አንድነት ፓርቲ ከ33ቱ ፓርቲዎች ስብስብ ጋር በመሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ ያቀዱት ሰላማዊ ሰልፍ በገዢው ፓርቲ (መንግስት) ክልከላ ሠልፉ ሊደረግበት ወደነበረው መስቀል አደባባይም ሆነ በአማራጭ ነት ያቀረቡት 9 አደባባዮች እንዳይንቀሳቀስ ተደርጎ ከአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት እስከ ቀበና አደባባይ ባለው አስፋልት ላይ ቁጥሩ ከ80 ሺህ በላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተገኙበት ደማቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ተደርጓል፡፡ ለዚህ ደማቅ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለሶስት ወራት የሚቆይ ህዝባዊ ንቅናቄ በስትራቴጅው መሰረት በመጀመር፤ በመላው አገሪቱ የሚገኙ አባላቶቹንና ደጋፊዎቹን በማንቀሳቀስ ሕዝቡን ያሳተፈ ትግል በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎችንና ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማከናወኑ የሚታወቅ ነው፡፡ የሚልዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ አራት መሰረታዊ ጥያቄዎችንና ወቅታዊ ጉዳዮችን ያነገበ ሲሆን እንደ […]

የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ዛሬም ታግተው ወደ አራዳ ፓሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡ አብረዋቸው የታሰዩት አመራሮችና አባላት እንደሚከተለው እንዘረዝራለን በፖለስ የታሰሩ አመራሮችና አባላት በከፊል ========================= ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ – የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር የተከበሩ ግርማ ሰይፉ – የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበር አቶ ስዩም መንገሻ – የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ – የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት […]

የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና ብቸኛው ተቃዋሚ የፓርላማ አባል አቶ ግርማ ሰይፉ፣ተክሌ በቀለ፣ ዳንኤል ተፈራ፣ አበበ አካሉ፣ ስዩም መንገሻ፣ሀብታሙ አያሌው፣ብሩ ብርመጂ የተባሉት የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አራዳ በሁለት የፖሊስ ፒካፖች ታግተው ወደ አራዳ ፓሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡ እገታውን የሚያሳየውን ቪዲዮ ከደቂቃዎች በኋላ እንለቃለን፡፡ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች በእስር ላይ ቢገኙም የፓርቲው አባላት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች በሜጋፎን በመታገዝ የቤት ለቤት […]

አንድነት እና የ33 ፓርቲዎች በጋራ የጠሩትን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ ለቅስቀሳ ዛሬ ማለዳ ወደ ፈረንሳይ አካባቢ ተንቀሳቅሶ የነበረ መኪና በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን እውቅና ለተቸረው ሰላማዊ ሰልፍ የሚደረገውን ቅስቀሳ ለመቅረጽና የህዝቡን ስሜት ለመመልከት ካሜራና ላፕ ቶፕ በመያዝ ከቀስቃሽ ቡድኑ ጋር የተጓዘው የፍኖተ ነጻነት ጋዜጠኛ አሸናፊ አሳምነው ከሌሎቹ የተለየ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ በስፍራው የሚገኙ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ […]

በደሴ፣ ጎንደር፣ ባህር ዳር፣ ፍቼ፣ አዳማ/ናዝሬት፣ ሮቢ/ባሌ፣ መቀሌ፣ ወላይታ ሶዳ፣ ጂንካ፣ አርባ ምንጭ …ሰላማዊ ሰልፎችና ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል። በአዋሳ፣ ድሬደዋ፣ ወሊሶ፣ አሶሳና ጋምቤላ፣ እቅዱ ዉስጥ የነበሩም ቢሆንም በገንዘብ አቅም ምክንያት ለጊዜዉ ሰልፎች ሊካሄዱ አልቻሉም። መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም ትኩረቱ አዲስ አበባ ፊንፊኔ ይሆናል። የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት የጀመረዉ የመጀመሪያዉ ዙር የሶስት ወራት እንቅስቃሴ የሚደመደምበት ! […]

የከቀኑ ስምንት ሰዓት ጀምሮ በሁለት ፖሊስ ጣብያዎች ታስረው የነበሩት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ በስተመጨረሻ በሃላፊዎቹ ጣብያውን ለቀው እንዲወጡ ተነግሯቸው በአሁኑ ወቅት ወደ ቢሯቸው እየተመለሱ ነው፡፡ የቀድሞውን ፕሬዘዳንት አስረው የነበሩት ፖሊሶች ፋታ በማይሰጥ ሁኔታ የስልክ ልውውጥ በማድረግ ነጋሶን ለቅቀዋል፡፡ በተያያዘ ዜና የጨነቀው ፖሊስ መኪኖችን ማሰር የጀመረ መሆኑ ተገለጸ፤ በጃንሜዳና ቄራ ፖሊስ ጣብያዎች ታስረው የዋሉት የአንድነት አባላት አመሻሹ […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የታሰሩ የፓርቲውን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ለማስፈታት ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የሽሮ ሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣብያ በማምራት ለፖሊሶቹ ‹‹ልጆቹ የፈጸሙት ህገ ወጥ ድርጊት የለም፣ሲቀሰቅሱ የነበሩትም እውቅና የተሰጠውን ሰላማዊ ሰልፍ ነው፡፡ቅስቀሳው ህገ ወጥ ነው የምትሉም ከሆነ እነርሱን የላኳቸው እኔ በመሆኔ እኔን ልታስሩኝ ትችላላችሁ ››ብለዋል፡፡ ፖሊስ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶክተር […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ የታሰሩ የፓርቲውን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ለማስፈታት ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ የሽሮ ሜዳ ፖሊስ ማዘዣ ጣብያ በማምራት ለፖሊሶቹ ‹‹ልጆቹ የፈጸሙት ህገ ወጥ ድርጊት የለም፣ሲቀሰቅሱ የነበሩትም እውቅና የተሰጠውን ሰላማዊ ሰልፍ ነው፡፡ቅስቀሳው ህገ ወጥ ነው የምትሉም ከሆነ እነርሱን የላኳቸው እኔ በመሆኔ እኔን ልታስሩኝ ትችላላችሁ ››ብለዋል፡፡ ፖሊስ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶክተር […]

አንድነት ፓርቲ በመጪው እሁድ መስከረም 19 ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 15 አባላቱ ህገወጥ እስር ተፈፀመባቸው፡፡ አባላቱ ከስድስት ኪሎ ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው ጎዳና በመኪና ላይ እየቀሰቀሱ ባለበት ወቅት ሚኒሊክ ት/ቤት ፊትለፊት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የሚተላለፈውን መኪና መንገድ በመዝጋት ቅስቀሳውን አደናቅፈዋል፡፡ በስፍራው የነበሩ በርካታ ሰዎች “ቀስቃሾቹ ህጋዊ ወረቀት ይዘዋል፤ልቀቋቸው” […]

21 ሰፕተምበር 2013 የግንቦት 7 ሳምንታዊ ርእሰ አንቀጽ በሚል ነሐሴ 25 እና 26 ቀን 2005 በኢትዮጵያዉያን አቆጣጠር ወያኔ በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የፈጸመዉን የመብት ጥሰት አስመልክቶ የወጣዉን ጽሑፍና አቶ ተክሌ በጽሁፉ ላይ ያቀረበዉን ትችት አንብቤአለሁ:: ወደ መሰረታዊ ጉዳዩ ከመግባቴ በፊት ግንቦት ሰባትም ሆነ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ከትግል ስልት ልዩነት በቀር ለአንድ አላማና ግብ ለሚታገሉ […]

ላለፉት ሶስት ወራት ስኬታማ ህዝባዊ ንቅናቄ ሲያደርግ የቆየው አንድነት ፓርቲ የመጀመሪያውን ዙር ለሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ከሰላሳ ሶስቱ ፓርቲዎች ጋር በሚያደርገው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ያጠናቅቃል፡፡ የህዝባዊ ንቅናቄው አካል የሆነው የበይነ መረብ ዘመቻ(online social media campaign) ከመስከረም 14-18 ቀን 2006 ዓ.ም ይደረጋል፡፡ ዘመቻው ትኩረት የሚያደርገው የሚሊዮኖች ድምፅ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ፓርቲውን ለቀጣዮቹ 3አመታት በሊቀመንበርነት ለመምራት ከተወዳደሩት 5 ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ 3ቱን ለመጨረሻው ዙር ውድድር እንዲያልፉ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መርጧል፡፡ ፓርቲውን በሊቀመንበርነት ለመምራት የተወዳደሩት አቶ ትግስቱ አወሉ፣ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው፣ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ አቶ ሽመልስ ሀብቴ እና አቶ ተክሌ በቀለ ናቸው፡፡ ዛሬ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት በሚስጥር ድምፅ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በጋራ በመሆን በመጪው መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚወጣ አስታወቀ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በበኩሉ ሰልፉ እንዲሳካ ከሰልፉ ዋና አስተባባሪ አንድነት ፓርቲ ባልተናነሰ ሁኔታ ንቁ ተሳታፊ እንደሚሆን ገልጿል። የአንድነት ፓርቲ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስራት ጣሴ እና የመላው […]

ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሠላማዊ ትግላቸውን አድማስ ለማስፋት ከወትሮው በተሻለ ሁኔታና መተጠናከረ መንገድ በመላ ኢትዮጵያ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ ይህ እንቅስቃሴያቸው ግን ከመንግሥት የሕግ ጥበቃ ከማጣቱ የተነሳ ፓርቲዎቹ ከፍ ያለ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ይህንን ሕገ-ወጥነት ሕዝቡ እንዲያውቀውና እንዲታገለው ይህንን መግለጫ ማውጣት አለስፈላጊ ሆኗል፡፡ ፓርቲዎቹ የተንቀሳቀሱባቸው ተግባራት በሕግ የተፈቀደላቸው ናቸው፡፡ አባላትን፣ ደጋፊዎችንና ሌሎችንም ዜጎች በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና […]

1. ከግንቦት ሰባትና የግንቦት ሰባት አመራር አባላት የማደንቅላቸው ድንቅ ነገር ቢኖር ሌሎችን ያለመተናኮስ ባህርያቸው ነው። ሌሎች ቢተነኩሷቸውም እንኳን፤ ምንም ምላሽ ያለመስጠት አቋማቸውን አደንቅላቸዋለሁ። እስካለፈው ሁለት ሳምንት ድረስ። ባለፈው ሁለት ሳምንት ግን፤ በራሳቸው አነሳሽነት አገር ቤት ያሉትን ድርጅቶች ወደመተንኮስ ያዘነበሉ ይመስላል። በተለይም ሰማያዊ ፓርቲን። ስለዚህም ጥያቄ ተነሳብኝ። 2. ግንቦት ሰባት፤ ነሀሴ መጨረሻ ላይ፤ http://www.ginbot7.org/2013/09/02/በሰማያዊ-ፓርቲ-አባላት-በደረሰው-ወያኔያ/ አንድ ርእሰ […]

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የዘመን መለወጫን በዓል ምክንያት በማድረግ ሰሞኑን በርከት ካሉ የመንግሥት ጋዜጠኞች ጋር ቃለ ምልልስ አካሂደዋል፡፡ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በቀጥታ በኤርትራ ቴሌቪዥን ጣቢያ በተላለፈው ቃለ ምልልስ፣ ፕሬዚዳንቱ በአገሪቱ ውስጥ ስላሉ ወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮችን ያብራሩ ሲሆን፣ የአካባቢውን ዲፕሎማሲያዊና ፖለቲካዊ ጉዳይ በተመለከተም ገለጻ አድርገዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በዚህ ሰፊ ቃለ ምልልሳቸው ስለአገሪቱ የግብርና ልማት፣ […]

አንድነት ፓርቲ ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር ለመስገረም 19 የጠራውን የተቃውሞ ሰላማዊሰልፍ የማደናቀፍ በመንግስት የተለያዩ ስብሰባዎች እየተጠሩ ነው፡፡ አንድነት መስከረም አምስት ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የተጠበቀውን ያክል ህዝብ እንዳይወጣ፣ መንግስት በአዲስ አበባ ባሉ የመንግስትና የህዝብ ት/ቤቶች ወላጆችን ለስብሰባ ጠርቶ የነበው፡፡ ሆኖም አንድነት ሰልፉን ወደ መስከረም 19 ሲያስተላልፍ ይሄንኑ የወላጆች ስብሰባ ወደ መስከረም 19 ማዛወሩን ትላንት ለስብሰባ […]

ቢቢሲ የ12 ሚሊዮን ሕዝብ ባለቤት በሆነችውና የተጠናወታት ድህነት ሳያንሳት በጦርነት ስትናወጥ በከረመችው ቻድ ያለው የስነ አእምሮ (psychiatrist) ሐኪም አንድ ብቻ ነው ይለናል። ቻድስ ሰብ ሰሃራ አፍሪካ ተብሎ በሚታወቀው ቀጠና ከሚገኙት አገሮች ሁሉ በባሰ ሁኔታ የድሆች ድሆች መሆኗ ታውቆላታልና ዜናው አያስገርምም።ለመሆኑ ገዳይና አካል አሰናካይ የሆነው የልጅነት ልምሻ (polio ) ተመልሶ ተዛመተባት ከተባለ በኋላ በማግስቱ ደግሞ የሕጻናትን […]

አንዱአለም አራጌና ቤተሰቦቹ “ዘሐበሻን እና ሌሎች ሚዲያዎችን የመድረስ አቅም ያላቸው እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን አንዷለም አራጌን የአመቱ ሰው አድርገው መምረጣቸውን መስማቴ ታላቅ ደስታ ሰጥቶኛል። አንዷለም ለህዝቡ እና ለአገሩ ብዙ ያበረከተ እና የተጠየቀውን መስዋዕት ሁሉ ካለ ምንም ስስት የከፈለ እና በመክፈል ላይ የሚገኝ ድንቅ ግለሰብ በመሆኑ ለአንዷለም ይኽን እውቅና በመለገሳችሁ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ። እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1998 ዓ.ም. […]

አርባ ቀኔ ሆነ ከተለየኋችሁ፣ ድምጼን ከሰማችሁ ዓይኔንም ካያችሁ፣ ከጠየቃችሁኝ ካነጋገርኳችሁ፣ አርባ ቀኔ ሆነ ከሄድኩኝ ትቻችሁ። ምን አደረጋችሁ እኔ ከተለየሁ፣ ጉልበቴ ከከዳኝ ትንፋሼንም ካጣሁ፣ ዝናብ ካረጠበኝ፣ ፀሐይም ከመታኝ ፣ ከተለየኋችሁ አርባ ቀኔ ሆነኝ ። ለአርባው ፍትሃት በሚዘጋጀው ዝግጅት ላይ ውድ ባለቤቱ እንድታነብለት ያሰበውን ግጥም የመጀመሪያውን ክፍል ጽፎ አረፍ አለ። አልጋ ውስጥ ሆኖ ሰው ያለ አይመስልም። ስጋው […]

አንድነት ፓርቲ በመስከረም 05 ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ ይታወቃል፡፡ ይሁን አንጂ መንግስት ሁለት ምክንያቶች በማቅረብ ለሐምሌ 19 እንዲተላለፍ ጠይቋል፡፡ በመስቀል አደባባይ አካባቢ በባቡር ግንባታ ምክንያት የታጠሩ ቆርቆሮዎችን ለማንሳትና አዲሱን ዓመት አስመልክቶ በአካባቢው ባዛር እየተደረገ በመሆኑ መንግስት እንዲራዘም ጠይቋል፡፡ ለመንግስት በአዋጅ የተሰጠው ስልጣን በቂ ምክንያት ሲቀርብ እንዲያራዝም ህጉ የሚፈቅድ በመሆኑ ፓርቲያችን ህግን ተከትሎ ተቀብሎታል፡፡ ስለሆነም ይህ […]

ሀገራቸን ኢትዮጵያን ለቀው ለስደት የተዘጋጁት ዜጎችን ቁጥር መገመት አስቸጋሪ ቢሆንም በአንድ ወይም በሌላ ምክንያት መውጣት የቻሉት ግን ላለመመለስ ብዙ ምክንያቶች አሉዋቸው፡፡ ይህን የዜጎች (በተለይ የተማሩና ወጣቶች) ስደት ሀገራችንን ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈላት እንደሆነ እና ወደፊትም ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያስከትል ለማወቅ ሊቅ መሆን የሚያስፈልግ አይመሰለኝም፡፡ አሜሪካኖች በዲቪ እንኳን ሊወስዱት የሚፈልጉት ፊደል ቆጥሮ አንድ ነገር ሊያደርግላቸው የሚችለውን እንደሆነ እናውቃለን፡፡ […]

“”አግሬን ለሰው ;;፦—– አግሬን ለሰው;;፦—– አልሰጥም አለ። ከሻአቢያ ጋር ለሚያብረው ጦር,,፣—–አልከትም አለ። ባገሬ—-መሬት,,—የሰላሙ—-ትግል——ይፋፋም አለ።!!”” እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሣችሁ፤! ! ! ! መጪው አመት ወያኔን የምንገላገልበት፤። ከሻአቢያ ጋር ያበሩትና ለማበር ያኮበኮቡት ሁሉ ልቦና የሚገዙበት ፤። ከሁሉ በላይ በሀገር ወሰጥ ሀይላችውንና ጉልበታችውን፤ እውቀታችውንና ጥሪታቸውን ሳይቀር በማሰባሰብ ፊት ለፊት ከወያኔ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ በመተናነቅ ላይ ላሉት ታጋይ የፖሎቲካ […]

ጋባዥ፥ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት የሰሜን አሜሪካ ግብረ ኃይል ተጋባዥ፥ ኢትዮጵያውያን ሚዲያዎች እና የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ዜጎች በስብሰባው ላይ የሚገኙት እንግዶች፥ 1)የተከበሩ አቶ ተክሌ በቀለ – የአንድነት ፓርቲ ትሬዠረር 2)አቶ ሀብታሙ አያሌው – የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ምክትል ሃላፊ 3)የሰላሳ ሶስቱ ፓርቲዎች ተወካይ እንደሚታወቀው ላለፉት ሦስት ወራት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል አንድነት […]

አንዱአለም አራጌ (የአንድነት ምክትል ሊቀመንበር) በኢሳት ሬዲዮና ቲቪ የ2006 የዓመቱ ምርጥ ኢትዮጵያዊ እና ዘሐበሻ ድህረ ገጽ የ2006 የዓመቱ ምርጥ ሰው ተብሎ ተሰየመ!!! ይገባዋል!! አንዱአለም እንኳን ደስ አለህ!! ለቤተስቦቹ እንኳን ደስ አላችሁ!! መጪው አዲስ ዓመት የሰላም የደስታ እና የንጻነት ዓመት እንዲሆንላችሁ የአቡጊዳ ድህረ ገጽ መልካም መኞቱን ይገልጻል!!

ውድ ኢትዮጵያን ወገኖቼ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ። እዲሱ አመት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ታላቅ ብስራት ይዞ የሚመጣ ይሁን። ያለምንም ደም መፋሰስ ይህ ዘረኛ የወያኔ ገዢ ቡድን መቃብር ገብቶ፤ ዘረኝነት፤ ጎጠኝነትና በታኝነት ከምድራችን ጠፍቶ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ተፋቅሮ ተከባብሮ፤ ሲያጠፉ የሚቀጣቸውን የሚሽራቸውን፤ ሲያለሙ የሚሾማችውን የሚሸልማቸውን መሪዎች በድምጹ መርጦ፤ የሚኖርበት፤ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከዘር ማንነቱ በፊት በኢትዮጵያ ሲምል ሲገዘት የምናይበት፤ […]

በብሄራዊ በዓላት ቀን በአብዛኛው ከወደ እስር ቤት የሚሰማው ዜና አስደሳች ነበር፡፡ይህንን አጼዎቹ ፣ሰው በላው የደርግ ስርዓትና ብሶት ወለደኝ ያለን ኢህአዴግ ሲያደርጉት ቆይተዋል፡፡ በዘንድሮው አዲስ አመትም የመንግስትን ይቅርታ በማግኘት ከወዳጅ ዘመዶቻቸው የተቀላቀሉ ስለመኖራቸው ተሰምቷል፡፡በአዲሱ ዓመት ይቅርታ ከተቸራቸው እስረኞች መካከል ታዋቂ ፖለቲከኞች፣አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች አለመኖራቸው ተፈቺዎቹ በደረቅ ወንጀል ታስረው የነበሩ መሆናቸውን ለመናገር ብዙ መድከም አይጠይቅም፡፡ መንገስት ጋዜጠኛ ውብሸት […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራሮች እድሜ ልክ ተፈርዶበት በቅጣት ቤት የሚገኘውን ሰላማዊ ታጋይ አንዷለም አራጌን ‹‹እንኳን አደረሰህ አዲሱ ዓመት ፍጹም ነጻነትህን የምትቀዳጅበት እንዲሆን እንመኛለን እንታገላለንም›› በሚል ስሜት ተነሳስተው ኬክ በማስጋገር ‹‹ከአንድነት›› የሚል ጽሁፍ አጽፈውበታል፡፡ የአንዷለም ጠያቄዎች በሩን አልፈው የያዙትን ኬክ ለማስፈተሸ አስቀማሽ ጋር እንደደረሱ አስቀማሹ ኬኩንና የተጻፈበትን እየተመለከተ አንዴ ቆዮኝ ብሎ ጥሏቸው ሄደ፡፡ አስቀማሹ ሃፊዎቹን […]

መቸም የዘመን ዑደት ማለት አሮጌው አልፎ አዲሱ የሚተካበት፣ ዘር አፈር ቅሞ ወሀ ጠጥቶ በቅሎና አብቦ የሚያሸትበት መስከረም ማለትም አይደል? አዎ አዲስ ዘመናችን ምድሪቱ ጭጋግን ለብሳ፣ አራዊቱ ያጠራቀሙትን ስብ እያቀለጡ የሚኖሩበት፣ አእዋፍ ስደት የሚጀምሩበትና የሰው ልጅ አንደ በቆሎ በልብስ የሚጠቀለልበት የበረዶ ወቅት ባለመሆኑ እርግጥም አዲስ አመት ነው። በምንም መስፈርት በማንም መለኪያ ዘመን አቆጣጠራችን ለኛ ተገቢም ትክክልም […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ላለፉት ሦስት ወራት ‹‹የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት›› በሚል መሪ ቃል በመላ ኢትዮጵያ ህዝባዊ ንቅናቄ ሲያደርግ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በጎንደር፣ በደሴ፣ በባህርዳር፣ በአርባ ምንጭ፣ በጅንካ፣ በፍቼና አዳማ ከተሞች ሕዝቡን ያሳተፉ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች ያጋጠሙ የገዥው ፓርቲ እንቅፋቶችን እየተራመደ በተሳካ ሁኔታ ያደረገ ሲሆን በተለያዩ ከተሞች ሕዝባዊ ስብሰባዎችንም አከናውኗል፡፡ ፓርቲያችን የመጀመሪያውን ሕዝባዊ […]

አዲሱ ዓመት ለዘመናት በህዝባችን ጫንቃ ላይ የተጫነው አምባገነነዊ መንግስት በሰላማዊ ትግላችን ተሸንፎ ነፃነት እና እኩልነት የሚሰፍንበት ፤ የእምነት ተቋማት የሀይማኖት ስርአታቸውን ያለማንም ጣልቃ ገብነት የሚያከናውኑበት፤ የሰላም ፤የፍቅር እና የጤና እንዲሆን ፤ እየተመኘን ይህ እንዲረጋገጥ ፓርቲያችን ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የጀመረውን ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥል እንገልፃለን ፡፡ ድል የህዝብ ነው !!!! ዘለዓለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ […]

እውነት የማይመስሉ ግን እውነት የሆኑ የሙስና ታሪኮች – በኢትዮጵያ። አሁን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ወደ 2006 ተሻግረናል። ከአመት ወደ አመት ስንሸጋገር ደግሞ ያለፈውን አመት የሙስና ነገር በገደምዳሜ ዳሰስ አድርገን ብናልፍ ክፋት የለውም። በመሆኑም የስራ ባልደረባዬ ክንፉ አሰፋ “ክፍል አንድ” ብሎ በጀመረው የሙስና ጉዳይ… “ክፍል ሁለት” ብዬ እኔ ቀጠልኩበት፤ አንብቡት። የጉምሩክ ከፍተኛ ሃላፊዎች ሲታሰሩ፤ በየፊናው የነበሩ ጉምቱ ባለስልጣናት […]

አንድየ ሆይ! ያላንተ እዚህ መድረስ አይታሰብምና ከሁሉ አስቀድሜ ለከበረው ስምህ ፣ ለማይደፈር ለማይገሰሰው ሰማያዊ ክብርህ ፣ ለቸርነት ፣ ምህረት ይቅርታህ ምስጋና ይድረሰው! አባታችን አዳም ትዕዛዝክህ ተላልፎ ታላቁን ስህተት ፈጸመ ፣ ከገነትም ተባረረ ! አባት ሆይ ! አዳም አጠፋ ብለህ አልተውከንም ! የምህረት አምላክ ነህና መንግስትህን እንወርስ ዘንድ በህግ ትዕዛዛትህ እንድንመራ አዘዝከን! ዳሩ ግን ትዕዛዛት ህግ […]

ከጉልበተኞች ጠመንጃ የሚወጣ ጥይት ስጋን እንጂ እምነትን ሊገድል እንደማይችለው ሁሉ፣ ከቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ ተነጥሎ ቅዝቃዜ በዋጠው ጠባብ ክፍል ውስጥ መታሰርም አካልን እንጂ ምናብን (ህልምን) ሊያስር የሚችልበት ጉልበት የለውም፡፡ ከቶስ እንደምናብ ሜዳውን፣ ተራራውን፣ ቁልቁለቱን፣ ዳገቱን፣ ሸለቆውን፣ ኮረብታውን በሰከንድ ክፍልፋዮች ከብርሃን ፈጥኖ በመምዘግዘግ ያለመዛነፍ ያሰበበት የሚደርስ ምን ኃይል አለ? ከጠባቧ ክፍል ውስጥ ‹‹ድርሻህ›› ተብላ በተሰጠችኝ 90 ሴንቲ […]

የተከበራችሁ የዲሲ እና አካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የነፃነት ወዳጆች ዛሬ ለዚህ መድረክ የማስተላልፈውን መልዕክት ከምን እንደምጀምር ሳስብ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መርዕ የተጀመረውን ህዝባዊ መነሳሳት መፍጠሪያ መድረክ እንደሚሆን ጥርጥር አልነበረኝም፤ ነገር ግን ሀገር ውስጥ በሚታተም አንድ መፅሄት ላይ ወጥቶ ለንባብ የበቃውን የአንዱዓለም አረጋጌን “የሐምሌ ጨረቃ” መጣጥፍ ሳነብና የእርሱን የሰለማዊነት መንፈስ ለገዥዎቻችን ግን የአሸባሪነት ድምፅ ትንሽ ማለት […]

ገዥዎቻችን መከፋፈል ስልጣንን ለሀያ ሁለት አመታት ያፀኑበት ዋና መሳርያቸው ነው። ሁሌም ለማራራቅ አጠንክረው ሲሰሩባቸው ከኖሩት ማህበረሰባዊ ልዩነቶች አንዱ በአገር ቤትና በውጪ አገራት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ መሀከልም ነው። አሁን አሁን ይህ በተጠናከረና በረቀቀ መንገድ እየተሰራበት እንዳለ በግልፅ ይታያል። በወያኔዎች ዘንድ ትላልቆቹን መህበረሰባዊ ልዩነቶች አይደለም ከቅርበት አኳያ የተወሰኑ ዜጎች የሀመረኖ የቀሩት ደግሞ የጎርፍ አሶጋጅ እድርተኛ መሆናቸው እንደ አንድ […]

የአዳማ ሰልፍ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተጠናቅቋል!!! ኢቴቪ በአዳማ የሁከት ድራማ በመስራት ለመቅረጽ ያደረገችው ሙከራ ከሸፈ ብራቮ አዳማዊያን! ጉዞ ወደ አዲስ አበባ! በጎንደር፣ ደሴ ፣ባህር ዳር፣ጂንካ፣ ወላይታ፣ባሌ ሮቢ፣ ፍቼ፣ አርባ ምንጭ ዛሬ አዳማ ቆይታ በማድረግ የሚልዮኖችን ድምጽ ያሰማው የአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ህዝባዊ ንቅናቄ ለመስከረም 5/2006 የመስቀል አደባባይ ሰለማዊ ሰልፍ ጓዙን ጠቅልሎ ሸገር ገብቷል፡፡ በዛሬው […]

በህገ መንግስቱ መሰረት ለአዳማ አስተዳደር አንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግና መስተዳድሩ ይህንኑ በማወቅ አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርግ በደብዳቤ ካሳወቀና መስተዳድሩም የሰልፉ ቀን ይቀየርልኝ በማለት ባቀረበው ምክንያት የተነሳ አንድነት ሰልፉን ለፊታችን እሁድ ማዞሩን አስታውቆ ቅስቀሳ ይጀምራል፡፡ ድራማ 1 በራሪ ወረቀቶች መበተን እንደተጀመሩ ፖሊስ አባላቶችን ጣብያ በመውሰድ መበተን አትችሉም አለ፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ አሳውቀናል፣ ይህ ወረቀት ለሰላማዊ ሰልፍ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት) ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንቅስቃሴ የበለጠ ተጠናክሮ ህዝቡ የትግሉ መሪ ተዋናይና ባለቤትነት እንዲረጋገጥ ላለፉት ሶስት ወራት ፓርቲያችን ባስቀመጠው ስትራቴጂ እቅድ መሠረት ሰፊ ህዝባዊ ንቅናቄ ሲያደርግ ቆይቱዋል፡፡ በሃገራችን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ማለትም ፖለቲካዊ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መረገጥ ፓርቲያችን “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል ሰኔ 13ቀን 2005 በይፋ ለጀመረው ሕዝባዊ ንቅናቄ […]

መግቢያ በዚህ አርዕስት ላይ ለመጻፍ ከአሰብኩ ረዥም ጊዜ ሆነኝ። እንደሚታወቀው አንድ ጥናታዊ ጽሁፍ ለማቅረብ ቀላል አይደለም። የመንፈስ ርጋታን የሚጠይቅ ብቻ ሳይሆን፣ ለአንባቢ የሚቀርበው ጽሁፍ ከርስ በርስ ቅራኔዎች የተላቀቀና አሳማኝ እንዲሆን አድርጎ ለመጻፍና ለማስነበብ ረዥም ጊዜን ይፈጃል። ብዙ ዕውቀትንና ምርምርን ይጠይቃል። ተመራምሮና የተለያዩ አስተሳሰቦችን አወዳድሮና አመዛዝኖ ለአንባቢ አንድ የሚያረካና እንደመመሪያ ጥናት ለማቅረብ ረዥም ጊዜ ብቻ ሳይሆን […]

አቶ ብስራት አቢ የአንድነት ፓርቲ የደብበ ወሎ ዞን ሰብሳቢ ዛሬ ነሃሴ 30 በምኖርባት ደሴ ከተማ በተለምዶ ባምቧ ውሃ የተባለው አካባቢ በአንድ መዝናኛ በረንዳ ላይ ከጓደኞቼ ጋር ተቀምጠን እየተጫወትን ነው፡፡ ሰዓቱ 9፡30 ይሆናል፤ ጎዳናው ላይ አንድ የገጠር አለባበስ የለበሰ ሰው ከፖሊሶች ጋር ለፀብ ሲገባበዝ ተመለከትኩት፡፡ ሰውየው ጠጥቷል እናም ፖሊሰቹን ለመተናኮስም ቃጥቶታል፡፡ ፖሊሶቹ የወሰዱት እርምጃ ግን ፍፁም […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት) ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንቅስቃሴ የበለጠ ተጠናክሮ ህዝቡ የትግሉ መሪ ተዋናይና ባለቤትነት እንዲረጋገጥ ላለፉት ሶስት ወራት ፓርቲያችን ባስቀመጠው ስትራቴጂ እቅድ መሠረት ሰፊ ህዝባዊ ንቅናቄ ሲያደርግ ቆይቱዋል፡፡ በሃገራችን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ማለትም ፖለቲካዊ፤ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የዜጎች ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መረገጥ ፓርቲያችን “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል ሰኔ 13 ቀን 2005 በይፋ ለጀመረው ሕዝባዊ […]