ኤርትራ ውስጥ የፖለቲካ ተሳትፎንና የአመራር ብቃትን ለማጠናከር ሲባል መንግስታዊ መስርያ ቤቶች በአዲስ መልክ እየተዋቀሩ እንድሆነ የሀገሪቱ ፕረዚዳንት አስታውቀዋል።

ለያዝነው የአውሮፓ 2013 ዓ.ም የአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሰባት ዕጩዎች ቀርበዋል፡፡

የዛሬው የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም የአድማጮችን የእንኳን ለአዲስ አመት አደረሳችሁ መልእክት እና የዜማ ምርጫ ያስተናግዳል፡፡

ወጣት ሮቤል ፍሊፖስ በቦስተን ማራቶን ላይ በተፈጸመው የቦምብ ጥቃት የሚጠረጠረው ዦኻር ሳርናየቭ ጓደኞች ጋር ቤቱ ውስጥ የገባ ቢሆንም አልገባሁም ሲል ለመርማሪዎች ዋሽቷል ለሚለው ክስ ጥፋተኛ አይደለሁም ብሏም።

የዚህ ሳምንት የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም የተለያዩ ምርጥ ምርጥ ዜማዎችን ያካተተ ሲሆን በ Billboard ሰንጠረዥ ላይ የበላይንቱን የያዙትን ዜማዎችን ጨምሮ ሙዚቃ ነክ ዜናዎችንም አካቷል፡፡

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከተመሠረቱት አዲሶቹ የፖለቲካ ድርጅቶች ወገን የሚመደበው የሰማያዊ ፓርቲ አሁንም የተቃውሞ ድምጹን የሚያሰማበት ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርግ መሆኑን ገለጠ።

Marthe Van der Wolf ከአዲስ አበባ ለአሜሪካ ድምጽ ባጠናቀረችው ዘገባ እንደጠቆመችው፤ ሰማያዊ ፓርቲ ከመቶ በላይ አባሎቹ ከታሰሩበት በኋላ ለትላንት እሁድ ጠርቶት የነበረውን ሕዝባዊ ትዕይንት መሠረዙን አስታውቋል።

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ
 የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት ከአክራሪነት ጋር ተባብረዋል የተባሉ የፖለቲካ ኃይሎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ፤ ወጣቶችም “ሥልጣን ፈላጊ” ላሏቸው መሣሪያ እንዳይሆኑ ማሳሰቢያ ተሰጠ፡፡

ማሳሰቢያው የተሰማው የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ላይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ነው፡፡

ሞቃዲሾና ጁባ ተስማሙ
የሶማሊያ ፌደራል መንግሥትና የጁባ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ በአዲስ አበባ በኢጋድና ሌሎች አህጉራዊና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አባላት ባስተባበሩት ድርድር እርቅና መተማመንን ለመገንባት የታለመ ስምምነት ተፈራራሙ።

ስምምነቱ በምሳሌነት ሊወሰድና ለጥቅም ሊውል እንደሚችል ተገልጿል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

በኢትዮጵያና በኬንያ የድንበር አካባቢዎች ከከትናንት በስተያው ቅዳሜ ወዲህ በተፈጠሩ የጎሣዎች ግጭቶች ቢያንስ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን አንድ የኬንያ ራዲዮ ጣቢያ ዘገበ፡፡