ኒው ዮርክ ላይ ሲካሄድ በሰነበተውና 14ዐ የሚሆኑ የመንግሥታትና የሃገሮች መሪዎች በተገኙበት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ የሐሙስ ውሎ ላይ የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ፕሬዚዳንቶች ተናግረዋል፡፡ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የሃገራቸውን ሠላም፣ የውጭ ፖሊሲና ሰብዓዊ መብቶችን ያካተተ ሰፊ አድማስ ያለው ንግግር …

"ታሪክ የነፃነት ወገን ነች" – ፕሬዚዳንት ኦባማ ለተመድ ያደረጉት ንግግር Read more »

በዘንድሮው የኢትዮጵያ ታላቅ ዕሩጫ ለህጻናት እንክብካቤ እስከ 1 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ድጋፍ ለማሰባሰብ ዕቅድ ተይዟል፡፡ እስካሁን 200 000 ብር የተሰበሰበ ሲሆን፤ አትሌት ሻለቃ ሐይሌ ገብረ ስላሴም “በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ” ብሎታል አላማውን፡፡ መለስካቸው አምሐ ከአዲስ አበባ ያጠናቀረውን ዘገባ፤ ዝርዝር ያድምጡ፡፡

የመስቀል በዓል በመላው ኢትዮጵያ በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል። «መስታወት፤» በዓሉ በልዩ ልዩ ባህላዊ ዝግጅቶች ከተከበረባቸው አካባቢዎች አንዱ ወደ ሆነው ደቡብ ኢትዮጵያ ይወስደናል። ለዝርዝሩ ዝግጅቱን ያዳምጡ።

በምርጫ 2002 አካሄድ እና ውጤት ላይ ያልተስማሙት ኢሕአዴግና የተቃዋሚ ፓርቲዎች በቀጣይ የፖለቲካ ሂደቶች ላይም ተቃራኒ አቋም አንፀባርቀዋል፡፡ እስክንድር ፍሬው ከ”መኢአድ” ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ዶክተር ታዲዮስ ቦጋለ እና ከ”መድረክ” ቃል አቀባይ ፕሮፌሰር በየነ ፔጥሮስ ጋር ውይይት አድርጓል። ዝርዝሩን ካጠናከረው ዘገባ ያድምጡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሰሞኑን በተጠናቀቀው የኢሕአዴግ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ አሁን ባለው አካሄድ ባጭር ጊዜ ውስጥ ታላቅ የምጣኔ ሃብት ዕመርታ ታሳያለች ሲሉ ይናገሩ እንጂ፤ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ይህን እንደማያምኑ አስታውቀዋል፡፡ እስክንድር ፍሬው ከአዲስ አበበ ያጠናቀረውን ዘገባ ያድምጡ፡፡

ለወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በተዘጋጀው የሩጫ ውድድር ላይ ወደ 2700 ሯጮች መሳተፋቸው በተነገረበት ሥነ ሥርዓት ቁጥራቸው 25,000 የሚደርስ ሰዎች መገኘታቸውን አዘጋጆቹ ይናገራሉ። የአንድነት ለፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲ መሪ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር መለቀቅ በመጠየቅ ሥነ ሥርዓቱን የጠራው መቀመጫውን በጀርመን ያደረገውና የኢትዮጵያውያን የመብት …

በቲዩቢንገን ከተማ (ጀርመን) ለብርቱኳን ሚደቅሳ የተዘጋጀ የሩጫ ውድድር Read more »

የኢትዮጵያው ገዥ ፓርቲ በሣምንቱ ውስጥ ስምንተኛ ጉባዔውን አካሂዷል፡፡ ጉባዔው ፓርቲውን በወጣት አመራር ለመተካት በሚቻልበትና ተስፋ በጣለበት የአምስት ዓመት የምጣኔ ኃብት ዕቅድ ላይ ለመነጋገር ነው አጀንዳ የያዘው፡፡ አዲሱ የፓርቲው አደረጃጀት ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሥልጣን የሚያጠናክር እንደሚሆን ተንታኞች ይናገራሉ፡፡ ጠቅላይ …

የኢትዮጵያ ፖለቲካ የአንድ ሰው አገዛዝ እንዳይሆን የሠጉ አሉ Read more »

«ኢትዮጵያ በጋዜጦች» የተሰኘው  ፕሮግራማችን ስለ  ኢትዮጵያ የተጻፉ የተወሰኑ  ጽሁፎችን  ጨምቆ  ያቀርባል። ኢትይጵያ የመካከለኛ ገቢ ሀገር ልትሆን ትችላለች ተባል። ኢትዮጵያና ጋና በሚለንየም ልማት መሻሻል አሳዩ። ግብጽ የአባይ ውሀ አጠቃቀምን እየቀነሰች ነው። ጋምቤላ አደጋ እንደሚጠብቃት ተገለጸ የሚሉትን ርዕሶች ነው ዛሬ የምንመለከተው።

በዩናይትድ ስቴትስ የ1994ቱ የሽብር ጥቃት የተፈፀመበትን ዘጠነኛ ዓመት ዓመት ለመዘከር ሃገሪቱ እየተዘጋጀች በነበረችበት ሰሞን በፍሎሪዳ ግዛት ጌይንስቪል ከተማ የሚገኘው ወደሃምሣ አባላት ያሉት “ርግብ ዓለምን የመድረስ ማዕከል” የተባለው ቤተክርስቲያን መሥራችና መሪ ፓስተር ቴሪ ጆንስ በመታሰቢያው ዕለት ቅዳሜ፣ መስከረም አንድ ምሽት ላይ …

‘በዞረ ድምር አላምንም’ – ዶ/ር አሕመድ ሞኤን Read more »

የኢህአዲግ 8ኛው ድርጅታዊ ጉባዬ መስከረም 3 ቀን 2003 ዓ ም በናዝሬት ከተማ ተካሂዷል፡፡ በጉባዬው መክፈቻ ላይም ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ንግግር አሰምተዋል፡፡ የቻይና የህንድና የተለያዩ አገሮች ተወካዮችም እንግድነት ተገኝተዋል፡፡ አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ በቦታው በመገኘት፤ ለጊዜ ከፍተኛ ግምት ሊሰጥ እንደሚገባ …

የኢትዮጵያ በዕድገት ጎዳና በፍጥነት መራመድ Read more »

17 የአፍሪቃ ሀገሮች ካለፍው ሚያዝያ እስከ መጪው ህዳር ወር ባለው ጊዜ 50ኛ የነጻነት በአላቸውን እያከበሩ  መሆናቸው ይታወቃል። እነዚህ ሃገሮችም ሆኑ በአጠቃላይ በ1960 ዎቹና ከዚያ በፊት ነጻነታቸውን የተቀዳጁት የአፍሪቃ ሃገሮች ሁኔታ እንዴት እንደነበር ኋላስ ምንመልክ እንደያዘ እንዲያብራሩልን፣ በ City University of …

17 የአፍሪቃ ሃገሮች 50ኛ የነጻነት በአላቸውን እያከበሩ ነው Read more »

የኢትዮጲያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ፤ ገዢው መንግስት በስልጣን ላይ የቆየው በህግ እንዳልሆነ ቅሬታውን ቢያሰማም፤ ወደፊት ኢህአዲግ ከተቃዋሚዎች ጋር አብሮ ለመስራት ፍቃደኛነቱ እውነት ከሆነ ግን መድረክ መሰረታዊ ናቸው ባላቸው ነገሮች ላይ፤ ለመደራደር እና ለመነጋገር ፍላጎት እንዳለው አሳሰበ፡፡  ዝርዝሩን ከመለስካቸው አምሐ ዘገባ ያድምጡ

መስጊዱ “ፈርስት ሂጂራ” ይባላል። በጆርጂያ አቨኑ ላይ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኝ የመኖሪያ አካባቢ ነው ያለው። ስፍራው በርካታ አፍሪካ አሜሪካዊያን የሚኖሩበት፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ሌሎች ስደተኞችና አሜሪካዊያኑም እየሰፈሩበት የመጣ በከተሜዎቹ አጠራር እያደገ የመጣ “አፕ ኤንድ ካሚንግ” አይነት ነው። በዚህ ሰፈር ከአምስት …

ረመዳን በዋሽንግተን ዲሲ Read more »

ከ2 አመት በፊት የተቋቋመው የባቱ ባልቻ አባነፍሶ ት/ቤት አቅም የሌላቸውን ወላጆች ለመርዳት ታስቦ ነው፡፡ ተመስገን ደምሰው በዚህ ት/ቤት ለመማር እድሉን ካገኙት ህጻናት አንዱ ነው፡፡ ወደፊትም ሐኪም መሆንን ይመኛል፡፡ ለማስተማር እና ለማሳደግ አቅም ከሌላቸው ቤተሰቦች ውስጥ አንዷ ሮዛ መሀመድ ሲሆኑ ይህንን …

የባቱ ባልቻ አባነፍሶ ት/ቤትና የአሜሪካ ከፍተኛ የልኳን ቡድን ጉብኝት Read more »

ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የብርን የውጭ ምንዛሬ ቀንሷል። የአንድ የአሜሪካ ዶላር በ16.4 ብር እንዲመነዘር ለባንኮች የተላለፈው መመሪያ ከነሃሴ 26 ቀን ጀምሮ በስራ ላይ ውሏል። ይህንን ተከትሎ ከውጭ አገር የሚገቡ ሸቀጦች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ተከስቷል። ሸማቾች እንደሚናገሩት ሰሞኑን የሸቀጦችና …

የብር ምንዛሬ ማስተካከያው የዋጋ ንረትን አስከተለ Read more »

«የዓለማየሁ ሩባያት፤» «ሃይኩ፤» እና «ግራፊቲ፤» በሚል ርዕስ ለህትመት በበቁ ሶስት የግጥም መፃህፎቹ መነሻነት ለእንግድነት ከጋበዝነው ወጣቱ ገጣሚ ዓለማየሁ ታዬ ጋር የጀመርነው ውይይት ሁለተኛና የመጨረሻ ክፍል ቃለ ምልልስ በሃይኩና ግራፊቲ ላይ ያተኩራል። የአስራ ስድስተኛውን ክፍለ ዘመን ጃፓናዊ ባለ ቅኔ ባሾን፥ ባለ …

ቃለ ምልልስ ከባህልና ማኅበረሰብ እንግዳ፥ ገጣሚ ዓለማየሁ ታዬ ጋር። Read more »

የኢትዮጵያ ትምህት ሚኒስቴር ያወጣዉ መመሪያ የግል ከፍተኛ ተቋማት የህግና የመምህርነት ትምህርት እንዳይሰጡ ያግዳል። በአገሪቱ የርቀት ትምህርትም እንዲቆም አድርጓል። የህዝብ ግንኙን ዳይሬክተር አቶ አበራ አባተ ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ምክንያቱን ሲያብራሩ፣ እርምጃዉ የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ ነዉ ብለዋል። ሁሉም ባይባሉ አብዛኞች የግል ከፍተኛ …

የግል ከፍተኛ የትምህር ተቋማት ማህበር ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ያወጣዉን መመሪያ ተቃወመ Read more »

የአውሮፓ ህብረት ታዛቢዎች ቡድን በኢትዮጵያ ምርጫ ላይ የሚያወጣው ማጠቃለያ ሪፖርት በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የብሪታንያ ሚኒስትር ለጋዜጠኞች ሲናገሩ፤ ይህ ማጠቃለያ ሪፖርት ይፋ በሚወጣበት ጊዜ ከኢትዮጵያ ተስፋ የሚያደርጉት መኖሩን ተናግረዋል። አንድሪው ሚሸል በአለም በትልቅነቱ ሁለተኛው የሆነውን አገራቸው ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የልማት …

የብሪታንያ የአለም አቀፍ ልማት ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ምርጫ ማጠቃለያ ሪፖርት Read more »

ወላጆቻቸውን ያጡ ህጻናትን ከማሳደግ አንፃር አለም አቀፍ ጉዲፈቻ፤ የመጨረሻ አማራጭ እንደሆነ የአሜሪካ ሴናተር ሜሪ ላንድሩ አስታወቁ፡፡ ባለፈው አመት ብቻ ከ 2100 በላይ ኢትዮጵውያን ህጻናት በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካ ሄደዋል፡፡ ባልቻ አባ ነፍሶ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የተሰራው በአሜሪካው ባክነር ኢንተርናሽናል የገንዘብ ድጋፍና፤ …

ጉዲፈቻ እንደ መጨረሻ አማራጭ Read more »

በዛሬው “ኢትዮያ በጋዜጦች” ቅንብራችን ስለ  ኢትዮጵያ ከተጻፉ ርዕሶች የኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስቴር የርቀት ትምህርትን አገድ በሳውዲ አረብያ የአምስት ኢትዮጵያውያን ሞት የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ትኩረት ሳብ ኢትዮጽያ የብርን ዋጋ አወረደች የአጼ ሃይለስላሴ የልጅ ልጅ ጊዮን ሆቴልን በሰባት ቢልዮን ብር እንደሚገነቡ ታወቀ የኢትዮጵያ …

በያዝነው ሳምንት ስለ ኢትዮጵያ ከተዘገቡት የተወሰኑትን ርዕሶች አቅርበናል Read more »

ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት ይፋ ባደረገችው እርምጃ አንድ የዩናይትድ ስቴትስ ዶላር በኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር ቀድሞ ከነበረው የ17 በመቶ ብልጫ ይኖረዋል። የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት IMF የአዲስ አበባ ተጠሪ፥ Sukhwider Singh Toor ጨምሮ አንዳንድ የምጣኔ ሃብት ባለ ሞያዎች በአዎንታ የተቀበሉት ቢሆንም፤ ተገቢ …

የኢትዮጵያ ብር የውጭ ምንዛሪ አቅም ተቀነሰ Read more »

በትናንትናው ዕለት የታተመው አዲስ ዘመን፤የሀገሪቱን የፍትህ ሚንስቴር በመጥቀስ እንዳተተው፣ በእነዚህ ሽብር በመፍጠር እና ምርጫ 2002ን ለማደናቀፍ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ ተያዙ ባላቸው ላይ፤ ፍርድ ቤት እስከ 20 አመት ፅኑ እስራት የሚደርስ ቅጣት ወስኖባቸዋል፡፡ ጋዜጣው ጨምሮ እንዳብራራው፤ 32 ተከሳሾች በሐገር ውስጥ …

ምርጫን ለማወክ አሲረዋል የተባሉ በእስራት ተቀጡ Read more »

የ አሜሪካ ወታደራዊ ሃይሎች ኢራቅን ከወረሩ ሰባት አመታት ተኩል ካለፉ በኋላ ፕረዚዳንት ኦባማ ወታደሮቹን ለአገልግሎታቸው አመስግነው  የውጊያ ትልዕኮአቸው እንዳባቃ ገልጸውላቸዋል። “የኢራቅ የነጻነት ተልዕኮ አብቅቷል። አሁን የኢራቅ ህዝብ የሀገሪቱን ጸጥታ የመጠበቅ ሃላፊነቱን ተረክቧል።” ፕረዚዳንት ኦባማ የፕረዚዳንትነቱን ስልጣን ከተረከቡ ወዲህ ከመስርያ ቤታቸው …

ኦባማ በኢራቅ አዲስ ምዕራፍ የሚከፈትበት ጊዜ መሆኑን ገለጹ Read more »

የአፋርንና የሰሜን ሱማሌን ክልልች የሚያዋስኑትን የአማራ ቆላማ ስፍራዎችን ጨምሮ፣ በአገሪቱ ዉስጥ ባለፉት ጥቂት ቀናት አዳዲስ የጎርፍ ማጥለቅለቅ መድረሱን በተባበሩት መንግስታት ድር፡ጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታዉቋል። በሰሜን ወሎ ዞን ባለፈዉ ነሃሴ 16 የጣለዉ ዝናብ ያስከተለዉ መሬት መንሸራተት የ19 ሰዎችን …

በኢትዮጵያ ሰሜን ወሎ 19 ሰዎች በጎርፍ አደጋ ሞቱ 24 ቆሰሉ Read more »

የሁለት ሺህ ሶስት አዲስ የትምህርት ዓመት በተቃረበበት ባሁኑ ሰዓት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የሚመለከተው መመሪያ መነጋጋሪ ሆኗል። የውሳኔው ተቃሚዎች ርምጃው የተማሪዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ ሲናገሩ መንግሥት ከቁጥር ይልቅ ለጥራት ቅድሚያ ለመስጠት ተብሎ ነው ብሏል ። ሁለት ሳምንት ከቀሩት አዲስ ዓመት …

በኢትዮጲያ የርቀት ትምህርት ተከለከለ Read more »

«መድበለ ፓርቲ ከ2002ቱ ምርጫ በኋላ አብቅቶለታል፤» የሚሉ ወገኖች «ኢትዮጵያ ወደ አንድ ብቸኛ ፓርቲ አገርነት እያመራች ነው፤» ሲሉ፤ ይሄን የሚከራከሩት ደግሞ «ሊባል የሚችለው፤ ኢትዮጵያ አብላጫ ድምፅ ባገኘ ጉልህ ፓርቲ እየተመራች ነው፤» ይላሉ። «የአንድ ፓርቲ በተቀባይነት ጎልቶ መውጣት ወይስ የአንድ ፓርቲ ብቸኛ …

የመድብለ ፓርቲ ዕጣ በኢትዮጵያ! Read more »

በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ ጎርፍ መከሰቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ። በአካባቢው የሚገኝ የሁለተኛ ድረጃ ትምህርት ቤት ክፉኛ በጎርፍ መመታቱን ቦሩ ሮባ የተባሉ የፈንታሌ ወረዳ ነዋሪ ለቮኦኤ ገልጸዋል። “የደረሰው ጉዳት በጣም ከባድ ነው። ጉዲና ቱምሳ GTS የተባለ ሃይስኩል (ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት) …

በኦሮሚያ ክልል የፈንታሌ ወረዳ ነዋሪዎች በጎርፍ ተጠቃን ይላሉ፤ አስተዳደሩ ጉዳቱ መጠነኛ ነው ብሏል Read more »

«ሩባያት፤» እና «ሃይኩ፤» የተባሉትን የሥነ ግጥም ዘይቤዎች የተከተሉትን መፅሃፎቹን ጨምሮ «ግራፊቲ፤» በሚል ርዕስ ካሳተማት ሌላ መፅሃፍ ጋር ሦሥት የግጥም መድብሎች ለንባብ አብቅቷል። ዓለማየሁ ታዬ ይባላል። ለበርካታ ዓመታት በራዲዮና በህትመት ጋዜጠኝነትም ሠርቷል። በግጥም ሥራዎቹ፥ በህይወትና ስነ ፅሁፍ ዙሪያ ከአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ …

የዓለማየሁ ሩባያት፤ ሃይኩ፤ እና ግራፊቲ Read more »

በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን በሃብሩ ወረዳ፣ በግዳን፣ ዋድላና በራያና ቆቦ ወርዳዎች፣ በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በደቡብ ወሎና በተለያዩ አካባቢዎች ጎርፍና የመሬት መንሸራተት በሰው ሕይህወት፣ በከብቶችና በሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል። አከታትሎ በመጣል ላይ ያለው ዝናብ በአምስት ወረዳዎች 37 ሰዎችን ሲገድል …

በአማራ ክልል ከጎርፍና ከመሬት መንሸራተት ጋር በተያያዘ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 37 ደረሰ Read more »

ሰሞኑን ጎርፍና የመሬት መናድ በኢትዮጵያ አደጋና ችግሮችን እያስከተለ ነው፡፡ እነዚህ ችግሮች እስከአሁን ወደ አርባ የሚጠጋ ሰው ሕይወት መጠየቃቸውን፣ በተለያዩ አካባቢዎች መፈናቀልና የንብረት ውድመት ማስከተላቸውን በተለያዩ ዘገባዎቻችን እያቀረብን እንገኛለን፡፡ የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኤጀንሲ ዋና ዲሬክተር አቶ ኪዳኔ አሰፋ የዚህ ክረምት የዝናብ ሁኔታ …

የክረምቱ ዝናብ ለሳምንታት ከተለመደው በላይ ተጠናክሮ ስለሚቀጥል ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጠ Read more »

በሀገር ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ጥሩ ግንኙነት አለ ማለት አይቻልም። ለዚህ ማሳያው፥ በሀገርአቀፉ ምርጫ ከኢሕአዴግ ቀጥሎ ያሉትን ሦስት ቦታዎች በመያዝ ባጠናቀቁት ሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ያለው ሁኔታ ነው። መድረክ፥ ኢዴፓና መኢአድ በምርጫው አካሄድና ውጤት ላይ ያላቸው አስተያየት ተመሳሳይ …

መኢአድ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ Read more »

በኢትዮጵያ የመንግሥታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኰሚሽነር ተጠሪ ሚስተር ሞሰስ ኦኬሎ በተለይ ለቪኦኤ በሰጡት ቃለ ምልልስ ግልጽ እንዳደረጉት የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝቦች በብዙ መንገድ አንድ ናቸው ብለዋል። ኤርትራ በሬፈረንደም እራሷን የቻለች ነፃ ሀገር ከሆነች ወዲህ፥ በዚያች ሀገር በተፈጠሩ ምክንያቶች ኤርትራውያን ወደ …

በኢትዮጵያ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ መፈቀዱ UNHCRን አስደሰተ Read more »

አቶ አሰፋ ነጋሲ በሀብሩ ወረዳ በመርሳ ከተማ ለረጂም ጊዜ የኖሩ የአገር ሽማግሌ ናቸው። አበይ ተራራ በሚባለው ስፍራ ከሰሩት ቤታቸው ቁልቁል ከተማዋን እየተመለከቱ የህዝቡ ብዛት ከጥቂት ሽዎች ወደ አስር ሽዎች ሲያድግ ተመልከተዋል። በግብርና ስራ የተሰማሩት አቶ አሰፋ ቤት እሁድ ሌሊት በመሬት …

በአማራ ክልል የመሬት መንሸራተት 19 ሰዎችን ገደለ Read more »

የEthiopia Reads (ኢትዮጵያ ታነባለች) መስራችና ስራ አስከያጅ አቶ ዮሃንስ ገ/ጊዮርጊስ በመቀሌ የመጀመሪያው በአህያ የሚጐተት ቤተ መፃህፍት አስጀመሩ፡፡ በተጨማሪም እሁድ ነሐሴ 16 የመጀመሪያው የህፃናትና የወጣቶች ቤተመፃህፍት ተከፍቶ የነፃ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ ቤተ መፃህፍቱ ሰገናት ቤተ መፃህፍት ተሰይሟል፡፡ “የመቀሌ መስተዳድር ለቤተ መፃህፍቱ …

በአህያ የሚጐተት ቤተ መፃህፍት በመቀሌ Read more »

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በጥቅምት ወር አዲስ መንግስት ይመሰርታሉ። አመራሩን በአጠቃላይ በአዲስ ትውልድ እንደሚተኩ ያስታወቁት አቶ መለስ ለዚህ አዲስ ትውልድ አዲስና እስካሁን እውን መሆን ያልተቻለ ፈተና አስቀምጠውለታል። የአምስቱ አመት የኢኮኖሚ ልማት ትራንፎርሜሽን እቅድ ተብሎ የሚጠራ ሰነድ አዘጋጅተው ለመጭው አመራር …

ኢትዮጵያ በ5 አመታት ከተረጂነት ለመውጣት የሚያስችሏት የልማት መሰረቶች አልተጣሉም ሲሉ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ገለጹ Read more »

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማሪያምን ጨምሮ አስራ ሁለት የቀድሞ የአንድነት ለፍትህና ዴሞክራሲ አባላትን አቃቤ ህግ ሰላም በመንስት ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል። አቃቤ ህግ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ለመጀመሪያ ፍርድ ቤት ለቂርቆስ ምድብ ፍርድ ቤት ባቀረበዉ ክስ መሰረት፣ ሚያዝያ ሃያ ቀን 2002 ዓም ከቀኑ …

አቃቤ ህግ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማሪያምን ከሰሰ Read more »

ትግራይ ውስጥ ካሉት በወተት ምርት የተሰማሩ ገበሬዎች አንዱ አቶ ሰለሞን ገሰሰ ይጠቀሳሉ፡፡ አቶ ሰለሞን በ1992 ዓ/ም ከፈረንጅ ላሞች ዘር ጋራ የተዳቀሉ ሁለት ላሞችን ገዝተው ማራባት ይጀምራሉ፡፡ በአሁኑ ሰዓት የላሞቹ ቁጥር ከ130 በላይ ደርሷል፡፡ ከነዚህ ውስጥ 82 ላሞች በተለያዩ ጊዜ ሸጠዋል፡፡ …

ከብት እርባታ በትግራይ፡- ከፈረንጅ ላም ጋር የተዳቀሉት በቀን እስከ 36 ሊትር ወተት ይሰጣሉ Read more »

አበበ ወንድሙ የተባሉ አድማጫችን ከባህር ዳር ላደረሱን ጥያቄዎች ሞያዊ ትንታኔ የሰጡት የታዋቂው የሜዮ ክሊኒክ የነርቭና የስነ አዕምሮ ህክምና ክፍል ዲሬክተር ዶ/ር ዮናስ እንዳለ ገዳ ናቸው። የአልዛሃይመር በሽታ መነሻ ምንድነው? መዳን ይቻላል ወይ? ህክምናውስ ምንድነው? በቡና ይባባሳል? ለእነኚህና ሌሎች ተዛማች ጥያቄዎች …

የአልዛሃይመር በሽታ ምንድነው? Read more »

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለፈው ሳምንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ የአምስት ዓመትየኢኮኖሚ እቅዳቸውን ይፋ አድርገዋል። አገሪቱን ለመጭዎቹ አምስት ዓመታት የሚያስተዳድረው የኢህአዴግ መንግስት በጥቅምት ወር የሚመሰርተው አዲስ መንግስት በርካታ ስራዎች ይጠብቁታል። አገሪቱ ከውጭ የምግብ እርዳታ ነፃ እንድትወጣና ኢኮኖሚው በአማካይ በዓመት ከ11-14 ከመቶ …

የመለስ ኢትዮጵያን ከውጭ እርዳታ ነፃ የማድረግ የ5 ዓመት እቅድ Read more »

የኢትዮጵያ የዉሃ ሃብት ሚኒስትር አቶ አስፋዉ ዲንጋሞ በአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ”ለጥያቄዎ መልስ” ዝግጅት ላይ ለአድማጮች ጥያቄ በሰጡት መልስ በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ በቅርቡ እንደገና ስለተፈጠረዉ ዉዝግብ አስረድተዋል። አቶ አስፋዉ፣ ባለፈዉ ሃምሌ 5 በዋሽንግተን ዲስ ሰልፍ ያደረጉ ኢትዮጵያዉያን የኢትዮጵያ መንግስት በወንዙ …

የኢትዮጵያ ዉሃ ሃብት ሚኒስትር አቶ አስፋዉ ድንጋሞ ስለአባይ ወንዝ አጠቃቀም ለአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ገለጹ። Read more »

ከ6 ዓመታት በፊት እንደ ዘበት ተጀምሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ በለም ዙሪያ እንደ ሰደድ እሳት የተቀጣጠለና ፍቅርን ለእንግዳ ሰው የማሳየት ጥረት ተደርጎ የተወሰደው እንቅስቃሴ ነው፤ “Free Hugs” በአንድ አውስትራሊያዊ ወጣት የተጀመረውና በአያሌ አገራት ወጣቶች በስፋት ሲካሄድ የቆየው የፍቅር ማዕበል ባለፈው ወር …

የማያውቁትን ሠው በነፃና በወዳጅነት ማቀፍ Read more »

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀውና በቅርቡ በተካሄደው በዚህ የህፃናት ፊልም ፌስቲቫል የቀረቡትን ፊልሞች በሙሉ፥ ተጀምሮ እስኪጨረስ፥ የፃፉትን ታሪክ መጫወት ጨምሮ፥ እንደ ካሜራ ባለ ሞያና እንደ ዲሬክተር የሠሩት ዕድሜያቸው በ9 እና በ15 ዓመት መካከል የሚገኙ ታዳጊ ህፃናትና ወጣቶች ናቸው። «አሳትፉኝ፤» በተሰኘው ፕሮግራም …

የመጀመሪያ የህፃናት ፊልም ፌስቲቫል በአዲስ አበባ Read more »

(VOA) — ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመጭው ጥቅምት አካሂዳለሁ ባሉት የመንግስት ለውጥ፤ እየተቀያየረ የሚሄደውን የኢትዮጵያን የወዳጅነት አቅጣጫ ተከትለው የሚዘጉና አዲስ የሚከፈቱ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እንደሚኖሩ አስታወቁ። ከሚዘጉት መካከል የመጀመሪያ የሚሆነው በስዊድን የኢትዮጵያ ኢምባሲ እንደሚሆን ተናግረዋል። “በኛና በስዊድን መካክል ትርጉም ያለው የልማት …

በስዊድን የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሊዘጋ ነው Read more »

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሚቲኦሮሎጂ ኤጀንሲ ዓለምአቀፍ ደረጃዎችን በጠበቁ መሣሪያዎች፣ መረጃ አሰባሰብ፣ አሠረጫጨትና አከመቻቸት የሚንቀሣቀስ ድርጅት መሆኑን የድርጅቱ ተ/ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ዱላ ሻንቆ አስታወቁ፡፡ ኤጀንሲው የዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት አባል መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀው ከ11 የዞን ፅ/ቤቱ አንድ ሺህ በሚሆኑ ሠራተኞቹ ጭምር የሚያሰባስባቸውንና የሚያደራጃቸውን …

የኢትዮጵያ ሚቲኦሮሎጂ ኤጀንሲ ተአማኒ መረጃ እንደሚሰጥ ገልጸ Read more »

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሚዚየም በኢትዮጵያዊው ተመራማሪ ዶክተር ዘረሰናይ አለምሰገድ ይፋ የሆነው የጥናት ውጤት እንደሚያመለክተው፤ ቅድመ-ሰው ከ3.4 ሚሊዮን አመታት በፊት ከድንጋይ የተሰሩ ቁሶችን ይገለገል ነበር። “ዛሬ ከፊት ለፊታችሁ የምገኘው በአለም ላይ የሰው ልጅ ቴክኖሎጂን ተጠቅሟል በሚል የተቀመጠውን ሳይንሳዊ መላምት በአንድ ሚሊዮን አመት …

ኢትዮጵያ የቅድመ-ሰው መገኛና የቴክኖሎጂ መጀመሪያ መሆኗን የሚጠቁም ግኝት ይፋ ሆነ Read more »

(VOA) — የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዛሬ ለአገር ዉስጥ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ለተለያዩ ጥያቄዎች መልስ ሰጥተዋል። በሶማሊ ክልል ከሚንቀሳቀስ ታጣቂ ሃይል ጋር በቅርቡ የተፈረመዉን ስምምነት መነሻ ያደረገዉ ጥያቄ አንዱ ነዉ። መንግስታቸዉ የሚደራደረዉ መሳሪያ ካነሱት ጋር ብቻ ነዉ? ወይስ ካኮረፉትም …

መለስ ዜናዊ ከተቃዋሚዎች ጋር እንደሚደራደር ገለጸ Read more »

ለማዳመጥ ከዚህ በታች ይጫኑ፤ [podcast]http://www.voanews.com/MediaAssets2/amharic/dalet/AMH-sa-david%20shinn%20on%20ogaden-%2008-07-10.Mp3[/podcast] (VOA) — የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በሶማሌ ክልል ማዕከላዊቱ ደገሕቡር አካባቢና በስተደቡብ ባለችው ቀብሪደሃር በሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ተጨማሪ ጥቃቶችን ማድረሱን በቅርቡ አስታውቋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የተባበረው የምዕራብ ሶማሌ ነፃነት ግንባር ከኢትዮጵያ …

ዴቪድ ሺን ስለ ኦጋዴን፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ኦብነግ Read more »

: በስሜን አሜሪካ ከሚገኘው ሲኖዶስ ጋር የተካሄደ የስላምና አንድነት ጉባኤ የተመለሱት:አንጋፋው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቅ መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ ዮሃንስ ባላፈው ቅዳሜ አዲስ አበባ እንደገቡ አርፈዋል። በደርግ ዘመን ፓትርያርክ ሆነው ባገለገሉት አቡነ መርቆርዮስ የሚመራንና እራሱን ህጋዊ የኢትዮጵያው ኦርትቶዶክስ …

አንጋፋው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቅ መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ ዮሃንስ አርፉ። Read more »

ከዋይት ኃውስ ቤተመንግሥትና ከዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደጃፍ  የወጡት በአንደኛው ጎራ የኢትዮጵያን መንግስት በመደገፍ ሲሰለፉ፤ እዚሁ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኙት የቻይናና የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ፊት ለፊት የተሰለፉት ደግሞ ሁለቱን መንግስታት በመቃወም የወጡ ናቸው። ዶ/ር ከፋለ ገብረ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያን መንግስት ለመደገፍ ከተደራጀው …

የሀሙሱ የዋሽንግተን ዲሲ የድጋፍና የተቃውሞ ሰልፍ የመነጋገሪያ ነጥቦች Read more »