ሚኪያ በሀይሉን በሀዘን ላጣችሁ ሁሉ ፈጣሪ አምላክ መፅናናትን ይላክላችሁ! በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን! የእግዚያብሔር አብ ቸርነት፤ የድንግል ማሪያም አማላጅነት፤ የልጇ የእየሱስ ክርስቶስ ምህረት፤ የመንፈስ ቅዱስ ፀጋና በረከት፤ የጻድቃን ሰማዕታት ተራዳኢነት እህታችንን በሀዘን ከተነጠቅነው ቤተሰቦች፤ ዘመዶች፤ አብሮአደጐች፤ጐረቤቶች፤ ጓደኞችና የጥበቧ አፍቃሪዎች ጋር ሁሉ ይሁን አሜን! እሱ ሀያሉ አምላክ ልዑል እግዚያብሔር ብርታቱንና መፅናናቱን ለሁላችንም ይስጠን […]

የቴዲ-አፍሮ እና የፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ የፍቅር ያሸንፋል ጽንሰ-ሀሳቦች ( concepts) ብዙ አይገቡኝም፤ ፍቅር ነክቶኝ ስለማያውቅ ወይም የፍቅር የስበት ሃይል ሳይገባኝ ቀርቶ አይደለም፣ በቤተሰብ ደረጃ ቢሆን ይገባኛል፤ ከቤተሰብ አልፎ ግን ፍቅር እንዴት አድርጎ የአንድን አገር ውስብስብ ችግሮች ሊፈታ እንደሚችል ባስብ ባስብ መልሱ አልታይህ ብሎኛል። ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ በአዲስ አድማስ ላይ “የኢትዮጵያ ( ሰላም) መሠረቱ ህዝቡ ነው፡፡ […]

ወጣት አብርሃ ደሳትን ጨምሮ በርካታ የአራና አመራር አባላት በሕወሃት ካድሬዎችን በአዲግራት እንደተደበደቡ በስፋት ኡእይተዘገበ ነዉ። አራና፣ አዲግራት በሚያደርጋቸው ስብሰባ ሕዝቡ እንዲሳተፍ በከተማዋ እየተዘዋወሩ ሲቀሰቀሱ ነዉ ተይዘው የተደበደቡት። ከአቶ አብርሃ በተጨማሪ፣ አቶ አሰግዴ ገብረስላሴ፣ አቶ አምዶም ገብረስላሴ ይገኙበታል። የተደበደቡት የአመራር አባላት ፣ ወደ ፖሊስ ተወስደዉ ፣ ለአራት ሰዓታት ታስረዉ፣ ስብሰባዉን እንዲሰርዙ ማስጠንቀቂያ ተሰቷቸው ተመልሰዋል። የደረሰባቸው ድብደባ […]

ፍርድ ቤቱ ለጥር 30 ቀጥሯቸዋል፤ ሬጅስትራር በበኩሉ ጥር 24 ቀን 2006ዓ.ም መቅረብ አለባቸው ይላል በነአቶ አንዱአለም አሬጌ ስም ያለው የክስ መዝገብን በሚመለከት በፌዴራል ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከተከሳሽ ጠበቆችና ከቤተሰቦች ጋር ብንቀርብም ፍርድ ቤቱ ቀጠሮው ትላንት ስለ ማለፉ ተናግሯል፡፡ የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው አጀንዳቸው ላይ የያዙት ዛሬ ጥር 16 ቀን 2006 ዓ.ም መሆኑን ቢገልፁም በዳኛ አዳነ […]

የአንድነት አመራር አባላት ከኢሳት ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ክፍል አንድ ማቅረባችን ይታወቃል። የቃለ ምልልሱ ክፍል ሁለትና ሶስትን ለማዳመጥ ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጫኑ ! ክፍል 2 ክፍል 3

የአንድነት ፓርቲ ወጣት አመራር አባክላት ም/ፕሬዘዳንቱ አቶኢ በላይ በፍቃዱና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊዉ አቶ ሃብታሙ አያለው ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልሶች ጠንካራ ጥያቄዎች ቀርበዉላቸዋል። ቢሳት የቀረቡት ጥያቄዎች ተመሳሳይነት ያላቸው ከመሆናቸውም በተጨማሪ የአንድነትን ፓርቲ አመራሮችን ተስፋ ለማስቆረጥና ኮርነር ለማድረግ ሆን ተብሎ ተመርጦ የተዘጋጁ ጥያቄዎች እንደሆኑ ብዙዎች እየተናገሩ ነዉ። ከኢሳት የተነሱ ጥያቄዎች ይዘት ተመሳሳይነት መኖራቸው የኢሳትን ገለልተኝነት […]

(ይህ ጽሁፍ የርዕዮት አለሙ የልደት በአል በአዲስ አበባ በተከበረበት ወቅት; ከውጭ አገር ንግግር እንዳደርግ በተጋበዝኩበት ወቅት… የስራ ባልደረቦቼን እስክንድር, ውብሸት እና ርዕዮትን በማሰብ የተዘጋጀ ነው) ይህ ሳምንት የታላቁ ማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በመላ አሜሪካ የሚከበርበት ነው:: በአሜሪካ ከክርስቶስ ልደት ቀጥሎ ስራ እና ትምህርት ቤት ተዘግቶ ልደቱ የሚከበርለት አንድ ሰው ቢኖር ማርቲን ሉተር ኪንግ ብቻ […]

አንደኛው መስከረም ጠብቶ ሌላኛው መስከረም እስኪጠባ ድረስ ባሉት የ365.25 ቀናት ውስጥ ስንት ጉድ መስማት እንዳለብን የሚጠቁም አሃዛዊ መረጃ ሊኖር እንደማይችል መቼም ግልጥ ነው፤ ነገር ግን የዘመናችን ኢትዮጵያ የታሪክ ጎርፍ ያመጣብን ከወያኔና መሰሎቹ በስተቀር ሌሎቻችን ያልጠበቅነው ዱብዕዳ ክስተት ምሥጋና ይንሳውና በዬቀኑ የማንሰማውና የማናየው ዕንቆቅልሽ እንዳይኖረን ሆነናል፡፡ በዚህ መልክ በተለይ ባለፉት 22.8 ዓመታት ውስጥ የታዘብነው የታሪክ ምፀትና […]

የሰማያዊ ፓርቲ በፌስ ቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ መሰረት፣ ቅዳሜ ጥር 17 ቀን በፓርቲዉ ጽ/ቤት በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ዙሪያ የዉይይት መድረክ አዘጋጅቷል። « ድንበራችንን ጉዳይ በተመለከተ በተጨባጭ መረጃ በህብረተሰቡ ውስጥ ግንዛቤ ይፈጠር ዘንድ ትምህርታዊ ውይይት መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን በዝግጅቱ ላይም በዘርፉ ለረጅም አመታት በመስራት የሚታወቁት የረጅም ጊዜ የጆግራፊ ባለሞያ የሆኑት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ድንበሩን በተመለከተ ሰፋ ያለ […]

የአንድነት ፓርቲ በሱዳን ድንበር ጉዳይ፣ ተደረጉ እየተባለ ያሉ ስምምነቶች ዙሪያ ለአማራዉ ክልል አስተዳዳሪ እንዲሁም ለጠቅላ ሚኒስተር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ማብራሪይ መጠይቁ ይታወሳል። እንኳን አንድ በአገሪቱ ያለ አብይ የፖለቲክ መሪ ቀርቶ፣ማንም ዜጋ በአገር ጉዳይ ላይ ጠያቄ ጠይቆ፣ ለጠያቄው ማብራሪይ የመቀብል መብት እንዳለዉ ቢታወቅም፣ የክልሉም ሆነ የፌደራል አስተዳዳሪዎች የሕዝብንም ሆነ የአንድነት ፓርቲን ጥያቄ ጆሮ ዳባ ልበስ ብልዉታል። የሱዳን […]

«አባቶቻችን በደምና በጥንታቸው ገትረው ያቆዩልንን መሬት ስንዝር አናሳልፍም» በሚል መርህ የሰማያዊ ፓርቲ በጎንደ ከተማ ታላቅ የተቃዉሞ ሰልፍ ጠርቷል። ሰልፉ የሚደረገዉ እሁድ ጥር 25 ቀን ሲሆን፣ ቦታውም በጎንደር መስቀል አደባባይ እንደሚሆን የሰማያዊ መግለጫ ይጠቁማል። ሰማያዊ ሌሎች የሲቪክ ማህበራት እና የፖለቲካ ድርጅቶ እንዲተባበሩ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ የአደባባይ ጥሪ ከማስተልለፍ ባሻገር፣ ምን ያህል ግን ሰልፉን በጋራ ለማቀናጀት ከሌሎች […]

የኢዜአ ማደናገሪያ ዜና – አንድ ተጨባጭ ምሳሌ January 20, 2014 ታደሰ ብሩ በቅድሚያ የሚከተለውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን (ኢዜአ) ዜና አጣጥሙልኝ። … ጎባ ጥር 10/2006 በባሌ ዞን ከእርሻ ስራ በተጓዳኝ በንብ ማነብ ፓኬጅ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ከ53 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘታቸውን የዞኑ የእንስሳት ሀብት ልማትና ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የእቅድና ግምገማ በለሙያ […]

አቶ አለማየሁ ለፌቦ የተባሉ በሲዳማ ጭሬ የአንድነት ፓርቲ አባል ከፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማግስት ወደ ክልሉ ሲመለሱ አርሲ ሚጣ ነሴቦ ወረዳ ወርቃ ከተማ ታህሳስ 26 ቀን 2006 ዓ.ም እንደተያዙ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከታሰሩበት ወረዳ ያንተ ጉዳይ የፖለቲካ ጉዳይ ስለሆነ እዚህ አይታይም በማለት ጥር 9 ቀን ወደ ሻሸመኔ ዞን ፖሊስ ተወስደው ታሰሩ፡፡ ዝርዝር ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ በነሀሴ ወር 2012 ዓ.ም. መሞታቸውን ተከትሎ በኢትዮጵያ የተተካው አዲሱ አመራር ሰብዓዊ መብቶችን የሚመለከቱ ማሻሻያዎች እንደሚያደርግ ተጥሎ የነበረው ተስፋ ተዳፍኗል፤ በ2013 ዓ.ም ተጨባጭ የሆነ የፖሊሲ ለውጥ አልታየም፡፡ ይልቁንም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ሃሳብን የመግለጽ፣ የመደራጀት እና በሰላም የመሰብሰብ ነጻነት ላይ የጣሉትን ጥብቅ ገደብ ማስፈጸማቸውን የቀጠሉበት ሲሆን የሲቪል ማህበራትን እና ነጻ መገናኛ ብዙሃንን እንቅስቃሴ […]

የኦሮሚያ ክልል የቱሪዝምና ባህል ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ሞሃመድ ጂሊ፣ የአኖሌ ሃዉልት እንደተሰራና በመሰራቱም ትልቅ ኩራት እንደሚሰማቸው፣ ገዛ ተጋሩ በተባለ የፕላቶክ ክፍል ቀርበው ገለጹ። የአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች በአርሲ የሴቶችን ጡት ቆርጠዋል የሚባለዉ ወሬ፣ የቀድሞ የሕወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት አቶ ተስፋዬ ገብረ አብ በጻፉት መጽሃፍ ከመጻፉና በአንዳድን አክራሪ የኦሮሞ ድህረ ገጾች ላይ ከመዉጣቱ መቀር፣ በታሪክ ባለሞያዎች […]

ጃኑዋሩ 22 ቀን 33ኛ አመቷን ታከብራለች። በሃይ ስኩል የእንግሊዘኛ አስተማሪ ነበረች። በሕገ መንግስቱ ላይ የተደነገገዉን መብት በመጠቀም፣ በተለያዩ አገር ውስጥ በሚታተሙ ሜዲያዎች ትጽፋለች። «እነርሱ እንዲጻፍ ከሚፈልጉት ዉጭ እንዲጻፍ የማይፈልጉት ባለስልጣናት፣ የሃሰት ክስ መሰርተዉ፣ ዳኛ ለተብዬዎች መመሪያ ሰጠዉ፣ መሰረተ ልማቶችን ለማፍረስ አሴራለች፣ ሽብርተኛ ናት» ብለዉ ፈረዱባት። ይች ሴት ርዮት አለሙ ትባላለች። ጡቷ አካባቢ ችግር ስላለበት ክትትል […]

በሱዳን፣ ግብጽና ኢትዮጵያ መካከል ሲደረግ የነበረዉ የሶስትዮች ንግግር መበተኑን አስመልክቶ ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት እንዲሁም የፓርላማ አባል፣ የግብጽን አቋም «የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቅ» እንደሆነ በመግልጽ፣ መንግስት የወሰደዉን አቋም ደገፉ። በአባይ ግድብ ዙሪያ እንኳን የተቀረዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የፓርላማ አባል የሆኑት እርሳቸዉም በቂ መረጃ እንደሌላቸዉ የገለጹት አቶ ግርማ፣ «የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ከዚህ አንፃር በጭፍን የአባይን ግድብ እንዲደግፉ እንጂ […]

የጥምቀት በዓልን ተሰባስበን በምናከብርበት አንድ ቤት ውስጥ ካለወትሮው ፓልቶክ ተከፍቷል። በዚያ የበዓል ድባብ፤ የፓልቶክ ንትርክ መከፈቱ ሳይገርመን፣ ርእሱ የሁላችንንም ቀልብ መሳቡ። በእርግጥ አንድም ቁም ነገር በንግግሩ አልሰማንም። አዲሱን ቋንቋ ልዋስና የፓልቶኩ ተናጋሪዎች ሙድ የሚያስይዙ ነበሩ። ሰዎቹ በዚህ ከቀጠሉ የእነ ክበበው ገዳን ገበያ መዝጋት እንደሚችሉ አያጠራጥርም። የድምጽ መነጋገርያውን የያዘው ሰው ጉሮሮውን ጠራርጎ ንግግሩን እንዲህ ሲል ጀመረ። […]

አዲስ አድማስ አቶ ሌንጮ ለታ አዲስ አበባ ገቡ ብሊ በዘገበዉ «አንጻር የአዲስ አድማሱ ዘገባ፣ በቀጥታ አቶ ሌንጮ ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ ከሰጡት ጋር የሚቃረን ሲሆን፣ ጉዳዩን በትክክል ለማጣራት ያደረግነዉ ሙከራ አልተሳካም።የአቶ ሌንጮ የጀርመኑ ቃለ ምልልስ ወይንም የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገባ ትክክል መሆኑ የሚያመላከት መረጃ እንዳገኘን ለአንባቢያ ግልጽ እናደርጋለን”” ብለን ነበር። አቶ ሌንጮ ለታ በሊቀመንበርነት የሚመሩት የኦዴፍ […]

«የቀድሞ የኦነግ አመራር ሌንጮ ለታ፣ አዲስ ፓርቲ ይዘው አዲስ አበባ ገቡ» ሲል አዲስ አድማስ በቅዳሜ ጥር 10 እትሙ ላይ ዘገበ። አቶ ሌንጮን ለማነጋገር ያደረግነዉ ሙከራ እንዳልተሳካለት የዘገበው አዲስ አድማስ ፣ መረጃዎን ያገኘነው ከምንጮቹ እንደሆነም ገልጿል። አቶ ሌንጮ በጀርመን ድምጽ ራዲዮ በቅርቡ ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ኢትዮያጵያ ዉስጥ ገብቶ በሰላም ለመታገል ፍልጎቱ እንዳላቸው ገልጸው፣ ከኢሕአዴግ ጋር ምንም […]

የከተራው በአል ከተራ ምንድን ነው? ከሚለው ትርጓሜ እንነሳ … በየዓመቱ የጥምቀት በዓል በድመቀት ይከበራል፡፡ ከበዓሉ በፊት የከተራ በዓል የሚከበርበትን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ገለጻ ከተራ ከበበ ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን […]

አቡጊዳ – ርዮት አለሙ ጡቷ ላይ ቱመር አለ፣ ግን ክትትል አላገኝችም ! ሴፍ ዎርልድ ፎር ዎማን ( safe world for women) የተሰኘው ለሴቶች መብት የሚሟገተዉ ድርጅት፣ ርዮት አለሙ እንድትፈታ የሚጠይቅ ፔትሽኖች እያስፈረመ ነዉ። ድርጅቱ, የርዮት አለሙ አባት አቶ አለሙ ጎቤዶን በመጥቀስ እንዳስቀመጠዉ፣ ርዮት አለሙ፣ በአንድ ጡቷ ላይ ቱመር ያለ ሲሆን ፣ ከጡቷም ደም እንደሚፈስ ይገልጻል። […]

ሁለተኛ መልስ ለኢሳቱ አቶ ፋሲል – ግርማ ካሳ ============================= ጤና ይስጥልኝ፣ ዉድ ወንድሜ አቶ ፋሲል። «የአንድነት ፓርቲ የመጪው ጊዜ ፈተና» በሚል ርእስ በጻፉት ላይ ለሰጠኹት አስተያየት፣ ለአንባቢያን ያቀረቡትን የመልስ መልስ አነበብኩ። ግሩም አቀራረብና ለዉይይት የሚረዱ ነጥቦች በማንሳትዎ ተደስቻለሁ። ዜጎች የተለያዩ ሃሳቦች ሊኗራቸው ይችላል። ብዙ ጊዜ፣ በተለይም በዳያስፖራ ፖለቲካ የተለመደው ፣ የሃሳብ ልዩነቶች በተፈጠሩ ጊዜ ያኛው […]

በኢትዮጵያ ዉስጥ በምርጫ ቢርድ ተመዝግቦ እየተንቀሳቀስ ያለው የሰማያዊ ፓርቲ ፣ በጎንደር ከተማ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት እየተዘጋጀ እንደሆነ ፓርቲዉ በፌስ ቡኩ ገጽ ባወጣው መግለጫ ገለጸ። «ሕወሓት ኢህአዴግ በህገ ወጥ መንገድ ሉዓላዊ መሬታችንን ለሱዳን መንግስት አሳልፎ አሳልፎ ለመስጠት እያደረገ ያለውን ህገወጥና ሀገር ቆርሶ የመስጠት ወንጀል በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ እሁድ ጥር 25 2006 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ታላቅ […]

አቡጊዳ – የፌዴራል ፖሊሲ አጽቢን ቶቆጣጥሯታል ፣ ሕወሃቶች በሕዝቡ ተናደዋል ፣ ህዝቡም ጥያቄዉን አላቆመም ከመቀሌ በስተሰምኔ 70 ኪሎሜተር ርቃ በምትገኘው የአጽቢ ከተማ በሕዝቡና በሕወሃቶች መካከል ትላንት የተፈጠረው ዉዝግብ ዛሬም ቀጥሎ ዉሏል። የአካባቢዉ ፖሊስ አቅም በማጣቱ በብዙ መኪና በተለያዩ አቅጣጫዎች፣ ኬሎች አካባቢዎች፣ ተጭነው የመጡ ፌዴራል ፖሊሶች ከተማዋን እንደ ጦር ካምፕ ወረዋታል። ወደ አካባቢዉ የደረሱ የሕወሃት አመራሮች […]

በርካታ ከሳውዲ ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ዜጎችን በሚመለከት የጀርመንና የአሜሪካ ራዲዮን ጨምሮ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን አንድ አይነት የሚመስል መረጃ ግፉአን ተመላሾችን እማኝ እያደረጉ መረጃ አቀብለውናል ።http://www.rappler.com/world/regions/africa/45783-ethiopia-s-colossal-human-airlift-from-saudi-arabia ” ራፕለር ” በታዝነው ሳምንት ባቀበለን መረጃ ሻንጣቸው ጠፍቷቸው በአንድ የሻንጣ ማጠራቀሚያ ግቢ ሻንጣቸውን ሲፈትሹ የሚያሳየውን ፎቶ አስደግፎ የተመላሾችን አስተያየት አካቶበታል። ዜጎች ወደ ሳውዲ ሲሰደዱ ከቤተሰብ ፣ ከዘመድ አዘመድ […]

አንድነት ፓርቲ በተሳካ ሁኔታ ጠቅላላ ጉባኤውን ፈጽሞ በበርካታ ወጣቶች የተገነባውን ካቢኔ ይፋ ካደረገ ጥቂት ሳምንታት አለፉ፡፡ በነዚህ ጥቂት ቀናትም የምንታገልለትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን ለማድረግ ቀን ከሌሊት መስራት ይገባል የሚል እቅድ አንግቦ ደፋ ቀና በማለት ላይ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለን ግን፣ የግል አስተያየት በማለት የኢሳቱ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም «የአንድነት ፓርቲ የመጭው ጊዜ ፈተና» በሚል የፃፈዉን […]

በምስራቅ ትግራይ የምተገኝ ወረዳ ናት። በ2007 ሕዝብ ቆጠራ መሰረት፣ ከመቶ አሥር ሺህ በላይ ነዋሪዎች ያሏት ናት። የአጽቢ ወረርታ ወረዳ ተብላ ትታወቃለች። በወረዳዋ መሃከል የምትገኝዉ ከተማ የአጽቢ ከተማ ናት። ከመቀሌ70 ኪሎሜተር በስተሰሜን፣ ከአዲግራት 94 ኪሎሜተር በስተደቡብ፣ ከዉቅሮ 20 ኪሎሜተር በስተ ምስራቅ የምትገኝ ናት። የዚህ ከተማ ነዋሪዎች በከፍተኛ ዉሃ እጥረት ምክንያት ከሕወሃት/ባለስልጣናት ጋር ትልቅ ዉዝግብ ላይ ናቸው። […]

የአንድነት ፓርቲ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይ ላይ እየሆነ ያለው፣ ሕዝብ በይፋ እንዲያወቀው መደረግ አለበት ሲል፣ ለአማራዉ ክልል አስተዳዳሪ ደብዳቤ አስገባ። ፓርቲዉ የአገርን ሉዓላዊነት በተመለከተ በሚደረጉ እንቅስቅቅሴዎች ዙሪያ፣ በሌሎች የዉጭ ሜዲያዎች በስፋት እየተነገረ፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ ግን መደበቁ ትልቅ ችግር እንደሚፈጠር በማሳሰብ፣ ጉዳዩ በአስቸኳይ ምላሽ እንዲያገኝና ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ አሳስቧል። ግልጽነትና ተጠያቂነት በሌለበት መልኩ በሚስጠር የሚደረግ ማናቸውም ስምምነቶች፣ […]

አንድነት ፓርቲ ለአማራ ክልል እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ የኢትዮ ሱዳን ድንበር ማካለል ጉዳይ በአጭር ግዜ ውስጥ ለህዝብ ግልፅ እንዲሆን በደብዳቤ አሳሰበ። ዝርዝር ዘገባ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

የኦነግ መስራቾችና አንጋፋ መሪዎች፣ እነ ዶር ዲማ ነግዎ፣ አቶ ሌንጮ ለታ የመሳሰሉት፣ የኦሮሞ ጥያቄ የመገንጠል ሳይሆን የዴሞክራሲ ጥያቄ ነዉ በሚል፣ ራሳቸውን ከኦነግ አግልለው፣ የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፎረም (ኦዴፍ) የሚባል ድርጅት ማቋቋማቸው ያታወሳል። ኦዴፍም በኢትዮጵያ አንድነት እንደሚያምን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ለኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮዮጵያዉያን ሁሉ እንቆማለን የሚል አቋም ፣ ድርጅቱ በተመሰረተ ሰሞን በስፋት ሲያንጸባርቅ ነበር። እንደዉም በፓልቶክ በተደረጉ […]

ሰሞኑን በስፋት የሚወራው ስለ አዲሱ የአንድነት ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው ነዉ። ነገር ግን የአንድነት ፓርቲ በተለያየ ጊዜ አባላቱና ደጋፊዎች ሲናገሩ እንደሚሰማዉ የአንድ ሰው ድርጅት ሳይሆን በርካታ ጠንካራ አመራር አባላት ያሉትብ ደርጅቱ መሆኑን ነዉ። ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ ይባላሉ። በሲቪል ኢንጂነሪንግ ባችለር ኦፍ ሳይንስ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን፣ በኢንተርናሽናል ሪሌሽንስ ሁለተኛ ባችለር ኦፍ አርት ተቀብለዋል። በአድንነት ጠቅላላ ጉባኤ […]

የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ለአንድነት ፓርቲ ባቀረበው ጥሪ መሰረት የፓርቲው ስራ አስፈፃሚዎችና ከ22 ከሚበልጡ የህብረቱ ሀገራት ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታወቀ፡፡ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለፍኖተነፃነት እንዳስታወቁት ትላንት ጥር 6 ቀን 2006 ዓ.ም በተደረገው በዚህ ውይይት የአንድነት ፕሬዝዳንት ፣የህዝብ ግንኙነትና የውጪ ግንኙነት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች እሁድ ጥር 4 ቀን 2006 ዓ.ም ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት በመሄድ የሙስሊም ማህበረሰብ የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴን ጎበኘ፡፡ ዝርዝር ለማንበብ እዚህ ያጫኑ!

«በሕገ መንግስቱ የመደራጀት መብታቸው የተጠበቀላቸው ፓርቲዎችን አልከሰስንም።ፓርቲዎችን ግን ሽፋን አድርገዉ ስርዓቱን ወይንም ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ እንቀሳቀሳለን የሚሉ ኃይሎችን ግን ዛሬም ፣ ነገም ፣ ሕጉን የማስከበር ግዴታና ሃላፊነት ስላለብን ከመከሰስ አያመልጡም ማለት ነዉ።» ኢቲቪ በቅርቡ በ«ሽብርተኝነት» ላይ፣ በቅርቡ ባቀረበዉ አሳዛኝ ዶኩሜንተሪ ላይ ፣ የፌደራል መንግስት አቃቤ ሕግ፣ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ የተናገሩት ነበር። እኝህ የሕግ ባለሞያ […]

በደ/ጎንደር ፎገራ ወረዳ ሻጋ ቀበሌ በ2007 ዓ.ም ለሚደረገው ምርጫ ዝግጅት ሲባል የአካባቢውን የወልና የግጦሽ መሬት ለወጣቶች እንዲሰጥ ብአዴን በደብዳቤ አዝዞ ነበር፡፡ እንደአሰተያየት ሰጪዎች የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት ባወጣው አዋጅና መመሪያ መሰረት የወልና የግጦሽ መሬት ለማከፋፈል 80% የማህበረሰብ ክፍል ፈቃደኛ መሆን እንዳለበት ይገልፃል፡፡ በአማራ ክልል የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኛ የሆኑ ግለሰብ ለፍኖጸ-ነፃነት እንደገለፁት ለምርጫ ሲባል በህገወጥ […]

የማለዳ ወግ … የመረጃዎች እውነት ፣ እውሸት ፍልሚያ ጅማሮ ! የተመላሾች ጉዳይ … በርካታ ከሳውዲ ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ዜጎችን በሚመለከት የጀርመንና የአሜሪካ ራዲዮን ጨምሮ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን አንድ አይነት የሚመስል መረጃ ግፉአን ተመላሾችን እማኝ እያደረጉ መረጃ አቀብለውናል ።http://www.rappler.com/world/regions/africa/45783-ethiopia-s-colossal-human-airlift-from-saudi-arabia ” ራፕለር ” በታዝነው ሳምንት ባቀበለን መረጃ ሻንጣቸው ጠፍቷቸው በአንድ የሻንጣ ማጠራቀሚያ ግቢ ሻንጣቸውን ሲፈትሹ የሚያሳየውን […]

የቀድሞ የአራና ትግራይ አመራር አባል፣ አቶ ገብሩ አሥራት፣ ከባለቤታቸው ጋር በመኢካን እይሄዱ እንዳለኡ ድንገት መኪናቸው በእሳት መቃጠሏ በስፋት ተዘግቧል። «የአቶ ገብሩ አስራት መኪና በእሳት ነደደች» በሚል ርእስ ሥር በአስራት አብርሃም የተጻፈ ዘገባ በፌስ ቡክ ተለቋል። ዘገባዉን እንደሚከተለው አቅርበናል፡ የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት እና የዓረና ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የውብማር አስፋው ጋር በመሆን በመኪና […]

ግርማይ ገብሩ የቀድሞ የህወሓት ታጋይና የአሁን የቪኦኤ (VOA) ዘጋቢና ደራሲ ነው። ዓላማዬ ስለ ግርማይ ገብሩ ለመፃፍ አይደለም፤ ግርማይ በፌስቡክ ገፁ ስላሰፈረው መረጃ ለመዋስ እንጂ። መረጃው ከዚህ በፊትም አውቀው ነበር። ግን ለማስረጃ ያህል ግርማይን ልጥቀስ: ምክንያቱም ግርማይ የህወሓት ታጋይ ነበርና። ግርማይ በ1969 ዓም የህወሓት (ተሓህት) ሦስቱ መፈክሮች ሲጠቅስ የመጀመርያውና ዋነኛው አድርጎ የፃፈው “አፄነት፣ መስፍንነትና የአማራ የበላይነት […]

የአንድነት ፓርቲ አዲሱ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ዲሲ ከሚገኘዉ የአንድነት ሬዲዮ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገዋል። በቃለ መጠይቁ፣ ወጣቶች በድርጅቱ ዉስጥ ስለሚኖራቸው ድርሻ፣ ስለመድረክ፣ ከኢሕአዴግ ጋር ሊኖር ስለሚገባው ብሄራዊ መግባባት፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ለመዋሃድ እየተደረገ ሳላለው ጥረት፣ በቅርቡ ይታወጃል ተብል ስለሚጠበቀዉ የሁለተኛ ዙር የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ዘመቻና ሌሎች ጉዳዮች ተዳሰዋል። ወጣቶችን በተመለከተ ለማዳመጥ መድረክን በተመለከተ ለማዳመጥ […]