መብራት ውሃ የስልክና የኢንተርኔት ኔትወርክ አገልግሎቶች መብቶች የህዝብ ናቸው!!!!! አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው …ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው::እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው የሚላተሙ የጆተኒ ተቃዋሚ […]

የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችን ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው አይችልም።የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 ዜጎች ነፍጥ ሳይዙ የመሰባሰብ፣ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች የማድረግ፣ ፔትሽኖችን የማሰባሰብ ሙሉ መብት […]

March 29, 2014 የጎሠኛነት አጭር ትርጉም ዓለምን በራሱ ጠባብ ኢምንትነት የሚለካ ሰው ነው፤ ለኪው መለኪያው ነው፤ መለኪያውም ለኪው ነው፤ ጎሠኛነት የዘረኛነት የባሕርይ ልጅ ነው፤ ዘረኛነትም ሆነ ጎሠኛነት መሠረታቸው ድንቁርና ነው፤ የድንቁርናው ዓይነተኛ መገለጫ ‹‹ንጹሕ›› የሚለው ቃል ነው፤ ለዚህ ዋና ምስክር አድርጌ የማቀርበው አዶልፍ ሂትለርን ነው፤ ስለ‹‹አርያን ዘር›› ማንነትና ‹‹ንጹሕነት›› የሂትለር Mien Kampf የሚለውን መጽሐፍ ነው፤ […]

እውነቱን ለመናገር በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምክንያት እንደሰሞኑን በግኜ የማውቅ ኣይመስለኝም። ኣቤት ክህደታችን! እንዴት ተክነንበታልሳ ወገኖች! ረጋ ብላችሁ በጥሞና ኣንድታነቡኝ ብርታቱን ይስጣችሁ፥ 1• በዛሬይቱ ኢትዮጵያችን ነባራዊ ሁኔታ ብሄር ማለት ምን ማለት እንደሆነ በትክክል የሚነግራችሁ ሰው ኣታገኙም። የብሄር ፖለቲካ ኣቀንቃኞቹ ራሳቸው የሚግባቡበት ወጥ የሆነ የብሄር ትርጉም እንኳን የላቸውም። ብሄር ለኣንዳንዱ በቋንቋ ነው የሚገለፀው፤ ለሌላው በዘርና ትውልድ ሃረግ ነው […]

የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችን ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው አይችልም። የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 ዜጎች ነፍጥ ሳይዙ የመሰባሰብ፣ ሕዝባዊ ሰላምዊ ሰልፎች የማድረግ፣ ፔትሽኖችን የማሰባሰብ ሙሉ […]

ሰሞኑን አንድ ኢትዮጵያዊ በቶሮንቶ የህሊና እስረኞችን ለመዘከር በግሉ አዳራሽ ተከራይቶ የአንዱዓለም አራጌን “ያልተሄደበት መንገድ” የሚለውን መጽሃፍ ለሽያጭ በአቀረበበት ቦታ ተገኝቼ ነበር። በዚህ አዳራሽ አንዱዓለምን፣ እስክንድርን፣ ርዕዮትን …ወዘተ ለመዘክር ብለው የተሰባሰቡ ሰዎች ብዛት ስመለከት “በእውነቱ እስረኞች እኛ ነን ወይስ እነ ዓንዱአለም?” የሚል ጥያቄ ጫረብኝ። አገርን ያህል ትልቅ ነገር ከራሳችን የፖለቲካና የግል ጠባብ ፍላጎት ዙርያ ቀንበበን ልንከተው […]

ወያኔ ኢህአዲግ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም የቆመ መንግስት አይደለም :: ሀገር ማለት የተለያዩ ብሄሮች ፣ የተለያዪ ጓሳዎች እና የተለያዩ ሃይማኖቶች ያሎቸው ሰዎች መኖሪያ ናት :: እኛም ሀገራችን ብለን የምንጠራት ሀገራችን ኢትዮጵያ አኩሪ ታሪክ ያላት የተለያዩ ህዝቦች መኖሪያ ሀገር ስትሆን ሕዝቦቾም ለዘመናት በፍቅር፣ በመተሳሳብ ፣ በመከባባር እና በመተባባር አብሮ ሲኖር የነበሩ ህዝቦች እንደነበሩ ከታሪክ መረዳድ […]

በአትላንታ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአዋሳ፣ በደንቬር የሚኖሩ ደግሞ በደሴ ለሚደረጉት የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነትና ለፍትህ እንቅስቃሴዎች የሚያስፈልግትን ወጭዎች ሙሉ ለሙሉ እንደሚሸፍኑ ማረጋገጣቸውን ፣ የሰሜን አሜሪካ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት፣ ሸንጎን እና የሽግግር ምክር ቤቱን ያሳተፈው የሚሊዮኖች ድምጽ የዳያስፖራ ግብረ ኃይል ገለጸ። የመጀመሪያዉን የአዲስ አበባ እንቅስቃሴን ላስ ቬጋሶች፣ በድረደዋ ከተማ የሚደረገዉን የደብተራዉ ፓልቶክ ክፍል ፣ የቁጫ ከተማ ደግሞ […]

ለለውጡ ዝግጅት ያስፈልጋል! እንዲህም ተብሏል ለውጥን ማዘግየት ይቻል እንደሆን እንጂ ገድቦ ማስቀረት እንደማይቻል ከትርክት አልፎ በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ በተለይ ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴን አፍኖ መዝለቅ የማያዛልቅ ሙከራ እንደሆነ በተለያየ ጊዜ በተለያዩ ሀገራት ታይቷል፡፡ በዓለም ላይ የማይለወጥ ነገር አለ ከተባለ ራሱ ለውጥ ነው የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩት ጆን ኦፍ ኬኔዲ ‹‹እነዚያ ሰላማዊ ለውጥን የማይቻል […]

የሀገራችን የተቃውሞ ፖለቲካ ወደ አንድ ጠንካራ የለውጥ አማራጭነት እንዲሰባሰብ እና ገዥውን ፓርቲ የሚገዳደር ወሳኝ ኃይል ሆኖ እንዲወጣ ማስቻል የብዙ ቀናት አሳቢ ኢትዮጵያውያን ፍላጎት እንደሆነ ይሰማኛል። እኔም ራሴን ይህ ዓላማ ከፍፃሜ እንዲደርስ ከሚፈልጉ ወገኖች ውስጥ እንደ አንዱ በማድረግ እቆጥረዋለሁ። ውህደት እንዲኖር መፈለግ አንድ ነገር ሆኖ፤ ማን ከማን ጋር ነው የሚወሃደው? የውህደት መስፈርቱን ምን መሆን ይኖርበታል? የሚለውንም […]

ኢሕአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ፣ በጎሳ የተደራጁ ድርጅቶችን በማሰባሰብ ፣ በ1991 በተደረገው የአዲስ አበባ ኮንፈራንስ ፣ የሽግግር መንግስት ቻርተር ተብሎ የሚታወቀዉን ሰነድ እንዲጸድቅ ማስደረጉ ይታወቃል። ቻርተሩ አሁን ያለውን በጎሳ ላይ የተመሰረተ ዘረኛ ፌዴራል አወቃቀር ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲገበር ያደረገ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየትኛው አገር የሌለ፣ ጸረ-ኢትዮጵያዊ የብሄረሰቦች የመገንጠልን መብትን በሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ የደነገገም እንደሆነ ይታወቃል። ዶር ነጋሶ ጊዳዳ […]

የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል የፓርቲውን ደብዳቤ ተቀብሏል የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ መሰረታዊ ችግሮች እየተባባሱ ከመምጣት ውጪ ለውጥ ማሳየት ባለመቻላቸው ለዚህ ተጠያቂ መሆን ያለበትን የከተማይቱን አስተዳደርና ገዢውን ፓርቲ የሚቃወም ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል መሪ ቃል መጋቢት 28/2006 ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደርግ አስታውቋል፡፡ በዛሬው እለት የፓርቲው ተወካዩች ለአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል […]

በሃይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ሰሞኑን አንዲት መጣጥፍ ጽፌ ለድረ ገፆች ልኬ ነበር፡፡ ለኅሊናቸው ተገዢ የሆኑ አወጡት – አስነበቡን፤ እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ ለባህልና ለይሉኝታ ያደሩት እንዲሁም እነሱ በሚፈልጉት ሙዚቃ ብቻ ታንጎና ማሪንጌ መደነስ የሚፈልጉት ወደቅርጫታቸው ከተቱት – ይክተቱት፡፡ ሁሉም የመሰለውን የማድረግ መብት አለውና ያነበበም ያስነበበም፣ ያፈነም ያሳፈነም የኅሊናው ዳኝነት ይፍረደው ከማለት ውጪ በዚህ በውዥንብር ዘመን መወቃቀሱም ሆነ […]

በአገራችን ኢትዮጵያ ሁሉም መብቶች ያለምንም ገደብ የሚከበሩበትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ላለፉት ዓመታት በርካታ መስዋዕትነቶች ተከፍለዋል፡፡ ዜጎች የመደራጀትና ሀሳባቸውን የመግለጽ ህገ-መንግሥታዊ መብት እንዳላቸው ጧት ማታ በመንግሥት ብዙሀን መገናኛዎች ቢለፈፍም፤ ሁሉም ነገር የይምሰልና የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልፅ ነው፡፡ ከሕግ በላይ የሆነ አገዛዝ ባለበት አገር በየስፍራውና በየክልሉ የሚገኙ ካድሬዎችና የስርዓቱ ባለሟሎች እራሳቸውን ከህግ በላይ […]

ተፈናቃዩቹ ከጎንደር አካባቢ ተነስተው ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ በመውረድ በእርሻ ስራ የተሰማሩ ገበሬዎች ናቸው፡፡ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ደረጃ ‹‹ክልላችንን ለቅቃችሁ ውጡ››ሲባሉ ቆይተዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማስፈራሪያው ወደ ግድያ፣ድብደባና ወከባ በማደጉ ለአቤቱታ አካባቢያቸውን ጥለው አዲስ አበባ ለመግባት ተገደዋል፡፡ ከተፈናቃዩቹ መካከል የተወሰኑት ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃን […]

በሕዝብ ብዛት ቁጥር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሁለተኛ ከአለም ደግሞ አሥራ አምስተኛ ናት። ወደ ሰማኒያ ሚሊዮን ሕዝብ ሲኖራት፣ ያን ያህል ሕዝብ ኖሯት የባህር በር የሌላት ብቸኛ አገር ናት። ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ብዙ ሕዝብ ኖርቷት የባህር በር የሌላት አገር፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ ሶስተኛ የሚሆን ሕዝብ ያላት ዩጋንዳ ናት። የቀድሞ ጥቅላ ሚኒስተር አቶ መለስ ዜናዊ፣ በባህር ወደብ ዙሪያ ሲጠየቁ «ለእድገት […]

መኢአድ እና አንድነት መጋቢት 11 ቀን የቅድመ ዉህደት ፊርማ ይፈረማሉ ተብሎ ሲጠበቅ ፣ ከመኢአድ ፕሬዘዳንት አቶ አበባው መሃሪ በተጻፈ ደብዳቤ፣ ላልተወሰነ ጊዜ ፊርማው እንዲዘገይ መደረጉ በስፋት ተዘግቧል። አቶ አበባዉ የቅደመ ዉህደቱን ፊርማ ላለመፈረም ሶስት ያልተፈቱ ነጥቦች የሚሏቸውን ያቀርባሉ። ነጥቦቹም የዉህድ ፓርቲው ስያሜን፣ የመሪዎች መመዘኛን እና አንድነት ከመድረክ ጋር ያለዉን ግንኙነት የሚመለከቱ ናቸው። አቶ አበባዉ ባቀረቧቸው […]

ከወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የእስርና እንግልት ማብራሪያ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ በደቡብ ቀጠና በወላይታ ዞንና በሲዳማ ዞን አዋሳ ከተማ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የፓርቲውን የትግል ስትራቴጅክ ዕቅዶች ላይ ማብራሪያ፣ ደንብና ፕሮግራም ለመስጠት እንዲሁም የስራ ጉብኝት ለማድረግ በ 12/07/06 ወደ ወላይታ ዞን ሶዶ […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ልሳን የሆነው ፍኖተ-ነጻነት ጋዜጣ በግማሽ ሚሊዮን ብር የራሱን ማተሚያ ማሽን በመግዛት እና በመትከል በቅርብ ቀን ሕትመቱ ለሕዝብ በገበያ ላይ እንድሚውል ተገልጸ፡፡ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ተፈራ እንደገለጹት፤ የአንድነት ፓርቲ እና የፍኖተ ነጻነት የኢዲቶሪያል ቦርድ ባለፈው አመት ያሳትማት የነበረችው ጋዜጣ በ2005 ዓ. ም. በጉልበት እንድትዘጋ በመደረጉ እና የመንግስት […]

የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋ ላይ ነው፡፡ የሟቹን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ ምስል ያለበት ቲሸርት የለበሱ ከ 10 የሚልቁ የመንግስት ካድሬዎች በወላይታ ሶዶ እየተደረገ የነበረውን አንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክርቤት ስብሰባን በሀይል ማደናቀፋቸውን ከስፍራው ለፍኖተ ነጻነት የደረሰው ዘገባ አመለከተ፡፡ ካድሬዎቹ የስብሰባ […]

ዴሞክራሲ ስርዓት በመገምባት ላይ በሚገኙ ወይንም የዴሞክራሲ በዳበረባቸው አገሮች ውስጥ እጅግ ብዙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ተቋሞች ከመንግስት ነጻ ሆነው ይመሰረታሉ። በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የጋዜጠኞች ማህበሮች፣ የጋዜጠኞች መድረኮች፣ የሰራተኛ ማህበሮች፣ የተማሪ ማህበሮች፣ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ የስነጽሑፍ ማህበሮች፣ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ አሳብ አቀንቃኝ ድርጅቶች፣ የፖለቲካ አሳብ አቀንቃኝ ቡድኖች፣ የህዝብ ጤንነት እና ኑሮ ሁኔታ መሻሻል ተቆርቋሪ ድርጅቶች፣ የመንግስት […]

የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባዉ መሃሪ በደብተራው ፓልቶክ ክፍል ቀርበዉ ባደረጉት ሰፊ ዉይይት፣ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ስላለዉ የዉህደት እንቅስቃሴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። «አንድነቶች እኮ ልጆቻችን ናቸው። መኢአድ የነበሩ ናቸው» ያሉት አቶ አበባዉ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል የፖለቲካ ፕሮግራም ልዩነቶች እንደሌሉ ተናገረዋል። «ታዲያ የሁለቱም ፓርቲዎች ምክር ቤቶች ከወሰኑ በኋላ ምንድን ነው ምክንያቱ መኢአድ ለመፈረም ያልቻለው ? » […]

ከአዲስ አበባ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ! ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!! ሌሎች አገሮች ለዋና ከተሞቻቸው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የየአገሮቻቸው ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ማሳያ በማድረግ አለም አቀፍ ተቋማትንና ጎብኝዎችን በመጋበዝ የከተሞቻቸውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደርጋሉ፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ ግን በብዙዎች የአፍሪካ አገራት የአህጉሪቱ መዲና ተደርጋ የምትጠቀሰው አዲስ አበበባችን ከጊዜ ወደ ጊዜ […]

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ዛሬ በጽ/ቤቱ መግለጫ ሰጠ ፡፡ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) ከአዲስ አበባ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ! ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!! ሌሎች አገሮች ለዋና ከተሞቻቸው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የየአገሮቻቸው ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ማሳያ በማድረግ አለም አቀፍ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) በመኢአድ በኩል የቀረበው ቅድመ ውህደት ያለመፈረም ሰበብ አሳዛኝና የሕዝቡን ጥያቄ ያኮሰሰ ነው!! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ለረዥም ዓመታት የሕዝብ ፍላጎትና አንገብጋቢ የሆነውን ተቃዋሚዎች ‹‹ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ›› ጥያቄ ለመመለስ በስትራቴጂና አምስት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በማካተት መንቀሳቀስ […]

በቦስተን እና አካባቢዋ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የውደሳ እና የምስጋና ቀን በቦስተን እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2006 / Sunday, March 30, 2014 ከቀኑ 2፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት ድረስ/From 2:00 PM to 6:00 PM በካምብሪጅ፤ ዋልደን የኮሚኒቲ አዳራሽ፣ 21 ዋልደን ስኩዬር ሮድ፤ ካምብሪጅ፤ ማሳቹሴትስ 02140፣ (Walden Square Community Rm, 21 Walden Sq. Rd., […]

የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግርን በተመለከተ የአባይን ልጅ ውሃ ጠማው እንዲሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከተማዋ በርካታ አካባቢዎች ውሃ በፈረቃ የሚያገኙበት ያልታወጀ አሰራር እየተስተዋለ ነው። ብዙ አካባቢዎች ከ24 ሰዓታት በላይ የመጠጥ ውሃ በተደጋጋሚ በመጥፋቱ ነዋሪዎች መደበኛ ሥራዎቻቸውን ጭምር በመተው ጄሪካን ይዘው ውሃ ፍለጋ ከቦታ ቦታ የሚንከራተቱበት ትይዕንት አዲስነቱ እየቀረ የመጣ ይመስላል። አቶ ድሪባ ኩማ ግን በያዝነው በጀት […]

በአዲስአበባ በተለይም በስራ መግቢያና መውጪያ ሰዓታት የሚታየው የትራንስፖርት ችግር ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ መምጣቱ ብቻም ሳይሆን ሠራተኞች በሰዓት ወደስራ ገበታቸው እንዳይገቡ በማድረግ በምርታማነት ላይ የራሱን አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ እንዲሁም አብዛኛውን ሠራተኞች ላልተፈለገ ወጪ በመዳረግ የኑሮ ውድነትን በማባባስ ረገድ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ከታክሲ የዞን ስምሪት አንስቶ ተጨማሪ አውቶብሶችን ወደመስመር በማስገባት በመንግስት በኩል የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም […]

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ETHIOPIAN JOURNALISTS FORUM (EJF) በጋዜጠኞች ላይ ያለ ማስረጃ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎች ባስቸኳይ እንዲቆሙ እንጠይቃለን! ማህበራችን ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ የምዝገባ ሰርተፊኬት ለማግኘት የጀመረው እንቅስቀሴ በቅርቡ ከመንግስት አወንታዊ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ በማድረግ የተቋቋመለትን አላማ ለማሳካት እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም ከማስጠበቅና የመናገር ነፃነትን ከማበረታታት ባለፈም ከአህጉራችን አፍሪቃ ጋዜጠኞች ጋር በመተባበር […]

አንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በሙሉ አደረጃጀቱን ሊዘረጋ መሆኑንና ይህንኑ በተመለከተም ከፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት፣ከወረዳ ሰብሳቢዎችና ከወረዳ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊዎች ጋር ምክክር እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ያሬድ አማረ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቀ፡፡ ግንኙነት ኃላፊው ወጣት ያሬድ እንዳስታወቁት ቅዳሜ መጋቢት13 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ […]

በመኢአድ ጽ/ቤት እሁድ መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም የመኢአድ እና የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት በእነ ዶክተር ያእቆም ኃይለማሪያም፣ በዶክተር ዳኛቸው አሰፋ አደራዳሪነት የተጀመረው የቅድመ የፓርቲዎች ውህደት ድርድር ውጪ የሚገኙ ተቃዋሚ ኃይሎች የቀመሩት አይደለም ሲሉ ከአደራዳሪዎቹ አንዱ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገለፁ። ስማቸው አይጠቀስ ያሉ ዶክተር አሁን የያዙትን ኃላፊነት በምን መልኩ እንዳገኙት ለሰንደቅ እንደገለፁት፤ “እኛ ይህን […]

በ2002ቱ ጠቅላላ ምርጫ መቃረቢያ ላይ ከ60 ያላነሱ ሀገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፓርቲዎችም እንገዛበታለን ብለው ከፈረሙበት በኋላም ሕግ ሆኖ የወጣው የስነ-ምግባር ደንብ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ እንደማይፈርም አስታወቀ። የፓርቲው ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ለሰንደቅ እንደተናገሩት፤ የምርጫ ስነ-ምግባር ደንብ በሀገሪቱ ፓርላማ ሕግ ሆኖ እስከወጣ ድረስ ፓርቲው እንደገና የሚፈርምበት ምክንያት የለም ብለዋል። ኢህአዴግን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች በሚሳተፉበት […]

“ከሰደበኝ ስድቤን አምጥቶ የነገረኝ” ይባላል፡፡ ዶክተር ዘላለም እሼቴ በተባለ ሰውዬ በአማሮች ላይ ተጻፈ በተባለ አንድ አጭር ደብዳቤ ላይ ተመሥርቶ አድማሱ በላይ የሚባል ሌላ አቃቂረኛ የሰጠውን ተገቢና ወቅታዊ ግብረ-መልስ በአቡጊዳ ድረ ገፅ ላይ አነበብኩና እኔም በማውቀው ቋንቋ በአማርኛ ትንሽ መናገር አሰኘኝ፡፡ የዶክተሩን ጽሑፍ ያነበብኩት የእንግሊዝኛ መዝገበ ቃላት አጠገቤ አስቀምጬ ከአንዴም ሁለቴና ሦስቴ ደጋግሜ ነው፤ አጭር በመሆኑም […]

በአዳማ/ ከተማ የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ የሆነው ወጣት ምርቱ ጉታ፣ ዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ገደማ በተለምዶ ዝቋላ ተብሎ በሚጠራው ገበያ አካባቢ መታሰሩን፣ የከተማዋ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ተስፋዬ ዋቅቶላ ለፍኖተ ነፃነት ገለፀ፡፡ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው እንደገለፀው ዝቋላ ተብሎ በሚጠራው ገበያ አካባቢ የሚገኙ አነስተኛ ነጋዴዎች፣ የገበያ ስፍራው እንዲለቁ መጠየቃቸውን ተከትሎ ሲያሰሙ […]

ሰባቱ የጣይቱ ሴቶች እና ሶስቱ ወንዶች ከአራ አንድ ቀናት በዋስትና መፈታታቸውን ዳዊት ሰለሞን ከአዲስ አበባ ዘገበ። «በመደበኛ ፍርድ ቤት ክሴን እንዳቀርብ ይፈቀድልኝ በማለት ቀበና ለሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ትናንት ጥያቄ አቅርቦ የነበረው ፖሊስ ዛሬ ማለዳ አስሩን ተጠርጣሪዎች ቀበና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቅርቧል፡፡» ሲል የዘገበው ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን «በወጣቶቹ ላይ ክስ ለመመስረት የሚበቃ ወንጀል […]

የተባበሩት መንግሥታት በ1948 ዓ.ም. ባወጣው የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ መግለጫ አንቀጽ 2 ላይ እያንዳንዱ ሰው በዘር፣ በቀለም፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ወይም በሌላ አስተያየት፣ በኅብረተሰብ ምንጭ፣ በሃብት፣ በትውልድ፣ ወይም በሌላ አቋም ምክንያት ምንም ዓይንነት ልዩነት ሳይደረግበት በመግለጫው ላይ በተጠቀሱት መብቶችና ነፃነቶች በእኩል የመጠቀም መብት እንዳለው የደነግጋል። ይህንን ድንጋጌም መነሻ በማድረግ ዘረኝነትንና ሌሎች ከሰብአዊ መብቶችና ነፃነቶች ጋር […]

እመቤት ግርማ ( 18 አመት ወጣት)፣ ንግስት ወንዳፍራዉ፣ መታሰቢያ ስዩም፣ ወይንሸት ንጉሴ፣ ምኞት መኮንን በሩጫ ወቅት ሁከት ፈጥራችሁላ ተብለው ከታሰሩ «የጣይቱ ልጆች» መካከል የሚገኙ ናቸው። የካቲት 30 2006 ዓ.ም እሑድ ቀን ነው። በተዘጋጀው የሴቶች የ500 ሩጫ በርካታዎች ይሮጣሉ። ቢጫ ኬኔቴራ ለብሰዋል። ሩጫዉ እንደተጀመረ ድምጾች መሰማት ጀመሩ። የስድብ፣ የክፉ አይደለም። «የጣይቱ ልጆችን ነን፤ የሚኒሊክ ልጆች ነን፣ […]

የአንድት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠራ ነው እንደሆነ የፍኖት ጋዜጣ ዘገበ። «በአዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣውን የውሃ፣የመብራትና የቴሌኮም አገልግሎት ጥራት መጓደልና የአገልግሎት መቋረጥ መንግስት በአፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ለመጠየቅ፣ የከተማዋን ነዋሪዎች በማነቃነቅ ደማቅ የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ የአንድት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ስራ አስፈፃሚ መወሰኑን የዞኑ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለፍኖተ ነፃነት […]

በአንድነት እና መኢአድ የዉህደት እንቅስቃሴ ላይ አስተያይተ የሰጡት የፓርላማ እና የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ግርማ ሰይፉ ምክር ቤቶቹ ይሄን ታሪካዊ ዉሳኔ ባሳለፉበት ወቅት የሚከተለውን ብለዋል፡ «ዛሬ በመኢህአድ ፅ/ቤት የመኢህአድ እና የአንድነት ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት የጋራ ስብሰባ አድርገው አንድ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል፡፡ ይህውም ለቀጣይ ሐሙስ መጋቢት 11/2004 ዓ/ም የቅድመ ውህደት ሰምምነት […]

በደቡብ ክልል፣ በጋሙ ጎፋ ዞን የምትገኝ ወረዳ ናት። ወደ 150 ሺህ የሚጠጋ ነዋሪ አላት። በዚያ ያሉ ገበሬዎች ከሚያርሱበት ቦታ በግድ እንዲፈናቀሉ ከመደረጉ በተጨማሪ፣ ብዙዎች ያታሰሩባት ወረዳ ናት። የቁጭ ወረዳ ትባላለች። በአንድነት ፓርቲ አነሳሽነት ለሕዝብ የፋ የሆነው የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ትኩረት ከሰጠባቸው ወደ አሥራ የሚሆኑ አካባቢዎች አንዷ ቁጫ ናት። በቁጫ ሊደረግ የታሰበዉን ትእይነተ ሕዝብ በመደገፍ፣ […]

በምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት ጠንካራ ፓርቲ ይባሉ የነበሩት መኢአድ እና ኤዴፓ ነበር። ሁለቱን ፓርቲዎች የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት እና የመኢአድ ላዕላይ ምክር አባላት ቤት መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም አባላት በጋር ባካሔዱት ስብሰባ፣ ሁለቱ ፓርቲዎች የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ እንዲያደርጉ መመሪያ ማስተላለፋቸውን ፍኖት ነጻነት ዘገበ። በምርጫ ዘጠና ሰባት ከመደረጉ […]

የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤትእና የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በጋር ባካሔዱት ስብሰባ ሁለቱ ፓርቲዎች የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ እንዲያደርጉ መመሪያ ማስተላለፋቸውን ስብሰባውን የተከታተለው የፍኖተ ነፃነት ባልደረባ ዘገበ፡፡ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት አባላት እና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ላዕላይ ምክር ቤት አባላት ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2006 […]

ሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ ሰባት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ስብሰባ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች ይደረጋሉ። ላስ ቬጋስ፣ ኔቫዳ፣ ከአዲስ አበባ ጋራ ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን፣ በአዲስ አበባ ለሚደረገዉ ሕዝባዊ ስብስበ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን […]

ወደ ስድስት የሚጠጉ የፖለቲካና የየሲቪክ ማህበራት ስብስበ የሆነው የኢትዮጶያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት፣ በዚህ ሳምንት በዳያስፖራ ለተቋቋመው የሚሊዮኖች ድምጽ ግብረ ኃይል በጻፉት ደብዳቤ ፣ ድርጅታቸው፣ በአገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈሉ ላሉ ታጋዮች ያላቸዉን አድናቆትና አክብሮት በመገጽል፣ አገር ቤት እየተደረገ ያለዉን የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ ጎን እንደሚቆሙ አረጋገጡ። ድርጅቶቹ በደብዳቤ ድጋፋቸውን […]

የሕወሐት አባል የሆነውና በአሜሪካ የሚኖረው ብስራት አማረ በርካታ ወንጀሎችን እንደፈፀመ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። ሕወሐት በረሃ እያለ የባዶ 6 እስር ቤት ዋና ሃላፊ የነበረው ብስራት አማረ የኢ.ህ.አ.ፓ አባላት የነበሩት እነ ፀጋዬ ገ/መድህን (ደብተራው) ጨምሮ በሕወሐት የተያዙትን በሙሉ ወረኢ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በነበረ እስር ቤት በጅምላ አሰቃይቶ እንደገደላቸው ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎች « ኢዲዩና ፊውዳል..» […]

“ ነፃነቴን ካልሰጣችሁኝ ሞትን እመርጣለሁ” ፓትሪክ ሔንሪ Give me Liberty or Give me Death ፍሬደሪክ ዳግላስ (1818- 1895) ከባርያ እናትና ከነጭ አባት የተወለደና ራሱም ቢሆን በቦልቲሞር (ሜሪላንድ) የቤት አሽከር ሆኖ የቆየ ሰው ነበር። አንድ ማለዳ ጁላይ 4 ቀን 1852 ን ተንተርሶ (አንተርሶ) በሮቼስተር ከተማ (ኒውዮርክ) ንግግር እንዲያደርግ ጥሪ ይደርሰዋል። ደብዳቤው ሲደርሰው እንደ እብድ ከራሱ ጋር […]

የ2006 ዓ/ም የኢትዮጵያ ሰማእታት ቀን በየካቲት ወር 12 ሐገሮች በሚገኙ በ27 ከተሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተከናውኗል። የአከባበሩም ስነሥርአት በሰላማዊ ሰልፍ፤ በሕዝባዊ ጉባኤ፤ ወይም በጸሎት ነበር። አዲስ አበባ የተከናወነው የካቲት 12 አደባባይ ሲሆን የአበባ ጉንጉን ኃውልቱ ሥር በማስቀመጥና ንግግር በማሰማት ነበር። እንደሚታወቀው፤ የሰማእታት ቀን በየዓመቱ የሚከበረው፤ በየካቲት 19-21፣ 1929 ዓ/ም ፋሺሽቶች አዲስ አበባ በሶስት ቀኖች ውስጥ […]