመዱ ላልሆነው የማይጨነቅ “ገለልተኛ ነኝ” ባይ፤ እኔ ፖለቲካ አልወድም ከሚለው አልፎ ፤የመቶ አመት ታሪክ እየጠቀሰ ተበድለን ነበር ፤ በተቃራኒው “ለዘመናት የነበረህን ቦታ ዛሬ ተቀማህ” እያለ ጢቂቶችን የሚያስጨበጭብ…. .ወዘተ አውቆም ሆነ ሳያውቅ የገዢውን ቡድን እድሜ የሚያራዝም በተቃዋሚው ጎራ ነኝ ባይ ቁጥሩ ቀላል አይደለም። የገዚው ቡድን አንደኛውን “ጠባብ” ሌላኛውን ደግሞ “ነውጠኛው ዳያስፖራ” ብሎ የጠራቸዋል። ለትግብርቱ ግን ቀዳሚው እርሱ ነው። ሁለቱም ቃላት ብዙውን ግዜ ያለቦታቸው ጥቅም ላይ ስለሚውሉ ባይመቹኝም ከላይ የተጠቀሱትን በተመለከተ ግን ሃቁን ያንጸባርቃሉ።

ጥሩም ሆነ መጥፎው፤ ክፉም ሆነ ደግ ያለፉት የኢትዮጵያ ታሪኮች ወደድንም ጠላን የጋራ ታሪኮቻችን ናቸው። ያለፈወን ታሪካችንን መዝግበን የምናቆየውና የምናስታውሰው መጥፎውን ላለመድገምና ጥሩውን ደግሞ ያለንበት ዘመን የሚፈቅድ ከሆነ ለማስቀጠል አሊያም በጥሩነቱ ለማስታወስ እንጂ ለቂም በቀል መጠቀሚያነት ለማዋል አይደለም። እዚህ ላይ በማንኛውም ህብረተብ በአብዛኛው ያለፉት ታሪካዊ ስህተቶች በስህተትነታቸው የሚታወቁት ከብዙ ጊዜ በኋላ እንጂ በወቅቱ ተጫባጭ ሆኔታ እንደ ስህተት ተደርገው አይቆጠሩም። ከነዚህ ስህተቱች ያመለጠና ፍጹም የሆነ የአለም ታሪክም የለም።

ህዝባችን የሚፈልገው የዛሬው ጎስቋላ ኑሮው የሚሻሻልበት፤ ነጻ አየር ተንፍሶ በመኖር የተሻላች ሃገር ለመጪው ትውልድ የሚያስተላልፍበትን ሁኔታ የሚያመቻችለትን እንጂ ብዙ አመታት ወደኋላ ሄዶ በታሪክ ያሳለፈውን ኑሮ እንዲኖር ወይም ከዛሬው መከራና ስቃይ በተጭማሪ ያሳለፈው ችግር እያስታወሱት ለጊዚያዊ የፖሊቲካ አላማቸው መጠቀሚያ የሚያደርጉትን የአዞ እንባ የሚያነቡለትን አይደለም።

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ ተደራጅቶ እንደታወቁት የአይሁዶች የኩባና የአይርላንድ ዳያስፖራ ድርጅቶች ደረጃ ለመድረስ ጊዜ የሚወስድ ቢሆንም፤ ያላቸውን ሃይልና ገንዘብ አንድ ላይ በማምጣት ልዩነትን አቻችሎ፤ ከመጠላልፍ መደጋገፍን፤ ከግትርነት ሰጥቶ መቀበልን በማስቀደም፡ ሁሉንም እኔ አውቃለህና ተከተለኝ እኔ ብቻ ልናገርና አንተ አድምጠኝ፡ ፍጹም ነኝና እኔን ለማረም አትሞክር የመሳሰሉትም ግብዝነትን ትተን፤ በተቃራኒውም የሚሰራ ሰው እንደሚሳሳት በመዘንጋት አሊያም ሆን ተብሎ ትግሉን ለማደናቀፍ የምንሰነዘረውን ቅጥ ያጣ ገንቢ ያልሆነ ትችትን፤ እንደ ጭቃ አንስቶ መለጠፍን አቁመን ለዋና ግባችን (የስርአት ለውጥ) አብረን ከሰራን፤ በየምንኖርበትርበት ሃገር የውጭ ፖሊሲ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖን በማሳደርና ህገር ውስጥ ለሚደረገው ትግል የተሟላ ድጋፍ በመስጠት ገዢው ቡድን ቢያንስ ወደ ክብ ጠረጴዛ እንዲመጣ ማድረግ ይቻላል። ያለ ጫና ከህወሃት/ኢህአዴግ እርቅ መጠበቅ ከየዋህነትም አልፎ ጅልነት ነው።

አላህ ኢትዮጵያን ከነ ህዝቦቿ ይባርካት

ባህር ከማል

ለአስተያየት [email protected]

አባዱላ: ምንድነው ጩኸቱ???!!!!! ቴዲ: ልምምድ ላይ ነን አሁን “አላምን አለና…..” እሚለውን ዘፈን ስጨርስ መምጣትህ ነው አባዱላ: ወይ ልጅ ቴዲ ልባም ነህ እኮ!! እንግዲህ አዝናለሁ…. በጅማ: በአዳማና…. ቴዲ: ይዘንባል? ከፊል ደመና? ጸሃያማ? አባዱላ: አንተ ልጅ ምንድነው ዛሬ ያጨስከው?!!…..ገና እሚያስጨስ ነገር ልነግርህ ነው! ቴዲ: ሌላ ልጅ ገጨህ ልትሉኝ እንዳይሆን??!!!!! አባዱላ: ወደ ገደለው ስንገባ ኦሮሚያ ውስጥ አትዘፍንም:: አሻፈረኝ ካልክ ሌላ መለስን ተማምኖ በረንዳ ያድር የነበረ ምስኪን ገጭቶ አመለጠ እንላለን ቴዲ: ምን አጥፍቼ ነው ይሄ ሁሉ መአት አባዱላ: ያው የሰሞኑ ክስ ነው …ቅዱስ ጦርነት….ሆሊ ዋር ቴዲ: አምለሰት ትሙ…ት አላልኩም!! ይህው መጽሄቱ አንብበው: በተጨማሪ ፌስቡክ…ፌስቡክ አለህ እንዴ?….ብቻ አሳውቄአለሁ..ሌላው የመጽሄቱ ኤዲተር በኢሜይል ለላከላቸው ሰዎች ስህተቱ የራሱ እንደሆነና ይቅርታ እንደጠየቀ ሳትሰማ አልቀረህም…እኔ ምን ማድረግ አለብኝ ከዚህ በላይ? አባዱላ: እንዲህ አይነት ስህተት የለም የቴክኒክ ችግር ያለውን ያጎድላል ቃላት ያባዳል ወይንም የሌላ ሰው ጽሁፍ አሳስቶ አንተ ውስጥ ይከታል…ተመሳሳይ ይሁፍ ደግሞ አልነበረም…ግን ደግሞ መጽሄቱ ተነባቢነቱ በእትም ስለሆነ ታትሞ በተበተነው ላይ የተባለው ስህተት የለም…ብቻ ግፊት አለብን ቴዲ: አያድርስ ነው አባዱላ አባዱላ: ግን አይገርምህም ህወሃቶች even በተመሳሳይ ሚዲያ ውስጥ ያሉት ድርቅ ብለው ጉዞ ወደቅዱስ ጦርነት ምናምን ነው እሚሉት ቴዲ: እነሱ ፖለቲካም ………ቆይ ለምን አልዘፍንም ምክኒያቴ አሳማኝ አይደለም?? አባዱላ: “ግፈኛውን ሚኒሊክ ያሞካሻል ይሄ ለኦሮሞ ህዝብ ያለውን ጥላቻ ያመላክታል” ይሉሃል ቴዲ: ይሄ ኮሜዲ ነው:: እኔኮ “ሚኒልክ ሚኒሊክ; ደግ አደረክ” እሚል ዘፈን አልዘፈንኩም:: ምኒሊክ የሚመሰገንበትን ከአድዋ ጋር ያለውን ስብእናውን ነው የዘፈንኩት እንደውም አድዋ የሁሉም ኢትዮጽያዊ ደም እና አጥንት ዋጋ መሆኑን ለመዘከር …… አባዱላ: ለማንኛውም እኛ ስፖንሰር እሚያደርገውን አካል ስምምነታችሁን እንድታፈርሱ ማስገደድ አንችልም ግን በሙዚቃ ዝግጅቱ ላይ ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ሃላፊነት እንደማንወስድና የጥበቃ ስራ እንደማንሰራ እናሳውቃለን… ቴዲ: ታዲያ ይሄ ዝግጅቱ አይካሄድ ብሎ ከመከልከል በምን ይለያል? አባዱላ: አራዳ እኮ ነሽ ቴዲ: ቀመርና አጫሉ በሚኒሊክ ለተፈጁ ሰዎች መታሰቢያ ዘፈን ሊለቁ ነው አባዱላ: እና ምን ለማለት ነው….ወዴት ወዴት ነው? ቴዲ: ኖ አባዱላ እኔ አስተሳሰቡን ነው…እኔ ሚኒሊክ ደግ አደረጉ ብዬ ሳልዘፍን የሳቸውን መልካም ስራ ስላሰብኩ ብቻ በክልሉ ሙዚቃ እንዳልጫወት ፈረዳቹ…እነ እጫሉ የሳቸውን ክፉ ስራ አሰባችሁ ብሎ ሰፈሬ አትምጥ የሚል የልጅ ስራ ተመሳሳይ ትርጉም አይዝም? አባዱላ: እኔ እንደዛ አስቤው አላውቅም በዚህ አይነት እነ እንትና በዚህ ሰፈር እነ እንትና በዚህ መንደር ሙዚቃ ማቅረብ አይችልም የፖለቲካ ትርጉሙ ሲሰፋ ደግሞ ሌላ ነው… ቴዲ …… አባዱላ……. ቴዲ…… አባዱላ……. as I clearly put in the note entitled “what is Oromofirst doing ?” I only stand against the campaign logo. evidences revealed so far dont support the claim given over there. however I enjoyed the mesmerizing vibe oromo ethiopians showed.

Image
“ፓርቲው ወደ ፊት ተራመደ ወይስ ወደኋላ” – በተቃዋሚ ፓርቲዎች ካምፕ የአመራር ንጥፈት ማሳያ
“የፖለቲካ ኃይሌ ተሟጦ አልቋል” በማለት ከፖለቲካው መድረክ የተገለሉት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ውስብስቡን የውህደት ማመልከቻ የመመርመር ታሪካዊ ኃላፊነት የወደቀባቸው ይመስላል። ኢንጂነር ግዛቸው የወጣቶች ሚና መጉላት እንዳለበት ደጋግመው ቢገልፁም፤ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ፓርቲው በእጃቸው ላይ እንዲወድቅ ሆኗል። ……የኢህአዴግ ፋሽን የሆነው “መተካካት” በተቃዋሚው ጎራ ውጤታማ እንዳልሆነም የሚገልፁ አልጠፉም። በተመሳሳይ መንገድ የእነ አቶ አዲሱ ለገሰን ወደ አመራር መመለስ በማየት በገዢውም ሆነ በተቃዋሚ ጎራ “መተካካት” ሳይሆን በስልጣን “መመላለስ” አድርገው የተገነዘቡም ይመስላል።የሀገሪቱን ፖለቲካ በትውልድ መነፅር የሚለኩ ወገኖች ዛሬም ቢሆን “የ60ዎቹ ትውልድ” የሀገሪቱን የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተቆጣጥሯል የሚል ቅሬታ እየተደመጠ ነው። አንድነትም ቢሆን የወጣት አመራር በማጣቱና በመቸገሩ በኢንጂነር ግዛቸው ስር መጠለሉን እንደመረጠና አማራጭም እንዳጣ በመግለፅ በማሳያነት የሚያቀርቡ አሉ።
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … -post.html

በፍራቻ የተዋጡ የመንግስት ሰራተኞች = የፍትህ ያለህ ….
ጥቅማ ጥቅምን ሽፋን አድርጎ የመንግስት እና የፓርቲ ስራ ደባልቆ መስራት ከባድ አደጋ አለው::

መርዛማዊ ሃይል ያዘለ የፖለቲካ መስፋፋት የመንግስት ሰራተኛውን የመስራት እንዲሁም የመኖር ህልውና አደጋ ውስጥ ከቶታል::
ምንሊክ ሳልሳዊ :- በኢያንዳንዱ የመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ ሁሉንም ፖለቲካኛ የማድረግ እና ለፖለቲካ ፍጆታው ለመጠቀም የሚፈልገው ሕወሓት መራሹ መንግስት ህገመንግስታዊ የዜጎችን የመስራት/ሰርቶ የመኖር መብት እየደፈጠጠ ነው:: በኢትዮጵያ ውስጥ አብዛኛው የከተማው ነዋሪ በመንግስት ስራ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል:; ይህ ዜጋ በተለያዩ አስተሳሰቦች እና እምነቶች የራሱ በሆነ ሂደት ውስጥ የሚጓዝ መሆኑ የማይካድ ሃቅ ነው::በተለያዩ ጊዜያት የተፈራረቁ መንግስታት ኢላማ የሆነው የመንግስት ሰራተኛው ዛሬም የፍትህ ያለህ የነጻነት ያለህ በማለት ላይ ነው::

በየትኛውም የአለም ክፍል ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ የሚያገለግለው ለቀጠረው ህዝባዊ አካል ሲሆን በመንግስት ሰራተኛው መሃል የተላያዩ የፖለቲካ አስተሳሰቦች ድጋፎች እና ተቃውሞዎች የመኖራቸውን ያህል ለፖለቲካ ግድ እስከሌለው ጀምሮ ፖለቲካ መስማት እስከማይፈልጉ እና ስራቸው ላይ ብቻ ማተኮር የሚፈልጉም ዜጎች አሉ :: ይህ ደሞ ህገመንግስታዊ መብታቸው እስከሆነ ድረስ ሊከበርላቸው ይገባል::

በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው መርዛማዊ ሃይል ያዘለ የፖለቲካ መስፋፋት የመንግስት ሰራተኛውን የመስራት እንዲሁም የመኖር ህልውና አደጋ ውስጥ ከቶታል::ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆኑ አለም አቀፍ የሰብኣዊ መብት ድርጅቶችም ይህንን በመንግስት ሰራተኞች ላይ የሚፈጸመውን በመስራት/በመኖር ላይ ያነጣጠረ ደባ አሳሳቢነት በይፋ ገልጸዋል::ከመንግስታዊ ጥቅማ ጥቅምም እንዲታገዱ እየተደረገ እንደሆነም ጩኸታችንን አሰምተናል::መንግስት ስንል ህዝብ ማለታችን መሆኑን ይገንዘቡልን..መንግስት የሚለው ቃል ወያኔን አይወክልም::

ወያኔ በህዝቦች ላይ የሚያራምደው አደገኛ የአገዛዝ ስልት የሚመለከቱ አብዛኛዎች የፓርቲው አባላት እና ካድሬዎች የትግል ቁርጠኝነታቸው ከመላሸቁም ሌላ ከፓርቲ ስራዎች ይልቅ በጥቅማዊ ጉዳዮች ላይ ማተኮራቸው ያሳሰበው ወያኔ አንድ ለአምስት በሚባል አደረጃጀት የፓርቲውን ስራ ከመንግስት ስራ ጋር ጎን ለጎን ለመተግበር ደፋ ቀና በማለት የዜጎችን ህልውና አደጋ ውስጥ ጥሎታል::የወያኔን ድርጅታዊ ስራ ከመንግስት ስራዎች ጋር ቀይጦ ለመተግበር መሞከር አደጋው ወደማይወጡበት አዘቅት ሊከት እንደሚችል መታወቅ አለበት ::

ወያኔ የስልጣን ጊዜውን ለማስረዘም ብቻ በሚያደርገው መፍጨርጨር በህዝብ እና በሃገር ላይ ሊመጡ የሚችሉትን አደገኛ እንቅፋቶች ከግንዛቤ አለማስገባቱ በላይ ማንጫውን ዜጋ ህዝብን በሚያገለግልበት የመንግስት ስራዎች ላይ መፈጸም የሚገባውን እንዳይፈጽም እና በድርጅታዊ ስራ ስፋን ለቢሮክራሲ ለሙስና ለህዝቦች እንባ በር መክፈት መሆኑን ልብ አለማለቱ የወያኔ ዝቅጠት ገሃድ አድርጎታል::
በልማት ስም እየተፈጸሙ ያሉት ደባዎች እና ሴራዎች አልበቃ ብሎት በኢኮኖሚ ድቀት እየተንገፈገፍ ያለን ህዝብ በድርጅታዊ ስራ ለመወጠር ማሰብ የፈነዳ እለት የሚያስከትለውን ችግር ማንም ሊወጣው እንደማይችል ለማረጋገጥ እንወዳለን ስለዚህ በመንግስት ሰራተኞች ዙሪያ እየተካሄደ ያለው እሽክርክሪት ሊታሰብበት ይገባል::

የ ኒዎርክ ታይምስ ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር) የዛሬ 96 አመት ስለ ዳግማዊ ምንሊክ የፃፈው ፅሁፍ ለአሁኑ ትውልድ ታሪካዊ ማስረጃ ነው
KING MENELIK HAS INVESTMENTS HERE; Abyssinia’s Ruler Said to be a Heavy Buyer of American… ታች ያለውን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ።

ኢትዮጵያ በየዘመኗ በሕልውናዋ ላይ የተቃጣባት የመበታተን አደጋን ያለፈችበት መንገድ የጦርነት መንገድ ብቻ አይደለም።ሆኖም ግን ከነበሩን የግጭት ታሪኮች በዘለለ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩ እና በሕዝብ ዘንድም የተወደዱ መሪዎች ነበሩን።ከእነኝህ ውስጥ ዳግማዊ ምንሊክ አንዱ ነበሩ። አፄ ምንሊክ ሀገር የማስተዳደር ጥበብን የተማሩት በአፄ ቴዎድሮስ እጅ ሆነው እድገታቸውን በንጉሡ ቤተመንግስት ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።ንጉሡ የቀደሙ አባቶቻቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ዮሐንስ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ አላማቸው እውን እንዲሆን ያደረጉ እድለኛ ንጉስም ናቸው።

አፄ ምንሊክ ኢትዮጵያን አንድ ከማድረግ አልፈው እስከ ኬንያ፣ሱዳን እና ሱማልያ ግዛት ድረስ ዘልቀው ገብተው በቅኝ ግዛት ይማቅቁ የነበሩ ህዝቦችን ነፃ ያወጣሉ የሚል ስጋት የነበረባቸው እና በወቅቱ በእነኚሁ የጎረቤት ሃገራት ላይ የጥቅም ፍላጎት የነበራቸው የአውሮፓ ሃገራት በብርቱ ተፈታትነዋቸው ነበር።በመሆኑም አዲስ የድንበር ውል ከኢትዮጵያ ጋር የመፈራረም ፍላጎት ከእንግሊዝ፣ፈረንሳይ እና ኢጣልያ በኩል ጥያቄ መነጻቱን የወቅቱ የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ።

ዛሬ ዛሬ በምንሊክ ላይ ታሪካዊ መሰረት የሌላቸው ቀድሞ አፄ ምንሊክ የቅኝ ግዛት ጥማታቸውን በገቱባቸው እና ቂም በያዙ ፀሐፊዎች የተፃፉ ናቸው ብለው ከሚነግሩን አስገራሚ ”የታሪክ” ፅሁፎች ውስጥ ”በምኒሊክ ዘመን እስከ አስር ሚልዮን ኦሮሞዎች አለቁ” የሚል ፅሁፍ በአንዳንድ የማህበራዊ ድህረ ገፆች ተለቀው ሲነበቡ መመልከት አስገራሚ የሰሞኑ ክስተት ነው።በፖለቲካው አለም በቂ ርዕዮተ አለምም ሆነ ፖለቲካዊ ፍልስፍና የጠፋባቸው አንዳንድ ወገኖች ”ትርፋማ” ብለው ያሰቡት የዘር ፖለቲካ በኢትዮጵያውያን መካከል መዝራት እና ከመቶ አመት በፊት የሆነውን የታሪክ ክስተት የአሁኑን ትውልድ በመውቀስ ትኩረት ለማግኘት ሲታትሩ መመልከት የዘመኑ አስቂኝ ተውኔት ነው።ዳግማዊ ምንሊክ ገና ብዙ የሚጠና ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ወታደራዊ ክህሎት ባለቤት ለመሆናቸው በወቅቱ ከወጡት የዓለማችን ድንቅ ጋዜጦች አንዱ የ ኒውዮርክ ታይምስን እትም መመልከት ይበቃል።

ከእዚህ በታች በሚገኘው የኒውዮርክ ታይምስ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሕዝብ ብዛትን 7,000,000 (ሰባት ሚልዮን) መሆኑን ያስቀምጣል። እዚህ ላይ አንዳንድ እራሳቸውን የታሪክ ምሁራን ነን በሚል ባልተጨበጠ ይልቁንም በምኒሊክ የቅኝ ግዛት ህልማቸው ከተደናቀፈባቸው ቂመኛ ፀሐፊዎች አነበብን የሚሉት እና የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ያማለሉ መስሏቸው ”ምንሊክ 10 ሚልዮን ኦሮሞ ገደሉ” እያሉ ኢትዮጵያ ከነበራት የህዝብ ብዛት (7 ሚልዮን) በላይ ቁጥር ሲጠሩ እፍረት አልተሰማቸውም።

”ማን ያውራ የነበረ” እንዲሉ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ ጋዜጣው አዲስ አበባ በነበረ በልዩ ዘጋቢው አማካይነት ስለንጉሡ እና ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታ ፅፎ ነበር።ጋዜጣው አፄ ምንሊክ እና አስተዳደራቸውን ከገለፀበት አረፍተ ነገር ውስጥ እነኝህ ይጠቀሳሉ –

– ኢትዮጵያን ወደ ህገመንግስታዊ የንጉሥ አስተዳደር ለመቀየር ሂደት ላይ መሆኗን፣

– የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 7 ሚልዮን መሆኑን፣

– አፄ ምንሊክ ንጉሰ ነገስት ሲሆኑ ጦርነት የነበረው የአፄ ዮሐንስ ተተኪ እሳቸው መሆናቸውን ካልተቀበሉት ጋር ብቻ እንደ ነበር፣

– የአውሮፓውያንን ስልጣኔ ወደሀገራቸው ለማምጣት የባርያ ንግድን ከመዋጋታቸውም በላይ ነፃ ትምህርት ዕድል ዜጎች እንዲያገኙ መሰረት መጣላቸውን፣

– ምንሊክ እራሱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ሰው መሆናቸውን። ከችሎታዎቻቸው መካከል ዲፕሎማት፣የፋይናንስ ባለሙያ እና ወታደር የሚሉት እንደሚጠቀሱ እና

– እንደ ዲፕሎማት እና ወታደር የጣልያንን ወረራ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ያደረጉበት ጥበብ መሆኑን፣

የሚሉ ይገኙበታል።የጋዜጣውን ሙሉ ፅሁፍ ከእዚህ በታች ያለውን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ።
የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይክፈቱ።

http://query.nytimes.com/mem/archive-fr … 5B898CF1D3

ከሩሲያውያኑ ቦልሼቪክና ሜንሼቪክ አንስቶ፣ የእኛዎቹ ኢህአፓና መኢሶን በፊት-አውራሪነት እስከ ተሳተፉበት ድረስ ያሉ በደም የጨቀዩ አብዮቶች በሙሉ በከተሞች የተካሄዱ ሲሆን፣ አብዛኛው አጋፋሪዎቻቸው
ደግሞ ልሂቃኖች እንደነበሩ በጉዳዩ ዙሪያ የተፃፉ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡ ይሁንና እነዚህ አብዮቶች (የተሳኩትም ሆነ የከሸፉት) ሰላማዊውንና ህጋዊውን መንገድ የተከተሉ ባለመሆናቸው ዛሬም ይዘገንናሉ፤ ለወደፊቱም ባልተደገሙ ያሰኛሉ፡፡ ስለምን ቢሉ? ግድግዳው ላይ የተቸከቸከው ፅሁፍ እንዲህ የሚል ምላሽ ያስነብባልና፡- በጭቁን ሕዝብ ስም የብዙሀኑን ቤት አፍርሰዋል፤ ሀገርና ታሪክ ለመቀየር የማይሳናቸው አፍላ ወጣቶችን እርስ በእርስ አጫርሰዋል፤ ‹አንቱ› ሊባሉ የሚችሉ ምሁራንን በአንድ ጀንበር ወደ ትንታግ ነፍሰ-ገዳይነት ቀይረዋል፤ ክስረቱም ከትውልድ ትውልድ የሚተላለፍ ጠባሳ ሆኖ ዛሬ ላይ ደርሷል…

በርግጥም ያ ወቅት መደማመጥ፣ መነጋገር፣ መወያየት፣ መቻቻልን… የመሳሰሉ ምክንያታዊ እሴቶች ህቡዕ ገብተው፤ መጯጯኽ፣ መነቋቆር፣ መፈራረጅ፣ መገዳደል… የገነኑበት ነበር፤ ለዚህም ይመስለኛል ሀገር ሊረከብ የተዘጋጀ አንድ ትውልድ፣ በተኮረጀ ርዕዮተ-ዓለም፣ ባልጠራ ፕሮግራም እቅሉን ስቶ ‹ማርክስ እንደፃፈው›፣ ‹ሌኒን እንዳብራራው›፣ ‹ማኦ እንዳስተማረው›፣ ‹ሆጃ እንደመከረው›… በሚል ጥራዝ ነጠቅ ዕውቀት ስቶ-በማሳት፣ ሀገር ምድሩን የጦር አውድማ አድርጎ ማለፉ የትላንት የቁጭት ትዝታ የሆነብን፡፡ በአናቱም ዛሬ ‹‹ነፃ አወጣናችሁ›› እያሉ ጃሎታ የሚመቱት የኢህአዴግ መሪዎች ከዚሁ ምንጭ የተቀዱ፣ ግና በቃላት ስንጠቃና በጎሳ ጠባብ አስተሳሰብ የተለዩ የትውልዱና የመንፈሱ ተጋሪ በመሆናቸው፣ የሁነቱ ‹ታሪክ›ነት ለተሰዉት እንጂ፣ ለእነርሱ ‹ሀገር እየመራንበት ነው› የሚሉበት ‹ፖለቲካ› ነውና፣ የነገይቷ የምንወዳት ኢትዮጵያችን መፃኢ ዕድል ገና ከእርስ በእርስ ግጭት ስጋት አለመላቀቁን ያመላክታል፡፡ በዚህ ፅሁፍም የምንዘመርለት የ‹አትነሳም ወይ?› ድምፅ አደገኛውን ስርዓት የመቀየሪያው ጊዜ አሁን በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ግን እነኢህአፓ ተቸንፈው የተሰናበቱበትም ሆነ ኢህአዴግ ድል አድርጎ የመጣበት መንገድ ለዘመኑ መልካም ተሞክሮ ሊሆን ይችላል እንደማለት አይደለም፤ ምክንያቱም በእኔ እምነት የእነርሱ ‹ፋኖተሰማራ…› ጊዜው በበየነበት ሙዚየምና የታሪክ ትምህርት ክፍል ውስጥ ብቻ ካልተገደበ ጉዳቱ በቀላሉ የሚጠገን ካለመሆኑም ባለፈ፣ የምንመኘውን ለውጥ ሊያመጣ አይችልምና ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ለትውልዱ ክቡድ ጥያቄ ስኬታማነት መንገድ መሪ አብርሆት መሆን የሚችሉ የደም ግብር ያልጠየቁ፣ ፍፁም ሰላማዊና ህጋዊ በሆነ መንገድ በከተሞች ተካሂደው ሀገርና ህዝብ ያለ ብዙ ኪሳራ በአሸናፊነት የወጡባቸው በርካታ አብነታዊ አብዮቶች (እንደ አረቡ ፀደይም ሆነ እንደ አውሮፓውያኑ ጆርጂያና ዩክሬን ብርቱካናማ-አብዮቶች) መኖራቸው እውነት ነው፤ እንዲሁም በእነርሱ መንፈስ መቀደስ፣ በእነርሱ ፀበል መጠመቅ የአምባገነኑንና የበደለኛውን ሥርዓት እድሜ ለማሳጠር የሚያበረታ ኃይል ማስረፁ እውነት ነው፡፡

ከተማን እንደ ጠላት

የ‹ያ ትውልድ› የጠብ-መንጃ ትንቅንቅን በድል የተሻገረው ኢህአዴግ (ከልቡ አምኖበት ባይሆንም) ይህንን ሁሉ መስዋዕትነት የከፈለው በተለይም ለአርሶ አደሩ ጥቅም መሆኑን በአገኘው አጋጣሚ ሳይናገር አያልፍም፡፡ በግልባጩ ደግሞ የከተማ ነዋሪዎችን ‹ጠላት› አድርጎ በመፈረጅ ሲገነግን ተደጋግሞ ተስተውሏል፤ በርግጥ የዚህ መግፍኤ በብሔር እና በሀይማኖት የከፋፈለውን ሕዝብ፣ በመደብም ለያይቶ የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያ ለማድረግ እና በየአምስት ዓመቱ በሚያካሄደው የይስሙላ ‹ምርጫ› ኮረጆ ገልብጦ ሲያበቃ የፈረደበት ምስኪን አርሶ አደር ‹መርጦኛል› ለሚለው የተለመደ ሰበቡ ‹ይጠቅመኛል› በሚል ለማመቻቸት ‹አዛኝ ቅቤ…› ተቆርቋሪ በመሆኑ ይመስለኛል፡፡ ይህም ሆኖ ድርጅቱ ይህንን የማጭበርበሪያ ስልት በደደቢት በረሃ ራሱ የቀመረው ነው ብሎ ለመከራከር የሚያስችል ገፊ ጭብጥ ይኖራል ብዬ አላስብም፤ ምክንያቱም በአንዳንድ የዓለማችን ሀገራት የፖለቲካውን ኃይል ከጨበጡ በኋላ በሕዝባቸው ላይ ነጋሪት ጎስመው ሞትን ከነዙ፣ ስቃይን ከረጩ እርኩሳን መሪዎች (ፓርቲዎች) ድርሳናት ቃል-በቃል የተገለበጠ መሆኑን የሚያስረግጡ (በስነ-አመክንዮ) የተቀኙ ማሳያዎች ማቅረብ ይቻላልና፤ እንደምሳሌም አንዱን በአዲስ መስመር እንምዘዘው፡-

የ‹ኬመር ሩዥ› መንገድ

በተለምዶ ‹ኬመር ሩዥ› (Khmer Rouge) በመባል የሚታወቀውና አክራሪ ኮምኒስታዊ የገበሬዎች ድርጅት እንደሆነ የሚነገርለት ‹‹Communist Party of Kampuchea /CPK/›› እ.ኤ.አ ከ1975-1979 ዓ.ም ድረስ፣ በወጣት የገበሬ ሠራዊት ታግዞ በካምቦዲያ መንግስታዊ ሥልጣን ተቆናጥጦ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ ጨካኝና አፍቃሪ ቻይና የሆነው የፓርቲው ሊቀ-መንበር ፖል ፖትም (Pol Pot)፣ ማኦ ዜዱንግ ‹‹የሀገሬን ኢኮኖሚ ያሳድግልኛል›› በማለት ያረቀቀውንና በግብርና ላይ የሚያተኩረውን ‹‹Great Leap Forward›› ፕሮግራም፣ ‹‹Super Great Leap Forward›› በሚል ተቀጥላ እንደወረደ በመኮረጅ ‹‹ሙሉ የካምቦዲያን ሕዝብ ወደ ‹እርሻ መር-ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ› (Agrarian Society) እቀይራለሁ›› ብሎ ያደረገው ሙከራ ወጪ-ኪሳራን ያወራረደው ሁለት ሚሊዮን ዜጎቹንለህልፈት በመዳረግ እንደ ነበር የታሪክ መፃህፍት ያትታሉ፡፡

ከሁሉም የከፋው ግን ፖል ፖትና ጓዶቹ ‹‹እውነተኛ ዜጋ ገበሬ ብቻ ነው›› በማለት የከተማ ነዋሪዎችን በጠላትነት ከፈረጁ በኋላ ‹‹ማህበረሰባችንን ለማንፃት›› በሚል የቁም-ቅዠት ምዕራባዊ አስተሳሰብ የተንፀባረቀበትን ማንኛውንም ጉዳይ፣ የከተማ ሕይወትን፣ ኃይማኖትን፣ ትምህርትን፣ አንድ ብርም ቢሆን በግል መያዝን… በአዋጅ ማገዳቸው ነበር፤ እንዲሁም ኢምባሴዎችን፣ ጋዜጣና ቴሌቪዥን ጣቢያን ዘግተዋል፤ በሁሉም የሀገሪቱ ከተሞች የሚኖሩ ዜጎችን በማፈናቀል ወደ ገጠር አግዘው፣ በግዳጅ የእርሻ ሥራ ላይ አሰማርተዋል፤ ከዋና ከተማዋ ‹ፈኖሞ ፔንህ› (Phnom Penh) ብቻ ሁለት ሚሊዮን ዜጎች ወደገጠር በእግር እንዲጓዙ በመገደዳቸው ሃያ ሺህ የሚሆኑት በጉዞ ላይ ወድቀው እንደወጡ ቀርተዋል፤ ገጠር የደረሱትንም ቢሆን ‹የግድያ ወረዳዎች› እያሉ በሚጠሯቸው የእርሻ ሥራ ላይ አሰማርተው ለአንድ ሰው በነፍስ ወከፍ በየሁለት ቀኑ አንዴ 180 ግራም ሩዝ ብቻ በመስጠት በረሀብ፣ በበሽታ፣ ብስቅየት እና በግድያ እንዲያልቁ አድርጓል፡፡ በመጨረሻም አገዛዙ በቬትናም ጣልቃ ገብነት እ.ኤ.አ በ1979 ዓ.ም በኃይል በመወገዱ፣ ፖል ፖት ከእነተከታዮቹ ሀገሩ ከታይላንድ ወደምትዋሰንበት ጠረፍ አካባቢ በመሸሽ፣ የትጥቅ ትግል እንደአዲስ ጀምሮ ለረዥም ዓመታት ከታገለ በኋላ፣ እ.ኤ.አ በ1997 ዓ.ም እርጅና ተጭኖት በህግ ቁጥጥር ስር በዋለ፣ በዓመቱ ከልብ ጋር በተያያዘ ህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉ ይታወቃል (በነገራችን ላይ ይህ ድርጅት የሽምቅ ውጊያ ከመጀመሩ በፊትም ሆነ በኋላ የተጠናከረበትን ምስጢራዊ መንገድ ጨምሮ የተከተለው ስልት ከሞላ ጎደል ከኢህአፓና ህወሓት አፈጣጠር ትርክት ጋር ተመሳሳይነት አለው)

ኢህአዴግ እንደ ‹ኬመር ሩዥ›

ከሁለት አስርተ ዓመታት የሥልጣን ቆይታም በኋላ፣ የከተማ ነዋሪዎችን በጠላትነት ካሰፈረበት ጥቁር መዝገቡ ላይ መሰረዙ ያልሆነለት ኢህአዴግ ‹እንደ ኬመር ሩዥ ሁሉንም የጭካኔ ተግባራት በአደባባይ ፈፅሟል› ተብሎ ባይወነጀልም፣ ተመሳሳይ ስልቶችን በመኮረጅ በረቀቀ መንገድ አለዝቦ መተግበሩን ግን መካድ አይቻልም፡፡ እንዲሁም የሁለቱ ድርጅቶች ዋነኛ ልዩነት ወደ እንዲህ አይነቱ የጥላቻ ጠርዝ
የተገፉበት ምክንያት ይመስለኛል፤ ይኸውም ፈላጭ ቆራጩ ፖል ፖት በከተሜው ላይ የከፋ ቂም የቋጠረበት መነሾ፣ ከገበሬ ቤተሰብ መገኘቱን ጨምሮ፣ ከአስተዳደጉ ጋር በሚያያዙ ‹ህመማቸው-ህመሜ› በሚል ሲባጎ የተቋጠረ ሲሆን፣ መለስና ጓዶቹ ደግሞ የሥልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም በማስላት ብቻ መሆኑ ነው፤ መቼም መሬት የረገጠውን እውነታ ተመልክቶ የሀገሬ አርሶ አደር ከፕሮፓጋንዳ ፍጆታ በዘለለ፣ ከከተሜው የተለየ የመልካም አስተዳደርም ሆነ የመሰረተ-ልማት ተጠቃሚ አለመሆኑን መረዳቱ አዳጋች አይደለም፡፡ የሆነው ሆኖ የኢህአዴግ ‹ፀረ-ከተሜነት› እንዲህ በግላጭ አፍጥጦ የወጣው ከምርጫ 97 በኋላ ነው፤ በወቅቱ ጠቅላይ ሚንስትሩ በቴሌቪዥን መስኮት ቀርቦ፣ ድርጅቱ በከተሞች መሸነፉን ከገለፀ በኋላ፣ በገጠር ሙሉ በሙሉ ስለተሳካለት መንግስት ለመመስረት የሚያስችል የመራጭ ድምፅ ማግኘቱን አውጇል፤ ይህንንም ተከትሎ ግንባሩን ያልመረጡ የከተማ ነዋሪዎች በተቀነባበረ ሴራ የጥቃት ዒላማ መሆናቸውን የሚያመላክቱ በርካታ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡ በተለይም በድህረ-ምርጫው ከተሜውን ዒላማ ያደረጉ በስራ ላይ የዋሉ አፋኝ ህጎች እና ፖሊሲዎችን ጨምሮ በደባ የተፈፀሙ መንግስታዊ ጥፋቶችን ዘርዘር አድርገን እንያቸው፡፡

መሬትን በተመለከተ የወጣውን የሊዝ አዋጅ በቀዳሚ ምሳሌነት እናንሳው፤ ፓርቲው በ1987 ዓ.ም ባፀደቀው ህገ-መንግስት የመሬት ፖሊሲውን አንዱ ዕማድ አድርጎ በማካተቱ፣ የመንግስት ጭሰኝነትን (Tenants of the state) በገጠሩ ክፍል ሲያሰፍን፣ የመሬት ከፊል ባለቤትነትን ደግሞ ለከተሞች እንዲፈቅድ አድርጎት ነበር፡፡ እናም የግል ይዞታን መሸጥ (መንግስት ለሚፈልጋቸው ‹‹ልማቶች››ም ሆነ
በሊዝ ለመቸብቸብ ዜጎችን የማፈናቀል መብት ከማግኘቱ ውጪ) እስከ 97ቱ ድህረ-ምርጫ ድረስ ተፈቅዶ የዘለቀበት ሂደት፣ በዚህ የሊዝ አዋጅ በመሻሩ የተነሳ፣ ነዋሪው መሬት በመሸጥ ሊያገኝ ይችል የነበረው ገቢ ተጨምቆ ወደ መንግስት ካዝና እንዲሻገር ሆኗል፡፡ የዚህን አዋጅ ‹ፖለቲካዊ ንባብ› ውስጥ የምናገኘው ጭብጥ፣ በከፊልም ቢሆን መሬት ላይ የቆመውን የሀብት መሰረት በመናድ፣ የተቃውሞ ኃይሉ የድጋፍ መዕከል እንደሆነ ያመነውን የማህበረሰብ ክፍል ክፉኛ ማድቀቁን ስንረዳ ነው፡፡ አዋጁን እንለጥጠው ካልን ደግሞ ግንባሩ በገጠሩ ያነበረውን የዜጎች የመንግስት ጭሰኝነት በጠመዝማዛ መንገድ፣ በተለይም በአዲስ አበባ የመፈጸም ዕቅዱ አድርገን ልንወስደው እንችላለን፡፡

የኢህአዴግ ከተማንና ከተሜዎችን የመፍራት አባዜ ከጫካ ትግሉ ጋርም በረዥሙ የሚተሳሰር ነው፡፡ በወቅቱ በጥላቻ ከመተያየት አልፎ ደም የተቃባቸው ኢህአፓን መሰል ኃይሎች መሰረታቸው ከተሞች ላይ እንደነበረ ይታወቃል፤ በአናቱም በትግሉ መጠናቀቂያ ዋዜማ እና ማግስት ሊገዛለት ያልቻለው (ማማለሉ ያልተሳካለት) ልብ በተለይ የአዲስ አበቤዎችን ነበር፤ በ1980ዎቹ መጀመሪያም ፓርቲው አንገት ላይ ታንቆ ሊደፋው የነበረው ዋነኛ ጉዳይ፣ ብሔር ተኮር ስርዓቱ ህገ-መንግስታዊ ድጋፍ ሲያገኝና የብሄር ፖለቲካ ብቸኛው የድጋፍም የተቃውሞም ተዋስኦ እንዲሆን መደረጉ ነበር፡፡ ይህንንም ተከትሎ በኢትዮጵያዊብሔርተኝነት መንፈስ ከተገራው የአዲስ አበቤ ብሔር ዘለል ማንነት ጋር እንዲህ በፊት ለፊት መጋጨቱ፣ ከተማይቱን በወረራ የያዛት እስኪመስል ድረስ በጥላቻ እንዲዘምቱበት አነሳስቷል፡፡

ሁለተኛው ምዕራፍ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትን ተከትሎ የመጣው የአሰብ ወደብን ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እንዲካለል የመፈለግ የከተሜዎቹ ግፊት ነው፡፡ ጦርነቱ ሲያበቃና የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ኋላ እንዲያፈገፍጉ ሲገደዱ የነዋሪው ቁጣ ብርቱ እንደነበር እናስታውሳለን፡፡ ይህ እውነትም ሌላኛው ፓርቲውን ቂም ያስቋጠረ ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡ በድህረ-ምርጫ 97 የፀደቀውና አፋኝነቱ በተግባር የተረጋገጠው የሲቪል ማህበረሰቡን የሚመለከተው አዋጅም ‹የብዙዎች ተቋማት ዋናመቀመጫ አዲስ አበባ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የወጣ ነው› በማለት ከየአቅጣጫው ይነሳ የነበረውን የተቃውሞ ውግዘት አጣጥሎ፣ በሥራላይ ባዋለበት ዓመት በርካታ ተቋማትን ከማፈራረሱ አኳያ፣ መጀመሪያውንም ለእንዲህ አይነቱ ክፉ እርምጃ ታስቦ የተዘጋጀ ነው ወደሚል ጥርዝ ይገፋል፡፡ በተጨማሪም ያለፉትን ሃያ ሁለት ዓመታት ሙሉ በአይኑ መዓት የሚያያቸው ምሁራን፣ የነፃው ፕሬስ አባላት እና በየዘመኑ ከባድ ተግዳሮት የፈጠሩበት የተቃውሞ ስብስቦች ጠንካራ መሰረት በከተማይቱ ውስጥ መሆኑ ጥላቻ እና የጭካኔ እርምጃዎቹን አብዝቶታል፡፡

ሌላው አገዛዙ በከተሜዎች (በሸማቾች) ላይ ያለውን ስር የሰደደ ጥላቻ የሚያሳዩት፡- ከምርጫው በኋላ ጤናማ ያልሆነ የዋጋ ንረት በከፋ ደረጃ ማሻቀቡ፣ ፍትሃዊ ያልሆኑ የተለያዩ የግብር ህጎች በእንጀራ እና ሽንኩርት ቸርቻሪዎች ላይ ሳይቀር መተግበራቸው ነው፡፡ በተለይም ካለፉት ስምንት ዓመታት ወዲህ የተከሰተው ከፍተኛ የዋጋ ንረት ዋነኛ አባባሽ ኃይል የምግብ ዋጋ መናር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በዚህ
የምግብ ዋጋ መናር በዋነኝነት ቋሚ ደሞዝ ተከፋዩ የከተማ ነዋሪው ተጎጂ መሆኑን የስርዓቱ ባለስልጣናትም ይቀበላሉ፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ከሁለት ወራት በፊት በ‹‹አዲስ ዘመን›› መፅሄት የተጠየቀው የፋይናስና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ ‹‹በ2006 ዓ.ም የሚጨመር ደሞዝ አይኖርም›› ከማለቱ ባለፈ ‹‹ነገ ይችን አገር ወደተሻለ የሚያደርስ በጎ መስዋዕትነት ነው›› ሲል በከተሜው መከራ ላይ አላግጧል፡፡ በርግጥ ይህ ሁሉ መዓት ከመውረዱ በፊት በ1998 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ራሱ አቶ መለስ በደቡብ ክልል ወደምትገኘው ይርጋለም ከተማ ድረስ ሄዶ የሙዝ አምራች አርሶ አደሮችን ሰብስቦ ካነጋገረ በኋላ፣ እንዲህ ለፍተው የሚያገኙትን ምርት ለከተሜው በርካሽ መሸጣቸው አግባብ አለመሆኑን ቀስቅሶ ዋጋውን በአራት እጥፍ እንዲጨምሩ በማድረጉ የተፈጠረው የገበያ እጥረት፣ ምንም እንኳ መልሶ አምራቾቹን ሰለባ ቢያደርግም፣ ኩነቱ የጠቅላይ ሚንስትሩን ቀጣይ ዕቅድ የሚያመላከት ነበር፡፡

በከተሞች ውስጥ እየተደረገ ያለው ‹‹የሰፈራ ፕሮግራም››ም (Urban Resettlement) አንዱ ሊነሳ የሚገባው ነጥብ ነው፡፡ በእርግጥ በዚህ ዕቅድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የተሻለ የመኖሪያ ቤቶች ተጠቃሚ እንደሆኑ ማየት እንችል ይሆናል፡፡ ጥያቄው የሚነሳው ግን፣ የአንድ አካባቢ ነዋሪዎችን ከሌሎች የፈረሱ የከተማዎቹ ክፍሎች ከሚመጡት ጋር በአንድ አዳብሎ በኮንዶሙኒየም ቤቶች አጥሮ የማስቀመጡ አንደምታ ላይ ነው፡፡ የዚህ ዕቅድ ክፉ ገፅ የሚገባን በረዥም የአብሮነት መስተጋብር (ሶስት መንግስታትን መሻገር የቻለ የአንድ አካባቢ ነዋሪነት) የተገነባው የጋርዮሽ ፖለቲካው አረዳድ እና የእርስ በእርስ ፍፁም መተማመን፣ 97ን ጨምሮ በተለያዩ ወቅቶች በተነሱ ተቃውሞዎች ወጥ ምላሽ እንዲሰጡ ማደፋፈሩን (አራት ኪሎን የመሳሰሉ አካባቢዎች) አስታውሰን፣ በመልሶ ማስፈሩ ደግሞ የአንዱን አካባቢ ነዋሪ በታትኖ ወደተለያዩ ሳይቶች መውሰዱን ስንመለከት ነው፤ ይህ መራራ እውነታም የገዥዎቻችን ጥላቻ ስር የሰደደ መሆኑን እና የአምባገነናዊ ስርዓቱን ዕድሜ ለማራዘም ያለመ እንደሆነ ይጠቁመናል፡፡

(ስርዓቱ በከተሜዎች ላይ የሰረፀበትን ጥልቅ የጥላቻ ፅንፍ እንዲህ ከተመለከትን፣ የከተማ አብዮት፣ ማኦኢዝም ከሚያዘው ከገጠር ከሚነሳው ብረታዊ ትግል ጋር ያለውን ልዩነት፣ በአረቡ ፀደይ ተሞክሮ በመንተራስ መፈተሹን፤ እንዲሁም የኢህአዴግ ግድፈቶች (Achilles’ heel) የከተማ አብዮትን ለማስነሳት ያላቸውን አስተዋፅኦ፣ በአደባባይ ሊያሰባስቡ የሚችሉ ጥያቄዎች ምን ቢሆኑ የተሻለ ነባራዊውን እውነት ያንፀባርቃሉ… የሚሉትን ጉዳዮች እና መንገዱን ስለሚመሩ የሚችሉትን መልከአ-ቡድኖች ማንነት ሳምንት እመለስበታለሁ)

ኢትዮሚድያ – Ethiomedia.com

ፖለቲካ ጨለማን ተገን አድርጋ ወንጌል ስትሆን !
(አሌክስ አብረሃም )

ወገኖቸ እሰብካችኋለሁ !! በደሌ ቢራ አትጠጡ እንደተባለ ሰምታችኋል…… እኔ ግን እላችኋለሁ ባጠቃላይ አልኮል መጠጥ አትጠጡ ! ለጤና ጠንቅ ነውና !! መጠሃፉ ‹‹ደሃ ድህነቱን እንዲረሳ የወይን ጠጅ ስጠው ›› ቢልም እኛ ኢትዮጲያዊያን <አስራ አንድ> በመቶ እያደግን ያለን ሃብታም ህዝቦች ነንና እኛን አይመለከትም !

አዎ ! መጠጥ አገር እያጠፋ ነው ትዳር እየበጠበጠ ነው ይሄ ሁሉ ያማረበት ጠጭ ብርጭቆውን በቄንጥ ይዞ ውሰኪውን የሚከነብል ይሄን ሆንኩ ሳይል ወጋኝ ፈለጠኝ ሳይል ድንገት የሚከነበለው ለምን ይመስላችኋል ……መጠጥ …..መጠጥ ነው ወገኖቸ !! ህዝቤ ቁሞ ይንከላወሳል እንጅ ጉበቱ እኮ የለም …..ሳንባውኮ በጥቃርሻ ተዥጎርጉሮ የሚያፈስ ኮርኒስ መስሏል ……ነብሱ አድፏል ! ይሄ ሁሉ የሆነው በምንድን ነው በመጠጥ !! መጠጥ እንዝህላል ያደርጋል ግዴለሽ ያደርጋል ዋጋ ቢስ ያደር …. ጋል ወገኖቸ …..

.ዛሬ እኮ ምፅአት ቀርባለችና ንስሃ ግቡ ሲባል ‹ሎ…ል› የሚል ወጣት ነው እያፈራን ያለነው …. ትውልዱ በቀቢፀ ተስፋ የሚይዝ የሚጨብጠውን አጥቷል ቤተስኪያኖቻችን ርግብና ዋነስ ሰፍሮባቸው ካለሰው እየዋሉ ቡና ቤቱ በሰው ተጨናንቋል ….. ጭፈራ ቤቱ ካፍ እስከገደፉ ሞልቷል …..

ስለሳምሶን ታሪክ ሰምታችኋል (ለነገሩ መቸ መጠሃፉን ታነቡና ፌስ ቡክ ላይ አፍጥጣችሁ እየዋላችሁ ) ሳምሶን ታላቅ የህዝብ ነፃአውጭ ነውና ሲረገዝ እናቱ የአልኮል መጠጥ በአፏ እንዳይዞር እግዜር አዟት ነበር ! ለትውልድ የምታስብ ሴት እንዲያ በክብርና በቅድስና ትኖር ዘንድ መፅሃፉ ያዛል !

ዛሬ ግን ሴቶቻችን በየመሸታው አኮሌ ሙሉ መጠጥ ሲገለብጡና ሲያሽካኩ ያመሻሉ ያድራሉ የረከሰ ትውልድ ከሰካራም እናት ይወለድ ዘንድ ስምንተኛው ሽ ቀርቧል ! ወንዱ መቸስ አንዴውኑ ጠጥቸ ልሙት ብሏል ! ደግሞኮ የድሮ መጠጥ ሲያሰክር ጀግና ያደርጋል የልብን ያናግራል
‹‹በቃኝ ባርነት …በቃኝ ጭቆና ›› የሚል ሰካራም ዛሬ አይታችሁ ታውቃላችሁ ?

…..የለም ! ወንዱ ሰክሮም ፈሪ ባይሰክርም ፈሪ ነው ! ቤቱ ገብቶ ሚስቱና ቤተሰቡ ላይ ነው የሚደነፋው ! ወገኖቸ ስካር ድሮ ቀረ !! ስለዚህ አልኮል መጠጥ አትጠጡ ! እንደአሸን የሚፈላው የቢራ ፋብሪካና መጠጥ ቤት የዝሙት ቤት ድራሹ ይጥፋ ለአንድ ሽ ሰው የስራ እድል ፈጠረ የምንለው የመጠጥ ስራ ሚሊየኖችን ከሰውነት ክብር ካወረደ አትጠጡ !!

ይሄ ውስጡ ኑሮ የሚጮህበት ህዝብ ጩኸቱን በጩኸት ለማጨናበር ዲጀ ማንትስ እከሊት ጭፈራ ቤት እያለ ሲያላዝን ያመሻል የውስጥን ጩኸት በውጭ ጪኸት ለጊዜው ነው ማጥፋት የሚቻለው …..እናም እላለሁ መጠጥ አትጠጡ !! አልኮል በደረሰበት አትድረሱ ! አልፎ አልፎ ምናለበት ለምትሉ ለእናተ እላለሁ መጠጥ ሞት አለበት መርከስ አለበት !! ወገኖቸ የቴዲ አፍሮን ዘፈን አታዳምጡ እንደተባለ ሰምታችኋል ….. እኔ ግን እላችኋለሁ ባጠቃላይ ዘፈን አታዳምጡ …..መጠሃፉ ዘፋኝነት ዝሙት ሴሰኝነት ሰውን መግደል ….. እኩል ሃጢያት ናቸው ብሏልና ትውልዱን እያዘናጉ ሲያስጨፍሩትና ሲያዘልሉት የሚኖሩትን ስለምን ትከተላላችሁ …..ዘፈን የዝሙት ቀኝ እጅ ነው ! ጥበብ ነው እያሉ ሌላ ነገር እንዳታስቡ የሚያጠቧችሁ ጠላቶቻችሁ ዘፋኞች ናቸው ! ብሶታችሁን ከመናገር ይልቅ ከበሯቸውን እየደለቁ ሴት አሰልፈው ሲያደንዟችሁ የሚውሉት እነሱ አይደሉምን …. የሰው አገር ዘፋኝ ስለነፃነት ይዘፍናል ስለህዝቡ ሃቂቃውን ይናገራል ያንተ አገር ዘፋኝ በአንድ አይኑ መንግስትን በሌላ አይኑ ብር እየተመለከተ ቀልቡ ሳይሰበሰብ ያላዝናል አንተንም ቀልበ ቢስ ያደርገሃል …..እጀጅ የሚል ዘፈኑን እጅ እጅ በሚል ሬዲዮና ቴሌቪዥን ይለቅና ሲኮፈስ ሲበጠር ይኖራል ፡፡ዘ ዘፈን እኮ ልመና ሁኗል ወገኖቸ !! ባሳዛኝ ቃልና ዜማ አስተዛዝኖ ገንዘብ ይቀበላችኋል ! ልበቢስና ያልተማረ ቁራ ሁሉ ነው ዘፋኝ ነኝ እያለ የሚያደነቁርህ ! እውነት እውነት እልሃለሁ ዘፈን አታዳምጥ ምንም አይቀርብህም….. እንደውም ሰላም ነው የምትሆነው ! ዘፋኞችህ ድድብናንና መሃይምነትን ነው ለትውልድ የሚረጩት ርኩሰትና ዝሙትን ነው ለወጣቱ የሚያስተላልፉት ! ሲመቻቸው በየጠንቋይና መተታሙ ቤት እየሰገዱ መርገምትን ለትውልድ እንደሚያከፋፍሉ የቅርብ ጊዜ ትዝታህ ነው አሁንም ያው ናቸው ! ትውልዱ ሂሳብ አይወድ ሳይንስ አይወድ አይምሮውን ቤቱ አስቀምጦ ሳይቀመጥ እግሩን ይዘረጋል ….. ሁሉም ዘፋኝ ሁሉም የፊልም ባለሙያ ሁሉም ሞዴል …. በቃ ትውልድ እየከሰረልህ ነው ለዚህ ሁሉ መነሻው አርቲስቶችህ ናቸው እነዚህ አጋሰስ ዘፋኞችህ ትውልድን አንድ እርምጃ እልፍ የሚያደርግ ሃቅ አይነግሩህም ! እልሃለሁ አንተ እና እኔ ዳሽቀናል ልጆቻችን ግን ሲቀለድባቸው መኖር የለባቸውም ዘፈን በቃ የማንም ዱርየ ጫት ቤት በሚፈጥረው ተልካሻ ጩኸት አያደናቁረን ! እደግመዋለሁ ዘፋኞችህ እዚህ ግባ የሚባሉ ፍጥረቶች አይደሉም !! ለማንም አርእያ አይሆኑም ! አንዲት አገር ሰበአዊ ሃብቷ ከዳሸቀ መንገድና ህንፃ የሚቀይራት እንዳይመስልህ …..ዘፋኞችህ ግን ውብ ቪላ ቀለበት መንገድ የሻማ ራት ሳዩሃል እስቲ ድህነትህን ውድቀትህን ያሳየ ዘፋኝ ማነው ….ስራ አጥነትህን ማነው ልሳን ሁኖ የተናገረልህ….. ፍትህ ማጣትህን ማን ዘፈነው …. በሙስና አገርህ ተቦጥቡጣ እርቃኗን መቅረቷን በድፍረት የዘፈነልህ ማነው አየህ ዘፋኝህ ሳንቲም ሰብሳቢ ለማኝ እንጅ የጥበብ ሰው አይደለም ! ቴሌቪዥንህ በዜና ያሳየህን ቀለበት መንገድ ከተሜው ዘፋኝ በክሊፑ ያሳያሃል …..ቴሌቪዥንህ በዜና ያሳየህን የሚዘናፈል አዝመራ የባህል ዘፋኝህ ቁምጣውን ለብሶ እየተወላገደ በክሊፕ ያሳየሃል የተቀናጀ ድንዛዜ ይረጭብሃል ! ዘፋኝህ በዝሙት የሰከረ ሴሰኛ እንጅ የፍቅር ሃዋሪያ አይደለም በየቀኑ ኑሮህን አሰልች ያደረገው ዘፋኝህ ነው ዘፋኝ ከሃኪም ከኢንጅነርና ከጋዜጠኛና ከሌላውም ባለሙያ በላይ ብሶትህን አቤት ሊልልህ ይገባ ነበር ግን ያንተ ዘፋኝ አስመሳይ ሆዳምና ጥገኛ ስለሆነ ሳንቲሙን እንጅ አንተ አራት እግርህን ብትበላ ግድ አይሰጠውም ! እና እልሃለሁ ዘፈን አታዳምጥ !! ካላመንክ ሞክረው አንድ ወር ዘፈን የደረሰበት ባትደርስ ውስጥህ የሚገርም ሰላም ይፈሳል ! ዘመኑ ደርሷል ፌስ ቡክ ላይ እንዳፈጠጣችሁ ምፅኣት ድንገት ከተፍ ብትል ‹‹ሎል›› ብላችሁ የምትተርፉ እንዳይመስላችሁ ወገኖቸ ! አንገት የተሰራው አዙሮ ለማየት ነው ነብሳችሁን ስሙ አለበለዚያ አለም የነፍሳችሁን አንገት በሜንጫ እያበረረች አገር ምድሩን ጭንቅላት አልባ ሰው ይሞላዋል ! ልብ ያለው ልብ ይበል !! ጆሮ ያለው ይስማ

ኢትዮጵያዊኑ ከሳውዲ ፖሊስ ተጋጩ፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ይዘጋ ብለዋል
ለ3 ሠአታት በኢትዮጵያ ቆንስላ ላይ ተቃውሞአቸውን አሠምተዋል

ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ከተለያዩ የሣውዲ አካባቢዎች በመሠባሠብ መጠለያ ጣቢያ የገቡ ስደተኞች፤ የኢትዮጵያ ቆንስላ ከፍተኛ እንግልት እንዳደረሰባቸው በመግለጽ ባሰሙት ተቃውሞ ከሳውዲ ፖሊስ ጋር ተጋጩ፡፡ እጃቸውን ለፖሊስ እንደሰጡና በ10 አውቶቡሶች ተጭነው ሹማሲ ወደተሠኘው የመጠለያ ጣቢያ እንደገቡ የገለፁት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከገቡበት ቀን ጀምሮ ለአምስት ቀናት በኢትዮጵያ ቆንፅላ ዳተኝነት የጉዞ ሰነድ በጊዜ ሣይዘጋጅልን ለእንግልት ተዳርገናል ብለዋል፡፡ ያለ ጉዞ ሰነድ መንገላታታቸውን በመወቃም እሁድ እለት በመጠለያ ጣቢያው ውስጥ ለ3 ሰዓታት ያህል ብሶታቸውን እንዳሰሙ ስደተኞቹ ተናግረዋል፡፡ የሃገሪቱ ፖሊስ አመፅ አስነስተዋል ያላቸውን ስደተኞች ለመደብደብ ሌሊት ወደ ጣቢያው እንደገባ ስደተኞቹ ጠቅሰው፤ በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ የአካል ጉዳት እንደደረሠባቸውና በፖሊስ ጥይት የተመቱ እንዳሉም ገልፀዋል፡፡ ኤምባሲው ወደ ሃገር ቤት ትመለሣላችሁ ብሎ ባቀረበው ጥሪ ወደ መጠለያ ጣቢያው እንደገቡ የተናገረች አንዲት ስደተኛ ለኤምባሲው ሰራተኞች ብንደውልም ድብደደባው ካለቀ በኋላ ነው የደረሱት ብላለች፡፡

በድብደባው እንደተጎዳ የተናገረ ሌላው ስደተኛ በበኩሉ፤ የኤምባሲው ሰራተኞች ዘግይተው ከመድረሳቸውም በተጨማሪ እንደቆሠልን እያዩ፣ ወደ ህክምና ቦታ ለመውሠድም ሆነ እርዳታ ለማድረግ አልሞከሩም ሲል አማሯል፡፡ ከተቃውሞና ከግጭቱ በኋላ፤ ለሴቶችና ለህፃናት ቅድሚያ በመስጠት የመመለሻ ሰነድ ተዘጋጅቶ እየተሰጣቸው መሆኑን የተናገሩት ስደተኞች፤ በድብደባ የተጐዱትን ጨምሮ በርካታ ወንዶች አሁንም በመጠለያ ጣቢያው እየተንገላቱ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሣደር ዲና ሙፍቲን አነጋግረን በጉዳዩ ላይ በሠጡን ምላሽ፤ በወቅቱ በሚዲያዎች የተነገረውን ያህል ባይሆንም፣ “ወደ አውቶቢስ ግቡ አንገባም” የሚል ችግር ተፈጥሮ እንደነበር ጠቅሰው፤ አንዲት ሴት ከመጐዳቷ ውጪ በሌሎች ላይ የደረሠ ጉዳት እንደሌለ ሣውዲ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንፅላ ፅ/ቤት ጠይቀው መረዳታቸውን ገልፀዋል፡፡ ከ145ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸውን ያስታወሱት አምባሣደር ዲና፤ አሁንም በመደበኛ በረራዎች በአማካይ እስከ 300 ሠው እየተመለሠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል በደቡብ ሱዳን ያለውን ውዝግብ ተከትሎ በሃገሪቱ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ ጉዳት እንዳይደርስ መንግስት ከሌሎች የኢጋድ አባል አገራት ጋር በመሆን የ24 ሠአት ክትትል እያደረገ መሆኑን ቃል አቀባዩ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡
source አዲስ አድማስ

የኢህአዴግ ሽሽት

ኢህአዴግ እስካሁን ብዙ ነገር ሸሸ። ቃል ሸሸ። የሰው ስም ሸሸ። የጣት ምልክት ሸሸ። ሸሽቶ ሸሽቶ ከራሱ መሸሽ ግን አልቻለም። የዛሬን አያድርገውና 97 ላይ ኢህአዴግ ቅንጅት የምትለውን ቃል አጥብቆ ፈራት። ጠላት። ሸሻት። እናም በየትኛውም ቃላት ውስጥ ቅንጅት የምትባል አማርኛ ላለመጠቀም ማለ። ጥምረት በሚል ቃል ለወጣት። በቀደሙት ‘ቀዳሚ እመቤታችን’ የበላይነት የሚንቀሳቀሰው የሴቶች ጥምረት ሥራውን የምታስተዋውቅለት “ቅንጅት’ የሚል ርዕስ ያላት መጽሔት አሳተመ። የዋሆቹ አዘጋጆች ‘ቃሉ ሌላ ፓርቲው ሌላ’ አሉና መጽሔቱን በየዋህነት በተኑት። የመንግሥት ተሞዳሟጆች ያቺ አደገኛ ቃል በመጽሔት ስም ላይ ሊያውም በራሱ በፓርቲው አባላት መጽሔት ላይ ተንጠላጥላ ስትመጣ ጊዜ ደንብረው ኡኡ… አሉ። ከዚያም ያቺ በስያሜዋ ካልታሰበችበት ቦታ የዋለች መጽሔት ከያለችበት ተለቃቅማ ታጎረች። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ‘ቅንጅት’ የምትል መጽሔት ድራሿ ጠፋ። ስያሜዋን ለውጣ ሸሸች።
በዚሁ ጊዜ ደግሞ የአሸናፊነት (ቪክትሪ) ምልክት ሆኖ የዘለቀው የሌባና የመሃል ጣት ቪ ቅርጽ ድራሹ እንዲጠፋ ተደረገ። ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ በምርጫ ምልክትነት ይጠቀምበት ስለነበር ‘ጣቱን የሚቀስር ጣቱን ይቆረጣል’ በሚል ማስፈራሪያ የአሸናፊነት ምልክቱ ከሁለቱ ጣቶች ወደአንዱ ወደአውራ ጣት እንዲዘዋወር ተደረገ። የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በዚያን ዘመን የሚገቡበት ጠፍቷቸው የሚኮሩበትን የክለባቸውን አርማ የሸሹበት ጊዜ ነበር። ኢህአዴግ ጣት ሸሸ።
ይህ ፓርቲ ሌላም ሌላም ነገር ይሸሻል። የቴዲ አፍሮ ዘፈንንም ሸሽቶታል። ዶክተር ብርሃኑ ‘ጃ ያስተሰርያል’ የሚለውን ዘፈን እወደዋለሁ ስላሉ ይህ ዘፈን በራዲዮ እንዳይዘፈን ተከለከለ። ቴዲ አፍሮም በፖለቲከኛ ዓይን ታየ። ፓርቲው የእኔ በሆነው ነገር የእሱ ድምጽ እንዳይሰማ አለ። ኮንሰርቱ ጭምር የሚዲያ ሽፋን ተነፈገ።
ይህ ፓርቲ ማንዴላ በኢትዮጵያ ወስጥ የነበራቸው ቆይታ ያለፉትን መንግሥታት በጎ ምግባር የሚያጎላ መስሎ ስለታየው ታሪክ ሸሽቷል። ደቡብ አፍሪካ ሄደው ማንዴላ ቀብር ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንኳን የኢትዮጵያንና የማንዴላን ጥምረት በተመለከተ አንዲት መስመር እንኳን አልተናገሩም። ምክንያቱም ፓርቲያቸው ሲወቅሳቸው ለኖሩት ላለፉት መንግሥታት ስም እንደመስጠትና እውቅናቸውን እንደመጨመር አድርጎ አስቦታልና ታሪክን በተዘዋዋሪ መንገድ ሸሽቶታል። ኢህአዴግ በተለይ ታሪክ ሽሽት ላይ አንደኛ ነው። ‘ኢግኖር’ ሲያደርግ የሚችለው የለም።
ኢህአዴግ እንደፓርቲ የሚቃወሙትን ያገልላል ይባላል እንጂ የሚሸሸው ራሱ ነው። ሌሎች አጠገቡ እንዳይደርሱ ሲያደርግ፣ በሚዲያው ስማቸው እንዳይነሳ ሲያዝዝ ራሱም እየሸሻቸው መሆኑን ያሳብቅበታል።
ብሎ ብሎ የሁሉም ሰው ሥጋት ኢህአዴግ ሕገ-መንግሥቱን እንዳይሸሸው ብቻ ነው። ሕገ-መንግሥቱን ያወጣውም ያጸደቀውም ያንቆለጳጳሰውም ራሱ ነው። አሁን ግን ተቃዋሚውም ዜጎችም ሕገ-መንግሥቱ የሰጠን መብት ተጣሰ እያሉት ነው። ሕገ-መንግሥቱን ትሸራርፋለህ ብለው እየወቀሱት ነው። ሕገ-መንግሥቱን ራስህ አውጥተህ ራስህ ነፍገሃል ብለው እያሙት ነው። ቢወቀስ ቢከሰስ ሁሌም በሕገ-መንግሥቱ አፈጻጸም ጉዳይ ላይ ሆኗልና ቃሉን የፈራው መስሏል። ቀስ በቀስ ሕገ-መንግሥት የሚለው ቃል በሚዲያ እንዳይነገር፣ በኢህአዴግ ስብሰባ እንዳይጠራ፣ ስሙ እንዳይነሳ ሊያደርግ ይችላል። ይህን ሁሉ ነገር ሸሽቶ አሁን በሕገ-መንግሥቱ ጉዳይ ላይ ሲመጡበት ምን እንደሚያደርግ አልለየለትም። ብቻ ሕገ-መንግሥቱንም እንዳይሸሸው ሰጋን።

የሕወሓት ስውር እጆች የግል ባንኮችን እያዳከማቸው ነው::
የውጭ ምንዛሬ ማለት ለአንድ ታዳጊ ሃገር እጅግ እንቁ የሆነ እና ሊንከባከቡት ሊያሳድጉት የሚገባ ብቸኛ የኢኮኖሚ ዋልታ ሲሆን ይህንንም በቁጠባ እና ብልሃት በተሞላበት የኢኮኖሚ አስተዳደር ከያዙት ትልቅ የኢኮኖሚ ግብ ላይ የሚያደርስ ነው:: የሃገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ምርኩዞች በላኪዎች እና በውጪ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከሚልኩት መሆኑ እሙን ነው::በላኪነት ስራ ላይ በብዛት ተሰማርተው የሚገኙት የገዢው መደብ አባላት እና ዘመድ አዝማዶቻቸው እንዲሁም በጥቅም ትሥሥር ላይ የተለጠፉ አቆርቋዥ ነጋዴዎች ንግድን ሽፋን ሃገሪቷን በማራቆት ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ::የወያኔ ባለስልጣናት ደሞ ከውጪ አገር ዜጎች ጋር የውስጥ ሽርክና በመፍጠር በጥቅም ትሥሥር ከመሬት ጀምሮ እስከ ማንኛውም ማተሪያሎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሃገር ውስጥ ሲገቡ በኢንቨስትመንት ስም ከሚመሰረተው ድርጅት ጋር የማይገናኙ ውድ እቃዎች ሳይቀሩ ገብተው ሃገሪቷ ማግኘት የሚገባትን እንዳተገኝ ባለስልጣናት ጋሬጣ ሆነዋል::

የወያኔ ባለስልጣናት ቤተሰቦች እና ዘመድ አዝማዶች በላኪነት ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ በግልጽ የሚታወቅ…ገንዘብን ምንም አይነት ዋስትና ሳያሲዙ በአነስተኛ ወለድ እየወሰዱ የማይከፍሉ እና ሰነድ የሚያስጠፉ ሲሆን ያለምንም ቀረጥ እና ታክስ ወደ ውጭ ሃገር ምርቶችን በመላክ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሃገር ቤት ከማምጣት ይልቅ በተለያዩ የአውሮፓ እና የኢሲያ ሃገራት ባንኮች ይዶሉታል::

ብሄራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬን ለመሸጥ እና ለመግዛት ዋጋ ቢወስንም የወያኔ ቴሌቭዥን ይህንን ቢናገርም በተግባር ግን እየተምታታ ያለው የውጭ ምንዛሬ ሂደት የግል ባንኮች ግን የውጭ ምንዛሬ መግዣ ዋጋን ወደጎን በመተው ከወያኔ የላኪ ድርጅቶች የውጭ ምንዛሬ በመሸጫ ዋጋ ሲሸምቱ እየተገኙ በዝምታ ታልፈዋል:: ይህም በሃገሪቷ የኢኮኖሚ ሂደት ላይ እንቅፋት የሆነ ሲሆን አንዳንድ ላኪዎች ከመንግስት ባንኮች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሬ በተዘዋዋሪ ለግል ባንኮች ሲቸበችቡ እየታየ በዝምታ እየታለፈ ነው::የሕወሓት ስውር እጆች የግል ባንኮችን እያዳከማቸው ነው::በመተማ በሞያሌ በመልካ ጀብዱ በኩምሩክ በሁመራ በሃርትሼክ ወዘተ በኢትዮጵያ ዙሪያ ገባ የድንበር ከተሞች ላይ በከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ ላይ የተሰማሩት በአብዛኛው የወያኔ አባላት እና የአከባቢ ባለስልጣናት ካድረዎች ከሚወጡ የሃገር ውስጥ ምርቶች የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለግል ጥቅማቸው እንደሚያውሉት ታውቋል::ይህም ጉዳይ በከፍተኛ ደረጃ ከብሄራዊ ባንክ ጀምሮ እስከ ድንበር ከተሞች የባንክ ቅርንጫፎች ድረስ በሙስና መረብ የተያያዘ የባለስልጣናት ስውር እጆች የተደባለቁበት ነው::

መሰረታዊ ለሆኑ የገቢ እቃዎች የጠፋው የውጭ ምንዛሬ ለሃገሪቱ የፖለቲካ ፍጆታ የመከላከያ እና የደህንነት መዋቅሮች ሲመደብ ማየት በህዝብ ጉሮሮ ላይ ቆሞ ስልጣንን በማስረዘም ሃገርን እየገደሉ መሆኑ በአደባባይ እያየነው ያለነው ሃቅ ነው:; የብሄራዊ ባንክ ከጊዜው የገዢ መደቦች ጋር በማበር የሃገርን ሀለቄታዊ የኢኮኖሚ ጥቅሞች አሳልፎ እየሰጠ ከባንክ አሰራር ውጭ ከፖለቲካው ጋር ግንኘነት ያሌላቸው አስመጪ ነጋዴዎች ማግኘት ያለባቸውን የውጭ ምንዛሬ ባለማግኘታቸው በ20 እና 30 % ጭማሪ ምንዛሬዎችን በመግዛት ጋሬጣ የተፈጠረባቸው ሲሆን ይህ ሁሉ የገዢው መደብ አባላት የፈጠሩት የውጭ ምንዛሬ ዘረፋ በሃገሪቷ ላይ የኑሮ ውድነት እንዲሰራፋ አድርጎታል::(ምንሊክ ሳልሳዊ)

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከሁለት ሳምንት በፊት በሱዳን ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል።በእዚህ ጉብኝት ላይ አቶ ኃይለማርያም ”እጅግ ለም የሆነ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን ለመስጠት ተስማምተዋል አሁን የቀረው ችካል ማስቀመጥ ነው” የሚል ዜና በኢሳት ሲዘገብ ቀናት ነጉደዋል።ትናንት ታህሳስ 16/2006 ኢሳት በአለም አቀፍ ራድዮ ስርጭቱ ላይ የኢትዮጵያ የድንበር ጉዳይ የሚከታተሉ ‘የኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴ’ የተሰኘ ኮሚቴ አባላትን በቃለ መጠይቅ አቅርቦ ነበር።እንደ ኮሚቴው ገለፃ ከሆነ አሁን መንግስት ለሱዳን መንግስት ለመስጠት መስማማቱ የሚነገረው መሬት ከቀድሞ ጀምሮ በኢትዮጵያ ይዞታ ላይ ያለ አሁንም ገበሬዎች የሚገኙበት እና ባዶው ቦታን ጨምሮ በትንሹ ካለምንም ማጋነን 15 ሚልዮን ሕዝብ አስፍሮ መመገብ የሚችል ቦታ ነው።15 ሚልዮን ልብ በሉ!

በሕዝብ ስም የሚደረግ ማንኛውም ውል ከህዝብ ሊደበቅ አይገባውም።ድንበር የማይቀዘቅዝ ትኩስ ደም ነው።ይህ ደም ደግሞ ለዘመናት የኢትዮጵያ አባቶች እና እናቶች ያፈሰሱት ደም ነው።ማንም መንግስት በሕዝብ ደም ሊደራደርም ሆነ ድንበር ሊሰጥ አይችልም።ለአንድ ‘ኩርማ’ መሬት ለባድሜ በሺዎች ያረገፈ ጦርነት ክተት ያወጀ መንግስት 15 ሚልዮን ሕዝብ የሚያሰፍር መሬት ለሱዳን ስለመስጠቱም ሆነ ስለ ውሉ ጉዳይ ዝርዝር ማብራርያ ለሕዝብ ሊሰጥ ይገባል።በትዊተር በብዛት የሚታዩት ባለስልጣናት ከሌላው ዜና ይልቅ የእዚህ አይነቱን ቅድምያ ሊሰጡት በተገባ ነበር።ድንበር የማይቀዘቅዝ ትኩስ ደም ነው።

http://www.youtube.com/watch?feature=pl … 86uyLReLdE

http://gudayachn.blogspot.no/2013/12/blog-post_26.html

የአጼ ምኒሊክን መቶኛ የሙት አመት መከበር ምክንያት በማድረግ በ DW ሬድዮ በተደረገው ጥያቄና መልስ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ, ዶ/ር ሓይሌ ላሬቦና ዶ/ር ሹመት ሲሳይ (የታሪክ ተመራማሪዎች) ቃለ መጠይቅ ተደርጎ በሚሰጠው መልስ ላይ ስለ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተናገሩት ላይ አስተያየቴን አቀርባለሁ።

አንባቢያንን ቃለመጠይቁን ቢያዳምጡ ጥሩ ነው ባይ ነኝ፤ ሁለቱ የታሪክ ምሁራን ትምህርታዊ ትንተና ይሰጣሉና

ውሸት ሲደጋገም እውነት ሊመስል ይችላል፤ በተለይም የአገራችንን የኢትዮጵያን ታሪክ ለማያውቁ እውነታው ምን እንደሚመስል መረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

አቶ ባልቻ ኦሮሞ ከባሌ እየተስፋፋ ሲመጣ ልብነ ድንግል እንዳይስፋፋ አቆሙት ይላሉ፤ ለምን ይህን ምሳሌ እንዳቀረቡም ግልጽ አይደለም ለሳቸው ትንታኔ የማይመች በመሆኑ፤ ለዛውም በአጼ ልብነ ድንግልና በኦሮሞች መሀከል ስለነበረው ግኑኝነት በከፊል ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ሊያስረድዋቸው ሞክረዋል፤ ስለመስፋፋቱና እንዲያውም አማራውን እንደገፋው ለአቶ ባልቻ መረጃ ላቅርብ

ጥንት ሌላ ስም የነበራቸው በኦሮሞ ከተያዙ ማግስት ስማቸው የተቀየረ፤ ደዋሮ- ጨርጨር, ጋፋት-ሆሮ, ገራሪያ- ሰላሌ, ዳሞት- ወለጋ, አበቤ- በቾ, ሽምብራ ኩሬ- ሞጆ…(የሃያኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያ ገጽ 50 በጥላሁን ገ/ስላሴ) በቅኝ ተገዛ የሚሉት ኦሮሞ ተጨማሪ ቦታ እንደያዘ እንጂ እንደተወሰደበት አይደለም ታሪኩ የሚመሰክረው፤

አቶ ባልቻ የኦሮሞን ታሪክ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ሊያዛምዱት ይሞክራሉ፤ ኦሮሞም እንደ ደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ሲረገጥ የኖረ ሕዝብ አድርገው ያቀርቡታል። መፈትሄውንም ሲጠይቁ reconciliation እርቅ ኦሮሞ ይቅርታ ተጠያቂ የተቀረው ይቅርታ ጠያቂ በተለይም የፈረደበት አማራ ለዚህ ወንጀል ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፤ ባለፉት አስተዳደሮች ስህተቶች አልተሰሩም ብሎ የሚከራከር የለም፤ ጥያቄው እንዴት አብረን ወደፊት መሄድ እንችላለን ነው?

እንደቅኝ ተገዛን የሚሉት ቡልቻ ደመቅሳ አገሪቱን በእርሻ ሚኒስቴርነትና በምክትል ገንዘብ ሚኒስቴርነት አስተዳድረዋል- ቸር ቅኝ ገዢ ነበር የነበራቸው፤ እኛ ቅኝ እየተገዛን ስለሆንን በሚኒስቴርነት ቅኝ ገዢዬን አላገለግልም ብለው አላንገራገሩም፤

ኦሮሞ በሲቢሉም ሆነ በወታደራዊው ክንፉ ታላቅ የሚባሉትን ስልጣኖች ይዞ የኖረና ያለ የህብረተሰብ ክፍል ነው፤ አገሪቱ ውስጥ ለነበሩትና ላሉትም ደግ ነገሮችም ሆነ ክፉ ነገሮች ተጠያቂነቱ እኩል ነው፤ አቶ ባልቻ ቅኝ ገዢ የሚሉትን የአማራውን ክፍለሀገር ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ ያስተዳድሩት ነበር- (ምሳሌ የሚያቀርብበት ደቡብ አፍሪካ የማስተዳደር ቅንጦት ይቅርና ነጭ በሚዝናናበት ቦታ ጥቁር መግባት አይፈቀድለትም ነበር)

ስለኦሮሞ ባለስልጣናት እስቲ እንመልከት

ምኒሊክ በሸዋ ሲነግሱ የረድዋቸው አብሮ አደግ ባልንጀራቸው ጎበና ዳጬ ናቸው፤ የወለጋውም አስተዳዳሪ ኩምሳ ምኒሊክን በደጃዝማችነት አግልግለዋል፤ እነ ባልቻ አባ ነፍሶም የማይረሱ ታልቅ ኢትኆጵያውያን ናቸው

የአጼ ሃይለስላሴ አባት ራስ መኮንን ወልደሚካኤል (ጉዲሳ) አባታቸው ኦሮሞ ነበሩ፤ እናታቸውም ወ/ሮ እመቤት እናታቸው ኦሮሞ ነበሩ፤

ራስ ዳርጌ የሸዋው ንጉስ ሳህለስላሴ ከወለድዋቸው አራት ወንዶች መሃከል አንዱ ሲሆኑ ጥናታቸው አርሲ ውስጥ የአንድ አካባቢ ኦሮሞ ባላባት ልጅ ነበሩ (አባ ቦራ በታቦር ዋሚ ገጽ 9)

ራስ አበበ አረጋይ መከላከያ ሚኒስትር

አቶ ይልማ ዴሬሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር, የገንዘብ ሚኒስትር

ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ የጎንደር አስተዳደር

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የእርሻ ሚኒስትርን ምክትል የገንዘብ ሚኒስትር

ሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ የክብር ዘበኛ አዛዥና I,ባህል ሚኒስትር

ደጀዝማች ገረሱ ዱኪ የኢሊባቡርና I,ጎሙገፋ አስተዳዳሪ

ሜጀር ጀኔራል ደምሴ ቡልቲ የሁለተኛው ክፍለ ጦር አዛዥ

ሌ ጀኔራል ጃጌማ ኬሎ የአራተኛው ክፍለጦር አዛዥና የባሌ አስተዳደር

ፊታውራሪ ለማ ወልደጻድቅ የሲዳሞ ምክትል አስተዳደር

ሜ ጀኔራል አበራ ወልደማርያም የአየር ሓይል ምክትል አዛዥ

ደጃዝማች በቀለ ወያ የጨቦና ጉራጌ አስተዳደር ከዛም የጨርጨር አስተዳደር

ደጃዝማች ካሳ ወልደማርያም የአዲስ አበባ ዩኒጸርሲቲ ፕሬዘዳንትና የእርሻ ሚኒስቴር

አንባቢያን መረዳት ያለብን ሁላችንም በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያውያን መሆናችን ነው፤ ሕዝባችን በጋብቻ, በእምነት በባሕል የተሳሰረ በመሆኑ መሰረት የሌለው ታሪክ እያነበነቡ ሊበታትኑን የሚያስቡትን ታሪካዊ መረጃ እያቀረብን ወግዱ ልንላቸው ይገባል፤ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ነው፤ ምኒሊክም ያስተማሩን መቻቻልን አንድነትንና ፍቅርን ነው፤
Moresh Info.

Image

ዛሬ ላስነብባችሁ ያሰብኩት ቀደም ሲል የጥራት እና ደረጃዎች መዳቢ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ተብሎ ይጠራ ስለነበረው አሁን ለአራት ተከፋፍሎ እንዲጠፋ ስለተደረገ ተቋም ነው፡፡ መስሪያቤቱ ምርት እና አገልግሎችን በመቆጣጠር የሸማቹን ደህንነት እና ጤንነነት ማስጠበቅ ፤ የገቢና ወጪ ምርቶችን ጥራት በመከታተል ጉልህ ድርሻ እንዲያበረክት ታስቦ የተቋቋመ ነው፡፡መስሪያቤቱን ለረጅም ዓመታት በበላይነት ይመሩ የነበሩት አቶ መሳይ ግርማ ሲባሉ በውስጡ የፍተሻእናካሊብሬሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የሰርተፊኬሽ አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክትሬት፣የደረጃዎች ዝግጅት ዳይሬክትሬት፣ የስልጠናአገልግሎት ዳይሬክትሬት እና የፋይናንስ ዳይሬክትሬት እና ሌሎች የአገልግጎች ዘርፎች ነበሩት፡፡አቶ መሳይ መስሪያቤቱን ከ16 ዓመት በላይ አስተዳድረዋል፡፡ድንገት ባልተጠበቀ ሰዓት ከአቶ መሳይ እውቅና ውጭ 3 ሰዎች አቶ ተክኤ ብርሀኔ ከመቀሌ፣አቶ ደቻሳ ጉሩሙ ከጅማ እና አቶ ዳንኤል ዘነበ ከሀረርጌተመልምለው ወደ መስሪያቤቱ ተመደቡ፡፡ሰዎች ሳይፈለጉ መመደባቸው ብቻ ሳይሆን በወቅቱ እንዲከፈላቸው የተፃፈላቸው የደመወዝ መጠንም በመስሪያቤቱ የደመወዝ ስኬል የሌለ፤ ካላቸው የትምህርት እና የስራ ልምድ ጋር ምንም አይነት ዝምድና ስለሌለው አቶ መሳይ መክፈል አልችልም በማለት አንገራገሩ፡፡እነሱ መች የዋዛ ቢሆኑ እና እስከ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተዘረጋ ሰንሰለት ስለነበራቸው በስልክ ተደውሎላቸው ሳይወዱ በግድ መክፈል ጀመሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በ2002 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እንዲረዳ ከየክልሉ ተፈልገው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ሀዋርያ ሁነው ወደ ፌዴራል መንግስት የመጡ ናቸው፡፡ተክኤ በስፓርት ፣ደቻሳ በሂሳብ እና ዳንኤል በማኔጅሜንት ተመርቀዋል፡፡ሲመጡ የሚያርፉበት የኪራይቤቶች የሚያስተዳድረው ሰፋፊ ግቢየተዘጋጀላቸው ሲሆን ዳንኤል ከአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጽ/ቤት አጠገብ፤ተክኤ እና ደቻሳ ደግሞ 22 አካባቢ ባለ ሰፋፊ ግቢ እንዲኖሩተመቻችቶላቸዋል፡፡ዋናው የቅርብ ጊዜ አላማቸውም በ2002 ለሚደረገው ምርጫ የመንግስት ሰራተኛውን ከኢህአዴግ ጎን ማሰለፍ እና ቀጣይ አመራሮችን ማዘጋጀትነው፡፡በዚህም መሰረት ባሉበት ቀበሌ በምርጫ ጣቢያ ሀላፊነት ተመድበው ይሰራሉ፡፡በተጨማሪም መንግስት በቢ.ፒ.አር.(business process reengineering) ብሎ ወደፊት ሊዘረጋ ላቀደው የሰራተኞች ማፈኛ መንገድ የራሱን ታማኝ የስለላ ሰዎች ወደመሲሪያቤቱ ያስገባል፡፡የአዲሶቹን ተመዳቢዎች አመጣጥ ተከተሎ በመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የፍረሃት ድባብ ተፈጠረ፡፡እነሱ ሰራተኞችን ወደሚጭነው ሰርቪስ ሲገቡ አንድም ሰው ትንፍሽ አይልም፡፡የአውቶቡሱ ሰው ሁሉ በጸጥታ ይዋጣል፡፡ጆሮ ጆሮ እያሉ ያንሾካሽካሉ፡፡በእረፍት ሰሀት እነሱ በተቀመጡበት አካባቢ አብሮ ተቀምጦ ሻይ ቡና የሚል የለም፡፡ሲመደቡ የኮሙኒኬሽን ሰራተኞች ተብለው ሲሆን ከመስሪያቤቱ እውቅና ውጭ ከነአቶበረከት ሰምኦን ጋር በየሳምንቱ ስብሰባ እና የመረጃ ልውውጥ ያደርጋሉ፡፡ከሳይንስና ቶክኖሎጂ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ ጋር ከፈለጉ በአካል መኪና አዝዘው ካልፈለጉ በስልክ በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ፡፡አቶ መሳይ እና ሌሎች የመስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች የማያውቁት መረጃ ከነሱጋ ይገኛል፡፡በዚህ የአንድ አመት ቆያታቸው በመስሪቤቱ ደጋፊዎችን ማፍራት አልቻሉም፡፡
በ2003ዓ.ም የቢ.ፒ.አር ጥናት ሲጀመር አዲስ የመጡት ካድሬዎች የጥናት ቡድን መሪ እየተባሉ ተመደቡ፡፡ቢ.ፒ.አር ለመስራት ቀርቶ ስለመስሪቤቱ አሰራር በቂ እውቀት የሌላቸው ሰዎች መስሪያቤቱን አፍርሶ እንደአዲስ የማደራጀት ስራ በእነዚህ ሰዎች ስር ወደቀ፡፡በዚህም ተቀራራቢ ስራዎችን በጋራ ማደራጀት በሚል ሰበብ ከብሄራዊ የጨረር መከላከያ አንዱን መምሪያ በማፍረስ፤የክሊነር ፐሮደክሽን መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ፤የሳይንስ መሳሪያዎች መስሪያቤትን ሙሉ በሙሉ አፈራርሰው አነዚህን መስሪያቤቶች ከደረጃ መዳቢ ባለስልጣን መስሪያቤት ጋር በማዋሀድ አራት የተለያዩ መስሪያቤቶችን ለመፍጠርጥናቱ ተጀመረ፡፡አዲስ የተጠኑት መስሪያቤቶች1.Meterology institute, 2.Accreditation biro, 3 .Standards agency4. Conformity assessment enterpriseይባላሉ፡፡ እነዚህ መስሪያቤቶች በተጠኑበት ወቅት ለጥናት ቡድኑ በየሳምንቱ በጣም ውድ በሆኑ ሆቴሎች የእራት ግብዣ እየተዘጋጀ ለ6 ወር ያክል ተደከመበት፡፡ወደመጨረሻው ምእራፍ ሲቃረብ የጥናት ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ናዝሬት ውስጥ ከ10 ቀን በላይ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠው እንዲሰሩ ተደረገ፡፡በመጨረሻም የጥናቱን መጠናቀቅ አስመልክቶ በአቶ ጁነዲን ሳዶ አማካነት አርባምንጭ ለሶስት ቀናት ድል ያለ ግብዣ ተደረገ፡፡ከአርባምንጭ መልስ ሁሉም በሳይንስ እና ቴክኔሎጂ ሚ/ር ስር የሚገኙ ሰራተኛ ለገሀር በሚገኘው የመንገድ እና ትራንስፖርት መሰብሰቢያ አዳራሽ ጠቅላላ ስብሰባ ተካሄደ፡፡በስብሰባው የየጥንት ቡድኑ ሀላፊዎች የጥናታቸውን ውጤት ይፋ አደረጉ፡፡የሀገራችን ችግሮች ተዳሰሱ፡፡ለችግሮች መፍትሄ ይሆናሉ የተባሉ አማራጮች ከየአቅጣጫው ጎረፉ፡፡አብዛኞች ወጣቶች ተስፋ ያደረጉትን በየመስሪያቤቱ ያለውን ብልሹ አሰራር እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል አስተያየታቸውን ሰጡ፡፡በዚህ ውይይት ከተነሱት ውስጥ እስካሁን የማሰታውሳቸው አቶገብረጊዳን ገብረመስቀል በቅጽል ስሙ(GG) “በየመስሪያቤቱ ያለውን የተማረ የሰው ሀይል እጥረት ለመቅረፍ መንግስት በውጪ የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ገብተው እንዲሰሩ ቢደረግ መልካም ነው፡፡ለምሳሌ እንደኢንጅነር ቅጣው እጅጉ አይነት ሰዎች ነበሩዋት ሌሎችም እንዲህ አይነቶች ይኖራሉ ብሎ ተናገረ፡፡”በእረፍት የንግድሚኒስትሩ የአቶ ታደሰ ሐይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሳይ ይህን የተናገረውን ልጅ ጠራቸው እና ስሙን ጠይቃ “አንተማ የእኛው ነህ እየውልህ ኢ/ር ቅጣው በመንግስታችን ላይ ሊሰራ አቅዶት የነበረውን ስለማታውቅ ነው እንዲህ ያልከው፡፡በቶሎ ቀጨው እንጂ ቢቆይ በጣም አደገኛ ነበር፡፡እንዲህ አይነቱን ሰው ስሙን መጥራት የለብህም” አለችው፡፡ይቅርታ ወ/ሮ አልማዝ እኔ እሱን አላውቅም ነበር ሲል መለሰላት፡፡ሌላው ከጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት የመጣ አቶ ጸጋዬ የሚባል አንድ ተናጋሪ በንግግራቸው መሀል ጣል ያደረጉዋት ቀልድ መሰል መልክት ሁሌም ትከነክነኛለች፡፡አቶ ጸጋዬ “አማርኛ እጅዋን አገኘች በግል ትምህርት ቤት ውስጥ አማርኛ መናገር እና ድንጋይ መወርወር ያስቀጣል ተብሎ በጉልህ ተጽፎ አንድትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ አንብቤያለሁ” ብለው አረፉ፡፡ሌላው ጠያቂ አብዲ ዱጋ ይባላል፡፡አብዲ ጥያቄውን ያቀረበው ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ነው፡፡ጥያቄው “ኦሮሚያ ክልል ውስጥ አየተካሄደ ያለው የአበባ እርሻ ልማት የአካባቢውን አፈር እና ውሃ እየበከለው ነው፡፡በዚህም የተነሳ እንስሳት ይሞታሉ ሰዎች ይታመማሉ፡፡የሰራተኞችም ህይወት አደጋ ውስጥ ነው የሚከፈላቸውም ገንዘብ እዚህ ግባ የሚባል አደለም፡፡እንዲያውም ባለ ሀብቶች ከሌሎች ሀገሮች ሲባረሩ ነው ወደዚህ ሀገር የመጡት ይባላል እና ይህን እንዴት ያዩታል? ሲል ጠየቀ፡፡አብዲን የገጠመው ከፍተኛ ውግዘት ነው፡፡ለውግዘቱ መነሻም በወቅቱ የአበባ እርሻ ልማት ሲጀመር አቶ ጁነዲን የኦሮሚያ ርእሰመስተዳድር ስለነበሩ እሳቸውን እንደተቃወመ ተቆጠረ፡፡አብዲም ያጠናው ባዮሎጂ ስለነበር ሙያዊ ትንታኔ መስጠቱን ቀጠለ፡፡ክርክሩ እየከረረ ሲሄድ ጓደኞቹ ዝም እንዲል አደረጉት፡፡ስልጠናው ለ5 ቀናት በፍረሃት እንደተዋጠ ተጠናቀቀ፡፡ከዚህ ሰብሰባ መልስ በቀጥታ ሁሉም መስሪያቤት ወደ ሰው ኃይል ምደባ እንዲገባ መመሪያ ተላላፈ፡፡
ስብሰባው አርብ ተጠናቆ ሰኞ ጠዋት አቶ መሳይ ከመስሪያቤቱ በፍቃዳቸው እንዲለቁ ትእዛዝ እንደተሰጣቸው ለሚቀርቡዋቸው ሰዎች ሲናገሩ የኮሚኒኬሽን ሰራተኞቹ እነ ተክኤ ደግሞ ምደባውን እንዳያስተጉዋጉል በማሰብ አስቀድሞ መባረሩን በየቢሮው እየዞሩ ያውጃሉ፡ይህን ተከትሎ መስሪያቤቱ ሰው የሞተ ያክል በኡኡታ በልቅሶ ታመሰ፡፡አብዛኖች መልካም ተግባሩን ለሰራተኛ አዛኝነቱን እያሰቡ አባታቸውን በሞት የተነጠቁ ያክል ከልብ አዘኑ፡፡በዚሁ እለት የንግድ ሚኒስትሩ የአቶታደሰ ሀይሌ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ ካህሣዬ መስሪያቤቱን እንዲያስተዳድሩ ተሾሙ፡፡የተለያዬ ዳይሬክተሮችን ሹመት ሰጡ፡፡በዚህ ወቅት ቀደም ሲል ወያኔን እንደሚቃወሙ የሚታወቁት እና ከአቶ መሳይ ጋር ቀረቤታ አላቸው የተባሉ ነባር ዳይሬክተሮች ተነስተው በምትካቸው የኢህአዲግ አባላትንመመደብ ተጀመረ፡፡ምደባውም የሚካሄደው እያንዳንዱ ሰራተኛ እየተገመገመባለው ችሎታነው ይባል እንጅ ነገር ግን አስገራሚው እና ያን ያክል የተደከመበት ጥናት የግምገማውን 75% የሚይዘው ከስራው ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው አመለካካት የሚባል ነገር ነው፡፡ሰራተኞች በወቅቱ ያነሱት የነበረው ጥያቄ አመለካከት በምን ሊለካ ይችላል የእኔን አመለካካት ምን እንደሆነ ማን ያውቀዋል የሚል ነበር፡፡ግምገማውን የሚሞሉት ቀደም ብየ የጠቀስኳቸው እነ ተክኤ፣ደቻሳ እና ዳናኤል ናቸው፡፡እነዚህ ሰዎች እንደመሰላቸው የግምገማ ነጥቡን መስጠታቸው ሳያንስ ምደባውን በዋናነት የሚመሩት እነሱ ናቸው፡፡ወደደረጃ መዳቢ መስሪያቤት የመጡትን የሌላ አዳዲስ መስሪያቤት ሰራተኞች መልካቸውን ሳይቀር የማያውቁዋቸውን ሰዎች ግምገማ በድፍረት ይሞሉ ነበር፡፡በመሀል በተቃዋሚነት ያልተፈረጁትን እና አባል መሆን የሚፈልጉ ካሉ በምደባ እና በእድገት አያባበሉ ወደድርጅቱ የማግባባት ስራ ተከናወነ፡እኔ ስራየን እንጂ የፓርቲ አባል መሆን ፍላጎት የለኝም ያሉት ደግሞ ቀደም ሲል በተለያዩ የውጭ ሀገራት ሳይቀር ከፍተኛ ስልጠናዎችን ተከታትለው ስራቸውን በብቃት ሲወጡ የነበሩ በርካታ ባለሙያዎች አብዮታዊ ዲሞክራሲን ባለመቀበላቸው ብቻ ዘራቸው እየታየ ከስራቸው ከተባረሩትመካከል ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ለማሳያ ያክል የቀረቡ ሲሆኑ አንድም የትግራይ ብሄር ተወላጅ አለመባረሩን አንባቢያን ሊገነዘቡት ይገባል፡፡ሌላው እና አስገራሚው ነገር በወቅቱ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን እያገለለ እየተካሄደ ያለው ምደባ ያሳሰባቸው የኢህዴድ አባላት ጥያቄያቸውን ለሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ቢያቀርቡም ወ/ሮ አላማዝ ካህሳይ እያንዳንዱን ኦሮሞ እቢሮአቸው ጠርተው አርፈው እንዲቀመጡ አለዚያ እንደሚባረሩ በዛቻ ገልጸውላቸዋል፡፡በወቅቱም ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰማው አቶ ሙሉጌታ መኮነን ያለስራ ለአንድ ዓመት ደመወዝ ብቻ እየተከፈለው ሊሰራ በማይችል ዘርፍ የቡድን መሪ ሁኖ ሲመደብ በስሩ ግን ምንም ሰው አልነበረም፡፡
ተ.ቁ ስም የነበራቸው ሀላፊነት ብሄር
1 አቶ መሳይ ግርማ የጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ኦሮሞ
2 አቶ ጋሻው ወርቅነህ የጥራት እና ደረጃ መ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር አማራ
3 አቶ ተፈራ ማሞ የኤሌክትሪክል ላብራቶር ሃላፊ ኦሮሞ
4 አቶ ሀይሉ የመሳሪያ ጥገኛ አገልግሎት ሃላፊ ኦሮሞ
5 አቶ ደሬሳ ፉፋ የሰርተፊኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር ኦሮሞ
6 አቶ መስፍን የስልጠና አገልግሎት ዳይሬክተር አማራ
7 አቶ አዱኛው መስፍን የጥራት ማኔጅሜንት አሰልጣኝ አማራ
8 አቶ እንዳ የኢንፎርሜሽን አገልግሎት ሀላፊ አማራ
9 አቶ አመሃ በቀለ የጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ አማራ
10 አቶ ሂርጳ የጥራት ማኔጅሜነት አሰልጣኝ ኦሮሞ
11 አቶ መረሳ የሰርትፊኬሽን ኤክስፐርት ኦሮሞ
12 አቶ ቴወድሮስ ዘካሪያስ የፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት አማራ
13 አቶ ልኡል የባህርዳር ቅርንጫፍ ሀላፊ አማራ
14 የሰርትፊኬሽን ሲስተም ኦዲተር የነበሩት ኦሮሞ
15 የድሬደዋ ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት አማራ
16 የናዝሬት ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት ኦሮሞ
17 የሀዋሳ ቅርንጫፍ ሀላፊ የነበሩት ደቡብ
ታማኝ የህወአት አባላት በባትሪ ከሌላ ቦታ ተፈልገው ያለ ልምድ እና ችሌታቸው በከፍተኛ አመራርነት ሲመደቡ የተለሳለሰ አቋም ያላቸውን እና የአባልነት ጥያቄ ሲቀርብላቸው ጥያቄውን የተቀበሉ ነባር የመስሪያቤቱ ሰራተኞች የፍርፍሪው ተቋዳሽ ሁነዋል፡፡በዚህ ምደባ እስከቡድን መሪ ያለው ሀላፊነት ያለ ፓርቲ አባልነት ወይም ያለ ትግራይ ተወላጅነት በምንም መልኩ ለተራው ሰራተኛ አይሰጥም፡፡

ተ.ቁ ስም ቀደም የነበራቸው ሀላፊነት አሁን የተሰጣቸው ሀላፊነት ብሄር
1 ወ/ሮ አልማዝ ካህሳየ የኢንስፔክሽን አገልግሎት ዳይሬክተር የደረዳዎች ዋና ዳይሬክተር ትግሬ

2 አቶ ወንዶሰን ፍስሃ የካሊብሬሽን አገልግሎት ሀላፊ የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ

3 አቶ አርአያ መከላከያ ኢንጅነሪንግ የአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ

4 አቶ ጋሻው ተስፋዬ የፍተሻ ላብራቶር ኤክስፐርት የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ትግሬ
አቶ ገብሬ ኝግድ እና ኢንዱስትሪ ኤክስፐርት በደረጃዎች ኢጀንሲ ዳይሬክተር ትግሬ

6 አቶ ብርሀኑ ተካ ረዳ የፋይንነስ አስተዳደር ዳይሬክተር የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የፋይናንስ ዳይሬክተር ጉራጌ

7 ወ/ሮ ገነት ገ/መድህን የፍተሻ እና ካሊብሬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር የአክረዲቴሽን ጽ/ቤት ዳይሬክተር ትግሬ

8 ወ/ሮ ብርሀን ብሂል የአዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጸሀፊ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሰው ሀብት እስተዳደር ሀላፊ ትግሬ

9 አቶ ብርሀኑ ተካ የሰርቪስ ሹፌር የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የተራንስፖርት መምሪያ ሀላፊ ትግሬ

10 አቶ ተክኤ ብርሀኔ የኮሙኒክሽን ሰራተኛ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ትግሬ

11 አቶ ዳዊት የሰርቪስ ሹፌር የሜትሮሎጂ ኢንስቲቲዩት የትራንትፖርትመምሪያ ሀላፊ ትግሬ

12 አቶ ጸጋዬ ኢንስፔክተር የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ሀላፊ ትግሬ

13 አቶ ዘነበ ኢንስፔክተር የገበያ ጥናት ሀላፊ ትግሬ
ቀደም ሲል እንደማናኛውም ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ የመንግስት መስሪያቤቶች የሚታዩ ችግሮች ቢኖሩም የተወሰደው እርምጃ ግን የወቅቱን የትግሬዎች የንግድ እንቅስቃሴ ያላንዳች ተቆጣጣሪ እንደፈለጉት ለማሽከርከር ታስቦ አንደሆነ ይታወቃል፡፡ለዚህም መነሻ የሚሆነው በተለያዩ ጊዜያት በቆርቆሮ፣በብረታብረት፣በማዳበሪያ፣በሳሙና፣በከብሪት፣በሲሚንቶ ፣በዘይት፤በጨርቃ ጨርቅ ፣ በባትሪ ድንጋይ፣በኤሌክትሪክ ገመዶች የመሳሰሉት ምርቶች ላይ ተደጋጋሚ ችግር ተከስቶ በበላይ አካል የስልክ ትእዛዝ ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶች ለህብረተሰቡ እንዲሰራጩ ተደርጉዋል፡፡ለአብነት ያክል የአቢሲኒያ ሲሚንቶ ፋብሪካ በጥራት ጉድለት ምክንያት እንዳያመርት አገዳ መስሪያቤቱ ሲያስተላልፍ በወቅቱ የከተማ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ካሱ ኢላላ ፍተሻውን ያከናወኑ ባለሙያዎችን በግላቸው ቢሮ ድረስ በማስጠራት ትክክል አደላችሁም፤ልማታችንን እያደናቀፋችሁ ነው፤ኢንቬስተሮች ወደ ሀገራችን እየመጡ እንዳይሰሩ መሰናክል እየፈጠራችሁ ስለሆነ አቁሙ ሲባሉ የመስሪያቤቱ ሀላፊዎች እገዳውን ባስቸኩዋይ አንዲያነሱ ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፈዋል፡፡መስሪያቤቱም እንዲፈርስ የተደረገው ባለሞያዎችም የተፈናቀሉት ሆን ተብሎ ያለ አግባብ መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲረዳው ያስፈልጋል፡፡

ህዝብን ማዳመጥ ያልቻለው ራሱን የሚያዳምጠው ወያኔ
ስብሰባ ስብሰባ ስብሰባ…..ይቀጥላል ይህ ወያኔያዊ የአውሬ ወለድ በሽታ

ምንሊክ ሳልሳዊ…የህዝብ ጥያቄዎች አለመደመጣቸው ውጤቱ የችግሩን ጥልቀት ስፋት እና እያስከተለ ያለውን ቀውስ ሊታየው ያልቻለው ወያኔ በአገር ኢኮኖሚ ላይ ከባድ ጫና ከመፍጠሩም በላይ ህዝቡን ወደባሰ የድህነት አረንቋ እየከተተው ነው:: ይህ ደሞ ወያኔ እንደ መንግስት ለህዝብ ጥያቄዎች አትኩሮት አለመስጠቱ ነው::ሕዝብ ችግሩን የሚናገረው በስብሰባ ብቻ አይደለም፡፡ በየቀበሌው፣ በየክፍለ ከተማው፣ በየከተማ አስተዳደር እርከኖች፣ በየመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ በየክልሉ፣ ወዘተ በማመልከቻ፣ በቃልና በጽሑፍ በየደቂቃውና በየሰኮንዱ አቤት እያለ ነው፡፡ የሰሚ ያለህ እያለ እየጮኸ ነው፡፡ መብቴ ተረገጠ፣ ንብረቴ ተቀማ፣ ጉቦ ካልሰጠህ ችግርህ አይፈታልህም ተባልኩ፣ አድልዎ ተፈጸመብኝ፣ ወዘተ እያለ ነው፡፡ ነገር ግን ሕዝቡ የሚያዳምጠው የሚያዳምተው አላገኘም ካድሬዎች ከህዝብ ጥያቄዎች በፊት ፖለቲካውን እና ተቃዋሚዎችን ወደ ማሳደድ አዘንብለዋል::

ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን እናዳምጣቹ በሚል ሰበብ ችግራችሁን ተወያይተን እንፍታ በሚል ሰበብ የተለያዩ ስብሰባዎች የህዝብን ጭንቅላት ለመስረቅ በጀት ለአበል ተመድቦ እበማካሄድ ምንም ፋይዳ ያሌላቸው እና ለሚዲያ ፍጆታ ለማዋል የሚደረጉ ከመሆናቸውም በላይ ወያኔ ግን የሚወስነው ጉዳይ ለህዝብ እንቅፋት የሆነ እና ከስብሰባው እና ከተሰብሳቢ ምልክታ ውጪ የፖለቲካ አጀንዳውን ለማስፈጸም ብቻ ነው::

በስብሰባ ስም የሰበሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የተጠሩበት አጀንዳ ውጪ ራሱ ተናግሮ ራሱ እንደፈለገ አውጥቶ እና አውርዶ ራሱ ወስኖ የራሱን ድምጾች እንደገደል ማሚቱ የሚያዳምጠው ወያኔ ምንም አይነት መንግስታዊ እና ህዝባዊ ፋይዳዎችን ሲፈጽም አልታየም::ህዝብን ማዳመጥ አለመቻሉ ህዝብ ጥያቄ ሲያነሳ እንደ ጭራቅ መመልከቱ የመብት ጥያቋ ያለሳ ሁሉ እንደ ጠላት እና እንደ ተቃዋሚ መፈረጁ ወያኔ ህዝብን ለማዳመጥ ጊዜ እንዳሌለው የሚያሳዩ ጉዳዮች ናቸው::ማንኛውም ኢትዮጵያዊ አውቅልሃለሁ ከተባለው ውጭ ጥያቄ አንስቶ ቢገኝ ህገወጥ ነው:: የፖለቲካ ፓርቲ ሰልፍ ቢጠራ ህዝብ በአደባባይ የአገልግሎት መብቱን ቢጠይቅ በስብሰባ ላይ የተሰማውን ቢተነፍስ ወዘተ…ህገወጥ ነው::

በአለማችን ላይ አንዱ አንዱን ካዳመጠ የማይፈታ የማይቀረፍ ችግር የለም:: በሰለጠነ ዘመን እኔን ብቻ ስሙኝ ብሎ ድርቅ ያለ አስተሳሰብ ማንጸባረቅ ተቀባይነት የለውም:: ህዝብን ማዳመጥ የቻለ መንግስት ነኝ የሚል ሁሉ ሃገራዊ ስኬቶቹ ጉልህ ናቸው::ህዝብን ማዳመጥ ያልቻለ በጉልበት የሚኖር መንግስት የግእዜ ጀግና ስለሆነ ይወድቃል:: ወያኔም እኔ ብቻ ነኝ ህዝባዊ ሌላው ህገወጥ ነው ቢልም ለህዝብ ችግሮች ግን ምንም አይነት መፍትሄ ሊሰጥ ባለመቻሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግሮች በስፋት እየጨመሩ መተዋል::

በየስብሰባው ገበሬው ነጋዴው መምህሩ ተማሪው ፖለቲከኛው ጋዜጠኛው ….ባጠቃላህ ህዝቡ ብሶቱን አሰምቷል::የህዝብን ችግር እናዳምጣለም በሚል ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦ ስብሰባዎች በየፈርጁ ተጠርቷል::ሁሉም ችግሩን ተንፍሷል:: …መፍትሄ ግን የለም:: የህዝብን ጥያቄ ግን ወያኔ ሊያዳምጥ አልፈቀደም ….ይልቁኑ ለሚዲያ ፍጆታ እና ለፖለቲካ አጀንዳነት ተጠቅሞበታል:: በየስብሰባው አላስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ተናግረዋል የተባሉ ታፍነዋል ታስረዋል ተሰደዋል ተገድለዋል ከስራ ተባረው ቤተሰባቸው እንዲበተን ተደርገዋል::ታዲያ ህዝብን ማዳመጥ ተብሎ የሚጠሩ ስብሰባዎች ወያኔ ራሱን እያዳመጠ ህዝቡን እየደፈጠጠ ነው::

ህግ አለ ህገመንግስት እናስከብራለን የሚለው ወያኔ መጀመሪያ ራሱ ህገ መንግስቱን እና ያወጣውን ህግ ማክበር አለበት::አንድ መንግስት ህዝብን ያዳምጥ ሲባል መለመን ወይንም ምጽዋት መጠየቅ አይደለም:; ህዝብም ማዳመጥ የማንኛውም አመራር ህጋዊ ግዴታ ነው::ህዝቦች ከህግ እና ከመብት አንጻር ተደምጠው መፍትሄ ሊሰጣቸው ይገባል::መንግሥት ሕዝብን የሚያዳምጠው በሕገ መንግሥቱ ግዳጅነት አይደለም፡፡ የሕዝብ ሰራተኛ ነኝ የሚል ሥልጣን የያዘ ፓርቲና መንግሥት፣ ሕዝብ መረጠኝ የሚል ፓርቲና መንግሥት፣ የሕዝብ ከበሬታና አመኔታ ሊያገኝና ዓላማውን በተግባር ላይ ሊያውል የሚችለው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሥልጣን ላይ የሚቆየው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ህዝብን የማያዳምጥ ራሱን የሚያዳምጥ የማይደመጥ ይሆናል፡፡

ነጻ አውጪ እስከመች???
የትግራይ ህዝብ ነጻ አልወጣምን??? ሕወሓት ማንን ነጻ ለማውጣት ነው በዚህ ስሙ የቀጠለው?
እውን አሁንም በትግራይ ህዝብ ላይ የተንሰራፋ የጨቋኝ ቡድን አለ?

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ከአነሳሱ ሲጠነሰስ የትግራይ ህዝብን ነጻ በማውጣት ሲሻው በመገንጠል ሲሻው ታላቋን ትግራይ በመመስረት ….በሚሉ የመከኑ ይሁኑ ገና ያልተሳኩ አሊያም (በፕሮሰስ ላይ ባሉ ?)ባልታወቁ መርሃግብሮች ላይ ተነድፎ ወደ ጫካ መግባቱ እውን ቢሆንም ያላሰለሱ ድሎች መገኘት የጀመሩት ግን በ1980ዎቹ የሃገራዊ ፋይዳው ታይቶ ከተፈጠሩት ሁሉን አቀፍ የጦር አውድማዎች በኋላ ነው::…ሕወሓቶች ኢሕዴንን እና ኦሕዴድን አጣምረው ኢሕኣዴግ በሚል ተሰይመው የነበሩት የዛኔዎቹ ታጋዮች ለዲሞክራሲያዊ ምስረታ እና ለህዝባዊ እኩልነት የታገሉ መሆኑ እሙን ቢሆንም የተነሱበት አላማ የተሰዉለት ይህ ነጥብ ግን ከአፈር ጋር ደባልቀውታል:: የሰምዓታቱንም ፍሬ እዛው በረሃ ጥለውት መተዋል::

የዳግማይ ወያኔ አነሳስ የትግራይን ህዝን ነጻ ለማውጣት ነው እስካለ ድረስ እና ራሱን የትግራይ ህዝቦች ነጻ አውጪ ብሎ ከሰየመ በኋላ ደርግን መፋለሙን ተከትሎ ከደርግ ጭቆና የትግራይን ህዝን ነጻ እንዳወጣው እየነገረን ነው::አሁንሳ ሕወሓት ማንን ነጻ ለማውጣት ነው በዚህ ስሙ የቀጠለው? እውን አሁንም በትግራይ ህዝብ ላይ የተንሰራፋ የጨቋኝ ቡድን አለ? ወይንስ ነገሩ ከወዲሁ ነው የቀድሞዎቹ ጨቋኝ መደቦች እነእንትና ካልወደሙ የህ ሕወሓት የሚለው ስሙን አይቀይርም??/

ሕውሓት የትግራይን ህዝብ ነጻ ወተሃል ካለው 22 አመት አልፎታል:: የቀድሞ ታጋዮች የአሁን ገዢዎች ግን አሁንም ይህንን ስም ይዘው ቀጥለዋል::ለምን ግን …? የትግራይ ህዝብ ነጻነቱ የሚረጋገጠው ሕወሃትም ስሙን ቀይሮ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ የሚባልበት ቀን ይናፍቃል:: ኢህዴን እንኳን መዐሕድን ተከትሎ /ቀንቶ ብኣዴን ተብሏል…ሕወሓት ግን እስከመቼ ድብቅ አላማ ይዞ እንደሚጓዝ አልረዳ ብሎናል:: ወይስ ይህን ስም የሚጠቀመው አንድ የትግራይን ነጻነት እንደኤርትራ በሪፍረንደም እስኪያስረግጥ ነው ወይንስ እነእንትና…እንስም አይጠሬ የድሮዎቹ የጨቋኝ መደቦች የሚል መጠሪያ የተሰጣቸው ኢትዮጵያውያን ዘራቸው ከምድረ እትዮጵያ ተጠራርጎ እስኪጠፋ…???? የህገመንግስቱ አንቀጽ 39 ባለበት የሚቆየው ምን እስኪመሰረት ድረስ ነው? የመጀመሪያው የሆነው ኢትዮጵያዊነትን ከአያት ቅድመ አያቱ የወረሰው የትግራይ ህዝብን በአምባገነኖች ጭቆና ስር ለማስቀጠል ይሆን??/ስላልገባን ይነገረን::

ዲይስፖራ ፖለቲከኞች እና ወያኔ = ለሃገር የማይበጁ የጥላቻ አንጃዎች
የህዝብን አንደበት እንተነፍሳለን::

ምንሊክ ሳልሳዊ ሁለቱን በየፈርጃቸው በትግል አካሄዱ ዙሪያ ስንመለከታቸው የፖለቲካ አጀንዳቸውን በኢኮኖሚ በደቀቀው ህዝብ እና በነጻነት ጥያቄ በሚያነባው ህዝብ ላይ ለመጫን እየተራወጡ የሚሄዱ በጥላቸ የተሞሉ አንጃዎች ናቸው:: የወደደ ይውደድ የጠላ ይጥላ የህዝብን አንደበት ግን እንተነፍሳለን::ምናልባት ወያኔን ተወት አድርጓት እና ዲያስፖራ ፖለቲከኛ ነኝ ጋዜጠኛ ነኝ የሚለው ጣማማ እና በጥላቻ የሚያነክስ ይህ ነገር ላይዋጥለት ይችላል::
===== መዋጥ ከቻለ ይዋጥ መወጥ ካልቻለ ያስመልሰው የራሱ ጉዳይ::=======

እኛ አንዴ በሃገር ውስጥ አንዴ በውጭው በስራ ጉዳዮች የምንኖር ዜጎች ከወያኔ በባሰ መልኩ እያንገበገብን ያለው በአውሮፓ እና በአሜሪካ ተደብቆ መሰሪ እና በሃገር ላይ የጥላቻ ድብቅ አጀንዳውን እያራመደ ያለው ፖለቲከኛ ነውሃገር ወዳድ በሰው አገር የሚከራተቱ ዜጎችን ከግራ ቀኝ በተደቋቆሰ ፖለቲካ የሚያላትመው እና የዲያስፖራውን ሃገራዊነት ካለሞሶሶ ለማስቀረት የኢቶጵያን ህዝብ ትግል የሰው ሃገር የመኖሪያ ፍቃድ ማስገኛ ያደረገው የዲያስፖራ ፖለቲከኛ የጥላቻ ፖለቲካ ተሞልቶ ዘላለሙን በወሬ ትግሉን እየገደለው ይገኛል:: በሃገር ቤት ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በከፍተኛ ፍጋት ውስጥ ሲያሳልፉ ግማሹ ትግሉን መጦሪያ ሲያደርገው የኢትዮጵያን ህዝብ ከጭቆና አገዛዝ ማላቀቅ አልተቻለም::

የወያኔ ካድሬዎች ከሕወሓት መራሹ መንግስት የሚያገኙትን ጥቅም ለማስጠበቅ በከፍተኛ ጥላቻ ተሞልተው በሃገር ውስጥ በህዝብ ስቃይ ሲደሰቱ የተቃወመውን ሁሉ በማፈን በመግደር ወደ ኢስር ቤት በመወርወር የተቃወመ ሁሉ ጠላት ነው በሚል የእኛ እናውቅላቹሃለን አስተሳሰብ ተሞልቶ ህዝብን ሰቆቃ ውስጥ ከቶታል በፍራቻ አንገቱን ሰብሯል:: ውስጥ ለውስጥ በሚነዛ ሽብር የህዝብ ሚዲያዎችን ለፓርቲ ፍጆታ በማዋል በሚደረጉ የፕሮፓጋንዳ ሩጫዎች ለሃገር የማይበጁ መጥፎ ምግባራት በስፋት እየተፈጸሙ ነው::

ወያኔ የሚያራምደው የጥላቻ ፖለቲካ በጋራ ህዝቦች ለሃገራቸው በየመስኩ አስታውጾ እንዳያደርጉ በሃገራቸው ጉዳይ እንዳይሳተፉ እያደረገ ሲሆን ዲያስፖራው በተቃራኒ የሚያራምደው የጥላቻ ፖለቲካ ቁም ነገር አላባ ትግሎችን በመፍጠር ለወያኔ የስልጣን እድሜ ማስረዘሚያ በሩን ከፍቶለታል:: ዲያስፖራው የእርስ በእርስ መኮራኮም የበዛበት ፖለቲካ የሚያራምድ እና ዘላለሙን የአምባገነኖችን የማውደም ትግል ሳይሆን የወያኔን ጥላቻ የሚሰብክ አንዱ ከፍ ብሎ ሲያይ እዛው የፖለቲካ ጥጉ ላይ ጎትቶ ገደል ለመክተት የሚራወጥ ለሃገር የማይበጁ በጥላቻ የተሞሉ ስብከቶችን የሚያበዛ ትግሉን ያደነዘዘ የህዝብ እንቅፋት ነው::

ዲያስፖራው የሞላበት የጥላቻ ፖለቲካ ማስወገድ ከትግሉ በፊት ቅድሚያ ተግባሩ ነው:: አብዛኛው ዲያስፖራ በየስብሰባው እንደምናየው ሊያጨበጭብ የሚመጣው በወያኔ ላይ ያለውን የጥላቻ ፖለቲካ ተመርኩዞ እንጂ በትግል ስልቱ ላይ ያለውን ግንዛቤ ይዞ ነው:: አጨብጭቦ ዶላሩን አፍሶ የመኖሪያ ፍቃዱን የሚያድስበት የትብብር ደብዳቤ ተከብሎ ከዛ ሃገር የራሷ ጉዳይ:: ጠንከር ያለ ትግሉን የሚያጧጡፍ ሃተታ የማይዋጥላቸው ጋዜጠኞችም አንደኛው የትግሉ እሾህ ናቸው::በፖለቲካ ሽፋን ሃገር እና ህዝብ ይበዘበዛሉ ዲያስፖራው በቅንጦት ይኖራል::ይህ የጥላቻ ፖለቲካ የወለደው ጎል ነው:: ዲያስፖራው ለሃገር የሚበጅ እንቅስቃሴ የሚያደርግበትን ጊዜ እንናፍቃለን::

የወያኔ አገዛዝ እንደ እሳት የፈጀን ዜጎች የዲያስፖራው የተልፈሰፈሰ ትግል ደሞ እያንገበገን ይገኛል::ስለዚህ የህ ለሃገር የማይበጅ የጥላቻ ፖለቲካ ተወግዶ በጋራ ሃገር ከአምባገነኑ የወያኔ አገዛ የምትላቀቅበትን የጋራ ስልት መንደፍ ተገቢ ነው::

ምንሊክ ሳልሳዊ…ትናንትና ማታም ኢቲቪ ስለ አቶ መለስ ዜናዊ የተመሰከረውን ቆረጠው፡፡ ያ በ1984 ቤተሰቦቻቸውን ያጡትና አሳዛኝ ሰውዬ ትናንትናም በኢቲቪው ዶክመንተሪ እያለቀሱ ታዩ፡፡ እነ ዶክተር መረራ ጊዲና፣ ፕሮፌሰር መስፍን፣ ኢንጅነር ይልቃል፣ ግርማ ሰይፉ በሽብርተኝነት ስም መንግስት እያሸበረን ነው በማለታቸው ተብጠልጥለዋል፡፡

በሌላ በኩል ያ መከረኛ ሰውዬ የሰጡት ምስክርነት አሁንም ተቆርጧል፡፡ ባይቆረጥ ኖሮ ሰውየው ‹‹ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው መለስ ዜናዊ ነው!›› ነበር የሚሉት፡፡ ማን ይናገር የነበረ ቢሆንም የአሁኖቹ ወጣት የኢቲቪ ካድሬዎች ግን ቆርጠውታል፡፡ አዎ! ኢቲቪ አሁንም ዳግመኛ ቆረጠው፡፡ በእነ ዶክተር መረራና በእነ ፕሮፌሰር መስፍን ላይ ደግሞ የሌለውን መረጃ ቆርጦ ቀጥሏል፡፡ እነ አንዱ ዓለም አራጌ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው ይህን ነው የሚባል ምስክር ሳይቀርብባቸው እስር ቤት ውስጥ ታጉረዋል፡፡ ቤተሰባቸው ላይ ማን ጥቃት እንዳደረሰ፣ ማን ተጠያቂ እንደሆነ የተመሰከባቸው አቶ መለስ ግን ምስክርነቱ ተቆረጠላቸው፡፡ እነ አንዱ ዓለም አራጌ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ መፍትሄ አፈላላጊ እንዲህ እያለቀሰ ‹‹ቤተሰቦቼን ፈጁብኝ! ለዚህ ሁሉ ተጠያቂዎቹ እነሱ ናቸው›› የሚል ቢገኝ መስካሪው ካለው ባሻገር ሆድ አደር ‹‹ተንታኞችና ተመራማሪዎች፣ ጋዜጠኞች›› ለጥጠው፣ ጨምረውበት ስንት ሰቅጣጭ ፊልም ይሰራበት ነበር፡፡

አንዳንዴ ሳስበው ካድሬዎቹና ኢቲቪ (ያው ካድሬ ነው) አቶ መለስን ከአምላክ በላይ ይፈሯቸዋል/ያከብሯቸዋል፡፡ ምክንያቱም ቅዱስ መጽሃፉ፣ የእምነት አባቶች እግዚያብሄር ሰውን በውሃም ሆነ በሌላ ነገር ማጥፋቱን አይደብቁም፡፡ እስኪ ስለ ይሁዳም ሆነ ሌላ ከየትኛውም መላክ በተቃራኒ ስለሚገኙት አካላት የምታወቁ ንገሩኝ? ተከታዮቹ ጥፋታቸውን ይደብቁላቸዋል እንዴ?

ምስክር ምስክር ነው፡፡ ደግሞም ከኢቲቪ፣ ከኢህአዴግ፣ ከአቶ መለስ ይልቅ ዶክተር መረራ፣ ፕሮፌሰር መስፍን፣ ኢንጅነር ይልቃል፣ ግርማ ሰይፉ ያሉትን አምነዋለሁ፡፡ ምክንያቱም እነ አንዱ ዓለም፣ አቡበክር፣ እስክንድር፣ ርዕዮት ሳይሆኑ የሚያስሸብሩን ካድሬዎቹ፣ ባለስልጣናቱ፣ ኢህአዴግ፣ ኢቲቪም ናቸው፡፡

ያን መከረኛ ሰውዬ ደግሞ ከምንም በላይ አምናቸዋለሁ፡፡ እንዴት አልመናቸው? እሳቸው ስለ ሽብር ሲያወሩ በቅርብ ስለሚያውቋቸው ቤተሰቦቻቸው ጭፍጨፋ እንጅ ስለ ስልጣን አይደለም፡፡ እናም ኢቲቪ የቆረጠውን እኔም አልቆርትባቸውም፡፡ ልክ ነዎት! ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው መለስ ዜናዊ ነው፡፡ ኦነግ ፈጸመው ለተባለው ብቻ ሳይሆን አሁንም ድረስ ቤተሰቦቻቸው እንዳያዩዋቸው ተደርገው ጨለማ ቤት ውስጥ ለሚታጎሩት ሰላማዊ ታጋዮች፤ ኑሮ፣ ካድሬ፣ የመለስ ራዕይ፣ አብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ የአቅርቦት እጥረት……ለሚያሸብረው የኢትዮጵያ ህዝብ ተጠያቂው፤ ሽብርተኝነትን በመንግስት ደረጃ አዋቅረው ያለፉት አቶ መለስ ናቸው፡፡ የፈለጋችሁ ሙት ወቀሽ በሉኝ፡፡ ይህን የአቶ መለስ ‹‹ሌጋሲ›› አልረሳውም፡፡ ቢያንስ ኢህአዴግ ራሱ አምኖ ‹‹ተሳስተን ነበር፡፡ ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው መለስ ዜናዊ ነው፡፡ እኛም ሆድ አደር ሆነን አብረን አጥፍተናልና ተጠያቂዎች ነን›› እስኪል ድረስ!

ሰማያዊ ፓርቲ ግንፍሌ አከባቢ የሚገኘውን እና በጽ/ቤትነት የሚጠቀምበትን ቢሮ በዛሬው እለት ከሰኣት በኋላ አቶ ሄኖክ የተባሉ አከራዩ ከ አራት ትግሪኛ ተናጋሪ ግለሰቦች ጋር በመምጣት ቤቱን ለነዚህ ግለሰቦች ስለሸጥኩላቸው እንድትለቁላቸው ሲል አሳስቧል:; ቤቱን ገዛሁት የሚለው ትግሪኛ ተናጋሪ ግለሰብ ቤቱን የገዛሁት ስለሆነ በአስቸኳይ እንድትለቁ ካልሆነ የራሴን እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አመራሮቹ ላይ ዝቷል::

ይህ ገዛሁት የሚለው ግለሰብ በማይመለከተው ጉዳይ በመግባት ከዚህ በፊት ልቀቁ ተብላችሁ በተደጋጋሚ እንደተነገራችሁ መረጃው አለኝ በማለት በአመራሮቹ ላይ ቁጣ የተቀላቀለበት ዛቻ በመዛት ሄዷል:; በወቅቱ ይዞት የነበረው ተሽከርካሪ ጥቁር የደህነንት መኪና የሆነች ቶዮታ ኤክስኪዩቲቭ ሲሆን የታርጋ ቁጥሩም ኮድ 2-89176 የሆነ ነው::

ሰማያዊ ፓርቲ ከዚህ ቀደም በመነን አከባቢ ተከራይቶት የነበረውን ጽ/ቤት ገና ሳይገባበት በዝግጅት ላይ እንዳለ የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ፖለኢሶች እና ቅጥረኞች ተባብረው በተቀናጀ አፈና ቢሮውን መንጠቃቸው ይታወቃል:: የነጠቁትንም ቢሮ ለካድሬያቸው በመስጠት ፔንሲዎን ከፍቶ እየሰራበት ይገኛል:: Minilik salsawi

Image

በእስር ከሚገኙ የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የተሰጠ መግለጫ
ሰኞ ታህሳስ 14/2006
Image
ኢትዮጵያ ከአንድ ሺህ አራት መቶ አመታት በፊት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ማህበረሰብ ካሰፈነው ፍትህ የላቀ ፍትህ ማስፈን ችላ ነበር። የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉስ በነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) አንደበት ‹‹በሐበሻ አንድም ሰው የማይበደልበት ንጉስ አለ›› ተብሎለታል። እንዲህ አይነት ፍትህ በዚህ መልኩ ለማስፈን ምን ያህል ፍትሀዊ፣ እውነተኛ እና የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት እንደሚጠይቅ ግልፅ ነው። በሀገራችን የነበረው ፍትህ በጊዜው ነፃነት እና ፍትህ ፍለጋ ይዋትቱ የነበሩትን ማስጠለል የቻለ እና ዘመናትን ተሻጋሪ ነበር። ግና የዛሬው አሳዛኝ እውነታ ‹‹ሰዎች ስለ ፍትህ ግንዛቤ ባልነበራቸው በዚያ ዘመን የፍትህ ጥግ የደረሰችው አገራችን ሰዎች ሁሉ ወደ ዲሞክራሲ እና ፍትህ ፊታቸውን ሲያዞሩ ለምን ጀርባዋን ሰጠች?›› ብለን እንድንጠይቅ አስገዳጅ ሆኗል።

ፍትህ ዘመን፣ ቦታና ሁኔታ የማይገድበው፣ በሃይማኖት፣ በሃገርና በብሔር ልዩነት የማይደረግበት፣ ሁሉም ለሁሉም እውን ሊያደርገው መጣር ያለበትና ሰው የመሆናችን ሚስጥር የሚፈታበት ጥልቅ እውነታ ነው። ግና ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ህጎች ፍትህን ቢደግፉትም ቅሉ በተጨባጩ ዓለም ግፍና በደል ተንሰራፍቶ ይገኛል። ቀደም ሲል አምባገነኖች በአደባባይ ይፈፅሙት የነበረውን ግፍ በዘመናችን ቅርፁን ቀይረው ፍትህ፣ ነፃነት እና እኩልነትን እየሰበኩ በተግባር ግን የህዝባቸውን ኑሮ የስቃይ ያደርጉታል።

መንግስት በሚዲያና በየስብሰባው ስለፍትህና ዴሞክራሲ በተደጋጋሚ ቢያነሳም መሬት ላይ ያለው ተጨበጭ ፍፁም ለማመን አዳጋች ነው፡፡ በማንኛውም ዘመን አምባገነኖች እንደሚያደርጉት ሁሉ ሰብዓዊነት የጐደለው ኢ-ፍትሃዊ ተግባር እየፈጸመ ሳለ ‹‹ህዝቡ ቦታ የሚሰጣቸው ሥነ-ምግባሮች፣ ህግጋትና መልካም እሴቶችን ለማስጠበቅ›› ሲባል የተሰራ እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። በመብት ትግላችን ሂደት ለሃይማኖታቸው ታማኝ በመሆን የፍትህና የነፃነት ጥያቄ ያነሱ ወገኖቻችን ሁሉ በመንግስት አካላት ስደት፣ እስራትና ሞት የደረሰባቸው ህብረተሰቡ የሚያከብራቸውን ስነ-ምግባሮች፣ እሴቶችና ህግጋት ሽፋን በማድረግ መሆኑ በእርግጥም ምጸት ነው።

ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳቸውና በወከላቸው ኮሚቴዎች አማካኝነት ለመንግስት ያቀረባቸው ጥያቄዎች ግልጽ፣ ቀላል፣ ሃይማኖታዊና ህገ-መንግስታዊ መብቶች መሆናቸውን መላው ኢትዮጵያዊና ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ያውቀዋል። መንግስት ግን ለሰው እምነት ከባለቤቱ በላይ ተቆርቋሪ፣ ለሃገር ደህንነትና ሰላም የሚያስብ ብቸኛ አካል እና ህገ-መንግስቱን አክባሪና አስከባሪ እንደሆነ በመደስኮር የመብት ጥያቄያችንን የሀሰት ቅርፅ ሊያስይዘው ሞክሯል። በመሰረቱ መንግስት ኃይልና ጉልበት ያለው አካል ሆኖ ሳለ በተቃራኒው ደግሞ ህዝብ ጉልበት ስለሌለው ሰላምንና ደህንነትን አጥብቆ የሚፈልገው ከመንግስት በላይ ህዝብ ነው። ህገ-መንግስት ደግሞ መንግስት ያለውን ኃይል በመጠቀም ህዝብ ላይ ግፍ እንዳይፈፅም የሚገድብ ህግ እንደመሆኑ በመንግስት እንጂ በህዝብ ሊጣስ አይችልም።

ከጅምሩ መንግስት የሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ከጀርባው ምንም ሴራ እንደሌለው የሚያውቅ መሆኑን ብንረዳም በአባላቱም ሆነ በማህበረሰቡ ላይ ብዥታ እንዳይፈጥር ዓላማችንን እና ጥያቄዎቻችንን ለሁሉም ግልፅ አድርገናል። ይህም ሆኖ ግን በተለያዩ ብሄሮችና ሃይማኖቶች መካከል መከባበር እንዲኖር የማድረግ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለበት መንግስት ሙስሊሙን እርስ በእርስ፣ እንዲሁም ሙስሊሙን እና የሌላ ሀይማኖት ተከታዩን ህብረተሰብ ለግጭት የሚዳርጉ ተግባራትን ሲፈጽም ቆይቷል። አሁንም እያደረገ ይገኛል። ይህ አደገኛ አካሄድ ሊከሽፍ የቻለው በህዝባችን ብስለት እና ጨዋነት ብቻ ነው። ኩሩው የኢትዮጵያ ህዝብ ከህዝበ ሙስሊሙ የመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ የመረጠው በሳል አካሄድ ሊመሰገን የሚገባው ነበር። ይህ በሳል የህዝብ ምላሽ ሙስሊሙን እና ክርስቲያኑን ሊያጋጭ ይችል የነበረውን የመንግስት እንቅስቃሴ ቀልብሶ የህዝባችንን ጨዋነት፣ ተከባብሮ የመኖር ብቃት እና አስተዋይነት ዳግም ማሳየት ችሏል። ክስተቱም በታሪክ መዝገብ ውስጥ በወርቃማ ጽሁፍ የሚሰፍርበትና ለትውልድ የሚተረክበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የፈጸማቸው በደሎች በህዝቡ ብስለት የከሸፉ ቢሆኑም ለህዝቡ ደንታ የሌለውና ስህተቱን አምኖ መቀበልን ውርደት አድርጐ የሚቆጥረው መንግስት ግን ህዝብ እየተቃወመው ህገወጥነቱን ቀጥሎበታል። በዚህም ምክንያት ‹‹መንግስት በሀይማኖታችን ጣልቃ አይግባብን! ያልመረጥናቸው ህገ-ወጥ የመጅሊስ አመራሮች ወርደው ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄድ! የማናምንበት እምነት በግድ አይጫንብን!›› ብሎ የጠየቀውን ህዝብ ከነወኪሎቹ ለእስር፣ ለስደት፣ ለእንግልት እና ለሞት ዳርጓል።

የኢፌደሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 17 ንዑስ አንቀጽ 2 ‹‹ማንኛውም ሰው በህግ ከተደነገገው ስርዓት ውጪ ሊያዝ፣ ክስ ሳይቀርብበት ወይም ሳይፈረድበት ሊታሰር አይችልም›› ይላል። ነገር ግን ለፀጥታ ተግባር የተሰማሩት አካላት ህጉን በመጣስ ሰላማዊ ግለሰቦችን ሲይዙ የታጠቀ የጠላት ኃይል ላይ እንኳ ሊፈፀም የማይገባውን ግፍ፣ ድብደባ፣ ወከባ እና ስቃይ ይፈፅማሉ። ከፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ ሳያገኙና ለባለቤቱ ሳይሰጡ ያስራሉ። ህግ ጥሰው ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት በኋላ የግለሰቦች ቤት ላይ ብርበራ ያካሂዳሉ። በብርበራው ወቅት በሚፈጥሩት ሁከት በቤተሰብ ላይ ከፍተኛ ስጋት እና ድንጋጤ ይፈጥራሉ። ይህ ሁሉ የሚካሄደው ህዝቡ በፍርሃት ከመብት ጥያቄው ወደ ኋላ እንዲል ቢሆንም ውክቢያውና እንግልቱ ግን የመብት ጥያቄው ይበልጥ እንዲፋፋም፣ ህዝቡ ፍርሃቱ ለቅቆት ለነፃነት የሚከፈል መስዋዕትነት ያለውን ልዩ ጣዕም እንዲያጣጥም እና ሙሉ መብቱን ወደ መጠየቅ እንዲሸጋገር ነው ያደረገው።

የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 18 ንዑስ አንቀፅ 1 ‹‹ማንኛውም ጭካኔ ከተሞላበት፣ ኢሰብዓዊ ከሆነ ወይም ክብርን ከሚያዋርድ አያያዝ ወይም ቅጣት የመጠበቅ መብት አለው›› ይላል። ህገ-መንግስቱ ይህን ቢልም ዜጐች መሆናችንን ጥርጣሬ ውስጥ በሚከት መልኩ ከያዙን በኋላ በማእከላዊ በክረምት ቀርቶ በበጋ እንኳን ቅዝቃዜው በማይቻለው ‹‹ሳይቤሪያ›› ተብሎ በሚጠራው ጨለማ ክፍል ለ3 ወራት አጉረውናል። መቋቋም የሚያዳግተውን የማሰቃያ ስልታቸውን በመጠቀም ያላሰብነውንና ያልሰራነውን ‹‹እመኑ! ተናገሩ! ፈርሙ!›› ብለው አስገድደውናል።

ለቀጠሮ ፍርድ ቤት ስንቀርብ የደረሰብንን ሰቃይ አሳይተን ቢያንስ ፍርድ ቤቱ ስቃዩን እንዲያስቆምልን ጠይቀን ነበር። ያገኘነው ውጤት ግን ወደ ማዕከላዊ ስንመለስ ከመርማሪዎቹ በቀልና ተጨማሪ ስቃይ ነበር። ፍርድ ቤቱ የደረሰብንን ስቃይና የተከሰስንበትን ጉዳይ አግባብ እንዳልሆነ አይቶ ዋስትና ሰጥቶን ሳለ ፖሊስ የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ጥሶ ዋስትናውን በመከልከል ክስ መስርቶብናል። አሰቃዮቻችን ስለ ህገ-መንግስት እና መብት ስንናገር ‹‹ህገ-መንግስቱን ቀደህ ጣለው!›› እና ‹‹እኛ መሰዋዕትነት ከፍለን ነው እዚህ የመጣነው!›› ወ.ዘ.ተ በማለት ለህግም ሆነ ለሰው ክብር ደንታ እንደሌላቸው አሳይተውናል። ይህ ሁሉ መከራ በተቃራኒው ህገ-መንግስቱን ለማስከበር መታገል የሚያስፈልግበት ትክክለኛ ወቅት ላይ መሆናችን እንዲሰማን፣ እውነተኛ ፅናትና ወኔ እንዲኖረንም አድርጎናል።

በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 19 ንዑስ አንቀጽ 5 ‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችል የእምነት ቃል እንዲሰጡ፣ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም። በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነት የለውም›› የሚለውን ድንጋጌ መሠረት በማድረግ እዚያው ማዕከላዊ የምርመራ እስር ቤት እያለን የደረሰብንን ስቃይና እንግልት ገልፀን ክስ አቅርበን ነበር። በምርመራ ጣቢያው ቃላችንን የሰጠነውም ሆነ የፈረምነው ተገደን መሆኑን ገልፀን ውድቅ እንዲደረግ ጠይቀናል። ሆኖም ግን ክሳችን ተዳፍኖ እና ተድበስብሶ እንዲቀር በመደረጉ በጊዜው ምላሽ ሳናገኝ ቀርተናል። ክስ ተመስርቶብን ወደ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርበን በኋላም በድጋሚ ጉዳዩን ያስረዳን ሲሆን አሁንም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ሙሉ ለሙሉ የሚያደምጥበትንና ምላሽ የሚሰጥበትን ቀን እየተጠባበቅን እንገኛለን።

ከቤተሰብ፣ ከጠበቃና ከሀኪም ጋር እንዳንገናኝ አድርገው የፈፀሙብን የህግ-ጥሰት እና አስገድደው በማስፈረም እና ድምፅና ምስላችንን በመቅረፅ የፈፀሙብን በደል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 424 መሰረት እስከ አስር አመት የሚያስቀጣ ኢ-ሰብዓዊ ተግባር ነው። ነገር ግን የፖሊሱም፣ የዐቃቤ ህጉም፣ የፍርድ ቤቱም አለቃ በሆነውና የፍትህ ስርዓቱን ሰብስቦ በያዘው ገዚው ፓርቲ አምባገነንነት በተቃራኒው እኛ ተከሳሾች ሆነን ጉዳያችን ‹‹በፍርድ ቤት›› በመታየት ላይ ይገኛል።

በማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ስቃይ አድርሰውብናል። ከአስራ አራት ሰዓታት በላይ ያለ እረፍት ቀጥ ብለን እንድንቆም በማድረግ፣ ጀርባችን ሰንበር እስኪያወጣ እና እስኪገሸለጥ ራቁታችንን በሽቦ በመግረፍ፣ በሰንሰለት በማሰር እና ዓይናችንን በጨርቅ በመሸፈን የውስጥ እግራችን እስከሚላጥ ገልብጦ በመግረፍ፣ ቀንና ማታ አሰቃቂ በሆነ ምርመራ እና ድብደባ እንቅልፍ በመንሳት፣ ሃይማኖታችንንና ክብራችንን በመንካት፣ ፂማችንን በመንጨትና እንድንላጭ በማስገደድ፣ እንዲሁም ሰላት በመከልከል፣ ቤተሰብ፣ ጠበቃ፣ ሀኪምና የሃይማኖት አባት እንዳናገኝ በማድረግ፣ ከአቅም በላይ የሆነን ስፖርት በግድ በማሰራት፣ ብልት በመግረፍ፣ ‹‹ልጅህን እንገለዋለን! ሚስትህን አስረን በፊትህ ቶርች እናደርጋታለን! ብልትህ ላይ ሀይላንድ በማንጠልጠል መሀን እናደርግሃለን!›› ሲሉ በማስፈራራት ከፍተኛ የሆነ እንግልትና ስቃይ አድርሰውብናል።

ይህም አልበቃ ብሏቸው በሃገሪቱ የቅጣት ጣሪያ የመጨረሻ የሆነውን የወንጀል አንቀፅ ጠቅሰው ከሰሱን። ‹‹ህገ-መንግስት ይከበር!›› ብለን በጠየቅን ህገ-መንግስትን ለመናድ በመንቀሳቀስ ወነጀሉን። ተቃውሟችን ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ሳለ ‹‹ከእኛ ውጪ ያሉ እምነቶች ከሃገሪቱ መጥፋት አለባቸው ብለዋል›› ሲሉ ከሰሱን። ሃይማኖታዊ የመብት ጥያቄያችንን ‹‹ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ ነው›› በሚል ሊያጠለሹ ሞከሩ። ‹‹ህዝብ ያልመረጣቸው የመጅሊስ አመራሮች በህገ-ወጥ መንገድ መጥተው አይመሩንም! ፍትሀዊ ምርጫ ይካሄድ!›› ባልናቸው ‹‹መንግስት ይውረድ! መንግስት አያስተዳድረንም! ብለዋል›› በሚል ወነጀሉን።

ያዘጋጁት ክስ የህግ ባለሙያ ቀርቶ ማንም የህግ ግንዛቤ የሌለው ሰው በሚረዳው ደረጃ በህግ ስህተቶችና አመክኖአዊነት በጐደላቸው ሃሳቦች የተሞላ፣ በህግ ወንጀል ያልሆኑ አረፍተ ነገሮች እና ቃላት ወንጀል ተደርገው የተጠቀሱበት ፍፁም ተራ እና የሃገሪቷን የፍትህ ሁኔታ የሚያስገምት ክስ ነው። ምንም እንኳን ‹‹ክሱን ዳኞች ስርዓት ሊያስይዙት ይገባል›› በሚል የፀረ-ሽብር አዋጁን በመቃወም እና ክሱ ላይ ያሉ ስህተቶችን ሁሉ ነቅሰን በማውጣት የክስ መቃወሚያ ያቀረብን ቢሆንም የዳኞች ብይን ክሱን ይበልጥ የማይገባና ውስብስብ አደርጎታል።

ከታሰርን ጀምሮ የደረሱብን የህግ ጥሰቶች እና የፍትህ እጦቱ ከፍርድ ቤት ሂደት ራሳችንን ሙሉ ለሙሉ እንድናገል የሚገፉ ነበሩ። ሆኖም ግን የተወነጀልንበት ክስ ምን ያህል ከእውነት የራቀ፣ ጥያቄያችን ሃይማኖታዊ እና ህገ መንግስታዊ መሆኑን እና እንቅስቃሴያችንም ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር ለህዝባችን በፍትህ አደባባይም ጭምር ለማሳየት ስንል የፍርድ ሂደቱ ውስጥ መግባቱ የተሻለ መሆኑን በማሰብ ሃሳባችንን ቀይረናል።

መንግስት በአግባቡ ሊተውነው ያልቻለውን አሳፋሪ የፍርድ ቤት ድራማውን ህዝብ እንዳያይበት ለመሸሸግ በመገደዱ ‹‹የተከሰሱ ሰዎች ክስ ከቀረበባቸው በኋላ ተገቢ በሆነ አጭር ጊዜ ውስጥ በመደበኛ ፍርድ ቤት ለህዝብ ግልፅ በሆነ ችሎት የመስማት መብት አላቸው›› የሚለውን ህገ-መንግስታዊ መብት በመጣስ ችሎቱ ዝግ እንዲሆን ተደርጎ ቆይቷል። በዝግ ችሎቱ የምስክር መስሚያ ጊዜ ብዙ አስገራሚ ድራማዎችን አይተናል። ዓቃቤ ህጎች ዳኞች የሚሰጡትን ብይን እንደማይቀበሉ እስከመግለጽ የደረሱበትን እና ምስክሮችን ማለት ያለባቸውን አሰልጥነዋቸው እንደሚያመጡ አምልጧቸው የተናገሩበትን አጋጣሚ ታዝበናል። በወቅቱ ‹‹ጋዜጠኞች፤ ዲፕሎማቶች እና ህዝባችን ምነው ይህንን አይተው በነበር?›› ብለን ከመመኘት ውጭ ምርጫ አልነበረንም።

ማንኛውም ታራሚም ሆነ ተጠርጣሪ በማረሚያ ቤት ሊያገኛቸው የሚገቡ በህግ የተደነገጉ መብቶች አሉ። መብቶች ግን እንደተለመደው ከወረቀት ዘለው መሬት ጠብ ማለት አልቻሉም። የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ላይ ሲሆን ደግሞ መብቶች በቅጣት ይተካሉ። ካለው የጋራ ችግር በተጨማሪ በእኛ ላይ በተለየ መልኩ በጥላቻ እና በበቀል ስሜት የደረሰብን እንግልት ህሊና ያለውን ሁሉ የሚጎዳ ነው። ከቤተሰቦቻችን መካከል ከጥቂቶች ጋር በስተቀር እንዳንገናኝ ተደርጓል። የምንጠየቅበትንም ሰዓት ከእስረኞች ሁሉ በመለየት በቀን ለሃያ ደቂቃ ብቻ እንዲሆን በማድረግ አድሎ እና መገለል ተፈፅሞብናል። በመካከላችን ልጆቹና ቤተሰቦቹ እንዳይጠይቁት የተደረገም አለ። ከሁሉም በላይ ከባድ ህመም ያለባቸው፤ ሆስፒታል ሄደው እንዲታከሙ የታዘዘላቸው፤ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላቸው የተመራላቸው እና በማእከላዊ የደረሰባቸውን ድብደባ ለመታከም የጠየቁ ለዓመት ከአራት ወር በላይ መፍትሄ ሳያገኙ ስቃዩን ይዘው ‹‹የፍትህ ያለህ!›› እያሉ ይገኛሉ። ማረሚያ ቤት የደረሱብን እና እየደረሱብን ያሉ አድሎዎችንና እንግልቶችን ሁሉ ዘርዝረን ጉዳያችንን ለሚመለከተው ፍርድ ቤት ብናቀርብም የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ፍርድ ቤት እንኳ ለመቅረብ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ሶስት ጊዜ ቀጠሮ አሳልፈዋል።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴውን ከጀመረ በኋላ መንግስት በነጋዴውና በተማሪው፣ በመንግስት መዋቅር ውሰጥ በሚሰሩ አካላት፣ በሃይማኖት አባቶች እና በአስተማሪዎች፣ እንዲሁም በኢስላማዊ ተቋማት ላይ ሰብዓዊነት የጎደለው እና ህገ-መንግስቱን የሚጻረር የመብት ጥሰት መፈጸሙን ቀጥሎበታል። በበርካታ የክልል ከተሞችና ሙስሊሙ ደስታውን በሚገልጽበት የዒድ ዕለት በአዲስ አበባ ፈጽሞ ልንረሳው የማንችለውና ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ፈጽሞብናል። የምንሳሳላቸው እና የምንወዳቸው ወገኖቻችንን እና ቤተሰቦቻችንን ለእስር፣ ለሞትና ለአካል ጉዳተኝነት ዳርጎብናል። ይህ ሁሉ ስቃይ እና መከራ በአንድ በኩል የመንግስትን ግፍ እና ለህግ ተገዢ አለመሆን ሲያጋልጥ በሌላ በኩል የህዝባችንን ፅናት እና ቁርጠኝነት አሳይቶናል። በየትኛውም ሃይማኖት፣ ባህል እና ልማድ ግፍ የተጠላ ሲሆን ለመብት ሲሉ መሰዋት ደግሞ ክብር ነው። ስለዚህ ለሃይማኖታችሁ፣ ለክብራችሁ እና ለደህንነታችሁ ለተሰደዳችሁ፣ ለታሰራችሁ፣ ለተደበደባችሁ እና ቤተሰቦቻችሁን ላጣችሁ ሁሉ ያለንን ክብር እንገልጻለን፤ በሀገራችን ለሚሰፍነው የሃይማኖቶች ነፃነት እና እኩልነት የመሰረት ድንጋይ የሚሆነው ዛሬ እናንተ የከፈላችሁት መስዋእትነት ነውና!

ለሁለት ዓመታት ያለ ምንም መሰላቸት እንግልቱ፣ ማስፈራሪያው፣ እስሩ፣ ድበደባው እና ግድያው ሳይበግራቸው እና ሰላማዊውን የተቃውሞ መስመር ሳይለቁ ለሃይማኖታቸው ያላቸውን ፍቅር ላሳዩ፣ እንዲሁም ይህን ድንቅ ታሪክ ለሰሩ አባቶች፣ የሃይማኖት መሪዎችና አስተማሪዎች /በተለይ ደግሞ ወጣቶች እና ሴቶች/ ያለንን ከፍ ያለ ክብር እና ምስጋና ልናቀርብ እንወዳለን። በሰራችሁት ሁሉ ተደስተናል፤ ኮርተንባችኋልም!

መንግስት የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር ያደረገውን ሙከራ ንቆ በመተውና ጉዳዩን በብስለትና በሰከነ መንፈስ በማየት፣ እንዲሁም እውነታውን ለመረዳት ጥረት በማድረግ ረገድ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ በተለይም ህዝበ ክርስትያኑ ላደረጋችሁት ትብብር ሳናመሰግን አናልፍም። በእውነቱ የሃይማኖት ልዩነት ሳያግደን በህዝብ ደረጃ ተከባብረን ስለመኖራችን ከተነሱ ምሳሌዎች ሁሉ በዚህ ሁለት ዓመት ውስጥ ያሳየነው መከባበር እና አንድነት ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ነው። ይህ ብሄራዊ አንድነት የበለጠ ተጠናክሮ በጋራ ለምንገነባት ሃገራችን ታላቅ ብርታት እንደሚሆን ጠንካራ እምነት አለን።

በተጨማሪም የፕሬስ ነፃነት በተነፈገበት ተጨባጭ የመብት ጥያቄያችንን እውነታ ለመገንዘብ ማስፈራሪያዎችን እና ዛቻዎችን አልፋችሁ፣ የመንግስትን የተሳሳተ እና ኢ-ህገመንግስታዊ አካሄድ ለይታችሁ ሂደታችን ላይ አዎንታዊ አስተያየቶች እና ገንቢ ትችቶችን ለሰጣችሁ ጋዜጠኞችና በሚዲያው ዘርፍ ለተሰማራችሁ ባለሙያዎች ሁሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ወገኖቻችሁ ያጡትን ፍትህ እና ነጻነት በሃገራችሁ ለማየት በመጓጓት የበኩላችሁን አስተዋጽኦ ለማበርከት የምትጣጣሩ በስደት የምትገኙ ሙስሊሞችና የሌሎች ሀይማኖቶች ተከታይ ወገኖቻችን በሙሉ ላደረጋችሁት ሁሉ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው። በሀገር ውስጥ ለተጠናከረው የአጋርነት ስሜት የእናንተ አስተዋጽኦ የመጀመሪያውን ድርሻ ይይዛል።

በአጠቃላይ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ነጋዴው፣ አርሶ አደሩ፣ አርብቶ አደሩ፣ ተማሪው፣ ሴቱ፣ ወንዱ፣ ወጣቱ፣ አዛውንቱና ሌላውም፣ እንዲሁም በመንግስት መዋቅር ስር ሆናችሁ የመንግስትን የተሳሳተ አካሄድ ስትቃወሙ የነበራችሁ ዳኞች፣ ዓቃቤ ህጎች፣ አባቶች፣ ፖሊሶች፣ የጦር ሰራዊትና የፓርላማ አባላት በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርብላችኋለን። የጥረታችሁን ፍሬ በቅርቡ ያሳያችሁ ዘንድም አላህን እንለምናለን!

መልእክታችን

1/ በሙስሊሞች መካከል እና በሙስሊሙና በክርስትያኑ መካከል የታየውን አንድነትና መከባበር ሁላችንም በጋራ እንድንጠብቀው፣ እንዲሁም መሰረቱ የፀና ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ እንድንጥር አደራ እንላለን። ሀገራችን ከእርስ በእርስ ሽኩቻዎች ወጥታ የእድገትና ብልጽግና ጉዞ እንድትጀምር ከተፈለገ ትክክለኛ የሃይማኖት ነፃነት፣ እኩልነት እና መከባበር በቅድሚያ እውን መሆኑ አማራጭ የሌለው ግዴታ ነው። የሃገራችንን እድገት የጋራ አላማ አድርገን፣ የጋራ ተጠቃሚ ሆነን መኖር የምንችለው ስጋትና ጥርጣሬውን በፍቅርና መተማመን ስንተካው ነው።

2/ በፅናት ሰላማዊ የመብት ትግሉን የምንቀጥል መሆኑንና የሚያስከፍለንን መስዋዕእትነት ሁሉ ለመክፈልም ዝግጁ መሆናችንን ለህዝባችንም ሆነ ለመንግስት መልእክት ለማስተላለፍ እንወዳለን። ለቀጣዩ ሰላማዊ የመብት ትግል እርከንም እኛም ህዝባችንም በሙሉ ዝግጅት ላይ መሆናችንንና ለመብታችን ተግተን ሰርተን መስዋዕት ከመሆን ወደኋላ የማንል መሆኑን ስንገልጽ በከፍተኛ ወኔ ተሞልተን ነው!

3/ መንግስት እየፈጸማቸው ያላቸውን ኢ-ህገ መንግስታዊ ተግባራት፣ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ እየፈጸመ ያለውን እስራት፣ ግፍ፣ መስጂድ ነጠቃ፣ የሀሰት ውንጀላና የሃይማኖት ሰዎችን፣ ጋዜጠኞችንና የመብት ጠያቂዎችን በሽብርተኝነት መፈረጅና መሰል ህገ መንግስታዊ የመብት ጥሰቶችን በአስቸኳይ እንዲያቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን። በማእከላዊና በተለያዩ እስር ቤቶች የሚፈጸሙት ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች እንዲቆሙና የህሊና እስረኞችም መለቀቅ እንደሚገባቸው ለመግለጽ እንወዳለን። መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእውነተኛ ሰላም፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲ እና ልማት ባለቤት ሆኖ ማየት የዘወትር ህልማችን መሆኑንም ሳንገልጽ አናልፍም፡፡

በመጨረሻም በቃል ኪዳናችን ጸንተንና መነሻው ላይ ከነበረው በተሻለ ሁኔታ ተንቀሳቅሰን ፍጹም በሰለጠነና በተጠና መልኩ የተሟላ ፍትህ እና ነፃነት ለማግኘት በጽናት እና በቆራጥነት ሁሉም ባለድርሻ አካል እንቅስቃሴውን ከዳር እንዲያደርስ አደራ ለማለት እንወዳለን። የእንቅስቃሴው ማብቂያ ድልና ስኬት እንደሚሆን አንጠራጠርም!

አላሁ አክበር!

ግልባጭ፡- እዚሁ አገር ውስጥ እና በውጭ አገራት ለሚገኙ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች

Image

በድህረ-መለስ ኢትዮጵያ የፖለቲካው ሥልጣን በስርዓቱ ልሂቃን መካከል ከሚደረገው የኃይል መተናነቅ አንጻር፣ ዛሬም ከመፈራረቅ ጣጣው የተላቀቀ የማይመስልባቸው ምልክቶች መታየታቸው እንደቀጠለ ነው፡፡ ከአራት ወር በፊት በዚህ መፅሄት ላይ ‹‹አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ›› በሚል ባቀረብኩት ፅሁፍ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ተፈጥሮ ከነበረው ክፍፍል የትኛው ቡድን የበለጠ ጉልበት አግኝቶ በአሸናፊነት መውጣት እንደቻለ ከገለፅኩ በኋላ ፅሁፉን የቋጨሁት እንዲህ በማለት ነበር፡- ‹‹የፓርቲው የታሪክ ድርሳን እንደሚነግረን ‹ይሆናሉ› የተባሉት ተቀልብሰው፣ ባልተጠበቁ ሁነቶች (የኃይል መገለባበጥ ተከስቶ) ፖለቲካው የሚመራበት አጋጣሚ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደሚችልም መዘንጋት አያስፈልግም፡፡››
እነሆ በዚህ ፅሁፍ ደግሞ በቅርቡ በተጨባጭ የታዩትን አዳዲስ ኩነቶች እና ይህንኑ ተከትለው ሊመጡ ይችላሉ ብዬ የምገምታቸውን ‹የቢሆን ዕድሎች› (Scenarios) ለማየት እሞክራለሁ፡፡
ሰላም የራቀው-ኢህአዴግ
በግንባሩ አባል ድርጅቶች መካከል ዛሬም ድረስ ሙሉ በሙሉ የተረጋጋ ፖለቲካ አልሰፈነም፤ የዚህ ዋነኛ ምክንያቱ ደግሞ፣ ቁልፍ የሥልጣን ቦታዎችን ጠቅልሎ ይዞ በነበረው በቀድሞ ሊቀ-መንበሩ ህልፈት ሳቢያ የተፈጠረው የአመራር ክፍተት እና እርሱን ሊተካ የሚችል መሪ ማግኘት ባለመቻሉ ይመስለኛል፡፡ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችም በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ከሕግ ይልቅ የጠመንጃ ኃይልና የግለሰብ አምባገነናዊነት በገነነበት ሀገር ‹የማይገመቱ ክስተቶች› (Unpredictable Event) ማምጣታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡

የሆነው ሆኖ በዚህ አጀንዳ ለመመልከት የምሞክረው ጉዳይ፣ በአሁኑ ጊዜ ሀገር እየመራ ያለው ኃይል ለሁለት የተከፈለ ቢሆንም፣ በአንፃራዊነት በጥምር የሚሰራ መሆኑን በማስረገጥ ነው፡፡ የእነዚህ ሁለት ቡድኖች የጉልበት ምንጭም የታጠቀውን ኃይል በመቆጣጠር እና የፖለቲካውን ሥልጣን በመያዝ ላይ የተመሰረተ ነው፤ ይኸውም ሠራዊቱ እና የደህንነት መስሪያ ቤቱ ሙሉ በሙሉ በህወሓት ሰዎች ሲንቀሳቀሱ፣ ፖለቲካውን ደግሞ የብአዴን መሪዎች፣ ከተወሰኑ የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት ጋር ተባብረው መያዛቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸው ነው፡፡
የህወሓት ኃይል
ህወሓት የቀድሞው ፍፁማዊ የበላይነቱን ለመመለስ ዋና ችግር የሆነበት በውስጡ ለተፈጠረው መከፋፈል እስካሁን መፍትሄው ተለይቶ አለመታወቁ ነው፤ ከዚህ ቀደም በዚሁ መፅሄት፣ አንዱ ኃይል የተሻለ ጉልበት በማግኘቱ ሌላኛውን (እነአዜብ መስፍንን ጨምሮ አባይ ወልዱና ቴዎድሮስ ሀጎስን የመሳሰሉ ከፍተኛ ካድሬዎች የተሰባሰቡበትን) በመብለጥ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንቅስቃሴያቸውን መገደቡ ተሳክቶለት እንደነበረ ማስነበቤ ይታወሳል፡፡ ይህ ክፍፍል ምንም እንኳ እንደ 1993ቱ ከፓርቲ እስከ ማስወጣት የሚደርስ አለመሆኑ ቢታወቅም፣ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ጌታቸው አሰፋ የተሰለፉበት ቡድን ተፅእኖ ፈጣሪ ሆኖ መውጣት ችሏል፤ ይህም ሆኖ ውስጥ ውስጡን የሚገመደው ተንኮልም ሆነ ሽኩቻ ገና መቋጫ አለማግኘቱ ግልፅ ነው፡፡
በዚህ ፅሁፍ ጠመንጃ የታጠቀውን ክፍል ‹የህወሓት ኃይል› እያልኩ የምገልፀበት ዓብይ ምክንያት፣ በጄነራል ሳሞራ የኑስ ኤታ ማዦር ሹምነት የሚመራው የመከላከያ ሠራዊት እና በማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ጌታቸው አሰፋ ስር ያለው የደህንነት ኃይል ለሚደግፉት ቡድን መጠናከር እያበረከቱት ያለውን አስተዋፅኦ ከግምት በመክተት ነው፡፡ ሁለቱም ሰዎች ለመለስ ፍፁም ታማኝ የነበሩ ቢሆንም፣ ከህልፈቱ በኋላ እንደእርሱ ተጭኖ ሊቆጣጠራቸው የሚችል ጉልበታም ህወሓትን ጨምሮ በሁሉም የግንባሩ አባል ፓርቲ ውስጥ አለመኖሩ፣ በፖለቲካው ‹ቼዝ› የ‹ዘመነ መሳፍንቱ›ን ሚካኤል ስሁል አይነት ሚና እንዲጫወቱ አስችሏቸዋል፤ ሁለቱም ከስራቸው የነበሩትንና ‹ስልጣን ሊጋፉ ይችላሉ› ብለው የጠረጠሯቸውን ባልደረቦቻቸውን አስቀድሞ ገለል ማድረጉ ከሞላ ጎደል የተሳካላቸው ይመስለኛል፡፡
በተለይም ጌታቸው አሰፋ ከራሱ ወንበር አልፎ ከእነአዜብ መስፍንና አባይ ወልዱ ጋር በመተባበር አንድ ቀን በጠቅላላው የመንግስት የሥልጣን እርከን ላይ ‹ናቡቴ ሊሆን ይችላል› የሚል ስጋት ያሳደረበትን እና ‹መለስ ዜናዊ ሞት ባይቀድመው በእርሱ ቦታ ሊተካው ነበር› እየተባለ የሚነገርለትን የመረጃ ኃላፊ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና የሚወነጀልበትን መንገድ አመቻችቶ ለእስር ባይዳርገው ኖሮ ‹‹ለቁርስ ያሰቡንን…›› አይነት ታሪክ ራሱን መድገሙ አይቀሬ ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡
ጄነራል ሳሞራ የኑስ በበኩሉ ተቀናቃኙ አድርጎ ይመለከታቸው የነበረው ሶስቱ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ ወልደስላሴ ‹ፍንቀላ መሳይ ነገር ሊሞክሩ ይችላሉ› ተብለው አይደለም፡፡ የእነርሱ የመጀመሪያው ችግር ከወታደራዊ ዲሲፕሊን በማፈንገጥ አለቃቸውን አለማክበራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ሳሞራ ‹በየትኛውም ምክንያት ከኃላፊነቴ ብነሳ የቆየ ፋይል አገላብጠው አደጋ ላይ ሊጥሉኝ ይችላሉ› በሚል ስለሚጠረጥራቸው ነው፡፡ እነዚህ መኮንኖች የሰሜን ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል ሰዓረ መኮንን፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ መልካም ግንኙነታቸው እንደቀድሞው እንዳልሆነ የሚነገረው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌፍተናንት ጄነራል አበባው ታደሰ እና የአየር ኃይሉ አዛዥ ሜጀር ጄነራል ሞላ ኃይለማርያም ናቸው፡፡ እናም ሰዓረ እና አበባው በቀጥታ ሠራዊት ከሚያዙበት ቦታ ተነስተው በመከላከያ ሚኒስትር ውስጥ በቢሮ ስራ ላይ ሲመደቡ፣ ሞላም ከነበረበት ኃላፊነት አኳያ ብዙም ይመጥነዋል የማይባል የቢሮ ስራ ተሰጥቶታል፤ በእርሱም ቦታ ሜጀር ጄነራል አደም መሀመድ ተተክቷል፡፡ የሳሞራ እና የሞላ ልዩነት በመለስ ዘመንም በአደባባይ የሚታወቅ እንደነበረ ሰምቻለሁ፡፡

ለጉዳዩ ቅርብ ከሆነ የመረጃ ምንጬ እንዳረጋገጥኩት የአስተዳደር ዘይቤውን በማኪያቬሊያዊ አስተሳሰብ (ከፋፍለህ ግዛ) የሚያሳልጠው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ለሞላ ትዕዛዝ የሚሰጠውም ሆነ ማንኛውንም ጉዳይ በተመለከተ የሚያነጋግረው የዕዝ ተዋረዱን ጠብቆ በኤታ ማዦሩ በኩል ሳይሆን፣ በቀጥታ በመገናኘት መሆኑ፣ አየር ኃይሉን ከመከላከያ ሚኒስቴር የተገነጠለ አስመስሎት ነበር፤ ይህ ሁኔታም በሁለቱ መኮንኖች መካከል ያለው ግንኙነት የሥልጣን ተዋረድን የጠበቀ እንዳይሆን በማሰናከሉ በጄነራሉ ላይ ደፍሮ የማይናገረው ቅሬታ ሊያሳድርበት ችሏል፤ ከመለስ ህልፈት በኋላም ሳሞራ ሂደቱን ለማስተካከል መሞከሩ፣ በየግምገማው ላይ እስከ መዘላለፍ አድርሷቸው ነበር (በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ እንደ ጦር ኃይሎች አዛዥነቱ፣ ከጄነራሎቹ ጋር መደበኛ /Official/ በሆነ መንገድ ትውውቅ አላደረገም፤ እነዚህ ሶስት ጄነራሎችም ለዚህ አይነቱ የአሰራር መፋለስ ጥፋተኛ የሚያደርጉት አለቃቸውን ሳሞራ የኑስን ነው፤ ከምንጮቼ እንደሰማሁት ከሆነም ከወራት በፊት ኃይለማርያም ደሳለኝ በተገኘበት ‹ጎልፍ ክለብ› በሚባለው የጄነራሎቹ መዝናኛ በተዘጋጀ ፕሮግራም ማጠናቀቂያ ላይ ሳሞራ አንድ ጠረጴዛ ከበው ወደ
ተቀመጡት እነዚህ ጄነራሎች ጋ ሄዶ ‹ኑ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ላስተዋውቃችሁ› ማለቱን እና እነርሱም በጥያቄው ተበሳጭተው ቢሮ ያላቸው መሆኑን እና ክብራቸውን በሚመጥን መልኩ መተዋወቅ እንደነበረባቸው በኃይለ ቃል መመለሳቸውን ነው)

የሳሞራ የኑስ እና ሰዓረ መኮንን መነቋቆር ከትግሉ ዘመን ጀምሮ የመጣ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ሳሞራ ከማንም በላይ የሚፎካከረውም ሆነ መበለጥ የማይፈልገው በሟቹ ጄነራል ኃየሎም አርአያ እንደ ነበር የቀድሞ ጓዶቻቸው ያስታውሳሉ፤ ይህ ሁኔታ ዛሬም ድረስ በስራ ላይ ያሉ መኮንኖችን ‹የሳሞራ› ወይም ‹የኃየሎም ተከታይ› በማለት መከፋፈሉ በጓዶቻቸው እና በፓርቲው መሪዎች አካባቢ የሚታወቅ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለማዕረግ እድገት የተለየ የድጋፍ አስተያየት የሚያገኙት በዛን ዘመን ‹የሳሞራ ተከታይ› የሚባሉት እየተመረጡ እንደነበረ በወሬ ደረጃ ይናፈሳል (በነገራችን ላይ ጄነራል ሳሞራ ከጤንነት ጋር በተያያዘ በአጭር ጊዜ ውስጥ በጡረታ ይሰናበታል በተባለበት ጉዳይ ላይ እያንገራገረ እንደሆነ ከመከላከያ አካባቢ የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፤ እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው ደግሞ ‹ለእኔ በጎ አመለካከት የላቸውም› በሚል የሚጠራጠራቸው ጄነራሎች በሥራ ላይ እያሉ የእሱ ጡረታ መውጣት ከመስሪያ ቤቱ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ያደሩ የሙስና ካርዶች የሚመዘዙበትን ዕድል ያሰፋዋል የሚል ነው፤ በተለይም በግዙፍ የቢዝነስ ሥራዎች ላይ በታላቅ ተፎካካሪነት እየተሳተፈ የሚገኘው ‹መቴክ› ምንም እንኳ ማረጋገጫዎች ባይቀርቡበትም በመከላከያ ሥር ከነበረበት ዘመን እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ ከግዥዎች ጋር ተያይዘው የሚነሱ በርካታ የሙስና ሁኔታዎች በመኖራቸው ነው፡፡
መቴክ ካለፉት አራት ዓመታት ጀምሮ በአዋጅ የልማት ድርጅት እንዲሆን ቢደረግም፣ ዛሬም ዳይሬክተሩ የሠራዊቱ አባል ብርጋዴር ጄነራል ክንፈ ሲሆን፣ መከላከያ ደሞዝ የሚከፍላቸው ጥቂት የማይባሉ ሠራተኞችንም እንዳቀፈ ይታወቃል፡፡ እናም ሳሞራ ሃሳቡ ከተሳካለት ለጥቂት ተጨማሪ ዓመታት በሥልጣኑ ላይ ሲቀጥል፣ አሊያም ‹የወንድ በር› ለማግኘት በትግሉ ዘመን የእርሱ ሰልጣኝ እንደነበረ የሚነገርለትን እና በቅርቡ ብቸኛው ከሜጀር ወደ ሌፍተናት ጄነራል ማዕረግ ያደገው ዮሀንስ ገ/መስቀል እንዲተካው መንገድ ጠረጋውን ማመቻቸቱ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት ጉዳይ ይመስለኛል)

ይህም ሆኖ የተኮረኮርን ያህል የምንስቀው ጄነራል ሳሞራ የኑስ በቅርቡ ለታተመው ‹‹ህብረ ብሔር›› መፅሄት ሙስና ለሠራዊቱ አደገኛ መሆኑን እንዲህ በማለት መግለፁን ስናነብ ነው፡-
‹‹ሙስና ሠራዊቱን ሊያበላሸው ይችላል፡፡ ሙስና ፀረ-ልማት ነው፤ ሠራዊቱን ሊበትነው እና ሕዝባዊ ባህሪውን እንዲያጠፋ ሊያደርገው ይችላል፤ አንድ ሠራዊት ሠራዊት ነው የሚባለው እንደ ወታደር እንደ አንድ አካል ሲያስብ እንጂ ለግሉ ሲያስብ አይደለም፡፡ …በአጠቃላይ (ሠራዊቱ) በዚህ ነው የሚፈርሰው፡፡››
መቼም ጄነራሉ ይህንን የተናገረው እራሱን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ መኮንኖች እንደ እንግሊዝ ንጉሳውያን ቤተሰቦች በተንጣለለ ቪላ ቤት ውስጥ፣ የተቀማጠለ ኑሮ መኖራቸውን ረስቶት አይመስለኝም፤ ‹ይህ የተንዛዛ ወጪያቸውም የሚሸፈነው ከደሞዛቸው በሚያገኙት ገቢ ነው› ብሎ ቧልት መሳይ ክርክር ሊያመጣ አይችልም፡፡ ይሁንና እታች ያለው ጭቁን የኢትዮጵያ ሠራዊት ምንም እንኳ በአለቆቹ ‹ቴክሳስ›ነት ላይ ለመቆጣት ባይደፍርም፣ እንደማንኛውም ዜጋ ለኑሮ ውድነትና አስከፊ ድህነት የተጋለጠ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡
የሆነው ሆኖ ተሰሚነታቸው እየተቀዛቀዘ የመጣው አቦይ ስብሃት ነጋ ከወራት በፊት ለ‹‹ውራይና›› መፅሔት ‹‹ህወሓት ትንሳኤ ያስፈልገዋል›› በማለት የሰጡትን ምክር ተከትሎ፣ ጄነራል ሳሞራ እና አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ከድርጅቱ ምክትል ሊቀ-መንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ጋር በመተባበር ህወሓትን ለማጠናከር እና በፖለቲካ ውስጥ የነበረውን የአንበሳውን ድርሻ ለማስከበር (ጉዳዩን ከለጠጥነው ደግሞ ‹ለማስመለስ›) እየሰሩ እንደሆነ ይነገራል (በነገራችን ላይ የሳሞራና ጌታቸው ተፅእኖ መጨመሩን ለመረዳት፣ መከላከያ ‹አገራዊ ጥቅምንና ደህንነትን ለመከላከል› በሚል ‹እጅግ ጥብቅ ሚስጢር ብሎ የሰየማቸውን የሰው ኃይል ፕሮፋይል፣ የሒሳብ መዝገቦችና ሰነዶች እና የክፍያ ማስረጃዎች ለማንም አካል እንዳይገለፅ› የሚያስችለውን ስልጣን፣ ደህንነቱ ደግሞ በስራ ላይ የሚፈፅማቸው ማንኛውም ጉዳዮች ወደፊት በህግ እንዳይጠይቅ እስከ መከላከል የሚደርሰውን አዲስ የተዘጋጁትን አዋጆች ማንበቡ በቂ ነው፡፡ በርግጥ እነዚህ ባለሥልጣናት እንዲህ ባለ ተመሳሳይ መንገድ እንዲጓዙ ያስተሳሰራቸው አንዱ ጉዳይ ‹ህወሓት ተዳከመ፣ ተሸነፈ፣ አበቃለት…› የሚለው የካድሬውና ደጋፊው ቁጭት እንጂ ወትሮም መልካም ግንኙነት ኖሯቸው አይመስለኝም)

ለማንኛውም በጥቅሉ ሲታይ የህወሓት ትልቁ ችግር ተብሎ በአመራር አባላቱ የሚጠቀሰው ‹በዚህ ወቅት ወደፊት መምጣት የሚችሉ ጠንካራ ቴክኖክራቶችን አለማፍራቱ፣ ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያደርግለትን የታጠቀውን ኃይል ተጠቅሞ የፖለቲካ ልዩነቱን ጨፍልቆ በአሸናፊነት ይዞት መውጣት የሚችል መሪ እንዳይኖረው አደረገ› የሚል ነው፡፡ በርካታ የላይኛ እና የታችኛው ካድሬዎችም ‹ለእንዲህ አይነቱ ክፉ ጊዜ ድርጅቱ የሚያስፈልገው፣ በትግሉ ዘመን ልምድ ያካበተ ታጋይ ብቻ ነው› የሚል አቋም እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ስርዓቱ ከሚያራምደው ርዕዮተ-ዓለም ጋር ጠንካራ ትውውቅ ያሌለውን እና የትግሉን ዘመን በአሜሪካን ሀገር በማሳለፉ ‹የምዕራባውያን ድጋፍ አለው› ለሚባለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የሚሰጡት ዝቅተኛ አመለካከት መግፍኤም ይኸው ይመስለኛል፡፡
ለነገሩ እርሱም ቢሆን በጠንካራ ድርጅታዊ ዲሲፕሊን ካለመታነፁ እና መሰል ጉዳዮች ጋር በሚያያዙ ምክንያቶች ለትንፋሽ ጊዜ የማይሰጠውን የድርጅት ሊቀ-መንበርነትንም ሆነ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የሚወራውን ያህል ይፈልገዋል ብሎ መደምደሙ አስቸጋሪ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ከዚህ ይልቅ በተፈጥሮ ከታደለው የተግባቢነት ባህሪው አኳያ እንደ ሕዝብ ግንኙነት የመሳሰለ ብዙም የማያጨናንቅ ሥራን ይመርጣል፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ከሰለጠነበት ሙያ ጋር የቀጥታ ተያያዥነት ያለውን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በሚመራበት ዘመን፣ ከውጭ ሀገር በርካታ የተቋረጡ ፈንዶችን እንደገና ለማስለቀቅ መቻሉ እንደ ታላቅ ስኬት የሚወራለት፤ አልፎ ተርፎም ‹ወባን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት ብርቱ ትግል አደረገ› ተብሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሳይቀር እስከ መሸለም የደረሰው እዚህ መስሪያ ቤት እያለ እንደሆነም ይታወቃል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በፓርቲውም ሆነ በመንግስት አስተዳደር ከህወሓት ሰዎች ትልቁን ስልጣን የያዘው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከምዕራባውያን ጋር የቆየ ቀረቤታ እንዳለው ሰምቻለሁ፤ እንደሚታወሰው ደብረፅዮን ከክፍፍሉ በፊት (የደህንነት መስሪያ ቤቱ እንዲህ እንደ ዛሬው እጅግ ዘመናዊ በሆነው የቻይና ቴክኖሎጂ ሳይጥለቀለቅ) ከነበረው ከፍተኛ የሥልጣን ቦታ ላይ ተነስቶ፣ ቁልቁል ወርዶ በሁመራ በአንድ ዞን እንዲሰራ የተመደበው (ሁላችንም ስንገምት እንደነበረው) የአንጃው አባል ወይም ደጋፊ ሆኖ አይደለም፤ ይልቁንም የእነስዬ-ተወልደ ቡድን በመባል የሚታወቀው (‹አፈንጋጩ› ኃይል) ደብረፅዮንን በሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ ወኪልነት የመክሰሱ ጉዳይ የድርጅቱን በርካታ አባላት ቀልብ በመሳቡ፣ መለስ ይህንን ተከትሎ ከሚመጣበት አደጋ ራሱን ለመከላከል የወሰደው እርምጃ በመሆኑ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት እስከ 1998 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በሁመራና ራያ አካባቢዎች በዞን ደረጃ ለማገልገል ተገዷል፡፡ እናም እርሱን የምዕራቡ ዓለም ፊት-አውራሪ አሜሪካና ሸሪኮቿ ወዳጅ ነው የሚያስብለው በቀድሞ መስሪያ ቤቱ በኩል በነበረው ግንኙነት ይመስለኛል።

የፖለቲካውን መዘውር የጨበጠው ኃይል
የዚህ ቡድን አምበል እንደ ድርጅት ብአዴን ቢሆንም፣ በቋሚ ተሰላፊነት ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ አባዱላ ገመዳ፣ ሙክታር ከድር እና ሬድዋን ሁሴን እንደሚገኙበት ይነገራል፤ ለብአዴን ‹በተሻለ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ላይ ለመገኘቱ መደላድል ፈጥሮለታል› የሚለውን ሙግት ምክንያታዊ የሚያደርገው ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ በረከት ስምዖን፣ የኢህአዴግን የካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከል በዳይሬክተርነት የሚመራው አዲሱ ለገሰ፣ ደርቦ ይዞት የነበረውን የትምህርት ሚኒስትርነት ለሽፈራው ደሳለኝ በመልቀቅ፣ በአሁኑ ወቅት ሙሉ የስራ ጊዜውን በግንባሩ ፅ/ቤት የሚያውለው ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባኤው ካሳ ተክለብርሃን የያዙት ሥልጣን ያለውን የፖለቲካ አቅም መመዘኑ ይመስለኛል፡፡ በመከላከያ ሠራዊቱ ውስጥም ከሳሞራ አንድ እርከን ዝቅ ባለ ሥልጣን ከሌሎች ሁለት ጄነራሎች ጋር የሚገኘው አበባው ታደሰ እንደ ቀድሞው በዕዝ አዛዥነቱ (በቀጥታ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወታደሮችን ማንቀሳቀስ የሚችልበት) ላይ ቢሆን ኖሮ ጥንካሬውን የተሟላ ማድረጉ አይቀሬ እንደነበረ መገመት ይቻላል፡፡
ከዚህ ሌላ ለእነበረከት ቡድን ተጨማሪ የፖለቲካ ጉልበት እየሆናቸው ያለው የኃይለማርያም ደሳለኝ ቢሮ እና በአባዱላ ገመዳ አፈ-ጉባኤነት የሚመራው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ነው፡፡ አባዱላ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ለማቅረብም ሆነ ለመታዘዝ ፍቃደኛ ያልሆኑ አንዳንድ ባለስልጣናት፣ በውስጥ መስመር በሚተላለፍለት ‹ጥቅሻ› በምክር ቤቱ በኩል የሚመለከተው የቋሚ ኮሚቴ አባላት አስጠርቶ የተሰጠውን ኃላፊነት የሚገመግምበት ስልት እየተገበረ ነው፡፡ በአናቱም ምን ጊዜም የሳምንቱን የሥራ መጨረሻ ቀን አርብን ጠብቆ የሚሰበሰበው የሚኒስትሮች ም/ቤትን ከሞላ ጎደል ይህ ቡድን እየጠቀመበት ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ሚኒስትሮቹ በሚገናኙበት አብዛኛውን ሰዓት ሳይግባቡ (በጭቅጭቅ) ማሳለፋቸው ይነገራል፤ የዚህ ምክንያቱ ደግሞ በአቶ መለስ ዘመን ም/ቤቱ የሚሰበሰበው የተለያዩ አጀንዳዎችን ለማቅረብ እና በቀረበው አጀንዳ ላይ ለመከራከር (ለመመካከር) ሳይሆን፣ መለስ ወስኖ የመጣበትን የሥራ ድርሻ ተቀብሎ ለመበተንና ሪፖርት ለመስማት የነበረው አሰራር፣ ዛሬ ተቀይሮ በርካታ የተነቃቁ ሚኒስትሮች የየራሳቸው ሃሳብ ተቀባይነት እንዲያገኝ (ለማንፀባረቅ) የሚታገሉበት መድረክ ወደ መሆን በመሸጋገሩ ነው፡፡ ይህም ሁናቴ ዋናውን የመንግስት ሥራ የመገምገም እና የማስፈፀም አቅምን ሳይቀር ከሚኒስትሮች ም/ቤት ወደ ኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ አሻግሮታል የሚያስብሉ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይሁንና በዚህስብሰባ ላይም ቢሆን ደፈር ብሎ ከበረከት ስምዖን እና አባይ ፀሀዬ የተሻለ አዳዲስ ሃሳብ የሚያቀርብ ባለሥልጣን እንደሌለ ሰምቻለሁ (በነገራችን ላይ ምክንያቱን ባላውቅም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር አማካሪ› ተደርገው የተሾሙት በረከት ስምዖን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ኩማ ደመቅሳ እና ዶ/ር ካሱ ኢላላ የሥራ ቦታቸው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት ሳይሆን መገናኛ አካባቢ በሚገኝ አንድ ህንፃ ላይ ነው፡፡ የተሰጣቸው ኃላፊነት ኃይለማርያምን በቅርብ እንዲያገኙ ከማስገደዱ እና በግልፅ ከሚታወቀው የአማካሪ አስፈላጊነት አኳያ ካየነው ግን ግራ የሚያጋባ ይመስለኛል)
ጠቅላይ ሚኒስትሩ…
ኃይለማርያም ደሳለኝ ይህንን ቦታ ከያዘ በኋላ፣ ብዙዎች በስልጣኑ የማዘዝ አቅሙ ላይ አመኔታ እንደሌላቸው (አንጋፋ ታጋዮች እንደ ‹አሻንጉሊት› ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ) ደጋግመው መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ በግልባጩ ‹አፈንግጦ ለመውጣት መሞከሩ አይቀሬ ነው› የሚሉ ግምቶች ነበሩ፡፡ በርግጥ እነዚህ መላ-ምቶች ዛሬም ድረስ እልባት ባያገኙም፣ እዚህ ጋ ያልጠቀስኳቸው አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ያሳያቸው ወጣ ያሉ አቋሞቹን ሳስተውል ግን፣ አሁን ያለው አሰላለፍ (የአነበረከት እና አባዱላ ፖለቲካዊ መጠናከር) ለእርሱም የተረፈው ይመስለኛል፡፡ እንዲሁም ከቤንች ማጂ የተባረሩ አማርኛ ተናጋሪዎችን አስመልክቶ በድርጅቱ ውስጥ ባልተለመደ መልኩ ‹አጥፊዎቹ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ› ከማለት አንስቶ (በነገራችን ላይ በአማካሪ ብዛት እንዲከበብ ካደረገው ምክንያት አንዱ ጓዶቹ በዚህ ንግግሩ መበሳጨታቸው ነው) በቅርቡ ህወሓትን ለመሸምገል በተዘጋጀ መድረክ ላይ ‹ሁኔታዎች እንዲህ እየተካረሩ ከሄዱ ወደ ማሰሩ መግባታችን አይቀርም› በማለት ማስፈራራቱ እና በቴዎድሮስ አድህኖም የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ የመቆጣቱ ጉዳይ ድረስ የሚካተቱ እውነታዎች ሰውየው የራሱን መንገድ ለመከተል እየሞከረ መሆኑን ያሳያሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
የሆነው ሆኖ እነዚህ ሁናቴዎች የፖለቲካውን ጉልበት ሙሉ በሙሉ በብአዴንና በተባባሪነት በጠቀስኳቸው የኦህዴድና ደህአዴን የአመራር አባላት አካባቢ ቢያከማቻቸውም፣ በማንኛውም ሰዓት ያሻውን ማድረግ የሚችለው የታጠቀው ኃይል ደግሞ ከህወሓት ጎን እንደተሰለፈ ይገኛል፡፡ መጪውን ጊዜም አዲስ ክስተት እንድንጠብቅ ገፊ ምክንያት ይህ አይነቱ የኃይል አሰላለፍ ይመስለኛል፡፡
ምን እንጠብቅ?
ከረጅሙ የፓርቲ ፖለቲካና መንግስታዊ መንገራገጮች በኋላ፣ የሁለቱንም የኃይል መሰረቶች ጠቅልሎ በመዳፉ ሥር የከተተው መለስ ዜናዊ በሞተ ማግስት ‹የኃይል መገዳደሮች ሊከሰቱ ይችላሉ› የሚለው የብዙዎቹ ግምት ነበር፤ ከወራት በፊት አስነብቤ በነበረው ከላይ በተጠቀሰው ፅሁፍም ግምቶቹ እውን መሆን እንደ ጀመሩ ማሳያዎች ማቅረቤ ይታወሳል፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ ራሳቸውን ያቧደኑት ኃይሎች ዋነኛ ግብ ከሥልጣን የሚነሱ ጥቅሞችና አነስተኛ የየራሳቸው ፓርቲ ፍላጎቶች የፈጠሩት በመሆኑ፣ እንደ ሟቹ ደመ-ቀዝቃዛ አምባገነን አይነት በጠንካራ መዳፍ ሥር የሚያሰባስባቸው ባለመገኘቱ በየጊዜው የኃይል መሸጋሸጎች ሊከሰቱ እንዲችሉ አድርጓቸዋል፤ አሁ&#4

ግንቦት 83/91 ላይ የኢትዮጵያ ሰማይ ክፉኛ በሃዘን ሲመታ ፣ ደመናው ሲጠለሽ ፤ ወንዞች መደፈራረስ ሲጀምሩ ፤
የሰውን ልብ ባር ባር ሲለው …….. የክፉው ቀን ጅማሮ ፣ የውርደት ሃሌታ ፣ የሃገር አልባነት ስሜትና የዜግነት
ውርደት ደጃፍ ላይ መውደቃችን እውነት ነበር ።

ውርስ ከአባት ወደ ልጅ ሊተላለፍ ካልቻለ ፤ አባት የጀመረውን ልጅ ካልቋጨው ፤ አዲስ መንግስት ሲቀየር
የድሮውን በጐ ነገር ሁሉ ብትንትኑን አውጥቶ ካጠፋ ፤ የትውልድ ቅብብሎሽ ገደል ገባ ማለት አይደል ? እናም
በአገሬ ምድር ላይ የእርግማን ዘመን ያኔ “ በ1991 “ “ ሀ “ ብሎ ጀመረ ።

ሌባው ከሳሽ … ቀማኛው ፈራጅ የሆነበት ፤ አባት ተቀምጦ ልጅ የሁሉ ነገር አዛዥ ሲሆን ፤ አህያ ወደ ሊጥ …
ውሻም ወደ ግጦሽ ከተሰማራ …. እነሆ ዘመነ ብልሹ ላይ መድረሱን ያልተረዳ ካለ … እሱ ባይፈጠር …. እናቱ ሆድ
ውስጥ ውሃ ሆኖ ቢቀር ይሻለው ነበር ።

አገር ሲገነጠል ዝምታ ፤ ንብረት ከመሃል አገር ተግዞ ሲያልቅ ዝምታ ፤ ገዳማት ሲታረሱ ፣ ቤተ ክርስቲያናት
ሲዘረፉና ታቦታት በየገበያው ሲቸበቸቡ ዝምታ ፤ ደን ሆን ተብሎ በሰደድ እሳት እንዲወድም ሲደረግ ዝምታ ፤
ግዙፉ የአገር መከላከያ ኃይል እንደተረት አይናችን ስር ሲበተን ዝምታ …….. የምንወደው ዝነኛው የአየር
ኃይላችንም አብሮ ተደርምሶ እንዳልነበረ ሲሆን ዝምታ ነገሰ ። የሚቆጭ ፤ የሚመክር ፤ የሚቆጣና ሃይ የሚል
ወንድ ጠፋ ። የአድዋና የማይጨው አርበኞቻችን የክብር ሃውልቶች ሲፈርሱም ዝምታ ፣ የጦር ካምፖቻችንም
ታሪካዊ ስያሜ በማን አለብኝነት ለጐጠኞች ስያሜ ሲውልም ዝምታ ነገሰ ።

ዛሬ ደግሞ ከአዲስ አበባ ዋሺንግተን በሚመላለሱና ከዘመነኞቹ ጊዚያዊ የይሁኝት ፈገግታ በተቸራቸው የኛና የኔ
ቢጤዎች አማካኝነት የቬተራን አሶሴሽን እናቋቁማለን ፤ የአየር ኃይሉንም ታሪክ እንፅፋለንና ለዕርዳታ እጃችሁን
ዘርጉ የምትል የኢሜል መልዕክት ደርሳን በትዝብት ተደምመናል ። እስኪ ከበጐ መንፈስ የመነጨ ነው ብለን
እንመን ። ግን ሥጋት አለን !

የአየር ኃይላችንን ታሪክ ለትውልድ ዘግቦ ማስቀመጥ ምንኛ የተቀደሰ ዓላማ ነው ! የአቭዬሽን ቬተራን ማህበርን
ማቋቋምስ እንዴት ትልቅ ራዕይ አለው ? ነገር ግን የአንድ መንደር ልጆችን ዓላማ አድርጐ በጐጠኝነት ማማ ላይ
እየተንጠለጠለ እኛ እና እነሱ ፤ የቀድሞውና አዲሱ ፤ ዲሞክራቲኩና የአንድነት አርበኛ እያለ ሊለያየንና
ሊከፋፍለን ሌት ተቀን የሚተጋው ጐጠኛና ሽፍታ መንግስት የሚገነባውን ከእውነተኛው አየር ኃይል በቅጡ
መለያየት ያስፈልጋል ።

ውሃና ዘይትን ለመቀላቀል በማምሺያ እድሜ መባጀት ጉልበት ማባከን እንዳይሆን ! የነፃነት አርበኛው ጀ/ል ተጫነ
መስፍንና የሽፍቶቹ ጀ/ል አበበ ተ/ሃይማኖት (ጆቤ) በምን ተዓምር ለአንድ ዓላማ ሊሰለፉ ይችላሉ ?
በምንስ ሂሳብ የህ.ው.ሃ.ቱ. አበበ ተ/ኃይማኖት (ጆቤ) የቬተራን አሶሴሽን መስራች ሆኖ በሸራተን አዲስ ይደግሳል ?
እነዚህ ሁለት ፍጥረታት ውሃና ዘይት ናቸው ። በዓላማም በራዕም አንድ አይደሉም ….. አሳዳጅና ተሳዳጅ !
ወንጀለኛና ወንጃይ … አርበኛና ባንዳ .. ውሃና ዘይት ናቸው ። ሊዋሃዱ አይችሉም ።

የእኛው አየር ኃይል በጅምላ ጨፍጫፊና ወንጀለኛ ተብሎ እንደ ጉም በተበተነበት ዘመን ላይ ተቆሞ ….. ለአገር
የደሙ ከያሉበት ታድነው በውርደት በየማጐሪያው ተወርውረው ልባቸው ተሰብሮና ጥሪት አልባ ሆነው በሰው
እጅ ላይ እንዲወድቁ በተበየነበት ዘመን ላይ ፤ ዛሬ ከሲሶው በላይ እውነተኛው አርበኛ አገር አልባ ሆኖና ተዋርዶ
አልጋ ላይ እየዋለ ያለ ደጋፊና አጋዥ ቀና ማለት ባቃተው ሰዓት ላይ የቬተራን አሶሴሽን እያቋቋምን ነው ሲሉንና
ግባታውን በገንዘብ እንድንደግፈው ስንጠየቅ እውን ለእውነተኛው የአየር አርበኛ አገልግሎት እንዲመስለን ይሆን ?

በእርግጥ ጥቂቶች ደም የተገበረበትን አርበኝነታቸውን ሳይሆን የሽንፈት ታሪካቸውን አሜን ብለው በመቀበል
በውርደት በጅምላ የተለጠፈብንን የጨፍጫፊነት ማንነት ፤ በተጨማሪም ለአገር በመሞታችንና ደማቸንን
በማፍሰሳችን ምክንያት እንደ ተራ ነፍሰ ገዳይ የሞትና የእድሜ ልክ ፍርደኞች መሆናችንንና/መሆናቸውን
ዘንግተው “ ማምሻም እድሜ ነው “ በሚል የመሰንበት ጉጉት በድለላ እያግባቡን ማየታችን ከላይ በበጐ መንፈስ
ተነሳስተው ነው የሚለውን አቋማችንን እየሸረሸረብን ተቸገርን ።

ለመሆኑ በማን አየር ኃይል ….. በነማንስ ደም ይቀለዳል ?
የእነ ሚሽካ ባቢቼቭ አየር ኃይል …. የእነ ባህሩ ካባ አየር ኃይል …. የእነ ጀነራል አበራ ወ/ማሪያም …. የእነ ጀነራል
አሰፋ አየነ … የእነ ጀነራል አሰፋ ገ/እግዚ …. የነ ጀነራል ታዬ ጥላሁን ….. አየር ኃይል እንዴት ሆኖ ከዚህኛው ዘመን
ጋር ይዋሃዳል ?

እነ ጀ/ል ለገሰ ተፈራ ፣ ኰ/ል በዛብህ ጴጥሮስ ፣ ኰ/ል ታደለ አለሙ ፣ ኰ/ል ትርሲት ፣ ኰ/ል ወርቁ ፣ ሻ/ል
ጥላሁን በዛብህ ፣ መ/አ አባይነህ ኃይሉ ፣ መ/አ ደመላሽ መኰንን የመሳሰሉት በምርኰና በእስር መስዋዕትነት
የከፈሉበት ፤
የነ መርዕድ ዳጨው ደም …. የነ አማኑኤል አምደ ሚካኤል …. የነ ጥላሁን ኃይሉ ፤ የነ ለዊ ደሬሳ …. የነ መንግስት
ዓለሙ … የእነ ሊ/ካዴት ይኩኖ ታደሰ ጨቅላና አድገው ያልጨረሱ ልጆች ደም ፤ የነ ተስፋዬ ብ/ሥላሴ …. የነ
ማ/ቴክ ደገፋ ሆራ …. የነ ኰ/ል ጥላሁን ቦጋለ ….. የነ ሰለሞን መክብብ …. የነ አብረሃም ስንቄ ደም ላይ እንዴት
ዳንኪራ ይጨፈራል ?

እነ ጀ/ል ፋንታ በላይ …. ጀ/ል አመሃ ደስታ …. ጀ/ል ሰለሞን በጋሻው …. ጀ/ል ተስፉ ደስታ … ጀ/ል ንጉሴ ዘርጋው
… ጀ/ል ገናናው መንግስቱ …… እንዲህ ደማቸው ደመ ከልብ ይሁን ? ለአፍታ ቀና ብለው ቢያዩስ ምንኛ
በባልንጀራቸው ያፍሩ ይሆን !

ዘመናቸውን ሙሉ ለአገራቸው የአየር ክልል መከበር ጨርቄን ማቄን ሳይሉ …… ንብረት ማፍራት …. ሃብት ማካበት
…. ሚስት ማግባትና የአብራካቸውን ፍሬ ለማየት ሳይጓጉ እድሜያቸውን የጨረሱ የአየር ኃይሉ ጌጦችና የአገር
አለኝታዎች እንደ ወሮበላ ማጅራት መቺ የሞትና የእድሜ ልክ ፍርደኛ በተሆነባት አገር ላይ እንዴት አይነቱ የአየር
ኃይል የአቪየሽን ቬተራን አሶሴሽን ይገነባል ?

እነ ኰ/ል ታከለ አበበ ፣ ሻ/ቃ አለማየሁ እሳቱ ፣ ሻ/ቃ ከበደ ጫኬ ፣ በላይነህ ተገኝ ፤ ደበበ ሞላ …. ደሳለኝ
ስሜነህ … …. ወዘተ በጉልበት ከአገር ተሰደው በበረሃ ላይ ያለ አልቃሽና ቀባሪ ነፍሳቸውን እንዲሰጡ ላደረገ ሽፍታ
፤ እነ ሻ/ል ፍሰሃ መለስን በእስር ቤት ለገደለ ወንበዴ እንዴት ብለን ክብራችንን ዝቅ አናደርጋለን ?
እነ ኰ/ል ብርሃነ መስቀል ፤ ኰ/ል ሰለሞን ከበደ ፤ ኰ/ል ግርማ አስፋው ፤ ሻ/ል ክፍሌ ውቤ ከእድሜያቸው ከሩብ
በላይ በእስር የገበሩበት ምክንያት ምን ይሆን ? ዘንግተነውስ ይሆን ?

እነ ማ/ቴክ ሽብሩን .. እነ ማ/ቴክ ፀጋዬ ሁሉቃን … እነ ማ/ቴክ ግርማ ሰቦቃንና የመሳሰሉትን በአጠቃላይ
አፕሬንቲሱን ፣ ኤርሜኑን ፣ ቴክኒሻኑን ፣ የአየር ፖሊሱን ፣ በራሪውን ፣ መኰንኑን ፣ ባሌ ላላ ማዕረግተኛውን
እንደ አሮጌ ቁና ሜዳ ላይ በትኖ በስተ እርጅና የሰው እጅ እንዲያዩ የተደረጉበትን እንደ ጨዋታ ቆጥረነው ይሆን ?

እነ ኰ/ል ብርሃኑ ከበደን ፤ ኰ/ል ብርሃኑ ውብነህ ፤ ኰ/ል ጣሰው ወዳጄነህን ….. ኰ/ል ጌታቸው መንገሻን ….
ኰ/ል መንገሻ ሁንዴን …. ኰ/ል የሺጥላ መርሻን ….. ኰ/ል ይልቃልን … አለማየሁ አጐናፍርን …. አለማየሁ ኃይሌን
…. ስንታየሁ አሽኔን … መስፍን መንግስቴን ….. በኃይሌ ደግፌን … ጂልቻ ዱራን …. ኰ/ል ነብዩን …. አሰፋ ተገኝን ፤
አቦነህ ነጋሽን … ዳዊት ወንዲፍራውን ፤ መስፍን ግርማን ……. በአጠቃላይ ስማቸው ያልተዘረዘሩትን የተዋጊውን ፣
የትራንስፖርትና የሄሊኮፕተር ስኳሮኖች በራሪና የቴክኒክ ባለሙያ ሲቪል ሰራተኞችን ሁሉ አገር አልባ አድርጐ …
እንዴትስ አይነት የአቪዬሽ ቬተራን ማህበር ሊመሰረት ይችላል ?

ጀነራል ተጫኔ መስፍን ደም ገብረው በአቀኑት አየር ኃይል ውስጥ አበበ ተ/ኃይማኖት አንዳችም የአየር ኃይል
ትምህርትና ዕውቀት ሳይኖረው የቬተራኖቹ አየር ኃይል አዛዥ ሆኖ በራሪ ተማሪዎችን ሲሸልም በአፍሪካ ውስጥ
በበረራ ሰዓታቸው ተወዳዳሪ የሌላቸው የተዋጊ አውሮፕላን በራሪና ኢትዮጵያን በተለያየ ጊዜ የተቃጣባትን ወረራና
ጥቃት በጀግንነት የመከቱ እውነተኛ የኢትዮጵያ ልጅ ጀነራል ተጫነ መስፍን በዚህ አይነት በአሳላፊነት
መታየታቸው ምን ያክል አገር አልባ እንደሆንን አያሳይ ይሆን ? እውን ታዲያ ይሄ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ነው ?
እንደዚህ አይነት አገር የማታከብረው ቬተራንስ የት አገር ነው ያለው ?

ጀነራል ተጫኔም በዚህ አይነቱ ሁኔታ እራሳቸውን ለማሳነስ ባይፈቅዱ እንዴት ጥሩ ነበር ? እነ ጀነራል መስፍን …
ጀነራል ተሻለ … ኰ/ል ጥላሁን ነብሮን የመሳሰሉት ባለ ወርቅዬ ታሪክ ባለቤቶች እንደ አገር አልባና ሁለተኛ ዜጋ
ተገልለውና ተጥለው ያለ ፎቶ ግራፍ ይኖሩ የለ ?
በእርግጥ በዚህ ዘመን ጀ/ል ተጫነ ከአቻዎቻቸው በተለየ ሁኔታ ከነ ሙሉ ክብራቸውና ጥቅማቸው በአገራቸው
በቬተራን ማዕረግ እየኖሩ ያሉ ብቸኛ ሰው ናቸው ። ቀደም ሲልም እንደ ጀ/ል ተጫኔ ሁሉ ጀ/ል ሰለሞን በየነ
በዚሁ በተንቆጠቆጠው ማማ ላይ ተሰቅለው እንዳሉ እናውቃለን ፤ ይህ እንግዲህ የልደታ አየር ምድብ አዛዥ
ተደርጐ ተሹሞ የነበረውን ሻለቃ ተስፋዬ ተገኝን ሳንዘነጋ ፣ የሚሊታሪ አታቼውንና ጀ/ሉን ኃይለ ሥላሴ ገብሩንም
ማ/ቴክ ረዳዕይና ማ/ቴክ ክንድያን እንዲሁም ካላዩ አፅበሃንም በማሰብ ነው …….. ። በእርግጥ አድሎው አይን
ያወጣ ቢሆንም ከወደ ኰረም ፣ አዲግራትና አድዋ የመወለድ ጣጣ ነው እያልን ቆይተናእነሆ ምክር እንለግሳለን …….

የአየር ኃይላችንን ታሪክ መፃፉን እናበረታታለን ። ይሁን እንጂ …….
ዛሬ የሚፃፍ ካለ … አየር ኃይሉ እንዴት እንደተመሰረተ ብቻ ሳይሆን እንዴትም እንደፈረሰ ፤ ለአገር የደሙና የሞቱ
እንዴት እንደወንጀለኛ በየማጐሪያው እንደተጋዙ … ህብረ ብሄሩ የኢትዮጵያ አየር ኃይል እንዴት ወደ አንድ ዘር
የሽፍቶች ስብስብነት እንደተቀየረ የሚተርክ ካልሆነ …. ጀ/ል ተጫነ መስፍን ፣ ኰ/ል አስፋው አየልኝንና
የመሳሰሉትን የትውልድም የታሪክም ተወቃሽ ፤ የአገርም ክህደት እንዳይሆን ይታሰብበት ።

የአቭዬሽን ቬተራን አሶሴሽንም ከመመስረቱ በፊት አርበኛውን ከጐጠኛው መለየት ፤ እውነተኞቹን የአየር
አርበኞችና ቬተራኖች ከብቀላ ፍርደኝነታቸው ነፃ ማድረግና ዝነኛውን አየር ኃይል በጅምላ ከተለጠፈበት
የጨፍጫፊነት ስያሜ እንድናላቅቅ የየበኩላችንን ጥረት ማድረግ ይገባናል ።

ጨረስን ።
ኢትዮጵያን እግዚአብሄር ይባርክ ።

ትብብር ለመልሶ ማቋቋም
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል
Source-ethioforum.com
Image

ተቃዋሚ ነን የሚሉ ፓርቲዎች እና ግለሰቦች ካለምንም አላማ በጥላቻ እና በስድብ ላይ ተመስርተው በእጅ ቅሰራ ላይ ስለተመረኮዙ ሁሌ እንዳወሩ ይኖራሉ::ጫካ ገብቶ መበርታት ከጀመረበት እና ሱዳን ላይ የተደላደለ የመሸጋገሪያ እርከኖችን ካገኘበት ጊዜ አንስቶ ወያኔ አለማቀፍ አሸባሪ እና ማፊያ ቡድን መሆኑ የታወቀ እና እስካሁንም ከመዝገብ ላይ ያልተፋቀ መሆኑ ይታወቃል::

ከሱ ለመስተካከል የሚራወጡ ሆኖም ያልተሳካላቸው ደሞ እየተፈጠሩ እየከሰሙ እየተፈጠሩ ነው….እነሱ ቀድመው ካልተናገሩ በስተቀር ሁሉ ነገር ከወያኔ የሚመጣ የሚመስላቸው ባዶ ካርቶን ዲያስፖራዎች ሰው አናት ላይ ሊሸኑ ይፈልጋሉ::

በእርግጥ አንገብጋቢ የህዝብ ጥያቄዎች ሲበረቱበት ወያኔ የሚፈጥራቸው የሃሰት ተባራሪ የአየር በኣየር ፕሮፓጋንዳዎች ባንድ ጊዜ ተለግተው አለምን ያዳርሳሉ :: ይህ ዛሬ ሳይሆን ከጅምሩ የተረጋገጠ ጉዳይ ሲሆን አልተነቃብኝም የሚለው ወያኔ ይህንን ይዞ እየተመመ ነው:: አንዳንድ ግዜ ደግሞ የዜና ማሰራጫዎች ከወጡት ዜናዎቻቸው ላይ የተወሰዱ ጉዳዮችን እና ሌሎች አላስፈላጊ ነገሮችን በወያኔ ላይ መለጠፍ አንድም የዲያስፖራው ስንፍና ነው ሌላም የትግል ድቀት ውጤት ነው::

ይህን አጋጣሚ ተጠቅሞ እንዴት እንደተሰራጬ ማጋለጥ እንጂ ሁሉንም የወያኔ ቋንቋ ማድረግ የዋህነት አይመስልም:: አብዛኛው ተቃዋሚ ነን የሚሉ ፓርቲዎች እና ግለሰቦች ካለምንም አላማ በጥላቻ እና በስድብ ላይ ተመስርተው በእጅ ቅሰራ ላይ ስለተመረኮዙ ሁሌ እንዳወሩ ይኖራሉ::

ጥያቄው የለውጥ ጥያቄ ነው ::ኢሕኣዴግ መስማት ከቻለ ጥያቄው ይህ ነው ::
የሕወሓት የንግድ ድርጅቶች ህዝብን ማእከል ያደረገ ድህነት እንዲፈጠር አድርገዋል::ሃገርን ለኪስራ ዳርገዋል::የሕወሓት ድርጅቶች በሞኖፖል የተቆጣጠሩ እና ፖለቲካው የሚያሽከረክራቸው የንግድ ድርጅቶች ለሃገር እድገት ጋሬጣ ከመሆናቸውም በተጨማሪ ለሙስና መስፋፋት ለስልጣን መባለግ እንዲሁም ለድህነት መንሴ ሆነው ተገኝተዋል::እነዚህ ድርጅቶች በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ነጋዴዎችን ከገበያ አባረዋል::አክስረዋል በመቶሺህ የሚቆጠሩ ዜጎችን ከሃገር አሰድደዋል::በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ከመንግስት አዘርፈዋል ዘርፈዋል:; በትሪሊኦኖች የሚቆጠር ገቢን መንግስትን አሳጥተውታል::ህዝብን ማእከል ያደረገ ድህነት እንዲፈጠር አድርገዋል::ሃገርን ለኪስራ ዳርገዋል::በተጭበረበር ፖለቲካ ላይ የተገነባ ኢኮኖሚ ዋጋቢስ ነው::

የፖለቲካ ተሃድሶ እንዳልን ሁሉ የኢኮኖሚ ተሃድሶም ያስፈልገናል::ያለውን የኢኮኖሚ እደምታ ለመገምገም ሳይሆን መጪው ጊዜ በለውጥ የታጀበ የኢኮኖሚ ፖሊሲ እንዲኖረን ለማሳሰብ ነው:: ባለፊት አመታት እያልን እንደፈረደብን ማላዘን ሳይሆን መጪውን ጊዜያት ማሰብ ካለብን ለዚህ የባከነ ትውልድ እረፍት እንሰጠዋለን::

ሕወሓት/ኢሕኣዴግ መራሹ መንግስት የያዘውን ስልጣን ለመቀራመት አሰፍስፈው በጥላቻ ፖለቲካ ለሚዳክሩት ሁሉ ሊሰለጥኑ እንደሚገባ ልንነግራቸው ይገባል::ካልሆነ እንደኢሕኣዴግ ያሉ የሃያላኑ ስልጡን ማፊያዎችን መጣል ከባድ ይሆናል::የሃገራችንን ኢኮኖሚ የመሰረቱት ከብሄራዊ ጥቅማቸው አኳያ ቅጥኛ የሆኑ ኢኮኖሚስቶችን አስርጎ በማስገባት ላለፉት 35 አመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ እንዲመሰረት አድርገውን ለኪሳራ አሳልፈው ሰተውናል::ህዝቦች ባልተጠና እና በቶሎቶሎ በተዘጋጀ የኢኮኖሚ ፖሊቺ እየተመሩ የሄዱበት ጉዙ እልህ አስጨራሽ ብቻ ሳይሆን ከስኬት ይልቅ ለኑሮ ኪሳራ ዳርጓቸዋል::ይህ ደሞ ሃገሪቱን እመራዋለሁ ከሚለው መደብ የተፈጠረ ዝብርቅርቆሽ ነው::

መንግስታዊ ውሸት በራሱ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውድቀት ትልቅ ሚና ተጫውቷል:: የመንግስት መገናኘ ብዙሃን በተለመደ መልኩ ውሸት ሲደጋገም ውነት ይሆናል በሚል ፈሊጥ ህዝባን እያታለሉ የልተፈጠረ እና ያልተደረገ ነገር እየደሰኮሩ ሃገርን ለኪሳራ መዳረጋቸው የአደባባይ ሃቅ ነው::ይህ ውሸት ደሞ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ያመጣው ተጽእኖ ቀላል የሚባል አይደለም ::
በተጨማሪ ሃገር በባዶ ካዝና እየተመራ ባለበት በዚህ ወቅት ከውጪው አለም የተለያዩ ብድሮችን በማምጣት 3 መጪ ትውልድ ሊከፍለው በማይችለው እዳ ውስጥ ሃገሪቷ እንድትነከር አድርገዋል::የመጣውን ብድር ህዝቦች ከድህነት እንዲላቀቁ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለሃገር የኢኮኖሚ ዋልታዎች ማደግ ከማዋል ይልቅ መንገድ እና ህንጻ በመስራት ገንዘቦችን ወደ ድንጋይ እንዲለወጡ መደረጉ ያለው አስተዳደር የአገዛዝ ብልሹነት እና የመልካም አስተዳደር እጦት ያመለክታል:: ይህ ደሞ ኢኮኖሚያችን በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ እንደተገነባ ያመለክታል::

Image
የአማራ ዴ/ኃ/ን ለሱዳን ተላልፎ በተሰጠው መሬት ዙሪያ “ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል” የሚል መግለጫ አወጣ
ጋዜጣዊ መግለጫ
“ዳሩ ካልተጠበቀ መሃሉ ዳር ይሆናል”!!
ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) የተሰጠ መግለጫ
ታህሣሥ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
በዓለም ላይ እስከአሁን የተከሰቱ መንግሥታት (ቅኝ ገዥዎችን ጨምሮ) ጨቋኝ (አምባገነን)፣ በዝበዥ፣ ዘራፊ (በሙስና የተዘፈቀ) … ወዘተ ሊሆኑ ይችላሉ። አሁን ኢትዮጵያን በመግዛት ላይ እንዳለው የትግሬ ዘረኛ ቡድን የሚገዛትን ሀገርና ሕዝብ የሚጠላና ሀገሩንም ለማጥፋት 24 ሰዓት የሚሠራ መንግሥት ግን እስከ አሁን በታሪክ አልታየም። ወደፊትም ከወያኔ በስተቀር የሚገዛትን ሀገር፣ ታሪኳንና ሕዝቧን የሚጠላና ሆን ብሎ ለማጥፋትም ቀን – ተሌት የሚጥር መንግሥት በምድር ላይ ይከሰታል ብለን አናምንም። ይህ የትግሬ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን መጥላቱን የሚያሳይ የድርጊቱን ሥንክሣር መዘርዘር ቢቻልም፣ በአሁኑ ሰዓት የተከሰቱ ሁለት ታላላቅ ብሔራዊ ጉዳዮችን ብቻ እንኳ ብናይ ዘረኛው ቡድን ምን ያህል የሚገዛትን ሀገርና ሕዝቧን አምርሮ እንደሚጠላ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፦
በሣዑዲ አረቢያ የወገኖቻችን ደም በግፍ ሲፈስስ፣ እህቶቻችን ያለርህራሄ በቡድን ሲደፈሩ፣ በ21ኛው ክ/ዘመን በሰው ልጅ ላይ የፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ኢሰብአዊ ግፍ ሲፈፀምባቸውና በአጠቃላይ በሀገሪቱ ላይ ብሔራዊ ውርደት ሲደርስ የትግሬው ዘረኛ ቡድን “የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት በሀገሩ ላይ ይህንን ማድረግ መብቱ ነው” ነበር ያለው።
በዚህ ሰቅጣጭ ሐዘን ውስጥ ተውጠንና በስቃይ ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ለመርዳት ላይ ታች በምንልበት ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ታጥቆ የተነሳው የትግሬው ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ ጠብቀው ያቆዩትን 1600 ኪ/ሜ ርዝመትና ከ20-60 ኪ/ሜ ወደ ኢትዮጵያ ጥልቆ የሚገባውን ከሱዳን የሚያዋስነውን ድንበራችንን በሕገወጥነት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ፈርሞ ለሱዳን አስረከበ። ምንም እንኳን በሚስጥር ሊይዘው ቢሞክርም የድንምበር ማካለሉ ከጥር ወር 2006 እስከ መስከረም 2007 ችካል በመቸከል እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ (አዴኃን) ይህንን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ የሚደረግ ሕገወጥ የድንበር ክለላ አጥብቆ መቃወምና ማውገዝ ብቻ ሳይሆን እንዳባቶቹ ደሙን አፍስሶና አጥንቱን ከስክሶ ታሪካዊ ድንበሩን ለማስከበር ቆርጦ ተነስቷል። ባንዳ የባንዳ ልጆች ከአባቶቻቸው የወረሱትን ሀገር የማጥፋትና የመሸጥ ውርስ ተግባራዊ ሲያደርጉ እኛ የአርበኛ ልጆች ነን የመንል ይህንን ደባ ዝም ብለን ብንመለከት ድንበር ላይ የተከሰከሰው የአባቶቻችን አጥንት እሾህ ሆኖ ይዎጋናል። በመሆኑም በአካባቢው ያላችሁ ታጋይ ኃይሎችና የገፈቱ ቀማሽ የሆንከው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ በርስቱና በሚስቱ ያልሞተ ወንድ ልጅ ወንድ አይደለምና ወንድ ልጅ ነኝ ያልክ ሁሉ ተባበረን፣ ከዚህ በላይ የሞት ሞት የለምና።

አዴኃን ይህንን ድርጊት አምርሮ የሚቃወመው እንዲያው በጭፍኑ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ሕጋዊ የሆነ ድንበር አይኑራት ብሎ አይደለም። የድንበር ስምምነቱ ኢትዮጵያን ጎድቶ ሱዳንን የሚጠቅም፣ ከ110 ዓመታት በፊት የፈረሰና ሕጋዊ ያልሆነ ውልን መሠረት ያደረገ፣ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረጉ ኢትዮጵያውያንን ጥናትና ውትወታ ግንዛቤ ውስጥ ያላስገባና በአጠቃላይ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ በደባና በሕገወጥነት የተፈረመ ውል በመሆኑ እንጅ።

በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ጥናት ያደረገው የኢትዮጵያ የድንበር ኮሚቴና ከዚያ በፊትም ጥናት ያደረጉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሑራን እንደሚሉን ከሆነ ይህ ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ ለተፈራረመው ውል ዋቢ የሚያደርገው ውል በዳግማዊ አፄ ምኒልክና በጊዜው የሱዳን ቅኝ ገዥ በነበረችው እንግሊዝ መካከል የተፈረመው እ.አ.አ 1902 ነበር። አፄ ምኒልክ ይህንን ውል የፈረሙት በኃይል ተገድደውና በይዞታቸው ሥር የነበሩ ብዙ መሬቶችን ለቀው ነበር። በዓመቱ በ1903 የእንግሊዙ የጦር መኮንን ሻለቃ ጉዊን ድንበሩን ከስምምነቱ ውጭ ብቻውን ሄዶ ከመከለሉም በላይ አፄ ምኒልክ ተገድደውም ቢሆን የፈረሙትን ካርታ አዛብቶ ኢትዮጵያን እየጎዳ ችካል ቸከለ።
ይህንንም ሻለቃ ጉዊን ከተሰጠው ሥልጣን በላይ ሄዶ መሥመሩን በማዛባት ከኢትዮጵያ መሬት እንደወሰደ በራሱ ሪፖረት ላይ በግልፅ ሳይደብቅ ጽፏል። እንግሊዞችም በ1902 የተፈረመበትን ካርታ ጥለው በችካሉ መሠረት በ1903 አዲስ ካርታ በመሥራት እነርሱ ከፈረሙበት በኋላ አፄ ምኒልክን ለማስፈረም ቢሞክሩም ከስምምነት ውጭ ለተቸከለው የጉዊን ክለላ ዕውቅና በመንፈግ ሳይፈርሙበት ቀርተዋል። የትግሬው ዘረኛ ቡድን አፄ ምኒልክ፣ አፄ ኃይለሥላሴና ደርግ የጉዊንን መሥመር ተቀብለዋል እያለ የሚያላዝነው ይህንን የመሰለውን ሐቅ በመካድ ነው። ይህንንም ዓይን ያወጣ የወያኔን ቅጥፈት አዴኃን ብቻ ሳይሆን ሰኞ 19 ኖቬምበር 2007 (እ.አ.አ.) ሱዳን ትሪቢዩን የተባለ ጋዜጣም “ድንበሩን አስመልክቶ የሱዳን መንግሥት ከቀደምት የኢትዮጵያ መንግሥታት ጋር የነበረው ግንኙነት ቀና አልነበረም። በድንበሩ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የመጀመሪያው ፈቃደኛ መንግሥት ገዥው የኢሕአዴግ መንግሥት ብቻ ነው” በማለት መሥክሮበታል።
ጥሪ፦
ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራትም ጭምር፣ ይህ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጀርባ በሀገር ከሃዲው የትግሬ ዘረኛ ቡድ ከጎንደር፣ ከጎጃም፣ ከወለጋና ከኢሊባቡር ክፍለ ሀገሮች ተቆርሶ ለሱዳን የሚሰጠው ለም መሬት የክፍለ ሀገራት ተወላጆቹ መሬት ብቻ አይደለም፤ የአንተም የኢትዮጵያዊው መሬት እንጅ። በመሆኑም አዴኃን ይህንን በባንዳ ልጆች የተጋረጥብንን ኢትዮጵያን የማጥፋት ታላቅ አደጋ ለመቀልበስ ስንል ያሉንን ጥቃቅን ልዩነቶች ወደጎን በመተው፣ ከምንጊዜውም በላይ እጅ ለእጅ ተያይዘንና ያለንን አቅም ሁሉ አስተባብረን በመነሳት የዜግነት ግዴታችን እንድንወጣ አስቸኳይ ጥሪውን ያስተላልፋል። “ዳሩ ክልተጠበቀ፣ መሀሉ ዳር ይሆናል” እንደሚባለው የትግሬውን ዘረኛ ቡድን በተባበረ ክንድ ዛሬውኑ ካላስወገድነው በስተቀር እናት ሀገራችን ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዕኩይ ተልዕኮው የድንበር መሬቶችን እየቆረሰ ለጎረቤት ሀገራት በመስጠት ብቻ ያቆማል ብሎ ማሰብ ፍፁም የዋህነት ነው።

ለመከላከያ ሠራዊት፣ የፖሊስ ኃይልና የኢሕአዴግ ደጋፊዎች፣ እናንተ የምትደግፉት ሀገር አጥፊው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አባቶቻችን ደረታቸውን ለጦር፣ እግራቸውን ለጠጠር ሰጥተው በደማቸው ያቆዩአትን ይህችን ጥንታዊትና ታሪካዊት ሀገራችንን እያጠፋት እንደሆነ ለእናነተ የተሠወረ አይደለም። ይህንን ሀገር የማጥፋት ወንጀል የሚፈፅመው ደግሞ እናንተን በመሣሪያነት በመጠቀም ስለሆነ ይህንን ተገንዝባችሁ አሁኑኑ ከሕዝባችንና አደጋውን ለመቀልበስ ከሚታገሉ ኃይሎች ጎን በመቆም ሀገራችሁን እንድትታደጉ ስናሳስብ፣ ጥሪያችን ችላ በማለት ለሀገር አጥፊው ቡድን ተባባሪነታችሁን ከቀጠላችሁበት ግን ታሪክና ሕዝብ ይቅር እንደማይላችሁ በጥብቅ ልናስጠነቅቃችሁ እንወዳለን።

ለብአዴን አባላት፦ “እሣት አመድ ይወልዳል” እንደተባለው ካልሆነ በስተቀር፣ አባቶቻችሁ ኢትዮጵያን ከሚያጠፋ ጠላት ጋር ተባብረው እናት ሀገራቸውን አላጠፉም፤ ይልቁንም ደማቸውን አፍስሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው የታፈረችና አንድነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለእናንተ አስረከቧችሁ እንጅ። እናንተ ግን የጀግኖች አባቶቻችሁ የባሕሪ ልጆች መሆን አቅቷችሁና አደራቸውን በልታችሁ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና አማራን ለማጥፋት ቆርጦ ለተነሳው የትግሬ ዘረኛ ቡድን አሽከር ሆናችሁ እናት ሀገራችሁንና ወገናችሁን እያጠፋችሁ ነው። “ለእንጀራየ፣ ለልጆቼና ለቤተሰቦቼ ስል ወይም ተገድጀ ነው ይህንን የማደርገው” የሚለው ውሃ የማይቋጥር ምክንያት እንደማያዋጣችሁ አውቃችሁ የጋራ ሀገራችንንና ወገናችንን ለመታደግ አብራችሁት እንደትቆሙ አዴኃን ከልብ የመነጨ የሀገር አድን ጥሪ ያቀርብላችኋል።

ወንድም ለሆነው የሱዳን ሕዝብ፦ የኢትዮጵያና የሱዳን ሕዝብ ለብዙ ሺህ ዘመናት ከአንድ ወንዝ ከተቀዳ ውሃ እየጠጣ፣ በመከባበር ላይ በተመሠረተና በመልካም ጉርብትና አንዱ ለሌላው የችግር ጊዜ ደራሽ ሆኖ የኖረ ወንድማማች ሕዝብ ነው። ነገር ግን ዛሬ የትግሬው ዘረኛ ቡድን በሀገር ውስጥ የሚገኙ ነገዶችን እርስ በእርሳቸው ከማናከስ አልፎ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም የአማራውን ነገድ ወንድም ከሆነው የሱዳን ሕዝብም ለማናከስ ቆርጦ የተነሳ በመሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዕውቅና ውጭ የተፈረመን የድንበር ስምምነት እንዳይቀበል በጥብቅ እናሳስባለን።

በመጨረሻም የዓለም ምንግሥታትና ዓለም – አቀፍ ሠላም ወዳድ ሕብረተሰብም የወያኔ ዘረኛ ቡድን ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ፈፅሞ እንደማይወክልና አሁን ከሱዳን መንግሥት ጋር በድብቅ የተፈራረመውንም የድንበር ስምምነት ንቅናቄያችን አዴኃን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደማያውቁት ተገንዝበው ስምምነቱ አሁንም ይሁን ወደፊት በሁለቱ ሀገራት ሕዝብ መካከል የሚፈጠረውን ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለስምምነቱ ዕውቅና እንዳይሰጡና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመውን ይህንን ሤራ እንዲቃወሙ አዴኃን ጥሪውን ያስተላልፋል።
በደም የተረከብናትን ሀገር በደም እንጠብቃታለን!!

እሁድ ታህሳስ 13/2006

በግፍ እስር ላይ የሚገኙትን ጀግኖቻችንን ንጽህና ለመመስከርና የህዝበ ሙስሊሙ ድምጽ መሆናቸውን በህግ ፊት በተጨባጭ ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በጀግኖቻችን ጠበቆች አማካኝነት እየተደረገ ያለው ይኸው ጥረት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ሲሆን ኮሚቴዎቻችን መንግስት ከለጠፈባቸው የሀሰት ውንጀላ ፍጹም የጸዱ መሆናቸውን በፍርድ ቤት ቀርበው የሚመሰክሩ ሰዎችን የማሰባሰቡ ሂደትም የፍቃደኝነት ፎርም በማስሞላት መልክ የተጀመረ መሆኑ ታውቋል፡፡

መሪዎቻችን በተለያዩ ህዝባዊ መድረኮች ላይ ህዝበ ሙስሊሙን በሰላማዊ አካሄድ ላይ አደራ ያሉባቸው በርካታ ንግግሮቻቸው በማስረጃነት እንዲውሉ ለማድረግ እንዲሰባሰቡ እየተደረገ ሲሆን በተለይ በመጀመሪያዎቹ የአወሊያ ፕሮግራሞች እና በኋላም በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች በተደረጉት የሰደቃና የአንድነት ፕሮግራሞች ላይ የተቀዱት የድምጽና የምስል ማስረጃዎች መሰባሰባቸው በዚህ ረገድ እጅግ ጠቃሚ መሆኑ ታውቋል፡፡

መሪዎቻችን በመሳጂዶች ላይ ከተደረጉት ፕሮግራሞች በተጨማሪ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በመቅረብ ሲያደርጓቸው የነበሩ ንግግሮችና የህዝበ ሙስሊሙን ሰላማዊና ግልጽ ጥያቄዎች ለማብራራት ቃለ መጠይቅ የሰጡባቸው የራዲዮ ፕሮግራሞች፣ ጋዜጦች፣ መጽሄቶችና ሌሎችም የሚዲያ ውጤቶች በጠበቆች አማካኝነት እየተሰባሰቡ መሆኑ ተዘግቧል፡፡

ህዝበ ሙስሊሙ ለህዝብ ድምጽ በመሆናቸው ብቻ መንግስታዊ የሀሰት ፍረጃ ሰለባ የሆኑትን መሪዎቹን ንጽህና ለማረጋገጥ እስከጥግ ድረስ መልፋት ያለበት ሲሆን በመንግስታዊ ተጽእኖ ስር በወደቀው የፍርድ ሂደትም ውስጥ ቢሆን የመሪዎቻችንን ንጽህና ለመመስከር ከምንጊዜውም በላይ ቆርጦ በመዘጋጀት የሚከፈለውን ሁሉ መስዋእትነት መክፈልም በትከሻው ላይ ያረፈ ሀላፊነት መሆኑ እሙን ነው!

ድምጻችን ይሰማ!