የአዉሮጳ ህብረት የአፍሪቃ ወታደራዊ ስምሪት

የአዉሮጳ ህብረት መንግስት አልባ እየሆነች በመጣችዉ በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ወታደሮችን ለመላክ ዛሪ ብራስልስ ላይ ተስማማ። የህብረቱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ካለፈዉ አጋማሽ ጀምሮ ቀዉስ በተጠናወታት በዚችዉ ሀገር ወታደሮቻቸዉን የሚልኩት እየተጠናከረ የመጣዉን ዉጥረት ለመግታት ነዉ።