በዚያን ጊዜ ሰዎች ለመከራ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ ይገድሏችኋል፤ በስሜም ምክንያት በሕዝቦች ሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፡፡ በዚያን ጊዜ ብዙዎች ሃይማኖታቸውን በመካድ ይሰናከላሉ፤ አንዱ ሌላውን አሳልፎ ይሰጣል፤ ሰዎችም እርስ በርሳቸው ይጣላሉ፡፡ ብዙ ሃሰተኞች ነቢያት ይነሣሉ፤ ብዙዎችንም ያሳስታሉ፤ ከክፋት ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች፡፡ እስከ መጨረሻ በትዕግስት የሚጸና ግን ይድናል፡፡ ለሕዝቦች ሁሉ ምሥክር እንዲሆን ይህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል […]

ደጋግመን መፈክር ስላሰገርንና፣ ደጋግመን በቃል ቃል ስለገባን ግባችንን በተግባር እንመታለን ማለት አይደለም፡፡ የምንጓዘው ዓላማችንን አንጥረንና አነጣጥረን መሆን አለበት፡፡ ተግባሩን እንጂ ተደጋጋሚ ወሬውን እንተው፡፡ቃል ስንገባ በስሜታዊነት አይሁን! ቃል ስንገባ በአድር-ባይነት አይሁን! ቃል ስንገባ ለይስሙላ አይሁን! ቃል ስንገባ በእርግጥ አደርገዋለሁ ወይ? ብለን ከልባችን ጠይቀን፣ በአዎንታዊነት እራሳችንን አሳምነን፣ በቁርጠኝነታችን ተማምነን እንጂ እንደው በሞቅ ሞቅና በሰሞነኛ መንገኝነት ተገፋፍተን እንዳይሆን […]

(ይሄን መልእክት እና ሌሎች ተመሳሳይ መልእክቶችን ያሰራጩ። ሕዝቡ መረጃ እንዲደርሰውና የእንቅስቃሴው አካል እንዲሆን የድርሻዎትን ይወጡ) ሐሙስ በመላው አገሪቷ፣ በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ አምቦ፣ ወለጋ፣ ደብር ብርሃን፣ ደሴ አርባ ምንጭ አዋሳ …የሥራ ማቆም አድማዎችን ያካተቱ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎች ይኖራሉ። ታክሲዎች አይንቀሳቀሱም። ሰራተኞች፣ ተማሪዎች ፣ አስተማሪዎች ሐሙስ ቀን ወደ ስራችሁ እና ወደ ትምህርት ቤታችሁ እንዳትሄዱ። ሐሙስ […]

የቅዱስ ሲኖዶሱን መግለጫ አየሁት፡፡ መጀመሪያ ነገር ቋሚ ሲኖዶሱ ተሰብስቦ መክሮበታል ብዬ ለማመን ይቸግረኛል፡፡ የተጻፈበት ቋንቋ ቤተ ክህነት ቤተ ክህነት አይልም፡፡ ለመሆኑ ለሰማዕታት የሚሆን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አጥታችሁ ነው? ይበልጥ ያስገረመኝ ደግሞ የሰማዕታቱ ዜግነት ለቤተ ክርስቲያኒቱ ምን እንደሚጠቅማት ነው፡፡ መንግሥት የዜግነትን ጉዳይ ቢያነሣ ኃላፊነቱ በዜጎቹ ላይ የተወሰነ ስለሆነ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግን ‹መልዕልተ ኩሉ› የተባለቺውን ዘንግታው […]

– እነ BBC፣ CNN የተገደሉት ኢትዮጵያዉያን ናቸው ሲሉ ወያኔዎች ማረጋገጫ የለንም አሉ። – ኢቢሲ የሊቢያውን ጭፍጨፋ የዘገበው እንደተራ ዜና በሶስተኝንት ነው። አል ጃዚራ ክርስቲያን ኢትዮጵያዊያንን አይሰስ፣ በሊቢያ ኢሰብአዊና ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት መልኩ እንዳረዳቸው ዘግቧል። CNN “ISIS operatives have beheaded two groups of prisoners, believed to be Ethiopian Christians, in Libya” ሲል፣ BBC ደግሞ “ISIS releases […]

* ይድረስ ለክቡር ዶር ቴዎድሮስ አድሃኖም … * ኢህአዴግን እንዴት እንምረጥ ? ትናንት በሁከት ፣ ዛሬ በመፈራረስ በሚመስል አደገኛ የለውጥ ሂደት ውስጥ ባለችው የመን የኢትዮጵያውያን የድረሱልኝ ድምጽ ከነኡኡታው ሰላም ይነሳል ። በደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያውያን ስደተኛ ወገኖቻችን ላይ ከኢራቅና ሶርያ አይ ኤስ አይ ኤስ ISIS ጽንፈኞች ባላነሰ ከፍ ሲል በሰብአዊው ዜጋ ፣ ዝቅ ሲል ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ […]

ከ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ጀምሮ፤ ለመብት፣ ለነፃነትና በሰላም ሠርቶ ለመኖር ያለው ትግል፤ ሳያርፍ በተከታታይ አሁንም እየተካሄደ ነው። በነዚህ ባለፉት ፵ ዓመታት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤ በትግሉ ከሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሕይወታቸውን ሠጥተዋል። ቆራጥ የሕዝብ ጠበቃዎች ወጥተዋል፤ ሕይወታቸውን ላመኑበት ዓላማ በቆራጥነት በመሥጠት በጀግንነት ተቆጥረዋል። ትውልድ አልፎ ትውልድ ተተክቷል። በግለሰብ ደረጃ፤ አጥንት የሚሰብሩ፣ […]

ወቅቱ ለክርስቲያኖች የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል ሰሞን እንደመሆኑ በዓሉ የሚመለከታቸውን አንባቢ ወገኖቼን “እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው [በሰላም] አደረሳችሁ” ማለትን እወዳለሁ፡፡ የደርግ ጊዜ አንድ ትዝታ አለኝ፡፡ በአብዛኛው በሀገር ወዳድ ደናቁርት የታጨቀው የደርግ መንግሥት ሠለጠንኩ ብሎ ሃይማኖተቢሱንና ሃይማኖተኝነትን ከልካዩን የሶሻሊዝም ሥርዓት ካወጀባት ጠማማ ዕለት ጀምሮ በዓል በመጣ ቁጥር በተለይም የአብዮቱ በዓል በሚከበርበት ወቅት “እንኳን ደረሳችሁ” ይል ነበር – […]

በቅርቡ የሽንጎው ከፍተኛ አመራር አካል የሆነው ምክር ቤት ባካሄደው የሁለት ቀን ስብሰባ ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበትን ሁኔታ በሰፊው መርምሮ ለቀጣዩም ትግል ምን መደረግ እንዳለበት መመሪያ በመሰጠት ተጠናቋል። በተጨማሪም የሽንጎው የተለያዩ የስራ ክፍሎች የስራ አፈጻጸምን በተመለከተ የቀረቡለትን ሪፖርቶች መርምሮ ትግሉ ተጠናክሮ የሚቀጥልበትን ተጨማሪ መመሪያ በመስጠት ተጠናቋል። በተለይም ደግሞ ሽንጎው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚያካሂደው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ የተገኙትን መልካም […]

ሆያሆዬ ሳይደርስ ሆያሆዬ .. ዉሮሸባዬ ሳይከፈት እስክስታ..ካለጊዜ ያውራዶሮ ገደል ማሚቱ ከመሆን አንድም ይሰውረን አንድም ያድነን::ምርቃት የማይደርስበት እርግማን እንደክፋት ላይገን ያደባበት የጊዜ ጀግንነት ለመደረብ የምንራወጥበትን ሰከን ብለን በሰውነት ጀግንነት የምንለካ ያድርገን::ጊዜን በአግባቡ እንደ ወርቅ ለመድመቅ ልንጠቀምበት የሚገባዉን ከአንዱ ይህ እይታውን ያደላዋል::የሚገባው በሚገባው ዘመን ላይ የማይገባው በሚያላዝንበት መደድ ላይ መሆናችንን መዘንጋት የለብንም:: በማንኛውም ደረጃ ላይ ቢሆን በትክክል […]

እንደ እውነቱ ከሆነ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዥ ቡድን በእብሪት ተወጥሮ ሀገራችንን ሲጫወትባት፤ “እኛ የኔ ድርጅት! የለም የኔ ድርጅት!” “እኔ ልምራ እናንተ ተከተሉኝ! የለም እኔ ልምራ እናንተ ተከተሉኝ!” “እኔ እበልጣለሁ! የለም እኔ እበልጣለሁ!” እየተባባልን፤ በሌለ ሥልጣን ሽሚያ ልባችን ተወጥሮ፤ ዛሬ ትናንት፤ ነገ ደግሞ ዛሬ እየሆነ ዓመታትን አስቆጠርን። ለምን? የሀገር ጉዳይ እያንዳንዳችንን የሀገሯ ተወላጆች እኩል አይሸነቅጠንም? ምን […]

* በ9ኛ ቀን በሳውዲ መራሹ ” ወሳኙ ማዕበል !” የአየር ማጥቃት ዘመቻ በየመን ሰማይ በተጠኑ ወታደራዊ የሁቲ አማጽያን ይዞታዎች ላይ አየር ድብደባው መቀጠሉን የዘመቻው መምሪያ ቃል አቀባይ ብ.ጀኔራል አህመድ አሲሪ ናቸው ፣ ጀኔራሉ በዚሁ መግለጫች በወደብ ከተማዋ በኤደንም የሁቲ አማጽያ አልበገርላቸው ካለው የአካባቢ ሚኒሽያ ጋር ውጊያ መግጠማቸውን አስረድተዋል * ከሁቲ አማጽያንን ኤደንን እንዳይቆጣጠሩ በአካባቢው ሚኒሽያ […]

እናት የለው አታነባ፡ ዘመድ ወዳጅ ውስጥ አይገባ፤ ምንም የለው፤ ጠያቂ አልባ፡፡ በከርቼሌ ተከርችሞ፡ ነብሱን ሰጥቶ፤ ውስጡ ታሞ፡ ህመም ቁስሉን ተሸክሞ፤ ስቃይን ሊቀበል፡ ጽናትን ሊካፈል ባመነበት ሊኖር ቆርጦ ሊገዳደር፤ ወስኖ ለራሱ፡ አምኖበት ከነብሱ፤ የሚኖረው ያ… ወንድሜ መጣ ዛሬ በምናቤ፡፡ ወደኋላ ‘ንዳይጎትቱት፡ ብርታቱንም እንዳይነጥቁት፡ ሚስት ልጁን ተሰናብቶ ሂዱ… ብሎ ተለይቶ፤ የቆረጠው ያ… ወንድሜ ዛሬ መጣ በምናቤ፡፡ መምህር […]

የኢህአዴግ ዘረኛ መንግስት በሰማያዊ እና አንድነት የድጋፍ ድርጅቶች አስተባባሪነት በዋሽንግትን ዲሲ ከተማ የተጠራውን የሰማያዊ ፓርቲ ስብሰባ ለማደናቀፍ የሠማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ውጭ እንዳይወጣ አገዛዙ በማን አለብኝነት ቢከለክለውም፤ በዛሬው እለት በዋሽንግተን ዲሲ በሽራተን ሆቴል የተጠራው ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል። በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጲያውያኖች በዛሬው ዕለት በቦታው በመገኘት በአገዛዙ በኩል እየተወስደ ባለው አስከፊ የውንብድና ድርጊቶች ሠላማዊ ትግላችን […]

ጊዜው 1997 ነው። አብዛኛዎቻችን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፥ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች እንዲሁም ተመርቀን ስራ አጥተን ሰፈር ውስጥ የምንውል ስራ አጦችና ( በኢህአዲግ አባባል አደገኛ ቦዘኔዎች) ወጣትነት ጉልበታችንን በስራ ለመፈተን እየተንቀሳቀስን የነበርን ወጣቶች ትኩስ ኋይሎች ነበርን። በወቅቱ በተነሳው የለውጥ እንቅስቃሴ አንዳችንን ከአንዳችን ሳይለይ በጊዜው የነበርነውን ሁሉ ማርኮን አጥብቀን በመከታተል በሂደቱ በተለያየ መልኩ ተሳታፊ ሆነን አገኘነው። በከፍተኛ ሁኔታ በለውጡ […]

ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፤ ከውጭም፣ ከውስጥም፣ ያላችሁ፦ ሕውሃት/ኢህአዴግ ጠንካራ ተቃዋሚ የለም በማለት በብቸኝነት በሚቆጣጠራቸው የመገናኛ ሚዲያዎች በሕዝቡ እያላገጠ በስተጀርባ ግን የፖለቲካ አመራሮችንና የፖርቲዎችን ሕልውና ማሣደድ ቀጥሎበታል፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት የአንድነት ፓርቲን ማፈራረሣቸው አልበቃ ብሏቸው አሁን ደግሞ በትናትናው ዕለት የሰማያዊ ፖርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ወደ ውጭ እንዳይመጣ በማንአለብኝነት በእብሪት በመወጠር ከቦሌ አለም አቀፍ አውሮኘላን ማረፊያ […]

ተቀምጦ ከማላዘን – የወሬ ትውልድ ከመቀፍቀፍ – የስሜት ናዳ ዶፍ ከማዝነብ – ብሎም በባዶ ሜዳ ስንፍናን ከማዛጋት ይሰውረን:: ኢትዮጵያችን አፈና የተንሰራፋባት.. ጭቆና የነገሰባት አገር … ነፃነት በእጅጉ የተሸረሸረባት አገር ከሆነች አመታቶች ተቆጠሩ::ወያኔ ህዝቦች የምንመኘውን ያላሟላ የዜጎችን ነፃነት ማክበር ሸክም ሆኖ የሚያስብ ቢያንስ ቢያንስ በታጋሽነትና በመቻቻል መንፈስ ትችቶችን ለማስተናገድ በቂ ችሎታ እና ዝግጁነት የሌለው አምባገነንነት ከተቃዋሚ […]

ለኔ እዉነተኛዉ የአንድነት ፓርቲ ትናንት በፍ/ቤት ዉሳኔ ተቀብሯል፡፡ዱባና ቅል አበቃቀሉ ለየቅል እንደሆን ቀድም ሲል አዉቀናል፡፡ ዳኛ ብርቱኳንም ፍርህይወትም ዳግም አልተከሰቱም፡፡ እንደ ኢህአዴጉ የምርጫ ዉጤት 99.6 ከመቶዉ አመራሩና አባላቱ በምርጫ ቦርድ እንዲበተኑ የተበየነበት እንዲሁም በደጋፊዎች የተገዛ ንብረት ያለፍ/ቤት ትእዛዝ በመንግስት ታጣቂ ፖሊሶች የተዘረፈበት አንድነት የፍትህ ተቋሙን ለመፈተሸ ም/ቦርዱን መክሰሱ ይታወቃል፡፡ ም/ቦርድን መክሰሳችን አግባብ እንዳልሆነ አንቀጽ ተጠቅሶ […]

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ክሱን ያቀረቡት ወገኖች የአንድነት ፓርቲን በመወከል ክስ ሊያቀርቡ አይችሉም ብሎአል። ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ ህወሃት ኢህአዴግ የሰጠውን የፖለቲካ ውሳኔ ማስፈጸሙን የገለጹት የፓርቲው የቀድሞ አመራር አቶ አስራት ጣሴ፣ የዛሬው የፍርድ ቤት ውሳኔም ህግና ደንብን የጣሰ ነው ብለዋል። የፓርቲው የስራ አስፈጻሚ አባላት አሁንም እንዳሉ የገለጹት አቶ አስራት ፣ ሁሉንም የፍርድ ቤት ሂደቶች ካጠናቀቁ […]

የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምጽ የሳምንቱን ዜናዎች እና የዜና ሃተታዎች :-የአቶ በቀለ ገርባ መፈታት – የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች አስቂኝ የካንጋሮ ፍርድ ቤት ውሎ – የድምጻችን ይሰማ የሳንቲም መሰብሰብ እና በራስ ላይ የመቆጠብ የትብብር መንፈግ ጥሪ ተግባራዊነቱ እና ስኬቱ – የትግራይ ምርጫ በሕወሓት እና በአረና መድረክ መካከል የሚደረገው ፍጥጫ – የሰማያዊ ፓርቲ የሰልፍ ውሎ እና የሕወሓት […]

ይሄንን ፎቶ ሳይ ያስታወሰኝ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዕከላዊን ሲኦል ጊቢ የረገጥኩበትን ቀን ነው። በዛን ቀን በጠዋቱ አራዳ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ብዙዎች ተገኝተናል። ዕለቱም ዞን9ኞችና ጋዜጠኞቹ የማዕከላዊ ሲኦል ቤትን የምርመራ ጊዜያቸውን ጨርሰው ክስ የሚመሰረትባቸው ቀን ነው። ምን ብለው ይከሷቸዋል ወይስ የሚከሱበት ምክንያት ስለሌላቸው ይለቁዋቸው ይሁን? የሚለው ጥያቄ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ነበር። በዛንው ቀን እንዲሁ አንድነት ፓርቲ በእነሀብታሙ አያሌውና […]

ሰሞኑን ያለማቋረጥ የመን ላይ እየተወሰደ ባለው የአየር ጥቃት ምክንያት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በከፍተኛ ችግርና ጭንቀት ውስጥ ነበሩ፡፡ ዛሬ በተደረገ የአየር ድብደባ ምክንያት ካምፕ ውስጥ የነበሩ 45 ኢትዮጵያዊን ሲሞቱ ከ60 በላይ ቆስለዋል፡፡ በIOM ካምፕ ላይ በስህተት የተወሰደ እርምጃ ነው በተባለው በዚህ ጥቃት ላይ ካምፕ ውስጥ የነበሩት የምስራቅ አፍሪካ ስደተኞች ናቸው የሞቱት የሚል መግለጫ IOM ቢያወጣም በዛ ካምፕ […]

የራስን እና የተፎካካሪን ስልትና ስትራቴጂ አለማስላት፣ የህዝብንና የሀገርን ፍላጐት አለማስቀደም፣ የመንገዶችን ኮረኮንችና ሊሾነት አለመለየት አባዜዎች ሁሌ እንደተፈታተኑን አሉ፡፡ ባለፉት የትግል ጊዜያት ብዙ አይተናል:: ብዙ ታዝበናል:: ብዙ ጉዳዮች አስደምመውናል:: ጠንካራነትን ብቻ ሳይሆን ደካማነትንም መገንዘብ ብልህነት ነው፡፡ አለመብሰል አለመሰልጠን እንደተገኘው መገስገስ ትግሉን በትንሽ ድል መወጣጠርና በትንሽ ሽንፈት መፍረክረክ ተጋጣሚን መናቅና ወሬን/አሉባልታን እንደ አቋም ወሱድ በሚደረገው ትግል ውስጥ […]

‹‹ተጨማሪ ምርመራ ይቀረኛል›› መርማሪ ፖሊስ ‹‹መረጃዎች ካሉ ክስ ይመስረትብን ካልሆነ ከእስር እንለቀቅ›› ተጠርጣሪዎች ———- በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የሚገኙት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ፣ ፍቅረማሪያም አስማማውና እየሩሳሌም ተስፋው ዛሬ ከሰዓት በኋላ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ፍርድ ችሎት ቀርበው ተጨማሪ የ28 ቀናት ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡ ሶስቱም ወጣት ተጠርጣሪዎች ችሎት ከመግባታቸው በፊት ሳቅ እና ፈገግ እያሉ በፍርድ […]

* በሳውዲ የሚመራው የአረብ ሀገራት ህብረት ጦር የአየር ድብደባው ተጠናክሮ ቀጥሏል * የየመን ባህርና አየር በሳውዲ አየር ሃይል ቁጥጥር ስር መዋላቸው ሲጠቆም ኢራንን ጨምሮ ለሁቲ አማጽያን ስንቅና ትጥቅ ማቀበያ በሮች መዘጋጋታቸውን የህብረቱ ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጀኔራል አህመድ አሲሪ አስታውቀዋል * ከዘመቻው መምሪያ ጋር በተደረገ ቅንጅት የመን የገባው የፖኪስታን ጃምቦ ጀት 482 ፖኪስታናውያንን ከመንን አውጥቷል […]

የሃይማኖት ሊቃውንት በጥንት ዘመን ፍጥረት ሁሉ በአንድ ቋንቋ ይነጋገር እንደነበርና ቆይቶ ግን ይህ በአንድ ቋንቋ የመግባባት ጉዳይ ብዙም ሳይዘልቅ እንደ ተቋረጠ ያትታሉ፡፡ ምክንያቱን ሲያብራሩም ጥንታውያኑ ባቢሎናውያን ገናና ሥልጣኔያቸው ጫፍ በነካ ማግሥት ሰማይን የሚታከክና የፈጣሪን መኖሪያ፣ ክብሩንና ልዕልናውን የሚዳፈር ረጅምና ግዙፍ የሆነ ታላቅ ግምብ ለመገንባት ተነሡ፡፡ ይህን ጊዜ ታዲያ የልባቸውን ትቢዕት፣ ክፋትና ዓመፃ አስቀድሞ ያየው ፈጣሪም […]

‹‹ህገ መንግስታዊ መብታችን ከቦሊ ቦል ስፖርት በታች ሆኗል›› አቶ አዲሱ ጌታነህ የባህርዳር ከተማ አስተዳደር እሁድ መጋቢት 20/2007 ዓ.ም የ9ኙን ፓርቲዎች ትብብር በባህርዳር ከተማ ሊያደርገው የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና እንዳልሰጠውና ሰልፉን ማድረግ እንደማይቻል የትብብሩ አባልና የባህርዳር ሰልፍን አስተባባሪ ለሆነው ሰማያዊ ፓርቲ በላከው ደብዳቤ አስታውቋል፡፡ አስተዳደሩ ለሰልፉ እውቅና እንዳልሰጠ የገለፀው ‹‹ሁለተኛውን አገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድር […]

1-የዛሬ ሁለት አመት አካባቢ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ወደዋሽንግተን ዲሲ መጥቶ ከኢሳት ጋር ያደረገውን ቃለምልልስ ተከትሎ፤ በመስከረም 2013 በጻፍኩት ጽሁፍ፡ በቃለምልልሱ ላይ አቶ ይሳያስ አፈወርቂን መስቀልና ማጋነን እንዳልነበረበት ተችቼ የሚከተለውን ጽፌ ነበር፡፡ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል ያንን ደም ያፋሰሰ ታሪክ እንዳልተፈጠረ አድርገን መናገር አንችልም። አንክድም። … ስለ ሻእቢያና ኤርትራ ክፉ ሳይወጣን፤ ስለኢሳያስ ቅንነትም ብዙ ሳናጋንን፤ ከኤርትራ ጋር […]

(አቶ ዮናታን ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ናቸው። ይህ ጽሁፍም ፓርቲን ወክለው ሳይሆን ራሳቸውን ወክለው የጻፉት ነው) ወቅታዊ አጀንዳ እና በቁንፅል የሚተው ባይሆንኝ ነው – በትግስት አንቡልኝ ጭቆና ሲበዛ ሰዎች ብዙ መንገድን ተጠቅመው መታገል ይሻሉ፡፡ የጭቆናውን ቀንበር ለመስበር ጨቋኙን ከመግደል አንስቶ ራስን እስከማቃጠል ድረስ የሚደርሱ በርካታ መንገዶችን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡ ከአገዛዝ ሰንሰለት ራስን ነፃ […]

ከምርጫ ዘጠና ሰባት በኋላ በኢሕአዴግ አደረጃጀት ዉስጥ ትልቅ ቦታ የነበራት ናት። ከሴቶች አደረጃጀት ሃልፊ ነበረች። ከዚያም በአዲስ አበባ የኢሕአዴግ ጽ/ቤት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ሆና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ትሰራለች። በአዲስ አበባ ይለ የኢሕአዴግ አባል የማያወቃት የለም። ከአዲስ አበባ የኢሕአዴግ ጽ/ቤት የድርጅቱ ጉዳይ ሃላፊነቷ በተጨማሪ በአዲስ አበባ የሴቶች መዋቅርም የአድን ክላስተር ሃላፊም ነበረች። አበባ ገብረ ሕይወት […]

ጋዜጠኝነት ትልቅ ክብር የሚሰጠው፣ የራሱ የሆነ መርህና ስነ-ምግባር ያለው፣ ጠያቂነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም በውስጡ የያዘ የሙያ መስክ ነው። ለዛም ነው ጋዜጠኛ የሕዝብ አንደበት፣ አይንና ጆሮ ነው የሚባለው። ሕዝብ በሚከበርበት ቦታ ሁሉ ጋዜጠኛም ይከበራል። ሕዝብ በሚዋረድበት፣ በሚታፈንበትና በሚዋከብበት ስፍራም ጋዜጠኛ ይዋረዳል፣ ይሳደዳል፣ ይታፈናል፣ ይዋከባል፣ ይታሰራል፣ ሲከፋም ይገደላል። ይህም በሕዝብ፣ በመንግሥትና በጋዜጠኛ መካከል ያለውን ቁርኝት በደንብ ያሳያል። […]

የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ንቅናቄ በሃገራችን ኢትዮጵያ አስተማማኝና ዘለቄታዊ ሠላም፣ እኩልነት፣ ፍትህና፣ የፖለቲካ መረጋጋት ይሰፍን ዘንድ ቀና ራዕይ አንግበው በተሰባሰቡ ወጣት ኢትዮጵያውያን የተመሰረተ፤ በሃገራችን ብቸኛው በወጣቶች የተገነባና የሚመራ ንቅናቄ ነው። ንቅናቄአችን ላለፋት አመታት የንቅናቄውን አቅም ለማጐልበት፤ ሰፊና ጠንካራ መሰረት ያለው ሁለገብ ተቋም ለመገንባት፤ የድርጅታዊ መዋቅሩን ጨምሮ ሌሎች ወሳኝ መሰረታዊ የማስፋፋትና የማደራጀት ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በመሆኑም ዛሬ […]

ሰማያዊ ፓርቲ ባህር ዳር ቅርንጫፍ ቢሮው እንደተዘጋበት አስታወቀ:: በጋሞ ጎፋ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ አባላት ታሰሩ:: የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍና የምርጫ ቅስቀሳ ለማካሄድ የመረጣቸውን 15 ከተሞች ይፋ አደረገ፡፡ ትብብሩ በተመሳሳይ ሰዓት በ15 ዋና ዋና የሀገሪቱ ከተሞች ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ለማድረግ ቀደም ብሎ አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በዚህ መሰረት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር መጋቢት 20/2007 […]

‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው አሸባሪ ህወሓት/ኢህአዴግ ነው›› አብርሃ ደስታ ‹‹የጦር ችሎት በሚመስል ችሎት እየተንገላታን ነው›› የሺዋስ አሰፋ በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ሌሎች በተመሳሳይ መዝገቡ የተካተቱ ተከሳሾች በተከሰሱበት ድርጊት ላይ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ፣ የአንድነት እና የዓረና ትግራይ አመራሮችን ጨምሮ 10 ተከሳሾች ዛሬ መጋቢት 10/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ […]

ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን:: ለውጥ እንፈልጋለን ብለን ለትግል ስንነሳ መንገድ ሁሉ አልጋ በአልጋ ይሆንልናል ማለት አይደለም::በትግሉ ውስጥ የሚከሰቱ እሾህ እና አሜኬላዎች እንቅፋት ሆነው ከስንዴው እኩል እንደ እሸት የሚያብቡ እንክርዳዶች እየሰረጉ በመግባት ትግሉን ለማኮላሸት አሊያም ደሞ ተያይዘው ለመጥፋት በሚያሴሩት ደባ የህዝብ ልጆች በሚያደርጉት ተጋድሎ እነዚህን እንቅፋቶች ማስወገድ እና በጥንካሬ ጋሬጣውን ማለፍ የሚጠበቅበት ወቅታዊ አጋጣሚዎች ሳንዘናጋ ልንጠቀምበት ይገባል:: […]

በዚህ ሳምንት እና ባለፈው ሳምንት በሻእቢያ ዙሪያ ዉይይቱ ጦዟል። መቸም አበበ በለዉን የማውቀ የለም። በጣም የሚመቸኝ የርዲዮ ተንታኝ ነው። አንድ ሁለት ጊዜ በርሱ ራዲዮ ቀርቤ አስተያየት የሰጠሁበት ጊዜም አለ። እኔ እስከማወቀው ድረስ አበበ በለለው የግንቦት ሰባት እና የኢሳት ጠንካራ ደጋፊ ነው። ለኢሳት በአበበ በለዉና በታማኝ መካከል ምን ልዩነት የለም። ሆኖም “ወያኔ ወያኔ ትሸታለህ” ተብሎ ዘመቻ […]

የካቲት 23 2007 (ማርች 2, 2015) የ119ኘዉ የአድዋ ድልና የሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ነዉ። አከባበሩ በሃገር ዉስጥ ቢቀዘቀዝም፤ በተዘዋዋሪዉ በአሉን የሚያከብረዉ በዉጭ ሃገር የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ ቁጥር እየጨመረ ይገኛል። በሰሜን አሜሪካ የድል በአሉ ቀን ከአፍሪካ አሜሪካዉያን ታሪክ መዘከሪያ ወር ጋር መያያዙና የየካቲት 12 ሰማእታትን መታሰቢያ ቀን ደግሞ ከሰላሳ በላይ በሆኑ ያለም ከተሞች መዘከሩ፤ በዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጰያዉያን ትኩረት […]

በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ስርዓት በማስመልከት በተለያዩ ድረገጽ እና የዜና አውታሮች ላይ የህዝብን ንቃተ ህሊና ሊይጎለብቱ የሚችሉ የተለያዩ ዘገባዎች ይቀርባሉ። በተለይም ደግሞ ፍትህ፣ነጻነት፣እኩልነትን አስመልክቶ እንዲሁም ሊጀመር ጥቂት ጊዜያት የቀረውንና የኢትዮጵያዊያንን አዕምሮ በያዘው የሀገራችን ምርጫ ዙሪያ መነጋገሩ፣ መከራከሩ እና ከምርጫው በፊት መስተካከል የሚገባችውን ነገር ማውሳቱ የሰሞኑ ዓቢይ ጉዳይ ሆኗል። በርግጥ የ1997ቱ ምርጫ የህዝብ ቅስም የተሰበረበት እና እስከአሁንም […]

‹‹ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!›› በሚለው በዚህ የሰውን ክብርና ልእልና ከፍ ባደረገው ፍቅር፣ ሰብአዊነትና ርኅራኄ ልባቸው የተሸነፈ የመቄዶንያ መስራች ከሆነው ከአቶ ብንያም ጀምሮ በበጎ ፈቃደኝነት በማዕከሉ ውስጥ እያገለገሉ ያሉ ወገኖቻችን በየጎዳናው ላይ የወደቁ፣ እርጅና ተጫጭኖአቸው፣ ጉልበትና ጊዜ ከድቶአቸው፣ በመጦሪያቸው ዘመን የቀኑ ሐሩር የሌሊቱ ቁር እየተፈራረቀባቸው፣ አምስትና አስር ሳንቲም ፍለጋ የእኛን እጅ የሚጠባበቁ፣ መውደቂያና መጠጊያ […]

እርሳቸው ግን አሁን ገና ኢትዮጵያዊ ሆንኩ ፣ምከንያቱም ኢትዮጵያዊ መብቴ የሚረገጥ ማለት ነውና››እያሉ ነው ‹ዳኛቸው፣ ዩኒቨርስቲውን እንደ ደጀንና ገዥ መሬት ተጠቅሞ መድፍ ሲተኩስብን ቆይቷል›› ሲሉ የነበሩ ህወሓቶች አሁን አንጀታቸው ቅቤ ሳይጠጣ አይቀርም፡፡ የፍልስፍና ምሁሩን ከዩኒቨርስቲው ማባረር ችለዋልና፡፡ስንብታቸውን አስመልክቶ ዳኛቸው ለአዲስ አድማስ እንደተናገሩት ‹‹ውሳኔው ፖለተካዊ መሆኑነን ማንም አይስተውም››፡፡ አደባባይ በመውጣት ሀሳባቸውን በመግለጽ ተለይተው የሚታወቁት ዳኛቸው በዩኒቨርስቲው ለሰባት […]

መድበለ ፓርቲ ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ የለም – የሰማያዊና መድረክ ተከራካሪዎች ሕወሃት በይስሙላው ምርጫ ደሞክራሲ አለ ለማስባል የመጀመሪያውን ክርክር አደርጓል። በክርክሩ ኢሕአዴግን ጨምሮ አምስት ድርጅቶች ተካፍለዋል። አትፓ (አዲስ ትዉልድ ፓርቲ) የሚባል አዲስ አበባ ዉስጥ የተወሰኑ ተመራጮችን ያስመዘገበ፣ ጠንካራውን ድርጅት ሕወሃት ምርጫ ቦርድን ተጠቅሞ ካገደ በኋላ ያቋቋመው የተለጣፊው አንድነትን እመራሉሁ ይለው ትግስቱ አወሉ፣ የብዙ ድርህቶች ስብስብ የሆነው መድረክ […]