የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ 702 ቦይንግ 767 አይሮፕላንን የጠለፈው ኃይለመድኅን አበራ ታላቅ ወንድም ታናሽ ወንድማቸው በአዕምሮ ጤና ችግር ላይ እንደሚገኝ ገለፁ፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት የተራቀቁ የስለላ ሶፍትዌሮችን እየለቀቀባቸው የኮምፕዩተሮቻቸውን ይዘት እንደሚሠርቅ እና የግል ግንኙነቶቻቸውንም እንደሚከታተል በውጭ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስሞታዎችን እያሰሙ መሆናቸው እየተነገረ ነው፡፡

አንድ የዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ነዋሪ በዩናይትድ ስቴትስ ፌደራል ፍርድ ቤት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ክሥ መመሥረታቸው፤ ሌላ አንድ ሰው ደግሞ ለእንግሊዝ ፖሊስ አቤቱታ ማስገባታቸው ታውቋል፡፡

ከትናንት በስተያ ማክሰኞ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ውስጥ በሚገኝ አንድ ፌደራል ችሎት የተከፈተ ዶሴ ከዚህ የስለላ አድራጎት ጀርባ ያለችው ኢትዮጵያ እንደሆነች ጠቁሞ ከሣሹ የአሥር ሺህ ዶላር የጉዳት ካሣ እንዲከፈለው ጠይቋል፡፡

እንግሊዝ ዋና ከተማ ለንደን ላይ በቀረበ ሌላ ክሥ እዚያ በስደት የሚኖሩትና የግንቦት ሰባት ሥራ…

በበረራ ቁጥር ET 702 የተመዘገበው የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አውሮፕላን በረዳት አብራሪው እንደተጠለፈ ታወቀ። ጠላፊው አሮፕላኑን ጄኔቫ ከተማ ሲያሳርፍ የስዊስ መንግሥትን የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቁም ተገልጧል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ኰሚዩኒኬሽን ጽ/ቤት በበኩሉ ጠላፊው ሊያመልጥም ነበር ብሏል። ጠላፊው በስዊስ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር ውሏል። ለዝርዝሩ ዘገባዎቹን ከዚህ ያድምጡ።

አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በርሚንግሃም ላይ ከትናንት በስተያ በተካሄደው የቤት ውስጥ 2 ማይልስ ወይም ሦስት ሺ 200 ሜትር ሩጫ ውድድር 9 ደቂቃ ከ4.8 ሰከንድ በመግባት አዲስ የዓለም ክብረወሰን አስመዘገበች፡፡

በምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮቹ የጋራ ልማት ባለሥልጣን – ኢጋድ አማካኝነት በሚካሄደው ድርድር ለመሳተፍ አዲስ አበባ የገቡት ሰባት ከእሥር የተፈቱ የቀድሞ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተቀሩት አራት እሥረኞችም እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ።

የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር – ኦብነግ በቅርቡ ኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ “ተጠልፈውብኛል” ባላቸው ሁለት ከፍተኛ የአመራር አባላቱ ላይ ድብደባና የሥቃይ አያያዝ መድረሱን ግንባሩ አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያና የግብፅ የውኃ ሚኒስትሮች ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ያደረጉት ስብሰባ ያለስምምነት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ለቪኦኤ ዛሬ ማምሻውን ገልፀዋል፡፡

ናይል ቤዚን ኢኒሽየቲቭ እየባለ የሚጠራው የናይል ተፋሰስ ጅማሮ ባለፈው ሣምንት አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው የምሥራቅ ናይል ሃገሮች ስብሰባ ላይ ግብፅ እንደማትሣተፍ በፅሁፍ አሣውቃ መቅረቷ ተገልጿል፡፡

የምሥራቅ ናይል ንዑስ ተፋሰስ መርኃግብር ሚኒስትሮች ምክር ቤት ደቡብ ሱዳንን አባል አድርጎ ተቀብሏታል፡፡

የግብፅ የመስኖ ሚኒስቴር ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ መሠረት ግብፅ ባለፈው ሣምንት ከጥር 21 እስከ ጥር 23 / 2006 ዓ.ም ቢሾፍቱ ላይ በተካሄደው የምሥራቅ ናይል ንዑስ ተፋሰስ የድርጊት መርኃግብር አባል ሃገሮች ስብሰባ ላይ እንደማትገፀ አስታውቃ ቀርታለች፡፡

የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር ሞሐመድ አብዱል ሙታሊብ ዩም-7 ለሚባል የሃገራቸው ጋዜጣ በሰጡት ቃል ግብፅ የናይል ተፋሰስ የትብብር ጅማሮ ወይም የናይል ቤዚን ኢኒሽየቲቭን የስብሰባ ጥሪ…