«ከምዕራብ ሸዋ ተፈናቅለው በፌዴሬሽኑ አፈ ጉባዔ አግባቢነት የተመለሱት ዜጎች መሬታቸውን በሃይል ተነጠቁ» ሲል ፍኖት ዘገበ። “ከሰላሳ የማያንሱ የምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ ባጅላ ዳሌ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ነዋሪዎች «ወደ ክልላችሁ ተመለሱ » ተብለው መሬታቸውን ለመነጠቅ መቃረባቸውን ለማመልከት አዲስ አበባ በመምጣት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃንን ካናገሩ በኋላ አፈ ጉባኤው ‹‹ወደ ቀዬአችሁ […]

መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም አንድነት በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የያዘውን ፕሮግራም እንዲያራዝም መጠየቁን ተከትሎ አንድነት ሰልፉን ለሚያዚያ 5 ቀን 2006 በማራዘም የእውቅና ደብዳቤ ጠይቆ ነበር፡፡ መስተዳድሩ በዕለቱ ሌላ ፕሮግራም መየዙን በማውሳት ሰልፉ ሚያዚያ 4 ቀን 2006 ሊደረግ እንደሚችል የእውቅና ደብዳቤ ለፓርቲው ጽፎ ነበር፡፡ ፓርቲው በበኩሉ ዕለቱ ለሰላማዊ ሰልፍ አመቺ አለመሆኑን አስረድቷል፣ መስተዳድሩ ፓርቲው […]

የሚቀጥለውን ትረካ ለመጻፍ ብዙ ሀሳብ ውስጥ ገብቼ ነበር፡፡ ብጽፈውስ ምን ዋጋ አለው የሚል ስሜትም ተጭኖኝ ነበር፡፡ ሆኖም ‹ጅብ በማያውቁት ሀገር ቁርበት አንጥፋልኝ› እንዲሉ ከላይ የተጠቀሰው ብርሃኑ ደቡር አባ መላ በአዲሶቹ አለቆቹ የተረቀቁለትን ቃለ መጠይቆች ሲያነበንብ መስማቱ ስለሰለቸኝ ‹ማን ያውጋ የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ› በማለት የልጅነት ጓደኛዬን ሳልወድ ለማጋለጥ ወሰንኩ፡፡ እኔና ብርሃኑ ዳምጤ በአንድ ማዕድ እየበላን […]

«በቅርቡ ከአንድነት ለደሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጋር ለመዋሃድ ጥረት እያደረጋችሁ ነው ያላችሁት። ሂደቱ ምን ላይ ይገኛል ? » በሚል ከአዉስትራሊያ ከሚገኝ ኤስ፣ብ.ሲ ራዲዮ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የመኢአድ ሊቀመነበር አቶ አበባዉ መሃሪ በአንድነት እና በመኢአድ መካከል ያሉ ልዩነቶች ከባድ እንዳልሆኑ በመግልጽ ፓርቲዎቹ ዉህደት እንደሚፈጽሙ ያላቸውን ሙሉ ተስፋ ገልጸዋል። «ተበታትነን ገዢዉን ፓርቲ ለማሽነፍ ከአብድ ነው» ያሉት አቶ […]

ዛሬ እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ/ም ዓረና ትገራይ ህዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ በምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወንበርታ ወረዳ ጠርቶ ያካሄደ ሲሆን ከትናትና ጀምሮ ህዝቡን ወደ ስብሰባው እንዲመጣ የሚቀሰቅሱ አባሎችና አመራሮች ከድንጋይ ውርወራና የቡድን ረብሻ ባለፈ ከተከራዩት አልጋ አስወጥቶ ሌሌት የትም ተጥለው እንዲወድቁ ለማድረግ እጅግ ኢ-ሰብአዊ ተግባር መፈፀሙን ተገልፆ ነበር ፡፡ የአፅቢ ፖሊስ አባላቶቻችን ከተከራየትና ገንዘቡን ከፍለው […]

የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ንቅናቄ በሚል የጀመረው እንቅስቃሴ፣ በዉጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ድጋፍ እያገኘ መጥቷል። ኢትዮጵያዉያን በአካባቢያቸው ካሉ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት ጋር በመሆን ከሚደግፉት በተጨማሪ፣ የተለያዩ ሲቪክ ማህበራት፣ በዉጭ አገር ያሉ የፖለቲካ ደርጅቶች እንዲሁም ግለሰቦች ሳይቀር፣ ጉዳዩ የአንድ ፓርቲ ብቻ ሳይሆን የሕዝብ ጉዳይ ነው፣ በሚል ከሚሊዮኖች አንዱ ነን እያሉ ነው። ከነዚህ፣ አገር ቤት እየተደረገ ያለዉን እንቅስቃሴ ከሚደግፉ […]

የአዲስ አበባ መስተዳድር የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባ ክፍል ኦፊሰር የሆኑትን አቶ ማርቆስ ብዙነህን ለማነጋገር ዛሬ ጠዋት ወደ ቢሯቸው ያቀኑት ሶስት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ አመራሮች በኦፊሰሩ ጥያቄያቸው ተቀባይነት ማግኘቱ እንደተነገራቸው ገልጸዋል፡፡ አንድነት ፓርቲ የ‹‹እሪታ ቀን›› በማለት የሰየመውን ሰላማዊ ሰልፍ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ለማድረግ ለመስተዳድሩ የእውቅና ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም መስተዳድሩ በከተማው የህዳሴ ግድቡን የተመለከቱ […]

አንድነት ፓርቲ ለመጋቢት 28/2006 ጠርቶት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ለህዝብ የተዘጋጀ በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በህገ ወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር ከዋሉት የአንድነት ፓርቲ አባላት መካከል በስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ የሚገኙት አክሊሉ ሰይፉና ወርቁ እንድሮ መታሰራቸውን በመቃወም የርሃብ አድማ መምታታቸው ታውቋል፡፡ ሁለቱ ወጣቶች እስከ ነገ የማይለቀቁ ከሆነ ሚክሲኮ በሚገኘው ፍርድ ቤት ከፖሊስ ጣብያ እንደሚቀርቡ ይጠበቃል፡፡ አንድነት የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ […]

መግቢያ በዚህ ጽሁፍ ሥር ለውይይት ይሆን ዘንድ የምናነሳው ኣሳብ constitutional patriotism ወይም ህገ መንግስታዊ ቀናዒነት ወይም ኣርበኝነት የሚባለው ጽንሰ ሃሳብ ባለፈው በተከታታይ ካቀረብኳት የ Conventional Cultural Unity ወይም በስምምነት ላይ የተመሰረት ባህላዊ ውህደት ካልኩት ኣሳብ ጋር እንዴት እንደሚለያይና በኢትዮጵያ ሁኔታ ከሁለቱ ኣሳቦች የትኛው ተገቢና ችግር ፈቺ ሊሆን እንደሚችል ኣሳብ ለማፍራት ነው። በቅድሚያ ኣንድን ፖለቲካዊ የሆነ […]

እኛ የምናውቃት ኢትዮጲያ ከግማሽ በላይ ህዝቧ በመብራትና በውሃ እጦት የሚሰቃይባት ፣ በስልክና በኔትወርክ ችግር የሚማረርባት ፣ በመልካም አስተዳደር እጦት አሳሩን የሚበላባት ፣ አብዛኛው ህዝቧ የዛሬን እንጂ የነገን ማቀድ የማይችልባት ፣ የተለያዩ ተንታኞችና አለማቀፍድርጅቶች “ችግር አለ” ብለው የሚያስጠነቅቋት ፣ ለዲሞክራሲ ፈር ቀዳጅ መሆን የሚገባው የፖለቲካ ስርዓት የሚያስፈራና ደም ደም የሚሸትባት፣ ብዙ ዜናና ትንታኔ ስለ አንዲት የመንግስት […]

የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪቃል በደሴ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ በስፍራው የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ ከፍተና አመራሮችና የዞን አመራሮች በሰልፉ ለተሳተፈው የደሴ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ‪የደሴ ነዋሪዎችም “እድሜ ለአንድነት አስተነፈሰን” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል። የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መሪ ቃል አንድነት ፓርቲ የጀመረውን ዘመቻ በማስመልከት የመጀመሪያውን ሰላማዊ ሰልፍ በደሴ ከተማ በተሳካ ሁኔታ ማድረጉ […]

ዛሬ በአለማችን ላይ መንግስታቶች ሊመሩት እና ሊያስተዳድሩት በላው ሕዝብ ላይ የሰብሃዊ መብት ረገጣ እስራት እና ግድያ በሕዝባቸው ላይ እንደሚያደርሱ ይታወቃል በተለይም የአፍሪካ መሪዎች እና መንግስታቶች በአንባ ገነንት እና የሕዝባቸውን ሰብሃዊ መብት በመርገጥ ግንባር ቀደም ተጠቃሾች ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ አገራችን ኢትዮጵያ አንዶ ናት :: በአሁኑ ሰአት በሀገራችን ኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ከጊዜ ወደ ጊዜ አይን […]

ነገ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም በሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅድቀሳእ በደመቀ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሆነ ተገልጸ። አቶ ሃብታሙ አያሌዉ ከስፋራዉ ይሄን አስተላልፈዋል ፡ ===================== “እረ ደሴ ደሴ ገራዶ ረጋዶ…….. አለቀልሽ ልቤ አንድነትን ወዶ” ይህንን የማጀቢያ ዘፈን እያሰማ ህዝቡ ከጎናችን ተሰለፈ …… ደሴ በአንድነት አባላትና ደጋፊዎች እንደደመቀች፤ ትንቅንቁም እንደቀጠለ …..ለዚህ ሰዓት ደርሰናል…ነጻነት ከፍርሃት አይገኝም!!! ድል የህዝብ ነው!! […]

የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረቦች ክስተቱን በፎቶግራፍ አንስተዋል —————– የአንድነት ከፍተኛ አመራሮችን ያካተተውን የቅስቀሳ ቡድን ተግባር ለማደናቀፍ ፖሊሶችና ደህንነት ነን የሚሉ ግለሰቦች በስውር ቪዲዮ በመቅረፅ እና ስለሙስሊሙ የመብት ጥያቄ የሚስተጋቡ መፈክሮችን ለማስቆም ሙከራ አድርገዋል፡፡ በተለይም የከተማዋ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ ቅስቀሳው በተደረገባቸው ስፍራዎች በመገኘት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን ለማስፈራራትና ከቅስቀሳ ቡድኑ አባል ላይ የቅስቀሳ ቁሳቁስ ለመንጠቅ ሲሞከር […]

የአንድነት ፓርቲ «ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን» በሚል ርእስ ዛሬ መጋቢት 26 ቀን 2006 ዓ.ም ይፋ ባደረገው መግለጫ «የአዲስ አበባ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በመጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በቁጥር አ.አ ከስ/1ዐ/3ዐ.4/236 በላከልን ደብዳቤ ሠላማዊ ሠልፉን ለማድረግ በጠየቅንበት ቀን ተመሳሳይ የህዳሴ ግድብ ፕሮግራሞች ስላሉ ተለዋጭ ቀን እንድናቀርብ ጠይቆናል፡፡ በዚሁ መሠረት ለመጋቢት 28 ቀን […]

የአዲስ አበባ አስተዳደር መጋቢት 26 ቀን ለአንድነት ፓርቲ በላከው ደብዳቤ ፣ አንድነት መጋቢት 28 ቀን ሊያደርግ ያሰበዉ ሰላማዊ ሰልፍ ፣ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ጠየቀ። ሰልፉ በታሰበበት ቀን ሌሎች ዝግጅቶች እንዳሉ የገለጸዉ የአስተዳደሩ ደብዳቤ «ተጨማሪ መስመርና ቦታ በመጥቀስ (ሰልፉን) የምታካሂዱበትን ሌላ ቀን ጭምር እንድታሳዉቁን እንገልጻለን» ሲል አስተዳደር ሕግና ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ ምላሽ ሰጧል። በመጋቢት 28 ቀን […]

በመኪና እየተዘዋወሩ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች የደሴን ሕዝብ ሲቀሰቅሱ ዉለዋል። ከደሴ 12 ኪሎሚዕት ርቃ በትምገኘዋ የኩታበር ከተማ ተመሳሳይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ ዜጎችን ፖሊሲ አስቆሞ ለማሰር ሞክሮ የነበረ ሲሆን በአካባቢው የነበረ ሕዝቡ ፖሊስን ከቦ « አታስሯቸዉም» ምንም አይነት ችግር ሳይፈጠር ፖሊሶች ገለል እንዳሉ ከደሴ የደረሰን መረጃ ይጥቁማል። የአንድነት አመራሮች ወደ ደሴ ነገ ጠዋት ያመራሉ :: የአንድነት ከፍተኛ […]

በአዲስ አበባ፣ በዛሬው ቀን በተደረገው ቅስቀሳ ከአምሳ ሶስት በላይ አባላትና ደጋፊዎች በሺሆች የሚቆጠሩ በራሪ ወረቀቶችን ሲያድሉ ዉለዋል። ከሃምሳ ሶስቱ ወጣቶች ስድስቱ ታስረዋል። እስረኞችን ለማስፈታት ወደ ፖሊስ ጣቢያዎቹ የሄዱት የአንድነት የአመራር አባላት፣ ለምን እስረኞች እንደታሰሩ የፖሊስ አዛዦችን ሲጠይቁ « ሰልፉ የተፈቀደ ሰልፍ ስላልሆነ ፣ ነገሩን እስክናጣራ ነው እንጂ አላሰርናቸው» የሚል ምላሽ ተሰጧቸዋል። «ለሰልፍ ፍቃድ አይጠየቅም። ማሳወቅ […]

«ዴሞክራሲ የለም! ሰልፍ ማድረግ አይቻልም! አርፋችሁ ተቀመጡ ! » የሚሉን ከሆነ ይንገሩን ። የአገሪቷ ሕግ የሚለው ግልጽ ነው። ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ሙሉ መብት አላቸው። አስተዳደሩ በይፋ ሕግ ወጥ ተግባር ነው እየፈጸመ ያለው። ሕጉ እንዲህ ነው የሚለው ፡ “ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ስፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለውም ምክንያቱን […]

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የእሪታ ቀን በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በተያዘለት ቀንና ቦታ እንደሚካሄድ ለመገናኛ ብዙሀን ካሳወቀበት ከትላንትናው እለት ማለትም መጋቢት 24/2006 ዓ.ም ጀምሮ ለከተማዋ ነዋሪዎች ስለሰልፉ ዓላማ የሚገልፅ በራሪ ወረቀት እያሰራጨ ይገኛል፡፡እስካሁን ድረስ ከ10.000 ሺ በላይ በራሪ ወረቀቶች ተሰራጭተዋል ፡፡ የነገውን ቅስቀሳ የአንድነት ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ እና የአዲስ አበባ […]

የሚሊዮኖች ንቅናቄ እንደዘገበው በአዲስ አበባ ቅስቀሳው ቀጥሏል። ፖሊሶች በርካታ ዜጎችን ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ እያሰሩ ሲሆን፣ አገዛዙ የዜጎችን መሰረታዊ የዉህ.፣ የኔትወርቅን የመብራትና የትራንስፖርት ችግሮችን ከመፍታት ፣ ጊዜና ጉኦልበቱን ሕግን በመናድና ዜጎንች በማሸበር ላይ ያተኮረ ይመስላል። የሚከተሉት ከሚሊዮኖች ንቅናቄ ፌስ ቡክ ገጽ የተወሰዱ ናቸው ፡ የአንድነት ወጣቶችን ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል:: ———————————————— አሁንም ፖሊስ እንቅስቃሴያቸውን እያወከ ይገኛል:: ———————————————— […]

የአንድነትፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን በአዲስ አበባ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ ማፊያው አስተዳደር የተለመደውን መልስ ሠጥቷል፡፡ ህግ እና ስርዓት ያፈነገጠ፡፡ በአስራ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ሶስት ያወጣው “ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ስርዓት” አዋጅ ቁ. 3/1983 የሚመለከተው አካል “ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ስፍራ ቢደረግ ይሻላል […]

የአንድነት ለዲሞክርሲና ለፍትህ ፓርቲ መጋቢት 28 ቀን በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ቢያሳዉቅም፣ አስተዳደሩ ሰልፉ እንዲደረግ የታሰበበት ቦታ፣ ትምህርት ቤቶች ፣ ዩኒቨርሲቲና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ያሉበት በመሆኑ እዉቅና እንደማይሰጥ የሚገልጽ፣ ከሕገ መንግስቱ የተጻረረ ደብዳቤ መላኩ ይታወቃል። የአንድነት ፓርቲ ፣ ምንም እንኳን ቀበና ከሚገኘው ጽ/ቤታቸው እስከ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ጽ/ቤት ድረስ ሊደረግ የታሰበው ሰልፍ […]

የዚህ ጽሑፍ ግብ በመንግስት ስልጣን ሽሚያ የተነሳ በአንድ ወገን በዮሐንስ እና በአሉላ ትውልድ በሌላ ወገን በምኒልክ እና በጎበና ትውልድ መካከል የነበረውን የፖለቲካ ባላንጣነት፣ ለስልጣን ሲሉ የተደራረጉትን እና የፈጸሙትን ስህተት መተረክ አይደለም። በመካከላቸው የነበረው ጸብ ዙፋኑ ለእኔ ይገባ ነበር የሚል ጸብ ነበር፡፡ የስልጣን ጸብ ነበር። በእርስ በርስ ጦርነት የሚፈጸመው ስርዓት አልባው የመንግስት ሽግግር ባህላችን የፈጠረው ጸብ […]

ግፍ ከበዛበት ወህኒ የአክብሮት ስላምታየ ይድረሳችሁ! እነሆ ለሁለተኛ ጊዜ ለአፍታ ያህል እድሉን አግኝቸ ወህኒ የመውረዴን እውነታ ላስረዳችሁ ግድ አለኝ ። ዛሬ አስረግጨ የምነግራችሁ ወህኒ የመውረዴ ምክንያት ሚስጥር ግምሽ እድሜየን ህግና ስርአቷን አክበሬ የኖርኩባትን የሳውዲት አረቢያን ህግ ተላልፊ አይደለም ! የስደተኛው ጉዳይ ያገባኛል በሚል የማቀርበው መረጃ ቅበላየ የማይመቻቸው ፣ ያመማቸው ከተሰረሰውና እየተሰራ ካለው ከእገታው ጀርባ ስለመኖራቸው […]

መጋቢት 28 የሚደረገዉን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ፣ የአንድነት አባላቶችንና ደጋፊዎች በአራት የከተማዋ አቅጣጫዎች በመሰማራት በራሪ ወረቀቶችን ለሕዝብ ሲያደርሱ እንደነበረ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። በአዲስ አበባ መንገዶች ሲሰራጩ ከነበሩ በራሪ ወረቀቶች መካከል ፡

መጋቢት 20/ 2006 ዓ.ም የወላይታ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሶዶ ውስጥ ስብሰባ ለማድረግ ዝግጅት እያደረጉ በነበረበት ወቅት ፖሊስ ምንም አይነት ምክንያት ሳይሰጥ ሰብስቦ እንዳሰራቸው ከአካባቢው የፓርቲው ተወካዮች ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት አመራሮቹ ድል በትግል በተባለው የፖሊስ ጣቢያ ታስረው ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅትም እስር ላይ ከሚገኙት መካከልም፡- 1. ወጨፎ ሳዳሞ የወላይታ ዞን ምክትል ሰብሳቢ 2. ታደመ ፍቃዱ […]

«በሀዋሳ ከተማ ታቦር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚማሩ የሲዳማ ተወላጆች የሚኒ ሚዲያ ፕሮግራም በሲዳመኛ ቋንቋ ይተላለፍ፣ ታቦር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚለውም ታፔላ በሲዳመኛ ቋንቋ ይጻፍ በሚል መነሻና ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ረብሻ ተፈጥሮ፣ የፌደራል ፖሊሶች ወደ ግቢው ሲጠጉ ተማሪዎቹ ድንጋይ በመወርወር በርካታ ፖሊሶች ቆስለዋል፡፡ ፖሊሶቹ በወሰዱት ርምጃ ብዙዎች ለጉዳት ተዳርገዋል» ሲል ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ከአዲስ አበባ […]

‪#‎udj‬@addisabeba የአዲስ አበባ የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባዎች ማሳወቂያ ክፍል ኦፊሰር የሆኑት አቶ ማርቆስ ብዙነህ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ላቀረበላቸው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ደብዳቤ ህገ ወጥ ምላሽ በመስጠታቸው ፓርቲው ደብዳቤውን የተቃወመበትን የህግ አግባብ በመጥቀስ ደብዳቤ ልኮላቸው ነበር፡፡ አቶ ማርቆስ በጽ/ቤታቸው በአካል የተላከላቸውን ደብዳቤ ምስክሮች ባሉበት ‹‹አልቀበልም ብትፈልጉ ክሰሱኝ››በማለት በህጋዊ መንገድ የቀረበላቸውን ደብዳቤ አልቀበልም በማለት መልሰዋል፡፡አንድነት ፓርቲ […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ስራ አስፈጻሚ በዛሬው ዕለት በፓርቲው ዋና ጽ/ቤት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ‹‹በህገ ወጥ መንገድ የሚቀለበስ ሰላማዊ የትግል ስልት ባለመኖሩ የአዲስ አበባ ህዝብ ለቀረበለት የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ምላሹን እንዲሰጥ በአክብሮት እንጠይቃለን››ብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ህገ ወጥ ደብዳቤ በመጻፍ ሰልፉን ማከናወን አትችሉም ማለቱ ከህግ በላይ ነኝ የሚል መንፈስ እንዳለው እንደሚያሳይ የገለጸው […]

የኢትዮጵያ ሬዲየና ቴሌቪዥን ድርጅት ከኅዳር 16 እስከ 18 ቀን 2004 ዓ.ም. በተከታታይ ሦስት ክፍሎች ‹‹አኬልዳማ›› በሚል ባቀረበው ዘጋቢ ፕሮግራም፣ክብርና ዝናን የሚያጠፋ በድምፅ፣ በምስልና በጽሑፍ በተቀነባበረ መንገድ ስሙን እንዳጠፋው በመግለጽ፣ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በመሠረተበት የፍትሐ ብሔር ክስ ተረታ፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ዘጠነኛ የፍትሐ ብሔር ችሎት መጋቢት 23 ቀን 2006 ዓ.ም. […]

አንድነት በቅርቡ ይፋ ባደረገው የሚሊዮን ድምጽ ንቅናቄ አሥራ አራት የተመረጡ ቢሆንም፣ ከአሥራ አራቱ ከተሞች ዉጭ ያሉ ሌሎች ከተሞችና ወረዳዎች ም «ለምን እኛ ጋር አልተደረገም ?» የሚሉ ጥያቄዎች እያነሱ እንደሆነ ይነገራል። ከነዚህ ቦታዎች አንዱ ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ የምትገኛው የደራሼ ልዩ ወረዳ፣ የምትገኘው የጊዶሌ ከተማ ናት። በወረዳው ያሉ ነዋሪዎች ፣ «የትግሉ መሪ እኛ ነን ። እባካችሁ በአደባባይ […]

እንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/ የፊታችን እሁድ መጋቢት28 ቀን 2006 ዓ.ም፣ በታላቋ የደሴ ከተማ፣ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርግ ለማረጋገጥ ችለናል። አስፈላጊው ባለስልጣናትን የማሳወቅ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ አንድነት በደሴ እና በአካባቢዋ ያሉ ነዋሪዎች በሙሉ፣ በነቂስ እንዲወጡና ሰላማዊ ሰልፉ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል። በከተማዋም ቅስቀሳ፣ በጥቂት ቀናቶች ዉስጥ ይጀመራል ተብሎ ይገመታል። ከስድስት ወራት በፊት፣ የሚሊዮኖች ድምጽ […]

«አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት፣ ዛሬ ባካሄደው ልዩ አስቸኳይ ስብሰባ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል መሪ ቃል የተጠራው ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ማወቅ ለሚገባው አካል ሁሉ የማሳወቅ ስራው የተጠናቀቀ በመሆኑ፣ የአደባባይ ቅስቀሳ ስራው ከነገ ማለትም መጋቢት 24 ቀን 2006 ዓ.ም፣ ጀምሮ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል እና ሰልፉ በተያዘለት ቀን እንዲደረግ ምክር […]

በመብራት መቆራረጥ የሚሰቃየው የኢትዮጵያ ህዝብ “እፎይ” የሚልበትን ቀን ሁሉም ይናፍቃል። የአባይ ወንዝ ከተገደበ በኋላ የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ከኢትዮጵያ አልፎ ለሱዳን እና ለግብጽ እንደሚበቃም ይነገራል። ከዚህ ግድብ በተጨማሪ የግልገል ጊቤ 2 እና 3 ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የሚኖራት የመብራት ሃይል በአስር እጥፍ እንደሚጨምር የዘርፉ ሙያተኞች ይመሰክራሉ። በዚህ አጋጣሚም በመብራት መቆራረጥ እና እጦት የሚሰቃየውም ህዝብ የሚካስበት አጋጣሚ ይፈጠራል። […]

ኢቲቪ ተመጣጣኝ የማስተባበያ አየር ሰዓት ለአንድነት ፓርቲ እንዲሰጥ ታዟል የዘገየ ፍትህ እንደተሰጠ ባይቀጠርም በአንድነት ፓርቲ እና በኢትጵያ ቴሌቪዥን መካከል “አኬልዳማ ዘጋቢ ፊልምን አስመልክቶ ለነበረው 3 አመታትን ለፈጀ ክርክር ለአንድነት ፓርቲ ፈርዶ መቋጫ ሰጥቶታል በመሆኑም ኢ.ቲ.ቪ የአንድነት ፓርቲን ስም በማጥፋቱ ተመጣጣኝ የማስተባቤ አየር ሰዓት ለአንድነት እንዲሰጥ ፍርድቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ችሎቱን የተከታተለው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ […]

‪በደሴ ከተማ የሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተባበር ወደ ስፍራው የተጓዙት የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ አቶ አዕምሮ አወቀ ድብደባና ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡ ዓርብ መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡15 ላይ በደሴ ከተማ በተለምዶ ቶታል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕራት በልተው ሲወጡ ታርጋ የሌለውና መስታወቱ ጥቁር በሆነ ኮብራ መኪና አጠገባቸው መጥቶ ሲቆም ከውጪ ሁለት ሰዎች […]

የአንድነት ፓርቲ መጋቢት 28 ቀን ሰልፍ እንደሚያደርግ፣ ለአዲስ አበባ አስተዳደር መጋቢት 15 ቀን ያሳዉቃል። «የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ አሰራር ሥነ-ሥርዓት በርካታ ትምህርት ቤቶች ዩኒቨርሲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ የተጠየቀዉን የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን» ሲል አስተዳደሩ ከ48 ሰዓታት በኋላ መጋቢት 17 ቀን ምላሽ ይሰጣል። […]

ትናንት እሁድ መጋቢት 21, 2006 ዓም ዓረና ከእንደርታ ህዝብ ጋር ለመወያየት በኲሓ ከተማ ሐየሎም አዳራሽ ቀጠሮ መያዙ ይታወሳል። ለስብሰባው በስፒከር ለመቀስቀስ ሞክረን እንደተከለከልን፣ የአመራር አባሎቻችንም መታሰራቸው እንደዉጤቱም የቅስቀሳ ሂደቱ መተጓጎሉ ጠቅሼ ነበር። ሁኖም ግን የዓረና አማራጭ ሐሳብ የያዘ በራሪ ወረቀት ለኗሪዎች በማደል የተወሰነ ቅስቀሳ አድርገናል። ከሌሎች አከባቢዎች ለየት ባለ መልኩ በእንደርታ ወረዳ በስፒከር እንዳንቀሰቅስ የተፈለገበት […]

በሀገራችን የኑሮ ውድነት ከእለት እለት እየከፋ የድሃውን ህዝብ ጉስቁልና እያበዛ እንደሆነ ነጋሪ የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ በቤተ መንግሰትና አካባቢ የሚኖሩት ይህ ጉዳይ አይመለከታቸውም፡፡ ለዚህ የኑሮ ውድነት አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት የዋጋ ንረት መሆኑን ብዙዎች ይረዳሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ዛሬ ለፅሁፌ ዋና ማጠንጠኛም የማደርገው የዋጋ ንረት ምንስዔው ምን እንደሆነ በተለይ የመንግሰት ሚና ከዚህ አንፃር ምን እንደሆነ ማስረዳት ነው፡፡ […]

በዛሬው እለት በቦስተን በተደረገው “የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የውደሳ እና የምስጋና ቀን” በርካታ ኢትዮጵያውያኖች በተገኙበት በደማቅ እና እጅግ በተሳካ ሁኔታ ተክናውኗል። በዚሁ ዝግጀት ላይ የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የሕይወት ታሪክ እና በኢትዮጵያ ውስጥ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር በሚደረገው የሰላማዊ ትግል ያደረገውን አስተዋጻኦ በተመለከተ የተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም የቀርበ ሲሆን፤ በወጣት ማሙሽ እና በወ/ሮ ደብረወርቅ የተዘጋጁ ጽሁፍ እና […]