አቡጊዳ – የአንድነት ፓርቲ የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይን በተመለከተ እንቅስቃሴዎች እያደረገ ነዉ
የአንድነት ፓርቲ በሱዳን ድንበር ጉዳይ፣ ተደረጉ እየተባለ ያሉ ስምምነቶች ዙሪያ ለአማራዉ ክልል አስተዳዳሪ እንዲሁም ለጠቅላ ሚኒስተር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ማብራሪይ መጠይቁ ይታወሳል። እንኳን አንድ በአገሪቱ ያለ አብይ የፖለቲክ መሪ ቀርቶ፣ማንም ዜጋ በአገር ጉዳይ ላይ ጠያቄ ጠይቆ፣ ለጠያቄው ማብራሪይ የመቀብል መብት እንዳለዉ ቢታወቅም፣ የክልሉም ሆነ የፌደራል አስተዳዳሪዎች የሕዝብንም ሆነ የአንድነት ፓርቲን ጥያቄ ጆሮ ዳባ ልበስ ብልዉታል።
የሱዳን ድንበር ጉዳይን በተመለከተ የሱዳን ጋዜጥኞች የተደረጉ ስምምነቶችን እንደ ድል እየዘገቡ ባለበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሆነ የምነግስት ባለስልጣናት ትንፍሽ አለማለታቸውና ጉዳዩን ከሕዝብ መደበቃቸው፣ በጣም እንዳሳሰበው የሚገልጸው የአንድነት መግለጫ፣ የስልጣን የበላይ አካል ለሆነዉ ለፓርላማዉ በድንበር ጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ጠይቋል።
የመንግስት አባላት ምላሽ ማራሪይ እንዲሰጡ በደብዳቤ ግፊት እማድረግ በተጨማሪ፣ ፓርቲዉ የጉዳዩ ባለቤት ከሆነ ሕዝብ ጋር ለመወያያት ጥር 18 ቀን 2006 ዓ.ም ስብሰባ ጠርቷል።
ሌላዉ አገር ቤት የሚንቀሳቀሰ፣ የሰማያዊ ፓርቲ በዚሁ በኢትዮ ሱዳን ድንበር ዙሪያ በጎንደር ከተማ ጥር 25 ቀን 2006 ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ ይታወሳል። ፓርቲዉ ሌሎች ሲቪክ ማህበራትና የፖለቲክ ድርጅቶ እንዲተባበሩት ጥሪ ያቀረበ ቢሆንም፣ በተግባር ግን ምን ያህል በመግለጫ ጥሪ ከማቅረብ ባለፈ፣ ከሌሎች ፓርቲ አመራሮች ግር ለመነጋገርና ሰልፉን ለማቀናጀት እየሰራ እንደሆን ብዙም አይታወቁም።
የአንድነት ሕዝባዊ ስብሰብ ጥሪን በተመለተ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
የአንድነት ፓርቶ ለፓርላማው የላከዉን ደብዳቤ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !