ወያኔ እና ባዶ ካርቶን ዲያስፖራዎች ሰው አናት ላይ ሊሸኑ ይፈልጋሉ::

ተቃዋሚ ነን የሚሉ ፓርቲዎች እና ግለሰቦች ካለምንም አላማ በጥላቻ እና በስድብ ላይ ተመስርተው በእጅ ቅሰራ ላይ ስለተመረኮዙ ሁሌ እንዳወሩ ይኖራሉ::ጫካ ገብቶ መበርታት ከጀመረበት እና ሱዳን ላይ የተደላደለ የመሸጋገሪያ እርከኖችን ካገኘበት ጊዜ አንስቶ ወያኔ አለማቀፍ አሸባሪ እና ማፊያ ቡድን መሆኑ የታወቀ እና እስካሁንም ከመዝገብ ላይ ያልተፋቀ መሆኑ ይታወቃል::

ከሱ ለመስተካከል የሚራወጡ ሆኖም ያልተሳካላቸው ደሞ እየተፈጠሩ እየከሰሙ እየተፈጠሩ ነው….እነሱ ቀድመው ካልተናገሩ በስተቀር ሁሉ ነገር ከወያኔ የሚመጣ የሚመስላቸው ባዶ ካርቶን ዲያስፖራዎች ሰው አናት ላይ ሊሸኑ ይፈልጋሉ::

በእርግጥ አንገብጋቢ የህዝብ ጥያቄዎች ሲበረቱበት ወያኔ የሚፈጥራቸው የሃሰት ተባራሪ የአየር በኣየር ፕሮፓጋንዳዎች ባንድ ጊዜ ተለግተው አለምን ያዳርሳሉ :: ይህ ዛሬ ሳይሆን ከጅምሩ የተረጋገጠ ጉዳይ ሲሆን አልተነቃብኝም የሚለው ወያኔ ይህንን ይዞ እየተመመ ነው:: አንዳንድ ግዜ ደግሞ የዜና ማሰራጫዎች ከወጡት ዜናዎቻቸው ላይ የተወሰዱ ጉዳዮችን እና ሌሎች አላስፈላጊ ነገሮችን በወያኔ ላይ መለጠፍ አንድም የዲያስፖራው ስንፍና ነው ሌላም የትግል ድቀት ውጤት ነው::

ይህን አጋጣሚ ተጠቅሞ እንዴት እንደተሰራጬ ማጋለጥ እንጂ ሁሉንም የወያኔ ቋንቋ ማድረግ የዋህነት አይመስልም:: አብዛኛው ተቃዋሚ ነን የሚሉ ፓርቲዎች እና ግለሰቦች ካለምንም አላማ በጥላቻ እና በስድብ ላይ ተመስርተው በእጅ ቅሰራ ላይ ስለተመረኮዙ ሁሌ እንዳወሩ ይኖራሉ::