ሰበር ዜና፤ አቶ ጌታቸው ገ/ስላሴ የከንቲባ ጽ/ቤት ሀላፊ ፣አቶ ወልዳይ የተባሉና የመቀሌ ዞን የፀጥታ ኃላፊ እንዲሁም ከመቀሌ ወጣቶች ማህበር ተወከልኩ ያለ ግለሰብ የአንድነት አመራሮቸን በመጥራት “መንግስት አጠቃላይ ግምገማ ላይ ስለሆነ የፀጥታ ኃይል እጥረት አለብን” በማለት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ አትችሉም ብለዋቸዋል፡፡ የአንድነት አመራሮችም መልሳቸሁ ህግ የተከተለ አይደለም፤ እኛ ህገመንግስታዊ መብታችንን ጠይቀናል በየትኛውም ሁኔታ ሰልፉን አንሰርዝም፡፡” የሚል […]

በታዬ ዘሐዋሳ
በሃገራችን በነበረው ፖለቲካዊ ቀውስ ወይም አመለካከት የተነሳበርካታ ኢትዮጵያውያን በስደት እንደሚኖሩ ይታወቃል:: የሚኖሩበትም ሃገር ብዛትና ስብጥር በራሱ ከሌሎች ሃገራት ዜጎች የተለየን ያደርገናል ብዬአስባለሁ:: እንደ ሃገራቱ ስብጥር እና ብዛት ሁሉ የሃበሻ አመለካከትም እጅግብዙ ነው:: ይህ ብዛት ያለው ስብጥር ደግሞ ወጥ የሆነ አመለካከት እንዳይኖረን አድርጓል:: ክፍፍላችንም እንደዚያውብዙ ነው:: ፍረጃችንም ጭምር:: የዛኑ ያክልም ኢትዮጵያዊ ዳያስፖራለመፈራረጅ ወይምለመሞጋገስ ከንፋስየፈጠነ ነው:: ፍረጃው ከተለያዩ አካላት ይጀመር እንጂ አብዛኛዎቹን ፍረጃዎች በማዳነቅና በማሟሟቅ ረገድ የሁሉም ድርሻ አለበት:: አንዲት የፌስቡክ ወዳጅ ስለፍረጃዎች ብዛትእና ጥልቀት ትዝብቷን አካፍላን ነበር:: ከነዚህ የርስ በርስ ፍረጃዎች ውስጥ የሚከተሉት በስፋትየምናስተውላቸው ናቸው:-
 . ኢቲቪ ወይም ኢሳት
 . ኢህአዴግ ወይም ተቃዋሚ
. አይጋፎረም ወይም ኢትዮጲያን ሪቪው
. አዲስዘመን ወይም ፍትህ
. ኢትዮጲያወይም ሞት ወይም ገንጣይ ተገንጣይ
. እምየሚኒሊክ ወይም አፄ ዮሃንስ
. ኢትዮጲያፈርስት ወይም ኦሮሞ ፈርስት
. ልማትወይም ሰብአዊ መብት
. ንኡስከበርቴ ወይም ደሃ
. ኪራይሰብሳቢ ወይም ልማታዊ
. ሰለፊስትወይም አህባሽ
. የውጪሲኖዶስ ወይም የሃገር ውስጥ ሲኖዶስ
. የምርጫትግል ወይም የትጥቅ ትግል
. ጠባብወይም አገር ወዳድ
. ባንዳወይም ጀግና
. የባንዳልጅ ወይም የጀግና ልጅ
. X ወይምY እያለ ይቀጥላል::
ይህን የፍረጃ ብዛት እና አይነት ለግዜው በዚህ እናብቃው:: የፅሁፌ መነሻ ርዕሥ በርካታ ሃሳቦችን ማስነሳት እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ዳያስፖራንበተመለከተ የተለያዩሃሳቦችን ማንሳትና ማወያየት እንደሚችል ግልፅ ነው:: አነሰም በዛም እነዚህን ሃሳቦች እያነሱ መወያየትም ሆነ መተራረም ስለ ድክመታችን አውቀን የማስተካከያ እርምጃ እንድንወስድ ይረዳናል:: ድክመቱን በገደምዳሜ እያየንየምናልፈው ከሆነግን ለሃገራችንም ሆነ ለህዝባችን ፋይዳ አናመጣም:: መፅሃፉ እንዳለውም አስቀድሞ በአይናችን ያለውን ምሰሶ ማውጣት ስንችል ነው የጓደኛችንን ጉድፍ ማየት የምንችለው:: ነገርግን የኛ ዳያስፖራ እሱ ያለው እንጂ ሌላው የሚለው ትክክል አይደለም ብሎ የማሰብ አዝማሚያ ያሳያል:: እናም ምናልባት የኔ ሃሳቦች ከተወደደው ዳያስፖራሃሳብ ጋር ካልተስማሙ የማይስማሙበትን ሁኔታ ለመስማት ዝግጁ መሆኔን አስቀድሜ ልግለፅ:: የባህርያችንን ጥልቀት ለማሳየትም ይመስላልኢትዮጵያየገባ አንድ ፀሃፊ በማግስቱ ስለ ኢትዮጵያውያን ከአንድ በላይ መፅሃፍ ሊፅፍ ይችላል:: በሁለተኛው ቀን ምናልባት ከተሳካለት ለጋዜጣየሚሆን መጣጥፍ ሊፅፍ ይችላል:: ሳምንት ሲቆይ ግን ሰው ስለ ኢትዮጵያውያን አንድአረፍተ ነገር እንኳ መፃፍ አይችልምአለየሚባለው:: ለማንኛውም ለዛሬ የሚከተሉትንእዛም እዛም የረገጡሃሳቦችንላንሳ:: ነገር ግን የማነሳቸው ሃሳቦች ከጥቂት ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎችጋር ግንኙነት የሌላቸው እና እንደማይመለከታቸውም ባውቅም ብዙሃኑን ይወክል ዘንድ እነዚያን ጥቂቶችም የፅሁፌ አካል አድርጌያቸዋለሁ:: ለዚህአስቀድሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ::

1)  የእርስ በእርስ ፍረጃ መፍትሄ ይሆነናል?
ፍረጃ በማንኛውም ልኬትቢለካ ወደምንፈልገው የልማት ግብ ሊያደርሰን አይችልም:: ክፍፍሎችንና ፍረጃዎችንእየተከተልን ስንጨቃጨቅእና ስንፈራረጅ ዓለም ጥሎን መሄዱ አይቀርም::  የፍረጃችንን ጥልቀትየሚያሳይ አንድ ትዝብት ላንሳ:: አንዱ የውጭ ሃገር ዜጋ ስለኛ ክፍፍል እና ፍረጃ ከሃበሻ ጋር ሲወያይእናንተኢትዮጵያውያን በእስካሁኑሂደት በብሄር፤ በጎሳ፤ በቋንቋ፤ በሀይማኖት እናበመሳሰሉት ተከፋፍላችኋል:: አሁን የቀራችሁ ነገር ቢኖር በስማችሁ ፊደል ቅደም ተከተል መከፋፈል ነው፡፡አለየሚባል መራራ የቀልድ እውነታ አለ:: በብዛት እንደምንታዘበውም አብዛኛውስለወቅታዊው ፖለቲካየሚያወራልን ኢትዮጵያዊሁሉ አንድነትን ወይም ህብረትን የሚሰብክልን የራሱብሄር ከፍታ ቦታ ላይ ሊሆን እንደሚችል ካሰበ ብቻ ነው:: የርሱን ብሔር የተመለከተ ሌላ ታሪክ ወይም ድርጊት ከተነገረ ከርሱ በላይ የዘር ፖለቲካን አራማጅ የለም:: ፍረጃውም በአይነት በአይነት ተደርድሮ ይቀርባል:: ይህንን አይነት አካሄድን የሚያሳየን ደግሞ በተለያዩ ግዜያት ጣል በሚደረጉ አመለካከቶች ስር የሚሰጡ አስተያየቶችን መመልከትስንችል ነው:: እንደዚህ አይነት አመለካከትና አካሄድምናልባት የምንፈራውን ከማፋጠን ያለፈ ፋይዳ የለውም:: ስለ አንድነት ሲሰብክ የነበረ ኦሮሞ ስለ ኦሮሞ እርሱ የማያምንበት ተፅፎሲያነብ ለዛ ፅሁፍ መልስ ወይም ማስተካከያ እና መከራከሪያ ሃሳብ ከማቅረብ ይልቅ የፀሃፊውን ዘር እያነሱ ጥንብ እርኩሱን በማውጣት ፍረጃ የሚያወጣለት ከሆነምኑን ስለ አንድነት ሰበከው? ስለዘር ፓለቲካ ጎጂነት አሳምሮ አቀነባብሮ የሚሰብከንሰው ስለትግሬ መጥፎነት በማውራት እና በመፈረጅ ካጠናቀቀው የቱላይ ነው አንድነትን የሚያሳየው? አንድነት ሃይል ነው እያለ የሚያስተምር ሰውስለ አማራ ጨቋኝነት እያነሳ እና አማራውን እየፈረጀ ሌላው ብሄር አማራን እንዲጠላ ከሰበከ የቱ ላይ ነው አንድነቱ ያለው? አንድ ነን እያለ ትግሬን አትመኑ ካለን፣ አንድ ነን እያለ አማራ በድሎናል በማለት ያለፈ ታሪክ ካወራ፣ አንድ ነን እያለ ኦሮሞ የመጣው ከዚያ ነው ካለ የቱ ጋር አንድነቱ ያለው? የሚወራው አንድነትስ የማን ነው? አንድነቱ ከግለሰቦች ካልጀመረ እንዴትስ አንድነት ይሆናል? ይህን ትዝብት ለግዜው እዚህ ልግታዉና ወደ ቀጣይ ሃሳብ ላምራ::
2)  ምን ያህል ዳያስፖራዎች ናቸው ሃገራቸውን የሚወዱት?
የግሌ መልስምናልባት20% የሚሆኑት ይወዱ ይሆናልባይነኝ:: ሃገርን የመውደድ ልኬቱ በኔና በነሱ ሊለያይ ይችላል:: ለኔ ሃገርን መውደድ ማለት የግል ፍላጎትን እና ምቾትን ለሃገር አሳልፎ መስጠት ነው:: ሃገርን መውደድ ማለት እራስን አሳልፎ እስከመስጠት ማለት ነው:: ሃገርን መውደድ ማለት መከራን እና ችግርን መሸሽ አይደለም:: አንድ ሰው ፖለቲከኛ ሲሆን ለግል ጥቅሙ ሳይሆን ለህዝብና ለሃገር ሊሰራ ቆርጦ ተነሳ ማለት ነው:: ሆኖም ግን አንድ ችግር ሲያጋጥመው የሚኮበልልከሆነ ቀድሞውኑ የተነሳው ለራሱ ግላዊ ጥቅም እንጂ ለሃገርና ለህዝብ አልነበረም ማለት ነው:: ከዚህ የፖለቲከኞች ቁማር ጋር በተያያዘ የበርካቶችን ታሪክ ማንሳት ይቻላል:: ነገር ግን ከዚህ በፊትም ብዙ ስለተባለ ልለፈው:: በኔ አመለካከት ፖለቲከኛ ለያዘው አላማ ሞትን የሚጋፈጥ እንጂ የሚሞዳሞድ ወይምወደ ባእድ ሃገር የሚፈረጥጥ አይደለም::
ሌላው በዚህ ርዕስ ስር የማነሳው ሃሳብ ሰልፍን ይመለከታል:: በተለያዩሃገሮች ላይ ሃበሾች ሰልፍ ሲወጡ ይታያሉ:: ለምንድን ነው ሰልፍ የሚወጡት? ሀገራቸውን ስለሚወዱወይስ በሌላ ምክንያት? ከላይ እንዳልኩት 80%ምክንያታቸው ሌላነው:: ሃገሩንና ህዝቡን የሚወድ ሰው በሩቁ ሆኖሊመታችሁነው ተጠንቀቁ” “ሊገላችሁ ነው ሽሹወይምገደላቸው ገረፋቸውእያሉ በባዶ ሜዳ መፈክር ማሰማት አይደለም:: ሃገሩን የሚወድ ሞትንም ቢሆን ተጋፍጦ ለሃገሩ ለውጥ ያመጣል እንጅ በተንደላቀቀ ኑሮ ላይ ሆኖ እንዲህ እኔ እንደምጽፈው መፈክር እያዘጋጁ መሰለፍ አይደለም:: ከተሰላፊዎቹ መካከልበርካታ የሃገሪቱ አንጡራ ሃብት ፈሶባቸው በከፍተኛ ደረጃ የተማሩ ነገር ግን ብር Read more ›

የደብሩ ምእመናን በፍ/ቤቱ ውሳኔ ግራ ተጋብተዋል ዋና ጸሐፊው ከሥራቸው ታግደዋል፤ በምትካቸው ሌላ እንዲመደብ ተጠይቋል በሰነድ ማጭበርበር እና ሰነድ ማሸሽ በተፈጸመ ከፍተኛ ሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ምሩፅ ትኵዕ በኀምሳ ሺሕ ብር ዋስትና መለቀቃቸው ተገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት የደብሩ ዋና …

(ተመስገን ደሳለኝ)

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለትንተና አዳጋች መሆኑን የሚናገሩ ምሁራን መከራከሪያቸው ፖለቲከኞቹ ከርዕዮተ-ዓለም ይልቅ ‹‹ሴራ››ን ማስቀደማቸውን በመጥቀስ ነው። በርግጥም አብዛኛው የፓርቲዎቹ የአመራር አባላት ከክህሎት እና ርዕዮተ-ዓለም መራቀቅ ይልቅ በዘልማዱ ፖሊቲካ የተካኑ ናቸው፡፡ በተለይም የ1966ቱ ‹‹አብዮት›› ያሰረፀው የ‹‹ፓርቲ ፖለቲካ›› የተደራ ‹‹ሴራ›› ምን ያህል ኩነትንም ታሪክንም መቀየር እንደሚችል አሳይቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ሞገስ Girma Mogesግርማ ሞገስ

የዜጎችን ፊርማዎች ማሰባሰብ የብዙ መቶ አመቶች ታሪክ ያለው ሰላማዊ ትግል ነው። የሚሊዮኖች-ድምጽ-ለነፃነት ዘመቻ አንዱ ግብ በኢትዮጵያ ሽብር ህግ ላይ ዜጎች ያላቸውን አቅዋም በፊርማቸው እንዲገልጹ ማድረግ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በደቡብ ወሎ ዞን በሀይቅ ከተማ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቤት ላይ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ብርበራ እንደተጀመረ የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡ የአንድነት ፓርቲ የወረባቡ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ እድሪስ ሰኢድ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቁት ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ “የጦር መሳሪያ ሰውራችኋል” በሚል ፖሊሶችና ሚኒሻዎች በሀይቅ ከተማ ባሉ ከ16 በላይ በሚሆኑ የአንድነት […]

“አሁን አዲስ አበባ ውስጥ በተፈጠሩት ሠላማዊ ሰልፎች ሚያዝያ 30/1997ን በቁጥርም፣ በምግባርም ድገሙት። ጠጠር እንኳን የማይወረወርበት እና ሠላማዊ፣ ሠላማዊ እና ሠላማዊ ሰልፍ አድርጉ።” ለዳያስፖራዎች:— “ሠልፍ በሚደረግባቸው አካባቢዎች ላሉ ዘመድ አዝማዶቻችሁ በመደወል አበረታቱዋቸው፤ የምትችሉትን ሁሉ አድርጉላቸው።” www.facebook.com/Zone9ers

በአዉሮጳ ኢትዮጵያዉያን የስፖርትና የባህል ፊዴሪሽን የዘንድሮዉን ዝግጅቱን በስዊዘርላንድ ጄኔቭ አጠገብ በምትገኘዉ ኒዮ ከተማ በደማቅ ዝግጅት አካሂድዋል።

በስመ ሥላሴ አንድ አምላክ አሜን! የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘርና በኃይማኖት በመከፋፈል እኩይ አላማውን በተለያየ መንገድ እያራመደ ያለው የወያኔ ‘መንግስት’ የተለመደውን የዘረኝነትና የከፋፋይነት ተግባሩን በተለይ በውጪ አገራት በሚገኙ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በሚገለገልባቸው አብያተ ክርስቲያናትና ኮሚኒቲዎች በማተኮር በውጪው ዓለም የአልሞት ባይ ተጋዳይነት መፍጨርጨር እያደረገ ይገኛል። ይህ በውጪው አለም እየደረሰበት ያለውን ኪሳራ ለማስቆም ሲል ተቃዋሚ በመምሰል ሰርጎ በመግባት፣አንዳንዶችን በጥቅም፣ አንዳንዶችን […]

ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፒያሳ ከሚገኘው ኑር መስጊድ አንስቶ ዙሪያውን ባሉ መንገዶች ላይ ቆሞ የረመዳንን ጁመዓ ስግደት ሲሰግድ  የዋለው ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ ፣ ከአንድ አመት በላይ ሲያሰማው ነበረውን ድምጻችን ይሰማ የሚለውን ተቃውሞ በከፍተኛ ድምጽ በማሰማት የፒያሳን አየር ተቆጣጥሮት ውሎአል። ድምጻችን ይሰማ፣ የተነጠቅነውን መስጂዶቻችን ለህዝቡ ይመለሱ፣ የተባረሩ ኢማሞች ይመለሱ፣ አሸባሪ አይደለንም፣ ኢማሞቻችን ይፈቱ፣ ጥያቄው …

ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሻለቃ ማእረግ ያለው ፖሊስ አዛዥ በተለያዩ የሰውነት ክፍሎቹ ላይ በጩቤ ተወግቶ መገደሉን የደረሰን ዜና ያመለክታል። ግድያውን ተከትሎ ፖሊስ በትናንትናው እለት እና ዛሬ ከፍተኛ ፍተሻ ሲያካሂድ ውሎአል። የገዳዮቹ ማንነት እስካሁን አልታወቀም። በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከወትሮው በተለየ ቁጥር በየቦታው ፍተሻ ሲያኪዱ የታዩት የፌደራል ፖሊሶች፣ ምናልባትም ግድያውን ከሙስሊሞች ጥያቄ ጋር ሊያያይዙት …

ሐምሌ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከስልክ ኔትወርክ ጥራት ጋር በተያያዘ በየጊዜው የሚነሳውን ቅሬታ ይፈታል የተባለ እና 1ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከ 27 ቢሊዮን ብር በላይ  ወጪ የጠየቀ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ ”ሁዋዌ”ለተሰኘው  የቻይና ኩባንያ ትናንት ተሰጠ። የፕሮጀክቱን ውል ስምምነት ትናንት ማምሻውን ኢትዮ ቴሌኮም  እና የቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ ጋር ተፈራርመዋል። ፊርማውን የኢትዮ ቴሌኮም ተቀዳሚ …

የተባበሩ መንግስታት ድርጅት የጸጥታዉ ምክር ቤት ከሃያ ዓመታት በላይ ያስቆጠረዉን ሶማሊያ ላይ የተጣለዉ የመሳሪያ ማዕቀብ እንዲላላ ወስኗል። የጸጥታዉ ምክር ቤት የመቅዲሹ መንግስት ራሱን ከጽንፈኛዉ አሸባብ ለመከላከል እንዲችል አቅሙ እንዲጠናከር በሚል ዉሳኔዉን ማሳለፉን አመልክቷል።

በአዉሮጳ ኢትዮጵያዉያን የስፖርትና የባህል ፊዴሪሽን የዘንድሮዉን ዝግጅቱን በስዊዘርላንድ ጄኔቭ አጠገብ በምትገኘዉ ኒዮ ከተማ በደማቅ ዝግጅት አካሂድዋል።

የተቃዉሞ ሠልፉና የሥብሰባዉ አስተባባሪዎች እንደገለፁት ዩናይትድ ስቴትስ፥ ካናዳ፥ አዉስትሬሊያ በተለያዩ የአዉሮጳና የመካካለኛዉ ምሥራቅ ከተሞች አደባባይ የወጣዉ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም የኢትዮጵያ መንግሥት ሐማኖታዊ ነፃነትን እና ሠብአዊ መብትን እንዲያከብር፥ ጠይቋል

በደቡብ ወሎ ዞን ኩታ በር ወረዳ ነዋሪዎች አንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. በደሴ ከተማ ያደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያወግዙ በከፍተኛ ጫና እና ማስገደድ ጥረት ቢያደርግም የጠበቀውን ያህል ሰው እንዳልወጣለት ምንጮቻችን ከስፍራው ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡ ኢህአዴግ ትናንት ሐምሌ 17 ቀን 2005ዓ.ም. ጠዋት በኩታ በር አንድነትን በሰላማዊ ሰልፍ እንዲቃወሙ የአስገዳጅ ጥሪ የተደረገላቸው አብዛኞቹ ነዋሪዎች ባለመሳተፋቸው ኢህአዴግ የወረዳውንና […]

ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሀምሌ ወር መግቢያ በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በቁጫ ወረዳ በሰላም በር ከተማ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የታሰሩትን  ከ60 በላይ የከተማዋ ታዋቂ ሰዎችን ለማስፈታት እና  ላቀረቡትም ጥያቄ መልስ እንዲሰጣቸው ለመጠየቅ በትናንትናው እለት 40 አገር ሽማግሌዎች ወደ አዲስ አበባ በመሄድ ጥያቄአቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቅርበዋል። ምክር ቤቱም ጥያቄውን የማየት ስልጣን ያለው …

ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ኃይል በፈረቃ የማዳረስ ተግባር በሚስጢር ማከናወኑን አጠናክሮ መቀጠሉን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ በተለይ በአዲስአበባ ከሰኔ ወር 2005 አጋማሽ ጀምሮ በተከታታይ የኤሌክትሪክ ኃይል በመቋረጥ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአንዳንድ የከተማዋ አካባቢዎች የኃይል መቋረጡ በተከታታይ እስከሶስት ቀናት የሚወስድ ጭምር መሆኑ ነዋሪውን ሕዝብ ግራ የሚያጋባ ሆኗል፡፡ የኃይል መቆራረጡ እንደባንክ፣ አየር …

ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስአበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2005  ጀምሮ ወደአሜሪካን ለሚጓዙ ሁሉ የቪዛ ሒደትን የሚያቃልል አዲስ አሰራር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡ ኤምባሲው ትላንት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንደጠቀሰው የአሜሪካን ኤምባሲ የቪዛ ሒደት ክፍያን ከፍለው …

የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ የአጭር ጊዜ ቪዛ አሳጣጥ አሰራሩ ላይ ለውጥ እንደሚያደርግ አስታወቀ Read more »

ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ወጪና ገቢ ንግድ ዕቃዎች የሚስተናገዱበት ዋና ጎዳና ላይ የዱከም ድልድይን ለመገንባት የተረከበው አክሽን ኢንጂነሪንግ ኩባንያ ሥራውን በውሉ መሠረት ባለማከናወኑ የኮንትራት ውሉ እንዲቋረጥ መወሰኑ ተገለጸ፡፡ ሪፖርተር ምንጮቹን በመጥቀስ እንደዘገበው  “ጎጊቻ” በሚባለው ወንዝ ላይ የተጀመረው የድልድይ ግንባታ በውሉ መሠረት እየተከናወነ ባለመሆኑና የግንባታው መጓተት እያስከተለ ያለውን ችግር ከግምት በማስገባት፣ ከኮንትራክተሩ …

ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መስተዳድሩ በሊዝ ለማልማት መሬት ወስደው በተቀመጠላቸው ጊዜ ውስጥ ካላለሙ 284 አልሚዎች መሆኑን የኢህአዴግ ልሳን ሆነው ፋና ዘግቧል። ባለፉት 5አመታት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት ከህገወጥ ወራሪዎች ተነጥቆ ወደ መሬት ባንክ መግባቱንም መስተዳድሩ አስታውቋል። ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ 155 ሄክታር መሬት በመልሶ ማልማት የለማ ሲሆን፥ …

ሐምሌ ፲፰(አስራ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ እንደገለጹት በሶሪያ የበሽር አላሳድን መንግስት ለመገልበጥ የተቃውሞ ትግል ከተጀመረበት ካለፉት 3 አመታት  ጀምሮ ከ100 ሺ ህዝብ በላይ ተገድላል። የተባበሩት መንግስታት ድርጀት ባለፈው ወር ካወጣው አሀዝ ጋር ሲነጻጸር የማቾች ቁጥር በ7 ሺ ከፍ ብሎአል። ባንኪሙን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒሰትር ጆን ኬሪ ጋር በመሆን ነው …

/መሰፍንወልደማርያም

 

ስምምንድንነው? መታወቂያነው፤ መጠሪያነው፤ ስም ማጥፋት ሲባል ስም አለ ማለትነው፤ ከስምም አልፎ የገነነ ስም አለ ማለት ነው፤ ስለዚህም ሊጠፋ የሚችለው የገነነ ስም ሲኖር ብቻ ነው ማለት ነው፤ ደራርቱ ቱሉ፣ ፋጡማ ሮባ፣ ኃይሌ ገብረሥላሴ የገነኑ ስሞች ናቸው፤ አንድ ሰው እነዚህን የገነኑ ስሞች አጠፋህ ቢባል ሊገባን ይችላል፤ ዘለቀ ወርዶፋ፣ አየለ ተከስተ ስማቸው ጠፋ ቢባል፣ መጀመሪያ የሚቀርበው ጥያቄ እነማን ናቸው? ዱሮስ የገነነ ስም ነበራቸው ወይ? የሚል ይሆናል፤ ስለዚህ መሰላሉን ያልወጣውን ሰው ውረድ ቢሉት ትርጉም የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የቶጎ ህዝብ የምክር ቤት እንደራሴዎቹን ለመምረጥ ዛሬ ድምፅ ሰጥቷል። ምርጫው ዛሬ የሚደረገው፣ በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚዎች መካከል በተፈጠረው ውዝግብ ሰበብሁለት ጊዜ ከተራዘመ በኋላ ነው።

በተጭበረበረ ውል ደብሩን ከ3 ሚልዮን ብር በላይ በማሳጣትና ሰነድ በማሸሽ ይጠየቃሉ ከጥቂት የሙዳይ ምጽዋት ገቢ ምርመራ ብቻ ከ2 ሚልዮን ብር በላይ ጉድለት ተገኝቷል የአብዛኛዎቹ የደብሩ ሕንጻ ሱቆች የኪራይ ውል በትክክለኛ ሰነድ የተፈጸመ አይደለም ለማተሚያ ቤት አገልግሎት በተከራየው ክፍል በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የማይታወቅ ሞዴላሞዴል እንደሚታተምበት ተጠቁሟል የፕሮቴስታንት ቤተ ጸሎት እንደሚያዘወትሩ የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል   በአዲስ አበባ …

የኢትዮጵያ ራእይ ፓርቲ ፤ በሀገሪቱ ሊያካሂድ ያሰበውን ፤ ያስፈልጋል ብሎ ያመነበትን የብሔራዊ መግባባትና ዕርቅ ያለውን መርኀ ግብር በዛሬው ዕለት ይፋ ማድረጉን የአዲስ አበባው ዘጋቢአችን ፣ ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር የላከልን ዘገባ ያስረዳል።

«ሒሳብ ተጭበርብሯል የሚለዉን ወቀሳ የሚያረጋግጥ መረጃ አለገኘንም። በዕርዳታ የተሰበሰበ ገብዘብ ተጭበርብሯል የሚለዉን ወቀሳ የሚያረጋግጥ መረጃም አላገኘንም።»

የኮርያ የዕርስ በርስ ካበቃ ዘንድሮ ስድሳ ዓመቱን ያዘ። በኮርያ ዕርስ በርስ ጦርነት ጊዜ በተመድ የኮርያ ዘማች ጦር ውስጥ በመሰለፍ ከደቡብ ኮርያዉያን ጋር የተሰለፉት ኢትዮጵያዉያን፤ የኮርያ ዘማቾች ማህበር በሚል ጥላ ስር ከተሰባሰቡ 20 ዓመት በላይ እንደሆናቸዉ ይናገራሉ።

አንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም. በደሴ ያደረገውን ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት ሐምሌ 16 ቀን 2005ዓ.ም. ደሴ በሚገኘው በወሎ ባህል አምባ አዳራሽ የተለያዩ የኃይማኖት አባቶችን ሰብስበው አንድነት ፓርቲ ያደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቆራርጦ በአዳራሽ ውስጥ በማሳየት የኃይማኖት አክራሪነት ይደግፋል የሚል የማጥላላት ዘመቻ ማድረጉን ተሳታፊ ምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡ በዕለቱ […]

ሐምሌ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው አመት የወር ደሞዛችን በአመት ከፍለናል አሁን ግን ዳግመኛ ለመከፈል አቅሙ ስሌለለን እና እየተባባሰ የመጣውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም  ስለማንችል፣ ከእንግዲህ ወዲህ ገንዘብ ልንከፈል   የምንችለው ባገኘንበት  ጊዜ ብቻ ነው ” በማለት በአማራ ክልል የሚገኙ የመምህራን ማህበራት አስታውቀዋል፡፡ መንግስት ከሐምሌ ወር ጀምሮ ከሰራተኛው ለመቁረጥ አቅዶት የነበረ ቢሆንም ፣  በክልል ቢሮዎች  …