በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ አዲስ የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ እየተገነባ ነው። የኢትዮጵያ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ ቅዱስ ቶማስ አኳይናስ አሁን ለጊዜው በካቶሊክ ካቴድራል ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው ያለው።

የሃዋሣ ዩኒቨርሲቲና የከሰሣቸው ጋዜጠኞች የችሎት ውሎ

የሃዋሣ ዩኒቨርሲቲ በመሠረተባቸው ክሥ ሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡት የኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣ ሁለት አዘጋጆች ወደ ዋናው ጉዳይ ገብተው እንዲከራከሩ ብይን ተሰጠ።

ሃዋሳ የሚገኘው የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩን የማየት መብት እንደሌለው ያቀረቡት መከራከሪያም ተቀባይነት አላገኘም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሁለቱ የጋዜጣው አዘጋጆችና ጉዳዩን ለመከታተል አብሯቸው የነበረው ባልደረባቸው እዚያው ሃዋሳ ከተማ በባጃጅ በመጓዝ ላይ እንዳሉ ባጋጠማቸው አደጋ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ሬይክያቪክ ጂዖ-ተርማል ​​
ኢትዮጵያ ሌላ ባለአራት ቢሊየን ዶላር የኃይል ማመንጫ ሥራ ልትጀምር ነው
የኢትዮጵያ ጂዖ-ተርማል ኢነርጂ መገኛ የስምጥ ሸለቆ ክልል ​​የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ሬይክያቪክ ጂዖ-ተርማል ከሚባል ኩባንያ ጋር የኩርቤቲን የከርሰ-ምድር እንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለማከናወን ውል ተፈራርሟል፡፡

ፕሮጀክቱ አራት ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወይም ወደ ሰማንያ ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ተገልጿል፡፡

ጂዖ-ተርማል ኢነርጂ ​​
ሬይክያቪክ ጂዖ-ተርማል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ግዙፍ የውጭ ቀጥታ መዋዕለ ነዋይ እና የግል የኤሌክትሪክ ኃይል አመንጭ ኩባንያ መሆኑ ነው፡፡

ይህንንና ሌሎችም በተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት ላይ የተቀናበሩ ዘገባዎችን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ዴሞክራሲ አለ’ ለማለት ያስቸግራል – ክቡር ገና
የፓርላማ አባላት ከተመረጡበት አካባቢና ሕዝብ ፍላጎት ይልቅ የፓርቲያቸውን ያስቀድማሉ ሲሉ አቶ ክቡር ገና አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ዴሞክራሲ አለ’ ለማለት ያስቸግራል” ብለዋል የኢኒሽየቲቭ አፍሪካ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክቡር ገና፡፡

“አብዛኛው ተቃዋሚ ኃይልም ከመንግሥት የተሻለ መሆኑን አላሣየም ወይም እስከአሁን በግልፅ አልወጣም” ብለዋል አቶ ክቡር አክለው፡፡

አቶ ክቡር ስለአዲሱ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት በአንድ መፅሔት ላይ ያሠፈሩትን ፅሁፍ መነሻ አድርጎ እስክንድር ፍሬው አነጋግሯቸዋል፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

በሙሥና የተጠረጠሩ ክሥ ተመሠረተባቸው
የኢትዮጵያ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አቃቢ ሕግ በሙስና የተጠረጠሩ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ዕውቅ ነጋዴዎች ላይ ትናንት ክሥ መሥርቷል።

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥራ አምስተኛ የወንጀል ችሎት ትናንትና ዛሬ በዋለው ችሎት የቀድሞ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታና ምክትላቸው የነበሩት የአቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ፣ የሃገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ የነበሩት አቶ ወልደሥላሴ ወልደሚካኤል፣ እንዲሁም አንዳንድ ከፍተኛ ነጋዴዎች በሃገሪቱ ላይ በመቶዎች ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት በማድረስ ተከስሰዋል።

የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሦስት የተለያዩ መዝገቦች፤ ባጠቃላይ በአርባ ሁለት ተጠርጣሪዎች ላይ ከመቶ በላይ ክሦችን መመሥረቱ ታውቋል።

ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና …

የአየር ንብረት ለውጥና ልማት በአፍሪካ ​​
የአየር ንብረት ለውጥና ልማት በአፍሪካ
የአየር ንብረት እየተለወጠ የመሆኑ ነገር እውነት መሆኑንና ለውጡ ለሚያስከትለው አደጋም የአፍሪካ መጋለጥ ምን ያህል የሰፋ እንደሆነ ለአህጉሪቱ ተጠራጣሪዎች ማስረዳትና እነርሱን ማሳመን የመጀመሪያው ተግባር መሆን እንደሚገባው ተገለፀ፡፡

አፍሪካ የልማት ጎዳናዋን ከበለፀጉ ሃገሮች መቅዳት አለባት የሚባለውም ስህተት ነው ሲሉም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ካርሎስ ሎፔዝ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በተከፈተው “የአየር ንብረት ለውጥና ልማት በአፍሪካ” ሦስተኛው ጉባዔ መክፈቻ ላይ ተናግረዋል፡፡

ዋና ፀሐፊው የአፍሪካን የዛሬ የአየር ንብረት ለውጥ ይዞታ አውሮፓን ከስድስት መቶ ዓመታት በፊት አጋጠሟት ከነበረውና ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ከፈጀው አጥፊ ወርርሽኝ ጋር …

አረንጓዴ – የሮማ ደንብን ስምምነት ፈርመው በፓርላማዎቻቸው ያፀደቁ፤ ቢጫ – የሮማን ደንብ የፈረሙ ግን በፓርላማዎቻቸው ያላፀደቁ፤ ቀይ – የሮማን ደንብ ያልፈረሙና የአይሲሲ አባል ያልሆኑ ​​
አፍሪካ ከአይሲሲ ጋር ያላት ግንኙነት

ሥራ ላይ ያሉ የሃገሮች መሪዎች እንዳይከሰሱ የሚያደርግ ከለላ ዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት – አይሲሲ እንዲሰጣቸውና በኬንያ መሪዎች ላይ የተከፈተው ክስም ላልተወሰነ ጊዜ እንዲዘገይ እንዲደረግም የአፍሪካ ሕብረት ሰሞኑን ጠይቋል፡፡

መሪዎቹ ባለፈው ቅዳሜ፣ ጥቅምት 2/2006 ዓ.ም አዲስ አበባ ላይ ባደረጉት ስብሰባ ጉዳዩን ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚያቀርብና የሚከታተለ ኮሚቴ አቋቁመዋል፡፡

ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም /ፎቶ ፋይል/ በሌላ በኩል ደግሞ ይህ የመሪዎቹ ጥያቄ አግባብነት የሌለው ነው ሲሉ የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር እና የሕግ …

አቶ ምኅረት ደበበ – የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ​​
ኅዳሴ ግድብ እና የዓለምአቀፉ ቡድን ሪፖርት
ታዋቂ የሆኑ ጋዜጦችና የዜና ወኪሎች ስለናይል ወይም ስለአባይ ወንዝ እና ስለኅዳሴ ግድብ እየፃፉ ነው፡፡

የኒው ዮርኮቹ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃን ብሉምበርግ፣ ዘ ዋል ስትሪት ጁርናል፣ ዘ ናሽናል ከእነዚያ መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

ዘ ዋል ስትሪት ጁርናል በረቡዕ፣ ጥቅምት 6/2006 ዓ.ም ዕትሙ ባሠፈረው ዘገባው ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በመጭው ሣምንት ማክሰኞ፣ ጥቅምት 12/2006 ዓ.ም እንደሚሰበሰቡ የኢትዮጵያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በምንጭነት ጠቅሶ ፅፏል፡፡
Ethiopia, Sudan, Egypt, Eritrea ​​
ይህ ስብሰባ የሚካሄደው በሦስቱ ሃገሮች የተመሠረተው የኤክስፐርቶች ቡድን የቅኝት ሪፖርቱን ካስገባ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ …

በምዕራብ ትግሪይ በአዲ ሃርሽ እና አዲ ዐይኒ መጠለያ ሠፈሮች ውስጥ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ይደርስብናል የሚሏቸውን በደሎች ያሰሙበትን፣ መብቶቻቸው እንዲከበሩ የጠየቁበትን ሰልፍ በቅርቡ አድርገዋል፡፡ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በተፈጠረ ግጭት ሕይወት ጠፍቷል፤ ሰው ተጎድቷል፡፡