ጥር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግብጽ ባለስልጣናት የአባይን ግድብ በተመለከተ ከኢትዮጵያና ሱዳን  ጋር ሲያደርጉት የነበረውን ድርድር ካቋረጡ በሁዋላ ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች ለጋሽ አጋራት ለመውሰድ መወሰናቸውን የግብጽ ባለስልጣኖች መናገራቸውን ተከትሎ ግብጽ በየትኛውም መድረክ ብትሄድ ምንም የምታመጣው ነገር እንደሌለ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት እየተናገሩ ነው። አንዳንድ የመገናኛ ብዙሀን የመንግስትን ባለስልጣናት በመጥቀስ  …

ጥር ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሶሪያ መንግስት እና የተቃዋሚዎች ተደራዳሪዎች በስዊዘርላንድ የተሰበሰቡ ሲሆን ፣ሁለቱም ተደራዳሪዎች ከማለዳው ሃይለ ቃሎችን ተለዋውጠዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሁለቱም ተደራዳሪዎች ወደ ገንቢ ውይይት እንዲመጡ ቢጠይቁም እስካሁን ተስፋ የሚሰጥ ነገር አልተገኘም። አንዱ እና ዋናው አጀንዳ ፕሬዚዳንት በሽር አላሳድ ስልጣን ላይ ስለመቆየታው ሲሆን፣ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ጆን ኬሪ …

ከኣንድ ወር በላይ ለዘለቀውና ከ 10 ሺህ በላይ ሰዎች ለሞቱበት የደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ውጊያ መፍትሄ ለመሻት ነገ ሐሙስ እዚያው ደቡብ ሱዳን ር/ከተማ ጁባ ውስጥ ሊካሄድ ታስቦ የነበረው የምስራቅ ኣፍሪካ የልማት ቤይነ መንግስታት ባለስልጣን ኢጋድ አባል ሓገራት መሪዎች ጉባዔ ቢሰረዝም የሰላም ጥረቱ ግን ተጠናክሮ መቀጠሉ ተሰማ።

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት እንዳስታወቁት አሁን ጦሩ በአሚሶም ዕዝ ሥር የተጠቃለለዉ በጋራ መንቀሳቀሱ የጦሩን ተዕልኮ ከግብ ለማድረስ ጠቃሚ በመሆኑ ነዉ።የወጪ ጉዳይም ከግምት የሚገባ ነዉ።አሚሶምን የተቀየጠዉ የኢትዮጵያ ጦር አራት ሺሕ ወታደሮች አሉት።

የሱዳኑ ፕሬዚደንት ኦማር ሀሰን ኣልበሺር በኤርትራ ያደረጉት ጉብኝት የሁለቱን ኣጎራባች ኣገሮች ግንኙነት ከማጎልበት ጎንለጎን በአካባቢያዊ እና ዓለም ዓቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገለጸ።

ኣልበሺር ከኤርትራው አቻቸው ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ባደረጉት የሶስት ቀናት ቆይታ የደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታን ጨምሮ

ከኣንድ ወር በላይ ለዘለቀውና ከ 10 ሺህ በላይ ሰዎች ለሞቱበት የደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ውጊያ መፍትሄ ለመሻት ነገ ሐሙስ እዚያው ደቡብ ሱዳን ር/ከተማ ጁባ ውስጥ ሊካሄድ ታስቦ የነበረው የምስራቅ ኣፍሪካ የልማት ቤይነ መንግስታት ባለስልጣን ኢጋድ አባል ሓገራት መሪዎች ጉባዔ ቢሰረዝም የሰላም ጥረቱ ግን ተጠናክሮ መቀጠሉ ተሰማ።

ኢትዮጵያ እያካሄደችው ያለው ግንባታ ማንኛውንም ዓይነት ሕግ የጣሰ አይደለም በማለት መንግሥት የግብፅን አቤቱታ ውድቅ አድርጓል፡፡

አል ሞኒተር የተባለ የግብፅ ሚዲያ የተለያዩ የአገሪቱ ባለሥልጣናትን በመጥቀስ፣ ግብፅ በኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ተቃውሞ ዓለም አቀፍ ማድረግ እንደምትፈልግ ዘግቧል፡፡

‹‹የህዳሴው ግድብ አሁን ባለው የግንባታ ደረጃ ተገንብቶ ዕውን የሚሆን ከሆነ በግብፅ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከባድ ነው፡፡ በመሆኑም ጉዳዩን ወደሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት መውሰድ እንደሚገባ፣ ለዚህም አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ነው፤›› ያሉት የአገሪቱ የመስኖና ውኃ ሀብት ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ካህሊድ ዋሲፍ ናቸው፡፡

‹‹ግብፅ የህዳሴው ግድብ ግንባታን ፈፅሞ አትፈቅድም፡፡ ይህንን ለማሳካትም ኢትዮጵያ ምንም ዓይነት የውጭ ዕርዳታ ለግድቡ እንዳታገኝ ግፊት እናደርጋለን፤›› ሲሉ በይፋ ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ የኢትዮጵያን ግድብ በማውገዝ ከግብፅ ጐን እንዲቆም አስፈላጊው ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ግብፅ በዓባይ ወንዝ ላይ በዓለም አቀፍ ሕግ የተከበረና የተረጋገጠ መብት አላት፡፡ ነገር ግን ይህ የግብፅ መብት በኢትዮጵያ እየተጣሰ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ግብፅ በዓባይ ወንዝ ላይ ሕጋዊ መብት አላት የሚሉት ቃል አቀባዩ፣ ማናቸውም የተፋሰሱ አገሮች ተፋሰሱን በመጠቀም ወደ ልማት መግባት ሲፈልጉ በቅድሚያ ግብፅን የማማከርና ይሁንታ የማግኘት ግዴታ አለባቸው ሲሉ የአገራቸውን አቋም አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ይህንን ግዴታ በመጣስ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ መጀመሯ በራሱ ሕግን የጣሰ መሆኑን፣ ነገር ግን የግብፅ መንግሥት ጉዳዩን በወዳጅነት በመያዝ ሲወያይ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ የህዳሴው ግድብ ግንባታ ምንም ዓይነት ጉዳት በግብፅ ላይ እንደማያደርስ ኢትዮጵያ ለማረጋገጥ እንቢተኛ በመሆኗ ግብፅ ከውይይቱ ራሷን እንዳገለለች አስረድተዋል፡፡

የግብፅ የቀድሞ የመስኖና የውኃ ሀብት ሚኒስትር ሙሐሙድ ናስር አል ዲን አላም በበኩላቸው፣ ግብፅ ከዚህ በኋላ በህዳሴው ግድብ ላይ ሌላ አማራጭ የላትም ብለዋል፡፡ የቀረውና በፍጥነት ተግባራዊ መሆን የሚገባው አማራጭ ጉዳዩን ዓለም አቀፋዊ ይዘት እንዲኖረው ማድረግ፣ በዋናነትም ይፋዊ ቅሬታና ተቃውሞ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማቅረብ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

‹‹ማንኛውም የዓባይ ተፋሰስ ተጋሪ አጋር በወንዙ ላይ ፕሮጀክት ከመጀመሩ በፊት የግብፅን ይሁንታ ማግኘት አለባት የሚለው ስምምነት ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነት ያለው ነው፤›› በማለት የሚከራከሩት የቀድሞው ሚኒስትር ኢትዮጵያ ይህንን ስምምነት በመጣስ ለጀመረችው ግንባታ በተባበሩት መንግሥትት ድርጀት ልትጠየቅ ይገባታል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል አሁን ያለውን አለመግባባት በተመለከተም ዓለም አቀፍ እውነት አፈላላጊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ማጥናት ይኖርበታል በማለት ተከራክረዋል፡፡

የግብፅ ባለሥልጣናት እያንፀባረቁት ስላለው አዲስ አቋም የተጠየቁት የኢትዮጵያ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅ አህመድ፣ ‹‹ኢትዮጵያ የቅኝ ግዛት ውል አይመለከታትም፣ ምክንያቱም አልፈረመችም፤›› ሲሉ የግብፅ ባለሥልጣናት መግለጫን አጣጥለዋል፡፡ የቅኝ ግዛት ውሉ የተፈረመው በግብፅና በእንግሊዝ መካከል መሆኑን ያስታወሱት አቶ ፈቅ፣ እንግሊዝ ቅኝ የገዛቻቸውን ኬንያ፣ ታንዛኒያና ኡጋንዳ በመወከል ስምምነቱን ፈርማለች፡፡ ይህ ግን ኢትዮጵያን ፈፅሞ አይመለከትም ብለዋል፡፡

የግብፅ የቀድሞው የመስኖና የውኃ ሀብት ሚኒስትር በተደጋጋሚ ይህንን መሳይ ነገር ያነሳሉ በማለት ያስታወሱት አቶ ፈቅ፣ ‹‹ሰውዬው ከሳይንስ ውጭ ነው የሚናገሩት፣ ከእሳቸው የሚጠበቅ አይደለም፤›› ሲሉ ወቅሰዋቸዋል፡፡

‹‹ኢትዮጵያ የጀመረችው የህዳሴው ግድብ ግንባታ የትኛውንም ዓለም አቀፍ ሕግ የጣሰ አይደለም፡፡ ወደፈለጉበት ቢሄዱ የሚመጣ ነገር የለም፤›› ሲሉ አክለዋል፡፡ ጉዳዩን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ መምራት ሊያተርፍ የሚችለው በሁለቱ አገሮች ያለውን የትብብር መንፈስ ማጥፋት ነው ሲሉ የግብፅ ባለሥልጣናትን የሰሞኑን ዘመቻ አውግዘዋል፡፡ Reporter

ከኡጋንዳ ኢንቴቤ ተነስቶ ወደ ሰንዓ የመን በመብረር ላይ የነበረ ንብረትነቱ የዩክሬን የሆነ አንቶኖቭ 28 የመንገደኞች አውሮፕላን ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ አቅራቢያ ለገዳዲ አካባቢ ተከሰከሰ፡፡

ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው፣ የአውሮፕላኑ አብራሪዎች ሰኞ ማለዳ ከባለሥልጣኑ ጋር ባደረጉት የሬዲዮ ግንኙነት ከኢንቴቤ ተነስተው በኢትዮጵያ በኩል ወደ የመን ለመብረር ፈቃድ ጠይቀው ነበር፡፡ ባለሥልጣኑም የበረራ ፈቃድ ሰጥቷቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ኤር ናቪጌሽን ክፍል ለአብራሪዎቹ የሚበሩበትን ከፍታ ሰጥቷቸዋል፡፡ አውሮፕላኑ የኢትዮጵያን አየር ክልል አቋርጦ በማለፍ ላይ ሳለ አዲስ አበባ አካባቢ ሲደርስ የሞተር ብልሽት ያጋጥመዋል፡፡ ይህንኑ ለአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራ መቆጣጠሪያ ማማ አሳውቆ ‹‹ኢመርጀንሲ ላንዲንግ›› እንደሚያደርግ (በድንገተኝነት እንደሚያርፍ) ሪፖርት አድርጐ፣ ከጠዋቱ 3፡35 ሰዓት ላይ ለማረፍ ወደ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በማምራት ላይ ሳለ ለገዳዲ አካባቢ ተከስክሷል፡፡

አደጋው እንደደረሰ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ፈልጐ ማዳን ቡድን ወደ ሥፍራው ተንቀሳቅሶ የአውሮፕላኑ አብራሪዎችን ወደ ሆስፒታል በመውሰድ ሕክምና እንዲያገኙ አድርጓል፡፡ በአውሮፕላኑ ውስጥ ተሳፋሪዎች እንዳልነበሩ ታውቋል፡፡ በአደጋው አብራሪዎቹ የተጐዱ ቢሆንም፣ ሕይወቱ ያለፈ ሰው እንደሌለ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የአውሮፕላን አደጋ መከላከልና ምርመራ ክፍል ባለሙያዎች የአደጋውን መንስዔ ለማወቅ ምርመራ ጀምረዋል፡፡ ባለሙያዎቹ አውሮፕላኑ ወደ ወደቀበት ሥፍራ በማምራት መረጃ በማሰባሰብ ላይ ይገኛሉ፡፡

ሩሲያ ሰራሽ የሆኑ አንቶኖቭ አውሮፕላኖች ከተመረቱ ረዥም ጊዜ ያስቆጠሩ በመሆኑ በየጊዜው እክል እየገጠማቸው በተለያዩ አገሮች በመከስከስ ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ዕድሜ ጠገብ አውሮፕላኖች ዋጋቸው ርካሽ በመሆኑ በአፍሪካ አገሮች በብዛት ይገኛሉ፡፡ ያረጁ በመሆኑና ተገቢ የሆነ ጥገና ስለማይደረግላቸው በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች በተደጋጋሚ አደጋ እንደሚያደርሱ የአቪዬሽን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ Reporter

ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ‹መዝገበ ቃላት› ለነፃነት የሚሰጠው ትርጓሜ ‹አራምደዋለሁ› ከሚለው ግራ-ዘመሙ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ብያኔ አንፃር የሚተነተን በመሆኑ፣ የየትኛውም ተቋም ነፃ ሆኖ የመንቀሳቀስ መብት ላይ ረዣዥም እጆቹን ደጋግሞ እየጫነ ሲጨፈልቅና ሲያስጨፈልቅ ለመኖሩ በርካታ ማሳዎችን ማቅረብ ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሁለተኛው ‹‹የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት›› ዘንድሮ በመጋቢት ወር መጨረሻ ይከናወናል፡፡ ለሀገሪቱ በጎ ሠርተዋል የሚሏቸውን ሰዎች ይጠቁሙ፡፡ ለጥቆማ የሚረዷችሁ ነጥቦች

  1. ለሀገር ሰላም፣ ለሕዝቦች መቀራረብና መደጋገፍ፣ ለውጥ አምጭ አስተዋጽዖ ያደረጉ፣

  2. በበጎ አድራጎትና ሰብአዊ ተግባራት ተሠማርተው የሰው ልጅን ሕይወት የለወጡ፣

  3. በሥነ ጽሑፍ፣ በኪነ ሕንጻ፣ በሥነ ጥበብና በመሳሰሉት መስኮች ለኢትዮጵያውያን የሚጠቅሙ፣ የኢትዮጵያን ስም ከፍ የሚያደርጉ፣ የሀገሪቱን ሥነ ጥበብ ወደ አንድ የላቀ ደረጃ የሚያደርሱ ሥራዎች የሠሩ፣

  4. በግብርና፣ በቢዝነስ፣ በኢንዱስትሪና በመሳሰሉት መስኮች አዲስ፣ የራሱ ወጥነት ያለውና ያልተደፈረ የሚመስለውን ሥራ ያከናወኑ፣ ለሀገሪቱ ዕድገትና ሥልጣኔም ለውጥ አምጭ አስተዋጽዖ ያደረጉ፣

  5. በጋዜጠኛነት መስክ ተሠማርተው ሙያውን የጠበቀ፣ ለሌሎች አርአያ የሚሆን፣ የሕዝቡን ኑሮ የሚለውጥ ሥራ ያከናወኑ፣

  6. በዲፕሎማሲው መስክ የሀገሪቱን ክብርና ደረጃ ያስጠበቁ፣ የሀገሪቱንም መብት ያስከበሩ፣

  7. በመንግሥትና በሥራ ተቋሞቻቸው የተሰጧቸውን የተለያዩ ሀገራዊ ግዳጆችን በብቃት የተወጡ፣ መሥዋዕትነት የሚጠይቁ ተልዕኮዎችን ያከናወኑ፣ ለትውልድ አርአያ የሚሆኑ ብቁ አመራሮችን የሰጡ፣ በአመራሮቻቸውም ድርጅታቸውንና መሥሪያ ቤቶቻቸውን የለወጡ፣

  8. ሀገራዊ ዕውቀቶችን በማስተማር፣ ቅርሶችንና ባህልን በማስጠበቅና በመከባከብ ለውጥ አምጭ ተግባር ያከናወኑ፣

  9. በጥናትና ምርምር መስክ ተሠማርተው ችግር ፈች የሆኑ ውጤቶችን ያስመዘገቡ፣

  10. በማስታረቅ፣ ግጭቶችን በመፍታት፣ ሀገራዊ የሽምግልና ሥራ የሠሩ፣

  11. በሌሎችም መስኮች የሚጠቀስ፣ ለሀገር የሚጠቅም፣ ለትውልድ አርአያነት ያለው፣ የሀገርን ክብር የሚጨምር፣ ታሪክና ማንነትን የሚያጎላ ተግባር ያከናወኑ ሌሎችንም ኢትዮጵያዊ ዜጎችን ይጠቁሙ፤

 ማስተዋሻ
    • የሚጠቁሟቸው ኢትዮጵያውያን በተቻለ መጠን ከዚህ በፊት ያልታወቁና ይህን መሰል ዕድል ያላገኙ ቢሆኑ ይመረጣል፣

    • በተቻለ መጠን ከአዲስ አበባ ወጣ ባሉ ቦታዎች ሰው ሳውቃቸው ለሀገራቸው አስተዋጽዖ የሚያደርጉ ዜጎችን በመጠቆም ይተባበሩ፣

    • ሲጠቁሙ የጠቆሙትን ሰው ስም፣ ያለበትን ቦታ፣ የሠሩትን በጎ ሥራ ዘርዘር አድርገው ይግለጹ፣ ከቻሉም ስልካቸውን ወይም ኢሜይላቸውን ይላኩልን፣

    • ጥቆማውን እስከ የካቲት 15 ቀን 2006 ዓም ያድርጉልን

    • ከሀገር ውጭ ሆነው ሀገራዊ ሥራዎችን የሚሠሩና ሀገራቸውንንና ሕዝባቸውን የሚጠቅሙትን በጎ ዜጎች እንጠቁም

    • ከጥቆማው በኋላ የተቋቋመው ኮሚቴ ሃያ አምስት ዕጩዎችን ይጠቁማል፤ በእነዚህ ዕጩዎችም ላይ ከተለያየ ሙያ፣ መስክ፣ ዕድሜ፣ እምነት፣ አካባቢ፣ የዕውቀት መስክ የተወጣጡ ነገር ግን እርስ በርሳቸው የማይተዋወቁ 100 ሰዎች ድምጽ ይሰጧቸዋል፡፡ በእነዚህ ሰዎች ድምጽም የመጨረሻዎቹ አምስት ሰዎች ይመረጣሉ፣

    ለመጠቆም ይህንን የኢሜይል አድራሻ ይጠቀሙ  [email protected]

    ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው የሠሩትን ዜጎቻችንን እናበረታታ፣ እንሸልም፣ ዕውቅና እንስጥ

    በምስራቅ ሃረርጌ ከ59 ሰዎች በላይ መገደላቸውን መንግስት ግጭቱን ሆን ብሎ መቀስቀሱን የኦሮሞ ጥናት ማህበር ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢብራሂም ገለጡ:: የማህበሩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢብራሂም ኢሌሞ ለኢሳት እንደገለጹት ባለፉት ጥቂት ወራት በአንያ፣ ማቶ እና ሙለቄ ቆላማ ወረዳዎች ላይ በፌደራል መንግስቱ እውቅና የተቋቋመውና ስልጠና የሚሰጠው ልዩ ሚሊሺያ እየተባሉ የሚጠሩት ሃይሎች በኦሮሞዎች ላይ በሰነዘሩት ጥቃት 59 ገድለው፣ 42 አቁስለዋል፤ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከልም ሴቶችና ህጻናት ይገኙበታል።

    “በድንበር አካባቢ የሚኖሩ ህዝቦች ሰላም ካገኙ ለተቃዋሚዎች ምቹ ቦታ ሊፈጥሩ ይችላል በሚል እሳቤ የሁለቱን ክልል ህዝቦች እያጋጨና እርስበርስ ተጠባብቀው እንዲኖሩ ለማድረግ ” መንግስት ግጭቱን ሆን ብሎ መቀስቀሱን የገለጡት ዶ/ር ኢብራሂም ፣ በግጭቱም እድሜውን ለማራዘም እንደሚያስብ ተናግረዋል። ማህበሩ ለአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ፣ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ለሌሎችም አገራት ደብዳቤ ማስገባታቸውን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል ። ኢሳት ዜና

    ምንሊክ ሳልሳዊ
    እኛ ሃገራችንን የምንወድ ኢትዮጵያን ስለ ፖለቲካ ድርጅቶች አያገባንም::እንዲያድጉ እንዲለሙ እንዲመነደጉ እናበረታታለን እንጂ በነዙ ስትራቴጂ አልባ ድፍን ደረቅ ፖለቲካ ውስጥ ገብተን አብረን በጭቃቸው መቡካት አንፈልግም::የወደደ ይውደድ የጠላ ይጥላ እትዮጵያ ውስጥ ወያኔን ጨምሮ ሁሉም የፖለቲካ ጎራ ጥያቄው የስልጣን እና የአገዛዝ ሩጫ ነው::የእኛ የዜጎች ጥያቄ ግን ፍትህ መልካም አስተዳደር የአገልግሎት አቅርቦት እና ሰላም ነው::

    ወያኔ የሚያደፈርሳቸው ተቃዋሚ ነን የሚሉትም በአቅማቸው የሚያደፈርሷቸው ሰላሞቻችን ይመለሱልን::ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን የሚበጅ አስተዳደር ለማምጣት መጀመሪያ የህዝቦች ጥያቄ መመለስ የለውጥ እርምጃ መምጣት አለበት::
    ለዘላቂ ልማት እንሰራለን በሚል ስርኣት ውስጥ የመሰረታዊ የዲሞክራሲ መብቶች በጊዜያዊነት መኖር እና እንደመነገጃ መጠቀም ህዝብን አገለግላለሁ ሳይሆን አጭበረብራለሁ እንደማለት ይቆጠራል:: የወያኔ ስርኣት ባለስልጣናት በፍርሃት ተውጠው በሚኖሩባት በዚች ኢትዮጵያችን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ አሁንም እጅግ መልስ የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው::ዜጎች በሃገራቸው እንዳይኮሩ በመኖር ደህንነታቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲያሳድሩ እየተደረገ ስለሆነ ይህ ደሞ ወያኔ በዘላቂነት የያዘውን ስልጣን ላለመነጠቅ የሚሰራው ፖለቲካዊ ደባ ውጤት መሆኑ እሙን ነው::

    ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን ወደ እውነት ያመጡ ህጎች በኢትዮጵያ አሉ የሚለው ወያኔ ህዝቦች ግን በተግባር ተጠቃሚ ሲሆኑ አላየንም::ህጎቹ በተግባር ይዋሉ ይህንን ህጎች በመመሪያ በደብዳቤ እና በስልክ የሚቀይሩ የሚደፈጥጡ በጥቅም የሚሸጡ የሚረጋግጡ የሚለውጡ ከየወንበራቸው ተሽቀንጥረው ይጣሉ:: የቀን ተቀን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ሂደት ውስጥ እጃቸውን እያጠለቁ ፍትህን የሚያዛቡ አስተዳደራዊ በደሎችን የሚፈጽሙ ባለስልጣናት የህዝብን ማህበራዊ ህይወቶች ከማፋለሳቸውም በላይ ፖለቲካው እንዲጭበረበር ኢኮኖሚው እንዲደቅ ሃገር በብድር እንድትዘፈቅ ህዝብ እንዲደኽይ ከባዱን ሚና እየተጫወቱ ነው::

    ህዝቦች ህግ እየጸደ ህግ እየተሽሞነሞነ እና እየተብለጨለጨ ቢቀመጥ ምንም የሚጠቅማቸው ነገር እንደሌለ መታወቅ ያለበት ሲሆ አንድ ህዝብ ባላረቀቀ ባልተወያየበት እና ባላጸደቀው ህግ እየተገዛ ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን እንዴት ማስፈን ይቻላል??? መተማመን እና የዜግነት ኩራቱን በሚሰብሩ ባለስልጣናት እየተሰበረበት ያለ ህዝብ ፍትህን እና አስተዳደራዊ እንዲሁም አገልግሎቶችን በተግባል ለማየት እና ለመጨበጥ አልቻለም:: ለተበደለና ፍትሕ ላጣ ዜጋ፣ መልካም አስተዳደር አጥቶ ለሚንገላታ ዜጋ ፍትሕና መልካም አስተዳደር እንዲኖር በአንቀጽ ተደንግጓል እያልን ብናወራ ዋጋ የለውም::

    ህዝብ ባለው ስርኣት ላይ እምነት የለውም:; ይህ ደግሞ ራሱ ስርኣቱ ያረጋገጠው ነገር ነው ኢትዮጵያውያን የስርኣቱ ታጣቂ ሃይሎች በሌሎች ወገኖቻቸው ላይ የሚያደርሱትን የሰብኣዊ መብት ጥሰት እያዩ በሃገሪቱ ህግ የለም እኔም ነገ እደበደባለሁ እታሰራለሁ ንብረቴን እነጠቃለሁ መብቴን እነፍርጋለሁ እጠቃልሁ እገደዳለሁ እሰደዳለሁ እገደላለሁ በሚል በስርኣቱ ላይ ያላቸው እምነት የተሟጠጠ ከመሆኑም በላይ ከትንሽ እስከ ትልቅ ከሃገር የመውጣት ንብረትን እና ሃብትን የማሸሽ ተግባር ላይ በመሰማራት በዜግነት አለመተማመን እንዲፈጠር በሩን በርግዶ ከፍቷል ይህ ደሞ ህጎች በተግባር ህዝብን አለማገልገላቸው እና በባለስልጣናት የመደፍጠጣቸው ውጤት ነው::

    በተግባር ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት የተነሳ ማንም የለም::ስርኣቱም በጥቅመኞች የሚመራ ህዝቡም ላላወጣው ህግ በዝምታ ደንታቢስነቱን እየገለጸ ነው; ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን የሚጥስና የሚያደናቅፍ የስርኣቱ ባለሥልጣን፣ ዜጋም ሆነ ግለሰብ፣ በማስረጃ ሲታይና ሲረጋገጥ ዕርምጃ ለመውሰድ ሕግ ፊት ለማቅረብ ምንም አይነት የተሰራ ስራ ካለመኖሩም በላይ በባሰ መልኩ በይፋ ህጎች ሲደፈጠጡ እያየን ነው:: ባለሥልጣንም ሆነ ባለ ሀብት፣ ታዋቂም ይሁን ተራ ዜጋ፣ ከፈለገው ብሔር ብሔረሰብ ይምጣ፣ የፈለገውን ሃይማኖት የሚከተል ይሁን፣ የጾታና የዕድሜ ልዩነት ሳይኖር ተቃዋሚም ይሁን ደጋፊ ሁሉም ሕግ ፊት፣ ፍትሕ ፊት፣ መልካም አስተዳደር ፊት እኩል መሆኑን አምነን በተግባር ለማዋል ቁርጠኝነት በፍጹም የለም:: ፍትህ እና መልካም አስተዳደር እንዴት ሊረጋገጡ ይችላሉ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እየተጓዝን ነው ጥያቄያችን ;ስለዚህ ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል::

    ጥር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለስልጣኑ ይህን የተናገሩት የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የደህንነት ሰራተኞች በተገኙበት በተደረገው ግምገማና ውይይት ላይ ነው። በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ድንበር የማካለል እንቅስቃሴ ከ1965 ዓም ጀምሮ በጊዜው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር በነበሩት ዶ/ር ምናሴ ሃይሌና በሱዳኑ አቻቸው ጃፋር ኤሊ ሜሪ መካከል የተጀመረ እና እስካሁኑም የዘለቀ መሆኑን ባለስልጣኑ አውስተዋል። …

    ጥር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የማህበሩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢብራሂም ኢሌሞ ለኢሳት እንደገለጹት ባለፉት ጥቂት ወራት በአንያ፣ ማቶ እና ሙለቄ ቆላማ ወረዳዎች ላይ በፌደራል መንግስቱ እውቅና የተቋቋመውና ስልጠና የሚሰጠው ልዩ ሚሊሺያ እየተባሉ የሚጠሩት ሃይሎች በኦሮሞዎች ላይ በሰነዘሩት ጥቃት 59 ገድለው፣ 42 አቁስለዋል፤ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከልም ሴቶችና ህጻናት ይገኙበታል። “በድንበር አካባቢ የሚኖሩ ህዝቦች …

    ጥር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት የቀድሞ የህወሃት ታጋይ አቶ ዘርዓይ አስገዶምየኢትዮጵኢያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር በመሆን መሾማቸው መንግስት ከምርጫ 2007 በፊት በፕሬሱ ላይ ለሚወስዳቸው እርምጃዎች ጠንካራ አስፈጻሚ በማስፈለጉ ሊሆን እንደሚችል ኢቲቪን የለቀቁ አንዳንድ ጋዜጠኞች ተናገሩ። የአቶ ዘርዓይ ከቴሌቪዥን ዳይሬክተርነት መነሳት በአቶ በረከት ስምኦን ምትክ …

    ጥር ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ላይ ወቀሳቸውን የሰነዘሩት ድርጅቱ ራሱን እንደ ሁለተኛ መንግስት በመቁጥር የጦር መሳሪያዎችንና አማጽያንን አስጠልሏል በማለት ነው። ፕ/ር ሳልቫኪር የተመድ ዋና ጸሀፊ አገሪቱን ማስተዳደር የሚፈልጉ ከሆነ በግልጽ ይንገሩን ያሉ ሲሆን፣ ተመድ ወደ አገራቸው ሲገባ ተጓዳኝ መንግስት ሆኖ መግባቱን አላውቅም ነበር ብለዋል። ተመድ …

    የኢዜአ ማደናገሪያ ዜና – አንድ ተጨባጭ ምሳሌ January 20, 2014 ታደሰ ብሩ በቅድሚያ የሚከተለውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን (ኢዜአ) ዜና አጣጥሙልኝ። … ጎባ ጥር 10/2006 በባሌ ዞን ከእርሻ ስራ በተጓዳኝ በንብ ማነብ ፓኬጅ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ከ53 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘታቸውን የዞኑ የእንስሳት ሀብት ልማትና ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የእቅድና ግምገማ በለሙያ […]

    ክንፉ አሰፋ

    የጥምቀት በዓልን ተሰባስበን በምናከብርበት አንድ ቤት ውስጥ ካለወትሮው ፓልቶክ ተከፍቷል። በዚያ የበዓል ድባብ፤ የፓልቶክ ንትርክ መከፈቱ ሳይገርመን፣ ርእሱ የሁላችንንም ቀልብ መሳቡ። በእርግጥ አንድም ቁም ነገር በንግግሩ አልሰማንም። አዲሱን ቋንቋ ልዋስና የፓልቶኩ ተናጋሪዎች ሙድ  የሚያስይዙ ነበሩ። ሰዎቹ በዚህ ከቀጠሉ የእነ ክበበው ገዳን ገበያ መዝጋት እንደሚችሉ አያጠራጥርም።

    ሙሉውን አስነብበኝ …

    አቶ አለማየሁ ለፌቦ የተባሉ በሲዳማ ጭሬ የአንድነት ፓርቲ አባል ከፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማግስት ወደ ክልሉ ሲመለሱ አርሲ ሚጣ ነሴቦ ወረዳ ወርቃ ከተማ ታህሳስ 26 ቀን 2006 ዓ.ም እንደተያዙ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከታሰሩበት ወረዳ ያንተ ጉዳይ የፖለቲካ ጉዳይ ስለሆነ እዚህ አይታይም በማለት ጥር 9 ቀን ወደ ሻሸመኔ ዞን ፖሊስ ተወስደው ታሰሩ፡፡ ዝርዝር ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

    የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትናንት ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ ባካሄዱት ስብሰባ በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ የሚካሄደውን ግጭት ለማስቆም የሚያግዙ ወታደሮችን ለመላክ ተስማምተዋል ። የአውሮፓ ህብረት የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ዘመቻና የጀርመን የአፍሪቃ ወታደራዊ ተልዕኮ የዛሬው አውሮፓ ና ጀርመን ዝግጅታች ትኩረት ነው ።

    ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ በነሀሴ ወር 2012 ዓ.ም. መሞታቸውን ተከትሎ በኢትዮጵያ የተተካው አዲሱ አመራር ሰብዓዊ መብቶችን የሚመለከቱ ማሻሻያዎች እንደሚያደርግ ተጥሎ የነበረው ተስፋ ተዳፍኗል፤ በ2013 ዓ.ም ተጨባጭ የሆነ የፖሊሲ ለውጥ አልታየም፡፡ ይልቁንም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሃሳብን የመግለጽ፣ የመደራጀት እና በሰላም የመሰብሰብ ነጻነት ላይ የጣሉትን ጥብቅ ገደብ ማስፈጸማቸውን የቀጠሉበት ሲሆን የሲቪል ማህበራትን እና ነጻ መገናኛ ብዙሃንን እንቅስቃሴ […]

    ጥር ፱ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት በመረጃዎች አያያዝ ዝርክርክነት ፣ በሳይበር በሚደረጉ ስለላዎች እና ከውስጥ ባሉ የመንግስት አካላት እየሾለኩ በሚወጡ መረጃዎች ህልውናየ አደጋ ላይ ወድቋል በማለት ግመገማ ማድረጉን ተከትሎ  ”የደህንነት ሰራተኞች ሃላፊነታችን ለማን ነው?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውን  ከደህንነት መስሪያ ቤት ለኢሳት የደረሰው በድምጽ የተደገፈ መረጃ አመለከተ። በስብሰባው ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት …

    ጥር ፱ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢትዮጵያ ከፍተኛ የገንዘብ ብድር የሚሰጡ 2  ባንኮችን ጨምሮ 17 የሚሆኑ የቻይና ኩባንያዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናት ስራዎችን ለተወሰኑ የቻይና ኩባንያዎች ብቻ እየሰጡ መሆኑን የሚገልጽ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ተከትሎ ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር መልስ መስጠቱን ሪፖርተር ዘግቧል። ጋዜጣው እንዳለው መንግስት ቅሬታዎችን ለማስተካከል ቃል ገብቷል። መንግስት የግዢ ስርአት እንደሚዘረጋና የመሰረተ ልማት ተቋማት …

    ጥር ፱ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የውጭ የመገናኛ ብዙሃን እንደዘገቡት በአዲስ አበባ ሁለቱን ተፋላሚ ሃይሎች ለማስማማት ውይይት ቢጀመርም፣ በመሬት ላይ እየተደረገ ያለውን ጦርነት ለማስቆም አልተቻለም። በዩጋንዳ መንግስት የሚደገፈው የመንግስት ጦር ቦር እየተባለ የሚጠራውን ስትራቴጂክ ከተማ ከተቆጣጠረ በሁዋላ በቅርቡ የተነጠቀውን ማላካልን መልሶ ለመያዝ ከፍተኛ ትግል እያደረገ ነው። መንግስት ከተማዋን መልሶ መያዙን ቢያስታውቅም፣ አማጽያኑ …

    ጥር ፱ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፕሬዚዳንት ያንኮቪች መንግስት የተቃውሞ ሰልፎችን በተመለከተ ያወጣው አዲስ ህግ ያስቆጣቸው ዜጎች ወደ አደባባይ በመውጣት ከፖሊሶች ጋር እየተጋጩ ነው። መንግስት የተቃውሞ ሰልፎችን ለመገደብ ያወጣው አዲሱ ህግ በሌሎች የአውሮፓ አገራት ሳይቀር ተወግዟል። ተቃዋሚዎች በፖሊሶች ላይ ድንጋይ ከመወርወራቸውም በተጨማሪ፣ መኪኖችን ሲያቃጥሉ ታይቷል። የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ያንኮቪች ድርጊቱ የዩክሬንን ደህንነት አደጋ …

    የኦሮሚያ ክልል የቱሪዝምና ባህል ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ሞሃመድ ጂሊ፣ የአኖሌ ሃዉልት እንደተሰራና በመሰራቱም ትልቅ ኩራት እንደሚሰማቸው፣ ገዛ ተጋሩ በተባለ የፕላቶክ ክፍል ቀርበው ገለጹ። የአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች በአርሲ የሴቶችን ጡት ቆርጠዋል የሚባለዉ ወሬ፣ የቀድሞ የሕወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት አቶ ተስፋዬ ገብረ አብ በጻፉት መጽሃፍ ከመጻፉና በአንዳድን አክራሪ የኦሮሞ ድህረ ገጾች ላይ ከመዉጣቱ መቀር፣ በታሪክ ባለሞያዎች […]

    የአዉሮጳ ህብረት መንግስት አልባ እየሆነች በመጣችዉ በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ወታደሮችን ለመላክ ዛሪ ብራስልስ ላይ ተስማማ። የህብረቱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ካለፈዉ አጋማሽ ጀምሮ ቀዉስ በተጠናወታት በዚችዉ ሀገር ወታደሮቻቸዉን የሚልኩት እየተጠናከረ የመጣዉን ዉጥረት ለመግታት ነዉ።

    የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በእንግሊዝኛው ምህጻሩ UDJ ሊቀመንበርነታቸውን መልቀቃቸውን አስታወቁ።

    ሊቀመንበርነታቸውን ብቻም ሳይሆን ከUDJ አባልነትም የተሰናበቱት ዶ/ር ነጋሶ ከዚህ በኃላ በማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ አልሳተፍም ብለዋል።

    ግብፆች ሕይወት፥ ደም አካላቸዉን መስዋዕት ያደረጉበት አብዮት የምክር ቤት እንደራሴዎቻቸዉን፥ ለመጀመሪያ ጊዜ በነፃ እንዲመርጡ አስችሏቸዋል።ፕሬዝዳታቸዉንም እንደዚሑ።ሕገ-መንግሥትም አፅድደቀዋል።ዳር ግን አልዘለቀም።ከ1952 ጀምሮ የግብፅን የሚቆጣጠረዉ ጦር ሐይል የግብፅ ሠላማዊ ሕዝብ ፍላጎትና ምኞት እንዲሳካ ሥልጣኑን መልቀቅ አልፈቀደም።

    ጃኑዋሩ 22 ቀን 33ኛ አመቷን ታከብራለች። በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉት ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት። ይች ሴት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል […]

    ሰሞኑን ኤፍሬም ሥዩም ያዘጋጀውን ‹ተዋነይ -ብሉይ የግእዝ ቅኔያት ፍልስፍና› የተሰኘ መጽሐፍ እያነበብኩ ነበር፡፡ አንዳንድ ‹ጻፍን› ብለው የሚያስቡ የኔ ብጤዎች የጥንቱን ሁሉ እንደ አሮጌ በሚያዩበት ዘመን ኤፍሬምን የመሰለ አስተዋሽ ማግኘት መታደል ነው፡፡ ባለማወቃችን ምክንያት የለንም ልንል ስንነሣ፣ እንዲህ የሚያስታውሱን አይጥፉ፡፡

    ቀደምት ኢትዮጵያውያን ፈላስፎች ሃሳቦቻቸውን የገለጡባቸውን የግእዝ ቅኔያት በግጥም መልኩ እየተረጎመ ግራና ቀኝ አድርጎ አቅርቦልናል፡፡ ኤፍሬም የግእዝ ቅኔያቱን የሰበሰበበት መመዘኛው ፍልስፍና ነክነት ይመስለኛል፡፡ ሊቃውንቱ ከምድር እስከ ሰማይ ያሉ ፍጡራንንና ኃያላንን የሞገቱበትንና የመረመሩበትን መንገድና ምጥቀት እናያለን፡፡ በመጽሐፉ ውስጥ 83 የግእዝ ‹ቅኔዎች› ቀርበዋል፡፡ አንዳንዶቹን አንብባችሁ ስትገረሙ ልትውሉ ትችላላችሁ፡፡

    ለምሳሌ እንዲህ ያለውን የአለቃ ገብረ ሐና ቅኔ ስታዩ፡-

    ኮንኖ ኃጥኣን ክርስቶስ ኢይደልወከ ምንተ

    አፍቅሩ ጸላዕተክሙ እስመ ትብል አንተ

    አንዳንዶቹን አንብባችሁ ደግሞ ስትመሰጡ ታነጋላችሁ፤

    እንዲህ የሚሉትን ስታነቡ፡-

    ሙሴ ፈጠረ ፈጣሪሁ፣

    ወፈጣሪ ፈጠረ ኪያሁ፤

    አንዳንዶቹ እንደገና እንደገና እንድትመራመሩ ያደርጓችኋል፤

    ባሕቲቶ ነቢረ እግዚአብሔር ፈርሀ

    እም ኢሀልዎ ንዋም እስመ ዓለመ አንቀሐ

    አንዳንዶቹም ብቻችሁን እያወራችሁ እንድትሄዱ ያደርጓችኋል፡-

    እመ ተናገርኩ ጽድቀ ሰብአ ዛቲ ዓለም ይጸልዑኒ፣

    ወከመ ኢይንብብ ሐሰተ ኩነኔ ዚአከ ያፈርሀኒ፣

    እም ኩሉሰ አርምሞ ይኄይስ ወይሤኒ

    በውጭው ዓለም አንድን ዕውቀት ለመረዳት ይቻል ዘንድ በየፈርጁ እንዲቀርብ ይደረጋል፡፡ ለምሳሌ የኤዞፕ ተረቶች አንድ ዓይነት ቢሆኑም በልዩ ልዩ ዘርፎች እየተዋቀሩ እንደገና እስካሁን ይቀርባሉ፡፡ ኤፍሬም ለግእዝ ቅኔያት ይህንን መንገድ አመላክቷል፡፡ ፍልስፍናውያን፣ ታሪካውያን፣ መንፈሳውያን፣ ትርጓሜያውያን፣ ዶግማውያን፣ ወዘተ እያልን በየዘርፉ ልናያቸውና በሚገባ ልናውቃቸው እንደምንችል አመላክቷል፡፡

    ባይሆን ኤፍሬም ለወደፊቱ የቅኔዎቹን ታሪካዊ ዳራ በግርጌ ማስተዋሻ በኩል ጣል ቢያደርግልን የኔ ብጤዎች በሚገባ ለመረዳት በር ይከፍትልናል፡፡ በመጽሐፉ መጀመሪያ ሊቀ ኅሩያን በላይ እና ራሱ ኤፍሬም የጻፏቸው መቅድሞችም የቅኔዎቹን ያህል ተወደውና ልብ ገዝተው የሚነበቡ ናቸው፡፡

    ይህንን በ190 ገጽ የተጠቃለለ፣ በ100 ብር የሚሸጥ፣ በሻማ ቡክስ የታተመ መጽሐፍ ታነቡት ዘንድ እየጋበዝኩ እስኪ ይኼን ቅኔ ፍቱ

    ድንግል ወለት ትመስለነ ዕቤርተ

    አኮኑ ትውዕል እንዘ ተሐቅፍ እሳተ

    መልካም ንባብ፡፡ 

    በሱዳን፣ ግብጽና ኢትዮጵያ መካከል ሲደረግ የነበረዉ የሶስትዮች ንግግር መበተኑን አስመልክቶ ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት እንዲሁም የፓርላማ አባል፣ የግብጽን አቋም «የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቅ» እንደሆነ በመግልጽ፣ መንግስት የወሰደዉን አቋም ደገፉ። በአባይ ግድብ ዙሪያ እንኳን የተቀረዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የፓርላማ አባል የሆኑት እርሳቸዉም በቂ መረጃ እንደሌላቸዉ የገለጹት አቶ ግርማ፣ «የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ከዚህ አንፃር በጭፍን የአባይን ግድብ እንዲደግፉ እንጂ […]

    የጥምቀት በዓልን ተሰባስበን በምናከብርበት አንድ ቤት ውስጥ ካለወትሮው ፓልቶክ ተከፍቷል። በዚያ የበዓል ድባብ፤ የፓልቶክ ንትርክ መከፈቱ ሳይገርመን፣ ርእሱ የሁላችንንም ቀልብ መሳቡ። በእርግጥ አንድም ቁም ነገር በንግግሩ አልሰማንም። አዲሱን ቋንቋ ልዋስና የፓልቶኩ ተናጋሪዎች ሙድ የሚያስይዙ ነበሩ። ሰዎቹ በዚህ ከቀጠሉ የእነ ክበበው ገዳን ገበያ መዝጋት እንደሚችሉ አያጠራጥርም። የድምጽ መነጋገርያውን የያዘው ሰው ጉሮሮውን ጠራርጎ ንግግሩን እንዲህ ሲል ጀመረ። […]

    ምንሊክ ሳልሳዊ አገር በኔ ብቻ ተመርታ አገር አትሆንም ብሎ፤ ኃይለኛውና አሸናፊው ከወጣበት መሠላል ዝቅ ብሎ፤ ግማሽ መንገድ ወርዶ እንነጋገር፣ እንወያይ የማለት ባህል፤ ተሸናፊውም ከቁጭቱ፣ ከቂሙ፣ ለመጣል እንጂ አብሮ ለመቀመጥ አልፈልግም የሚልበትን ግትር አቋም ትቶ፤ እኔም የሀገር ጉዳይ ያገባኛል፣ “እንድትሰፉ እንጂ እንደትጠፉ አልፈልግም” ብሎ፤ መንገድ መሻት ያሻዋል፡፡

    ቤት ንብረት በሀራጅ ከሚያስሸጥ ድህነት ይሰውረን፡፡ በሎተሪ ከሚያሳምን የገጠመኝ ዘመን ያውጣን፡ ከሁሉም በላይ ግን ለመለመን እንኳ ጥቂት የራስ መንቀሳቀስ እንደሚያሻን መገንዘቢያ የሚሆነን ልብ ይስጠን!!በሀገራችን ከድህነት እኩል የሚፈታተነን ችግር፤ ቢያንስ ግማሽ መንገድ እንኳ ሄዶ ለመደራደር ዕውቀቱን፣ ጥበቡን አሊያም ቀና ልቡናውን ማጣታችን ነው፡፡ ግማሽ መንገድና የመቻቻል፣ ልዩነትን የማስተናገድ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን የመልመድ ትልቅ ፀጋ ነው፡፡

    የኋላ ታሪክ የሌለው የሚያውቀው ዛሬን ብቻ ነው፡፡የአንድ ቀን ታሪክ የሌለው የሚያውቀው ዛሬን ብቻ ነው፡፡ አንድ ቀን ባዶነት መሰማቱ አይቀርም፡፡ ከሌላ አካል ተከፍሎ መፈጠር ዕድሜ ልክ ሙሉነት ሳይሰማን እንድንኖር ማድረጉ አሌ አይባልም፡፡ ራስን ችሎ፤ በራስ ተማምኖ ለመኖር ራስን ሆኖ መፈጠርን ይጠይቃል፡፡በሀገራችን በፖለቲካ መከፋፈል እንጂ ተስማምቶ መጓዝ አይሆንልንም፡፡ ከረዥም ጊዜ ጀምሮ እንደባህል የተያዘ ፈሊጥ ነው፡፡

    አይጥና ድመት የታረቁ ለታ ባለግሮሰሪው/ባለንብረቱ ወዮለት! አይጥና ድመት እንኳ ታርቀው ጠላታቸውን የሚያጠቁበት ቀን ይመጣል ነው የሚሉን፡፡ “የማይለወጥ ነገር የለም – ከለውጥ ህግ በስተቀር” ታሪካችንን ወደኋላ ብንመረምር ምን ያህል እንደተለወጥን ወይም እንደተለዋወጥን መገንዘብ ቀላል ነው፡፡

    ስለተሰሩ መንገዶች፣ ስለፈረሱ ቤቶችና ስለተሠሩ ህንፃዎች፣ ስለታሰሩ ሰዎችና ስለተፈቱ ሰዎች፤ ስለተፃፉ ደንቦችና ስለተጣሱ ህጐች፤ ስለማይሸጡ መሬቶችና በሊዝ ስለተወሰዱ መሬቶች፤ ስለማይነኩ ሰዎችና ኋላ ስለተወረወሩ ሰዎች፡፡ ለውጥ አይቀሬ ነው፡፡ ህገመንግስቱን እንኳን “የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አይደለም ሰው ነው የፈጠረው ሰው ይለውጠዋል፡፡” ብለው ነበር የቀድሞው መሪ፡፡ የብሔር ብሔረሰብ አካሄዳችንም ወደ ኢንዱስትሪ ልማት የሚሸጋገርበት ቀን ሊመጣ ይችላል፡፡

    “ዘለዓለም ውሻ ሆኖ ከመኖር አንድ ቀን አንበሳ ሆኖ መሞት” የሚለውን መዘንጋትም ተገቢ አይሆንም፡፡ ሁሉም ወቅት ወቅት አለውና! ሁኔታዎችን እንደየአመጣጣቸው መመዘን፣ እንደየልኬታቸው ዓይነተኛ መፍትሔ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ በደስታ ሰዓት ደስታችንን መግለጽ እንደተጠበቀ ሆኖ፤ የሚያዘናጉንን ሁኔታዎች፤ ይሆነኝ ብሎ ማሰብ ወሳኝ ነው! ይሄ በፖለቲካም፣ በኢኮኖሚም፣ በባህልም፣ በሥነ አዕምሮአዊ ሂደትም፤ ቁልፍ ጉዳይ ነው፡፡ መንግሥትም፣ ፓርቲም፣ ግለሰብም ተሁኖ ቢታሰብ፤ ዋናው ነገር ይሄው ነው፡፡

    የአባይ ጉዳይ ላይ ያጠላበት የፖለቲካ ድባብ አሁን ሊገፈፍ ይገባል!! ግርማ ሠይፉ ማሩ

    የውሃ፣ ኢነርጂና መስኖ ሚኒስትር በአባይ ተፋሰሰ ሀገሮች መካከል በተለይም በግብፅ፣ በሱዳን እና ኢትዮጵያ መካከል ሲደረግ የነበረውን ውይይት እንዲሁም የህዳሴ ግድብ ያለበትን ደረጃ አሰመልክቶ ለምክር ቤት አባላት በባለሞያ የታገዘ ገለፀ ለማድግ ህዳር 22/2006 በምክር ቤቱ ተገኝተው ነበር፡፡ ይህ ገለፃ እና ማብራሪያ ከዚህ ቀደም ለዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ ቀርቦ የነበረ መሆኑ በሚዲያ ተከታትለናል፡፡ በእኔ እምነት ቀድሞ መቅረብ የነበረበት ለምክር ቤቱ ሆኖ ከዚያ ቀጥሎ በየደረጃው ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ቢቀርብጥሩ የፕሮቶኮል አካሄድ ነው ለማለት እችል ነበር፡፡ ለማነኛውም ፕሮቶኮሉን እነተው እና በዚህ ደረጃ ለህዝብ ለማቅረብ ተነሳሸነቱ መፈጠሩ የዘገየም ቢሆን ተገቢ ነው ብዬ መውሰድ አልቸገርም፡፡ “ዘገዬ” የሚለውን ቃል ኢህአዴግና ሹሞቹ በጓዳ ግምገማ ካልሆነ በአደባባይ ውይየት ጊዜ ደስ አይላቸውም፡፡

    በነገራችን ላይ ይህ ማብራሪያ አሁን መቅረቡ ጥሩ መሆኑን፤ ነገር ግን ዘግይቷል በሚል ለውሃ፣ መሰኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ለሰጠሁት አስተያየት ሚኒስትሩ “አልዘገየም ድርድሩ እዚህ ጋ የደረሰው በጥቅምት ወር ነው፡፡” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በእኔ እምነት ኢትዮጵያዊያን ማወቅ ያለባቸው የሶስትዮሽ ድርድሩን ሳይሆን አጠቃላይ መንግሰት ግድቡን ለመገንባት የሄደበትን መንገድ ነው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያዊ ምሁራን እና ጋዜጠኞች ከግብፅ እና የግብፅ ወዳጆች በተለያየ መልክ በሚያስረጩት መረጃ ሳይሆን በቀጥታ ከሀገራቸው ታማኝ መረጃ አግኝተው ጠንካራ አቋም እንዲይዙ ማድረግ የግድ የሚል ነው፡፡ የምሁራኑ እና የጋዜጠኞች መረጃ ማግኘት ያለጥርጥር ህዝቡ ሀገር በቀል መረጃ እንዲያገኝ ዋናኛ መንገዶች ናቸው፡፡ የዘገየ ማብራሪያ የምለውም ስለግድቡ አጠቃላይ ሁኔታ ነው እንጂ ስለ ሶስትዮሽ ውይይት ሂደትና ውጤት አይደለም፡፡ ለምሳሌ በአባይ ተፋሰስ ላይ ቀደም ሲል በአሜሪካ ድጋፍ ቀጥሎም እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2005/6 በተፋሰስ አገሮች ትብብር ሱዳን እና ግብፅ ጨምሮ በተደረገው ጥናት ሶሰት የግድብ ቦታዎች ተመርጠው የአሁኑ “ቦርደር ሳይት” በመባል የሚታወቀው የግንባታ ቦታ በሁሉም ተመራጭ እንደነበር ብዙ የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ በአቶ አለማየሁ ተገኑ አገላለፅ “ፕሮጀክቱ ግማሽ
    ድረስ በትብብር የተሰራ ነው”፡፡ ይህን የትብብር ስሜት ያፈረስው ምን አልባትም የግብፅ ከልክ ያለፈ አልጠግብ ባይነት እና በኢትዮጵያ ምድር ላይ የሚገኝ ቢሆንም አባይን የሚመለከት ፕሮጀክት በባለቤትነትን የመያዝ እና የማስተዳደር ፍላጎት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የመጣው ከንቀት ጭምር ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ከግብፅ ጋር በሽግግር መንግስት ወቅት የገቡት ቃል ወይም ስምምነት ለመናቃችን አንዱ የቅርብ ምሳሌ ነው፡፡ ኦቶ መለስ ይህን ቃላቸውን አጥፈው፣ ይህ ፕሮጀክት በኢትዮጵያዊያን ቁጥጥር እና ባለቤትነት እንዲካሄድ የወሰዱት አቋም ተገቢም ትክክል ነው፡፡ የዚህ ዓይነት ተመሳሳይ አቋሞች በብዙ ሁኔታዎች የታዘብን ቢሆንም
    በዋነኛነት “ባንዲራ ጨርቅ ነው” በባንዲራ ቀን አከባበር፤ “የአክሱም ሀውልት ለወላይታ ምኑ ነው” በብሔር ብሔረሰቦች በዓል አከባበር ቀጥሎም በብሔር መለያየትን “ልዩነታችን ውበታችን” በሚል መፈክር መታጀቡ እና በሌሎች ሁኔታዎችን የተገነዘብን ሰዎች የሶስት መቶ ስልሳ ዲግሪ መታጠፍ አድርገን ልንወስደው እንችላለን፡፡ ለማንኛውም ኢትዮጵያን እና ህዘቦቿን ወደሚጠቅም አቋም በፈለጉት ዲግሪ መታጠፍ ቢዘገይም በአዎንታ መቀበል ይኖርብናል፡፡

    በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሚደረገው የሶስትዮሽ ድርድር ጥሩ አካሄድ ሊባል የሚችለው የውጭ ዜጎችን በመጠቀም ዙሪያ በመንግሰት የተያዘው አቋም ነው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከወንድሞቻችን ኤርትራዊያኖች ጋር በመሪዎች ፍላጎት በገቡት “የድንበር” ተብዬ ግጭት፣ ችግሩን ለመፍታት በተለይም የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስጠበቅ የሀገር ውስጥ ባለሞያዎችን እና ታሪክ አዋቂዎቸን ባለመጠቀም የደረሰባትን ኪሳራ በደንብ የተረዱት ይመስላሉ፡፡ በአባይ ጉዳይ ዋናዎቹ ተዋናዮች ኢትዮጵያዊያኖች እንደ ነበሩ ለመረዳት ችለናል፡፡ ይህ ብቻም አይደለም በቀጣይ ይህን ጉዳይ አስመልክቶ በሚደረግ ውይይት ከውጭ የሚባል አይኖርም፤ የሚያስፈልግ ባለሞያ ቢኖር ቀጥረን አገልግሎት ከመስጠት በዘለለ ገብቶ መፍተፈት አይፈቀድም፡፡ የሚል አቋም ኢትዮጵያ ይዛለች የሚለው መስመር እሰይ የሚያስብል ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት አቋም የሚመራው በኢህአዴግም ቢሆን መደግፍ የግድ ይለናል፡፡

    በዚህ አጋጣሚ እሰከ ዛሬ በነበረው ውይይት ከውጭ ሀገር ማለትም ከጀርመን፣ ከእንግሊዝ፣ ከፈረንሳይ እና ከደቡብ አፍሪካ ተወክለው ምክረ ሃሳብ ያቀረቡት ባለሞያዎች ጥንቅር “ለምን ከወዳጆቻችን ከነቻይና አልመጣም?” የሚል ፈገግ የሚያሰኝ በዚያውም የህውሃት አባላት አሁንም መንግሰት ሶሻሊሲት እንደሆነ የሚያሳብቅ ጥያቄ አንድ የምክር ቤት አባል ሰንዝረዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ነጭ ካፒታሊዝም ነው የምንከተለው ይበሉ እንጂ አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በዚህ የሚስማሙ እንዳልሆነ በተለያየ መግለጫ ታዝበናል፡፡ እኛም ብንሆንን የምንስማማው አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በሚገልፁት መስመር ነው፡፡ የኢህአዴግ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከካፒታሊዝም ሳይሆን ወደ ሶሻሊዝም የሚጠጋ ርዕዮት እንደሆነ ነው የሚገባን፡፡ መድበለ ፓርቲ ስርዓት፣ ነፃ ገበያ፣ የግል ሀብት፣ ወዘተ ለእርዳታ ሰጪዎች ሲባል የሚቀርቡ ሹፈቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሹፈቶች ግን ይዋል ይደር አንጂ ዋጋ የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡

    በግሌ የኢህአዴግ በደል ከፍቶ ፅዋው ሞልቶ ቢፈስ እንኳን የሀገሬን ጥቅም አሳልፌ የምሰጥበት ምንዳም ሆነ የግፍ መጠን እንደሌለ በተደጋጋሚ ይፋ አድርጊያለሁ፣ ከዚህ የግል እምነቴ ጋር የሚፃረር ፓርቲም ሆነ ሌላ ስብስብ ጋር እንደማልሰራ አውቃለሁ፡፡ እንደዚያም ሆኖ የመንግሰት ሹማምንት የአባይ ግድብን ያህል ትልቅ ፕሮጀክት ይዘው ተቃዋሚና ገዢ ፓርቲ የሚል ክፍተት መፍጠር እንደሌለባቸው ሲነገራቸው፣ በተግባር የሚሰሩትን ሀቅ ወደ ጎን ትተው ጉዳዩን በሙሉ ፕሮፓጋንዳ ያደርጉታል፡፡ ኢህአዴግ ለፕሮፓጋንዳ የሚከፍለው መሰዋዕትነት የፈለገ ውድ ቢሆን ለመክፈል ዝግጁ ነው፡፡ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ስለግድቡ በቂ መረጃ በሌላቸው እና ይልቁንም ግርማ ሠይፉ ማሩ በመንግሰት የሰብዓዊ መብት አያያዝ ፍፁም ደስተኛ ባልሆኑበት ሁኔታ፤ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን መንግሰትን ደግፈው ገንዘባቸውንያለምንም ጥያቄ እንዲቸሩ ይጠይቃል፡፡ በሀገር ውስጥም ቢሆን ሁሉን ተዉት ገንዘብ አምጡ ዘመቻ የሚያስገርም ነው፡፡ በውጭ የሚኖሩኢትዮጵያዊያን ይህን ግድብ በሚያስደንቅ ሁኔታ ሊገነቡት የሚችሉበት አቅም እንዳለ ተገንዝቦ ግብፅን አንገት የሚያስደፋ መንገድ ከመቀየስ ይልቅ አሁንም በውጭ የሚገኙትን ዜጎች መከፋፈል ተገቢ አይደለም የሚል እምነት አለኝ፡፡ መንግሰት ከዚህ አንፃር
    የሚጠበቅበት ለውጥ፤ ግብፅን አና ወዳጆቿን እሞኑኝ ብሎ ለልምምጥ ከሚያጠፋው ጉልበትና ሀብት የሚበልጥ አይደለም፡፡ መንግሰት ከዚህ አንፃር የሚከተለውን የኮሚኒኬሽን ስትራቴጂ እንደገና መገምገም እና ሁሉንም በሚያሳትፍ መልኩ መቀረፅ እንዳለበት ማስገንዘብ ቢዘገየም የረፈደ አይደለም፡፡ ኢህአዴግ ግን የሚሰማ አይመስልም፡፡ ማን ነው ኢህአዴግ ሀፍ እንጂ ጆሮ የለውም ያለው?

    በአባይ ዙሪያ በኢየትዮጵያ ለሚታሰብ ማንኛውም እንቅስቃሴ በቂ ተቃውሞ በግብፅ ስለ አለ በሀገር ውስጥ ሌላ ጠላት ለምን ትፈልጋላችሁ? ለሚል ጥያቄ ኢህአዴግ ሆደ ሰፊ መሆን አይችልም፡፡ ኢህአዴግ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ማግኘት የሚፈልገው፣ ለአብታዊ ዲሞክራሲ እግረ መንገዳቸውን ገብረው እንዲሆን ይፈልጋል፡፡ እኔ እንደ ተቃዋሚ ፓርቲ አባል ለስልጣን ነው ትግል የማደርገው፡፡ ስልጣን ብንይዝ ይህች ሀገር ኢነርጂ እንደሚያስፈለጋት ለማወቅ ስልጣን መያዝ የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ ስለዚህ የአባይን ግድብ ለመገንባት መንግሰት የሚያወጣውን ዕቅድ በተመለከተ የተሟላ መረጃ እንዲኖረኝ የግድ ይላል፡፡

    የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ከዚህ አንፃር በጭፍን የአባይን ግድብ እንዲደግፉ እንጂ መረጃን መሰረት አድርገው ትንተና እንዲሰሩ እና የራሳቸውን ምክረ ሃሳብ እንዲሰጡ እድል የላቸውም፡፡ ለዚህ ጉዳይ የሚፈለጉት ልማታዊ የሚባሉት ጋዜጠኞች ብቻ ናቸው እነርሱም መንግሰት የሚለውን እንደ በቀቀን መድገም ነው የሚጠበቅባቸው፡፡ በግብፅ ግን የግልም ሆነ የመንግሰት ሚዲያዎች ለሀገራቸው ይጠቅማል ያሉትን እንዲዘግቡ መረጃ ይስጣቸዋል፡፡ ማግለል ይቅር ስንል የፖለቲካ ፓርቲዎችን እና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን
    ወይም ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ሳይሆን ሚዲያውንም ጭምር ነው፡፡ አሁንም የአባይ ጉዳይ እና መረጃ ሁሉም ሚዲያዎች በሚያሳትፍ መልኩ ለሚዲያዎች መሰጠት ይኖርበታል፣ ሚዲያዎችም ይህን ኃላፊነት እንደሚወጡ ጥርጥር የለኝም፡፡ ለዚህም ማሳያ የ “ፋክት” አምደኞች ቤተሰብ የነበረችው መፅሄት አዲስ ታይምስ ከዓመት በፊት የአባይን ጉዳይ በልዩ ዕትም ቅፅ 1 ቁጥር 9 ህዳር 2005 ማውጣቷ እና በዚህ ዕትም ያስተላለፈችው መልዕክት ድጋሜ መነበብ የሚገባው ነው፡፡

    በዚህ አጋጣሚ በኤክሰፐርቶች ፓናል ውስጥ ተሳታፊ ለሆናችሁ ኢትዮጵያዊያን ወገኖች ሁሉ ከመቀመጫዬ ብድግ ብዬ አድናቆቴን መግለፅ እፈልጋለሁ፡፡

    ግብፆች የአባይ ጉዳይ ሲነሳ የፖለቲካ ልዩነታቸውን ትተው እንደ ግብፅ ሲያስቡ እኛን መለያየት ለምን ያስፈልጋል? የአባይ ግድብ ፕሮጀክት በተግባር የኢትዮጵያ ህዝብ ፕሮጅክት አንዲሆን የፖለቲካ ድባቡ ላይ ያጠላው የፕሮፓጋንዳ አዚም ሊገፈፍ ይገባል፡፡ አንድነት ፓርቲ ኢትዮጵያ የአባይ ወንዝን መጠቀም ተፍጥሯዊ መብቷ ነው ይላል፡፡ ይህ የማይገሰስ መብት ላይ ምን ፕሮፓጋንዳ ያስፈልጋል፡፡ የዛሬው መልዕክቴ ዋና ማጠንጠኛ በሀገር ጉዳይ እንዳንግባባ አዚም ያደረገብን ማን ነው? የዚህ አዚም መፍቻ ቁልፍ መተማመን እና ሀገራዊ ዕርቅ ይመስለኛል፡፡
    መልካም በዓል ቸር ይግጠመን !!!!!!

    [email protected]