ፍኖት ታትማ ወጥታለች ኢቲቪ (ወይም አዲሱ ስማችውው ኢቢሢ)፣ የኢትዮጵያ ሬድዮ፣ አዲስ ዘመን ጋዜጣ በመንግስት ገንዘብ የሚተዳደሩ የመገናኛ ብዙሃን ናቸው። የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 29 ንኡስ አንቀጽ 5 “በመንግስት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም በመንግስት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማስተናግገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል።” እንደሚለው የተለያዩ አስትያየቶችን ፣ በአገሪቷም ያሉ በሕግ የተመዘገቡ ሲቪክና የፖለቲካ ድርጅቶችን ከኢሕአዴግ […]

ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም መኢአድ እና አንድነት ዉህደት ይፈጽማሉ ተብሎ ተጠብቆ እንደነበረና የሕወሃት ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ አመራር እውቅና አልሰጥም በሚል ዉህደቱን ማጨናገፉ ይታወቃል። ከሁለት አመታት በላይ በአቶ አበባው መሐሪ ከሚመራው መኢአድ ጋር ደብዳቤዎች ሲጻጻፍ የነበረው ምርጫ ቦርድ ፣ አንድም ጊዜ በአመራሩ ላይ ጥያቄ አንስቶ ሳያውቅ፣ ዉህደት ሊደረግ ሲል፣ ሸንካላ ምክንያት በመፍጠር ሆን ብሎ ዉህደቱን ማጨናገፉ፣ […]

”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” ለሚለው ለአቶ አንተነህ መርዕድ ጽሁፍ መልስ፣ ቁ. 1 ዛሬ ኦክቶበር 8/2014 ምሳ ሰዓት ላይ አንድ ጓደኛዬ ደውሎ ”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” የሚለውን ጽሁፍ አንብቤው እንደሆን ጠየቀኝ። ይህ ሰው በፕሮፌሰር መስፍን ማንነት ላይ ይቅርታ ጠይቄው ስለነበር ”ቢጤህ የጻፈውን እየው” ለማልት ማሾፉ ነበር። ለፕሮፌሰር መስፍን ከወጣትነት በተለይም የትግራይ ብሄረተኞች ስልጣን ላይ ሊመጡ አጥቢያ ጀምሮ በየአደባባዩ […]

በገዥው ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ክንፍ የደ.ህ.ዴ.ን ፖለቲካ ፖርቲ አባላት ወዳጆቸ ባደረጉልኝ ግብዣ መሰረት በደ.ህ.ዴ.ንን 22ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ተገኝቸ ነበር ። እንደ ዛሬው የደ.ህ.ዴ.ን በዓል ፍሪዳ ተጥሎ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ድርጅቶች የልደት በዓላቸውን ሲያከብሩ እግር ጥሎኝ ስገኝ በምባረርበት የጅዳ ቆንስል ግቢ በሚገኘው የኮሚኒቲ አዳራሽ ተገኝቸም ኬክ እስኪቆረስና ሙዚቃው እስኪጀመር ያለውን ፕሮግራም ተከታትያለሁ። በልደት ፕሮግራሙ በቀረበው የድርጅቱ የትግልጉዞ “የስምጥ […]

የምስራች! ነገ ጠዋት ቅዳሜ ጥቅምት 29 2007 በጉጉት የምትጠብቋት ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣችን በገበያ ላይ ትውላለች፤ እንግዲህ ዝም ያልኩ መስሎዎታል ሲታሰብ ነው እንጂ ዝም ማለት የታል! እንደተባለው፤ አሁንም እስሩ ሲበረታ ዝም ምል መስሎታል መታገል ነው እንጂ እጅ መስጠት የታል! እያላችሁ አንብቧት።

አምባገነኑ የኢህአዴግ ስርዓት ፖለቲካዊ እስርን እንዳንድ ተቀዋሚዎች የማዳከሚያ ስልት በመውስድ ህግ ወጥ በሆነ ሁኔታ አባሎቻችን በማሳርና በማዋከብ ላይ ይገኛል። አንድነት ከምስርታው ጀምሮ አመራሮቹና አባላቱ የተለያየ ሽፋን በመጠቀም ለእስርና ለእንግልት ተዳርጓል፤ አሁንም እየታሰሩና እየተዋከቡ ይገኛሉ፤ በቅርብ ደግሞ ለየት ባለ ሁኔታ አጠቃላይ ፓርቲው በሚያዳክም መልኩ በሁሉም የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚገኙ የአንድነት አባላት እያሳደደ በማሰር ላይ እንደሚገኝ ከየአከባቢው የሚደርሱን […]

የሺዋስ አሰፋ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባል ነው። ሰማያዊ ከመቋቋሙ በፊት ነው የማውቀው። ሰማያዊ እንደተመሰረተ የሰማሁት ከርሱ ነው። የድርጅቱን ድህረ ገጽ ልኮልኝ ከጅምሩ ስለሰማያዊ ፓርቲ አላማ ይነግረኝ ነበር። የሰማያዊ ፓርቲም ደጋፊ ነበርኩ። ሰማያዊ የመጀመሪያዉን ሰልፍ ሲጠራ በዉጭ ያለን አንድነትን የምንደግፍ ድጋፋችንን ለሰማያዊም እንድንሰጥ መጠየቄን አውቃለሁ። የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ መዋቅርም በወቅቱ ሰማያዊ በጠራው ሰልፍ መተባበራቸውም አስደስቶኝ […]

ህወሀት የትግራይ ክልልን የግል ሜዳው በማድረግ ስለሚቆጥር ክልሉ ከፓርቲው የተለየ ባንዲራ እንዳይኖረው እስከማድረግ መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ከትግራይ ክልል ውጪ ህወሀት አልጋ ሆኖ የማያውቅ ቢሆንም የህትመት ውጤቶች በትግራይ ብርቅ ሆነው ህዝቡ ከህወሀት ውጪ እንዳይሰማ፣ ፕሮፌሰር መስፍን ባንድ ወቅት እንዳሉት፣ ከአንድ ፋብሪካ እንደ ወጣ ምርት፣ አንድ አይነት አስተሳሰብ እንዲይዝ ህወሀት የቻለችውን አድርጋለች፡፡ በትግራይ ክልል ከህወሀት የተለየ አጀንዳ […]

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ የዝግጅት ክፍል አባላት ወደ ቂሊንጦና ቃሊቲ እስር ቤቶች በማቅናት እስረኞችን ጠይቀዋል፡፡ እስረኞቹ ያስተላለፉትን መልዕክት ነገረ ኢትዮጵያ እንደሚከተለው ጠቅለል አድርጋ አቅርባዋለች፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ አይቀርም›› እስክንድር ነጋ በማህበራዊ ድረ-ገጽም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች መልካም ልደት ለተመኛችሁልኝ ሁሉ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ የቡርኪናፋሶው አምባገነን መውደቁን በመስማቴ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ ይህ ለእኔ ውድ የልደት ቀን ስጦታየ […]

ዜጎች መታሰራቸው እየቀጠለ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ አባላት (በጎንደር፣ በትግራይ፣ በመቱ፣ በአዲስ አበባ ፣ በወላይታ ….) ። ብዙዎች ከፍተኛ ደብደባ እየደረሰባቸው ነው። ሕወሃት ፣ በሕዝብ እንደተጠላ ስላወቀ የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ እየሰራ ነው። አንድነት ሊያሸንፈው እንደሚችል ስላወቀ። የድርጅቶች መተባበር አስፈላጊ በመሆኑ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ተስማምቶ የቅድመ ዉህደት ስምምነት ፈርሞ ነበር። ሁሉም ነገር […]

በዚህ የምርጫ ወቅት እየተቃረበ ባለበት ወቅት ስርዓቱ የመንግስትን ተቋማት ተገን አድርጎ የአንድነት አባላትን በመላ ኢትዮጵያ በማሰርና በማዋገብ ላይ ይገኛል። ለጥቅምት 25/2007 ዓ.ም. አጥቢያ ላይ በምዕራብ አምርማጭሆ አብርሃ ጅራ ከተማ የሚገኙ የአንድነት አባላት አቶ አንጋው ተገኝ የአካባቢው የአንድነት ሰብሳቢ፣ አቶ አባይ ዘውዱ እና አቶ እንግዳው ዋኘው የተባሉ የአካባቢው የአንድነት አመራር አባላት የፌደራል ፖሊሶች የቤታቸውን በር ገንጥለው […]

በመቀሌ የአንድነት አባል የሆነው ወጣት ሺሻይ አዘናው በዛሬው ዕለት ጥቅምት 26 2007 ዓም በመንግስት የድህንነት አካላት ከሚሰራበት መስሪያቤት የወሰዱት ሲሆን ከዚያ ወደ ቤቱ በመውሰድ ቤቱን ፈትሸው እዚያ ያገኙትን ወረቀት ሁሉ አፋፍሰው ከያዙ በኋላ በሽፍን ላንድኩረዘር መኪና ወደ አልታወቀ ቦታ ይዞውት ሄደዋል። ወጣት ሽሻይ አዘናው ቀደም ሲል አንድነትን ከመቀላቀሉ በፊት የአረና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረ ሲሆን፤ […]

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሰሜን ጎንደር ዞን በፓርቲው አባላት ላይ በዘመቻ የሚደረገውን እስርና እንግልት በመቃወም መግለጫ አወጣ

በዛሬው ዕለት ጥቅምት 26 ቀን 2007 ዓ.ም ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዳንኤል ሺበሺ ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ የሺዋስ አሰፋ ፣ የአረና ፓርቲ የአመራር አባልና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም እና በተመሳሳይ መዝገብ […]

ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡ ‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ […]

የአንድነት ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች መዋቅሩን የዘረጋ ድርጅት ነው። ወደ አምስት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ በሚኖርባት አዲስ አበባ ፣ ፓርቲው እስከታች በመዝለቅ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድርጅታዊ መዋቅሩን ዘርግቶ የሚንቀሳቀስ ነው። – የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተቋቋመው በአዲስ አበባ ከሚገኙ 23 የምርጫ ወረዳዎች በተወከሉ ስድስት ስድስት አባላት ነው። በአጠቃላይ 138 አባላት አሉት። – በ23ቱም የምርጫ ወረዳዎች ፣ […]

“በሽብር” ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የፓርቲ አመራሮች ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት፣ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ፣ የሺዋስ አሰፋ የሰማያዊ ፓርቲ ም/አፈ ጉባኤ፣ መምህርና የአረና ፓርቲ የአመራር አባል አብርሃ ደስታ እንዲሁም የአ/አ ዩኒቨርስቲ የማስትሬት ተማሪ ዘላለም እና ተመሳሳይ መዝገብ የተከሰሱ ሌሎች 5 ግለሰቦች ነገ ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ […]

የምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረው አቶ ደረጀ ክበበው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ አቶ ደረጀ በጠና ታሞ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትላንት ጠዋት በአዳማ ከተማ ቀበሌ 07 በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ያረፈ ሲሆን የቀብር ስነስርዓቱ በትላንትናው ዕለት ከቀኑ በ 7፡00 ሰዓት አዳማ በሚገኘው መድኃኒአለም ቤ/ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ ፓርቲው በአቶ ደረጀ ክበበው ሞት […]

– የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል። – የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል። – የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች “ተከታይ ” ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል። – የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ። በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ […]

በደቡብ ጎንደር የፎገራ ወረዳ የአንድነት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አለበል ዘለቀ በዛሬው ዕለት ከሚሰሩበት የእርሻ ቦታቸው ላይ በፌዴራል በፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን እንዲሁም በአማራ ክልል ምዕ/ጎጃም ደጋ ዳሞት ወረዳ የወረዳው አንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ጥላሁን አበበ በተጨማሪም በወረዳው ያሉ 3 የአንድነት አባላት ከቤታቸው በፌዴራል ፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸው ከስፍራው ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የደረሰው ዜና […]

የወላይታ ዞን ዋና ከተማ ፣ የሶዶ ነዋሪ ናቸው። ዘር ኃይማኖት ሳይጠይቅ ሁሉንም ዜጋ ለማቀፍ በሩን ክፍት ያደረገው፣ ለሁሉም ዜጎች የቆመው የአንድነት ፓርቲ አባል ናችው። ፓርቲው የሚሊዮኖች ንቅናቄ ለነጻነት በሚል መርህ በበርካታ ከተሞች ህዝብባዊ እንቅስቃሴ ባደረገበት ወቅት በሶዶ ለተደረገው እንቅስቃሴ በየመንገዱ ከፍተኛ ቅስቀሳ ማድረጋቸው፣ ህዝቡ ማነጋገራቸዉና ማሳመናቸው በአገዛዙ ካድሬዎች አልተወደደላቸውም። “ለምን ወረቀት አሰራጭሽ?” በሚል ክስ ተመሰረተባቸው። […]

ውድ ታጋይ ኢትዮጵያዊ፤ በምኞት የምንጋልበው ፈረስ፤ ከፈለግነው ቦታ በፍጥነት የሚያደርሰን፤ በምኞት ዓለም ውስጥ ብቻ ነው። እኛ አሁን በአንድነት ያጋጠመን የምኞት ችግር ሳይሆን፤ የሀገራችን ተጨባጭ ሀቅ ነው። ይህ ደግሞ ተጨባጭ መፍትሔ ይጠይቃል። ሀቁን ተረድተን፣ ማድረግ ያለብንን ለይተን፣ ከትናንት ዛሬ፤ ከዛሬ ደግሞ ነገ የተሻለ ግስጋሴ የምናደርግበት ትግል እንዲሆን መጣር አለብን። በተናጠል በግለሰብና በየራሱ ድርጅት ለየብቻ የሚደረገው ትግል፤ […]

ፍትህ ! ፍትህ ! ፍትህ ! በሰላማዊ ጥያቄ ፍትህን ለማረጋገጥ ባለመቻሉ በህዝባዊ እምቢተኝነት ይረጋገጣል!!! እኛ ኢትዮጵያዊያንን በላያችን ላይ እየነቀዙ ያሉትን ነቀዝ አምባገነኖች ለማስወገድና ፍትህ ዲሞክራሲ ነጻነት እና ሰላም ለመቀናጀት ካደቀቀን የኑሮ አለንጋ ለመላቀቅ በጋራ አደባባይ በመውጣት ስርአቱን የምንገረስስበት ወሳኝ ጊዜ ላይ መሆናችንን አውቀን የተነፈግነውን ፍትህ በሃቀኝነት ማረጋገጥ አለብን። የበሃገራችን የተንሰራፋው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት የፍትህ ስርአቱ […]

ጥቅምት 22 ቀን 2007ዓ.ም ለተሰዉ ሰማዕታትና የህሊና እስረኞች በማሰብ የሻማ ማብራት ሥነ ስርዓት አደረገ በዛሬዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ የተሰበሰበው የአዲስ አበባ አንድነት ክር ቤት ስብሰባውን የከፈተው ጥቅምት 22 ቀን 1998 ዓ.ም ለተሰዉት ሰማዕታትና የህሊና እስረኞችን በማሰብ የሻማ ማብራት ሥነ ስርዓት በማድረግ ነበር፣ የሻማ ማብራቱ ሥነ ስርዓት እንደተጠናቀቀ በፓርቲው ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተሄደ፡፡ በውይይቱ ላይ […]

‹‹በእነሀብታሙ ላይ የተደረገው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እጅግ አሳፋሪ ነው›› ‹‹ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት ቤት እንደጀግና መታየት አለባቸው›› ‹‹ከመኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲዎች ጋር ተዋህደን መስራት አለብን›› አቶ በላይ ፍቃዱ /የአንድነት ሊቀመንበር ‹የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁ አሸባሪ ነው›› ‹‹ዘንድሮም አዋጁ ይሰረዝ ብለን መጠየቃችንን እንቀጥላለን›› አቶ ግርማ ሰይፉ /የፓርላማ ተወካይ የአንድነት ም/ፕሬዚዳንት/ ——————————– ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጥቅምት 20 ቀን 2007 ዓ.ም፣ አንድነት […]

ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን ወደ እውነት ያመጡ ህጎች በኢትዮጵያ አሉ የሚለው ወያኔ ህዝቦች ግን በተግባር ተጠቃሚ ሲሆኑ አላየንም::ህጎቹ በተግባር ይዋሉ ይህንን ህጎች በመመሪያ በደብዳቤ እና በስልክ የሚቀይሩ የሚደፈጥጡ በጥቅም የሚሸጡ የሚረጋግጡ የሚለውጡ ከየወንበራቸው ተሽቀንጥረው ይጣሉ:: የቀን ተቀን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ሂደት ውስጥ እጃቸውን እያጠለቁ ፍትህን የሚያዛቡ አስተዳደራዊ በደሎችን የሚፈጽሙ ባለስልጣናት የህዝብን ማህበራዊ ህይወቶች ከማፋለሳቸውም […]

ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አሥራ አንደ በመቶ በላይ፣ ለበርካታ አመታት እንዳደገ ይናገራል። በአገሪቷ በተለይም በአዲስ አበባ ግንባታዎች ይታያሉ። መንገዶች ይሰራሉ። ነገር ግን ግንባታዎቹ በአብዛኛው ከዉጭ በልምና በመጣ ገንዘብ የተሰሩ እንደመሆናቸው የኢትዮጵይን ምርታማነትና እድገት አመልካች አይደለም። የብር የመግዛት አቅም ከማሽቆልቆሉ የተነሳ፣ በቀን አንድ ጊዜ ብቻ የሚመገበው ሕዝብ ቁጥር በጣም እየጨመረ መጥቷል። የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት ተመዝግቧል የሚሉት […]

በትናትናው ዕለት ጥቅምት 19/2007 የአንድነት ኦዲቶሪያል ቦርድ እንዳዲስ የተዋቀረ ሲሆን በአዲሱ የኦዲቶሪያል ቦርድ አባላት ሆነው የተመረጡት አቶ ሰሎሞን ስዩም፣ አቶ ዳኒኤል ተፈራ፣ አቶ ጌታቸው ሃይሉ፣ አቶ ደረጀ ጣሰው፣ አቶ አስራት አብርሃም እና አቶ ሲሳይ ሲሆኑ፤ አቶ ሰሎሞን ስዩም የኦዲቶሪያሉ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ደረጀ ጣሰው ደግሞ ፀሐፊ ሆነው ተመርጠዋል። የፍኖተ ነፃነት ዋና አዘጋጅ አቶ ነብዩ ሃይሉ […]

በሽብር ተጠርጥረው በማዕከላዊ እስር ላይ የሚገኙት እነ ሀታብሙ አያሌው ልደታ ፍ/ቤት ቀረቡ ************************************** በማዕከላዊ እስር ቤት ከ115 ቀን እስር በኋላ ዛሬ ክስ ተመሰረተባቸው **************************** በትላናው ዕለት አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ሊቀርቡ ያልቻሉት የፓርቲ አመራሮች፣ በድብቅ ትላንትናውኑ ልደታ ፍ/ቤት መቅረባቸውንና ዳኛ ባለመሟላቱ ለዛሬ ጠዋት ተቀጠረው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ከታሰሩበት ማዕከላዊ ፍርድ ቤ/ት ፖሊስ አጅቦ […]

ባሳለፍናቸው አመታቶች የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሃገር አቀፍ በብሄር አቀፍ እና ቤተሰብ አቀፍነት ተመስርተው ከስመዋል። ሲንደባለሉ ለአሁኑም ወቅታዊ ጡዘት የደረሱም እያዛጉ እና እያፋሸኩ በፖለቲካ አንጎበር እየተናጡ በገሺው አምባገነን ፓርቲ እየተደቆሱ ላለመሞት በወንዳታነት እየተፈራገጡ ይገኛል። የተቃዋሚ ሃይሎች እና የለውጥ ፈላጊ ሃይሎች አንድነት የሚያስፈልግበት ወቅታዊ እና ወሳኝ ትግል ላይ መድረሳችን ለሕዝብ ያለንን አክብሮት ለማሳየት እና ግባችንን በመምታት ለህዝባዊ […]

ክስ ሳይመሰረትበት ለአራት ወራት በማእከላዊ እስር ቤት የሚገኘው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ ከፍተኛ ኢሰብአዊ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ ታወቀ። ሃብታሙ አያሌው ለአንድ ሳምንት ወደ መጸዳጃ ቤት እንድዳይሄድ በመከልከሉ በፌስትታል ይጠቀም እንደነበረ፣ ለሶስት ሳምንታትም ቁጥር ስምንት በምትባል የጨለማ ቤት ዉስጥ ለብቻው እንዲቀመጥ መደረጉንም አረጋግጠናል። “ወደ ፖለቲካው የማትመለስ ከሆነ ትወጣለህ። አለበለዚያ እዚሁ ነው የምትሞተው” […]

“ይምርጡን ሳናዳላ፤ ሳንገል፤ ሳናስር፤ሳንዋሽና ሳንሰርቅ ፍፁም በሆነ አገራዊ ፍቅር አክብረንህ እናስተዳድራለን ”። የምርጫ መሪ ቃል ብትሆን ያልኳት። ጎሽ እንዲህ ነው መቅደም። አገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ዘጠኝ ድርጅቶች በጋራ ለመታገል መስማማታቻውን ስሰማ ሀሴት ነው ያደረኩት። መጀመርያ ዜናውን ስሰማ ጥሩ ነው አልኩ። አንድነትና መድረክ ስይካተቱ የሚፈለገውን ውጤት አያመጣም በሚል አላካበድኩትም ነበር። ደስታዬን ሙሉ ያደረገው ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በኢሳት […]

እለተ አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2007 ይላል የቀን መቁጠሪያው ። በጠዋቱ ተነስቸ መብተክተክ ይዣለሁ ፣ መነሻየ ከሳምንት በፊት በሃገረ ሊባኖስ መዲና ቤሩት ስሟን ለደህነንነት ስል የማልገልጻት ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ በግድያ ወንጀል ተጠርጥራ ባለችበት ሁኔታ በነፍሰ ገዳይነት ውንጀላ መክሻሸፍ አስመልክቶ አዳዲስ መረጃን ለወዳጆቸ ለእናንተ ለማቀበል ነው ። ብዙም ሳልቆይ ቤሩት የመረጃ ምንጭ ወዳጆቸ ስልክ ደወልኩ … […]

ጠይም ፊትሽ መጥቆሩን፣ ትንፋሽሽ፣ ጥሎሽ መሸሹን፣ የፊትሽ ወዝ ማጠፈፉን አካል ቁመናሽ መርገፉን ሰማሁ እናቴ ሰማሁ፣ አይቻል የለ ችያለሁ። በዝምታ ተውበሽ በሰው ሸክም ተሞሽረሽ በኡኡታ … በዋይታ… መሸኘትሽን ሰማሁት አይቻል የለ ቻል አ’ረኩት የሆንሽውን ሳልጠይቅሽ ሳትነግሪኝ ጎንሽ ሆኜ ሳላዋይሽ ሳታዋይኝ ሞተሽ ቀብርሽ ሳልቆምልሽ ከቀረሁኝ እናቴ ሆይ! ፍረጂልኝ ፍረጂብኝ ምን ላድረገው? ምን ታረጊኝ? ስደት ዶጋ አመድ ያድርግህ! […]

የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊና የሚሊዮኖች ግብረ ኃይል ሰብሳቢ የነበሩት፣ አቶ ሃብታሙ አያሌው በጸና መታመማቸዉንና ዛሬ በሆስፒታል መዋላቸዉን ለማረጋገጥ ችለናል። የማእከላዊ እሥር ቤት ብዙ ቶርቸር የሚደረግበት እስር ቤት እንደሆነ ይታወቃል። አቶ ሃብታሙ አያሌው ከብሎገር አብርሃ ደሳታ፣ ዳን ኤል ሺበሺና የዚዋስ አሰፋ ጋር ሐመሌ 1 ቀን የታሰሩ ሲሆን፣ ፖሊስ «መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ይሰጠኝ» በሚል አራት […]

“ማር እንኳን 23 አመትት ቢላስ ይመራል ። 23 አመት እንደ ኢሕአዴግ ላለ ፓርቲ እጅግ በጣም ረጅም አመት ነው” “ሕዝቡ ለዉጥ ይፈልጋል። በዚህ ላይ ምንም አነት ጥርጣሬ የለም፡፡በመላው ኢትዮጵያ ሲኬድ ይሄን አይነትት ስሜት አለ” “ትልቁ ነገር አማራጭ ሆኖ ሕብረተ ሰቡ ተስፋ ሊይደርገው የሚችል ፓርቲ ሆኖ መዉጣት የውወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ይመስልኛል” “አንድነት የሁሉም ኢትዮጵያዊያኖች ቤትና ፓርቲ እንዲሆን […]

የበርካታ የአገዛዙ ባለስልጣናት የግል ቢዝነሶችና ፎቆች በፍጥነትና በጥራት እየተጠናቀቁ ባለብት በአሁኑ ወቅት፣ በ2002 ዓ.ም ለሕዝብ ይፋ ከሆነውና ላለፉት በርካታ አመታት በኢቲቪ ሲነገርለት ከቆየው፣ የአምስት አመቱ የእድገትና የትራስፎርሜሽን እቅዶ ዉስጥ በዋናነት ከሚጠቀሱት ሁለቱ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ፣ በአምስት ኮሪደሮች የታቀደው የባቡር ግንባታ መሆኑ ይታወቃል። ከታቀደው የ2300 ኪሎሜተር የባቡር መስምር ፣ ከመቶ ኪሎሜትር በላይ እንዳልተሰራ፣ አቶ ግርማ ሰይፉ፣ […]

የቀድሞ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው በፍቃዳቸው ሃላፊነታቸውን በመልቀቃቸው ፣ በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ፣ አቶ በላይ ፍቃዱን አዲሱ የድርጅቱ ሊቀመንበር እንዲሆኑ መምረጡ ይታወቃል። አቶ በላይ፣ ዛሬ እሁድ ጥቅምት 9 ቀን 20006 ዓ.ም ፣ አብረዋቸው የሚሰሩ 12 የሥራ አስፈጻሚ አባላትን መርጠው በብሄራውዊ ምክር ቤቱ አጸድቀውዋል። ከተመረጡት 12 የሥራ አስፈጻሚ አባላት ፣ 6 ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ሊቀመንበር የነበሩ ጊዜ፣ የሥራ […]

ጥቅምት 2 ቀን 2007 ዓ.ም የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት ከጠዋቱ 3፡00 ሠዓት ጀምሮ በመሰብሰብ በሁለት አጀንዳንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉን የብ/ም/ቤቱ ሴክሬታሪያት ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ የብሔራዊ ም/ቤቱ መወያያ አጀንዳ የነበረው 1- የአዲሱን ፕሬዚዳንት ካቢኔ ማፅደቅ 2- የአማካሪ ሸንጎ መመሪያን ማፅደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ሲሆን በመጀመሪያው አጀንዳ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ ለብሔራዊ […]

በመጀመሪያ “ወያኔ፣ … እና እኛ” በሚል ርዕስ የማቀርባቸውን ጽሁፎች ዋና ዓላማ ለአንባቢያን ግልጽ ላድርግ። ዛሬ አገራችን ለምትገኝበት አስከፊና ውስብስብ የፖለቲካ ሁኔታም ሆነ በየግላችን ለደረሰብንና ለገጠሙን ቁሳዊና መንፈሳዊ ኪሳራዎች ሁሉ ተጠያቂው ወያኔ ነው ብለን ስለደመደምን እርግማኖቻችን፣ ነቀፌታችን፣ ዝልፊያችን፣ ወቀሳችን፣ ውንጀላችን፣ ዛቻና ማስፈራሪያችን ሁሉ ወያኔ ላይ ያነጣጠሩ ናቸው። እርግማንና ዝልፊያ ግፍንና ግፈኞችን ጠራርገው የሚያጠፋ ቢሆን ኖሮ ባለፉት […]

“ውሻ በበላበት ይጮኻል” እንደሚባለው አማረ አረጋዊም የወያኔን የዘረኞች ሥርዓት ከውድቀቱ ለመታደግ በሚመስል ቀቢፀ ተስፋ ባለ በሌለ ኃይሉ ላንቃው እስኪበጠስ እየጮኸ ነው፡፡ የወያኔ የቁርጥ ቀን ውሾች ሁሉ ካላንዳች ይሉኝታ ጩኸታቸውን ሲያቀልጡት ማየት በተለይ የዚህ ዘረኛ የወሮበሎች ቡድን ፀሐይ መጥለቅ ከጀመረችበት ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በጣም የተለመደ ሆኗል፡፡ ለወያኔ መልካም ሽኝት፤ ለውሾችም መልካም ጩኸት እንዲሆንላቸው ከመመኘት ውጪ […]