ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ቴሬንሴ ሊዮንስ በዋሽንግተን ፖስት ላይ “ነጻና ፍትሀዊ ምርጫን ከኢትዮጵያ ጋር ምን አገናኘው?”በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ በመጪው ግንቦት 16 በ ኢትዮጵያ የሚካሄደው ምርጫ የመርሀግብር ማሟያ እንጂ ትርጉም ያለው እንዳልኾነ ገልጸዋል። ሂደቱ ከቅድመ-ምርጫ ጀምሮ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ እንዳልነበር በስፋት ያብራሩት ጸሃፊው ”ዜጎች አዲስ መንግስት የማይመርጡበት ትርጉም የለሽ ምርጫ”ሲል …

ዱሮ ዱሮ ምዕራባውያን የሶቭየት ኅብረትን ኮሚዩኒዝም መስፋፋት ለመቋቋም ከእሥራኤል ሌላ አጋር ሊሆኑ የሚችሉ አገሮችን ሲያስሱ፣ ኢትዮጵያ፣ ቱርክና ፋርስ እየታጩ ነበር፤ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የተወዳጀበትና በአስመራ ቃኘው ጣቢያን የተከለበት አንዱ ምክንያት ይኸው ነው፤ የፋርስ ጉዳይ ከንጉሠ ነገሥቱ መፈንቅለ መንግሥትና ሞት ጋር አበቃ፤ ቱርክ እያንገራገረም ቢሆን የሰሜን አትላንቲክ አገሮች ማኅበር ውስጥ አለበት፤ እሥራኤል በአረቦች አካል ላይ እሾህ […]

በበረራ፣ ጥገና፣ ድጋፍ ሰጪ፣ ዘመቻና አስተዳደር ከ200 በላይ አባላቱን በከፍተኛ ወጪ ለ6 ወራት ሲያሰለጥን የባጀው አየር ኃይል የሰላም ማስከበሩ ተልዕኮ ወደሚከናወንበት ደቡብ ሱዳን ሊጓዙ የተመረጡት መንገደኞች ከየአየር ምድቦቻቸው ተነስተው ደብረ ዘይት ከከተቱ በኋላ ጉዞው ድንገት ተዘርዟል፡፡ ጉዞው የተሰረዘባቸው ምክንያቶች በአባላትና አባላት፣ በአባላትና አመራሮች እንዲሁመም በአመራሮችና አመራሮች መካከል አለመተማመን በመስፈኑ፤ ያለመጠን ስር ሰዶ የተንሰራፋው ጎሰኝነት ተባብሶ […]

የግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ የሆኑት የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እህት ወ/ሮ ብዙአየሁ ፅጌ ለኢትዮጵያ ህዝብ መልዕክት አስተላለፉ! እነሆ መልዕክቱን ያንብቡ፤ ሼር በማድረግም ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ይደርስ ዘንድ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ ታደርጉ ዘንድ በአክብሮት ተጠይቃችኋል! “ለውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ” ከአንዳርጋቸው ጽጌ እህት (ወ/ሮ ብዙአየሁ ፅጌ) ይድረስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ እንዳሸዋ ተበትናችሁ የምትገኙ ወገኖቼ እኔ የተጎዳሁትን […]

በገዢው የኢህአዴግ መንግስት ላይ የትጥቅ ትግልን እያካሄዱ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ወደ ጥምረት እና ውህደት የሚወስዳቸውን ውይይት መጀመራቸውን ባለፈዉ አርብ ይፋ አደረጉ ። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፥ የጋምቤላ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፥ የቤኒሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፥ የአማራ ዴሞክራሲ ሀይል ነቅናቄ፥ እና የአርበኞች ግንቦት ፯ ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ የጥምረት ብሎም የውህደት ዉይይቶችን መጀመራቸውን አስታወቁ ። “ሀገርን እና ህዝብን …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ 22 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖረው የ25 ዓመቱ ሲሳይ ተሾመ በቅጽል ስሙ ገብሬ ያለፉትን 8 ዓመታት በቃሊቲና በዝዋይ እስር ቤቶች እየተመላለሰ አሳልፏል። በተለይ ወደ ዝዋይ እስር ቤት ከተላለፈ በሁዋላ ፣ ሃጎስ የተባለው የእስር ቤቱ ሃላፊ ” አንተ የነፍጠኛ ልጅ እንበቀለሃለን፣ በእኔ እጅ ነው የምትሞተው” እያሉ …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢሳት በናይል ሳት ሲያስተላልፈው የነበረው ስርጭቱ በ2 ሳምንታት ውስጥ የኢህአዴግ አገዛዝ ባሳደረው የዲፕሎማሲ ጫና ከአየር ላይ እንዲወርድ ከተደረገ በሁዋላ፣ በአሞስ ስርጭቱን ቢጀምርም፣ ከአገሪቱ በሚለቀቀው ሞገድ እንደገና በመታፈኑ ከአየር ላይ እንዲወርድ ተደርጓል። ኢሳት ባለፉት 5 አማታት 8 የሳተላይት ጣቢያዎችን እየቀያየረ ስርጭቱን ሲያቀርብ ቆይቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢሳትን …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የተለያዩ አለማቀፍ ድርጅቶች የመስክ ጉብኝት በማድረግ ባወጡት ሪፖርት በሲቲ ዞን ባለፈው ወር ብቻ በተከሰተው ድርቅ ከ2 ሺ በላይ በጎችና ፍየሎች ሲያልቁ ነዋሪዎችም እየተሰደዱ ነው። በረሃቡ ምክንያት በሃዲጋላ ወረዳ ጉርጉር ቀበሌ በጎች የሌሎችን በጎች ቆዳ ሲበሉ መታየታቸውን በስእል የተደገፈው ሪፖርት ያሳያል። አይሺያ፣ ሃድሃጋላ፣ ከፊል ሽንሌ፣ ከፊል ደምበል፣ …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የህወሃት/ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የአምስት ዓመት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅዶች መካከል የስኳር ፕሮጀክቶች በዋነኛነት በፋይናንስ እጥረት ምክንያት እንዳልተሳኩ ከስኳር ኮርፖሬሽን የተገኘ መረጃ ጠቆመ፡፡ በሰኔ ወር 2007 መጨረሻ የሚጠናቀቀው የአምስት ዓመት መርሃግብሩ ከተያዙት ፕሮጀክቶች አንዱ የስኳር ፕሮጀክቶች ሲሆኑ ለፕሮጀክቶቹ ተስፋ ተጥሎባቸው የነበሩት አበዳሪ ተቋማት ገንዘብ ሊሰጡ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ምክንያት …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት አይኤስን ለማውገዝ ሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም በጠራው ሰልፍ ላይ ሁከትና ብጥብጥ አስነስተዋል የተባሉትና በወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት ተከሳሾች ላይ መደበኛ ክስ ተከፈተ። በዚህም መሰረት የሚሊዮኖች ድምፅ ጋዜጣ አምደኛና የአንድነት አባል የነበረው ወጣት እስማኤል ዳውድን ጨምሮ በሌሎች 18 ተከሳሾች ላይ የፌደራል ዐቃቤ ህግ ክስ …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እየተዋከቡ፣ እየታሰሩና ደብደባም እየተፈጸመባቸው መሆኑን በየጊዜው የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ። የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች አንድ ጊዜ የቡና ሌላ ጊዜ የእድር እያሉ በተለይም እናቶችን እየሰበሰቡ ኢህአዴግን እንዲመርጡ፣ ልጆቻቸውንም አመጽ እንዳያስነሱ እንዲመክሩ ለማግባባት ይጥራሉ። መራጮች በኢህአዴግ ካድሬዎች የቅስቀሳ መንገድ …

በምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢዎች በሚሊሻዎች ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ በቃሉ አዳነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ታዛቢዎቹ ‹‹ከአሸባሪ ፓርቲ ጋር አብራችሁ እየሰራችሁ ነው›› እየተባሉ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የገለጹት አቶ በቃሉ ቀሪዎቹን ‹‹ከአሸባሪ ፓርቲ ጋር ሲሰሩ አገኘናቸው ብለን እንከሳችኋለን›› እያሉ እያስፈራሯቸው ነው ብለዋል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር የምትገናኙበት ነው በሚልም ስልካቸውን […]

    ቢቢሲ ባወጣው መረጃ መሰረት አንድ የሊቢያ ባለስልጣን ለቢቢሲ እንደገለፁት በሜዲትራኒያን ባህር በህገወጥ መንገድ ሰዎችን ወደ አውሮፓ አዘዋዋሪዎች ከስደተኞች ጋር ታጣቂዎቹን በመቀላቀል ወደ አውሮፓ እንዲገቡ እያደረጉ ነው ታጣቂ ቡድኑ በሰሜን አፍሪካ ጀልባ ባለቤቶች ስራውን እንዲሰሩ በመፍቀድ ከገቢያቸው ደግሞ 50 በመቶ ያህሉን ይቀበላሉ እንደ ቢቢሲ ዘገባ የአይ ኤስ ታጣቂዎች በባህር በሚደረገው ጉዞ ከሌሎቹ ስደተኞች በምን […]

በጋሞጎፋ ዞን ቁጫና ቦርዳ ወረዳዎች የደኢህዴን/ኢህአዴግ ካድሬዎች የህዝቡን ካርድ እየተቀበሉ የምርጫ ካርዱ ላይ የንብን ምልክት በስቴፕለር በማያያዝ ኢህአዴግን እንዲመርጡ እያስገደዱ እንደሚገኙ በጋጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ አቶ ወንድሙ መኩሪያ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ካድሬዎቹ ህዝቡን 1ለ5 በማደራጀት የንብ ምልክት የተለጠፈበት ካርድ በማደል ‹‹የምትመርጡት ኢህአዴግን ነው›› እያሉ እያስገደዱ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ የዞኑ፣ የወረዳውና የየ ምርጫ ክልሉ ምርጫ አስፈጻሚዎች […]

በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች መጪውን ምርጫ ተከትሎ በርካታ ዜጎች እየታሰሩ መሆናቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች የደረሰን መረጃ አመለከተ፣ በክልሉ ምስራቅና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች መጪውን ምርጫ ተከትሎ በርካታ ዜጎች እየታሰሩ መሆናቸውን የገለፀው መረጃው በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል የሚንቀሳቀሰው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑ ንፁሃን ዜጎችን በትጥቅ ትግል ከሚንቀሳቀሰው ግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል ሰንካላ ምክንያት የስርዓቱ ካድሬዎች ባሰማሯቸው በሆዳቸው […]

ሃይለማርያም ከስልጣን ሲባረር እ አ አቆጣጠር በ2009 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጥቅምና ምቾት ለመወሰን የወጣው አዋጅ ለሃይማርያም የማያገለግልና ሃይለማርያም የዚህ ተጠቃሚ እንደማይሆን ታውቋል።

ሃይለማርያም ከስልጣን ሲባረር እ አ አቆጣጠር በ2009 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ጥቅምና ምቾት ለመወሰን የወጣው አዋጅ ለሃይማርያም የማያገለግልና ሃይለማርያም የዚህ ተጠቃሚ እንደማይሆን ታውቋል።
ቀደም ብሎ ህወሃት ሃይለማርያምን ለማስወገድና የህወሃቱን ቴድሮስ አድሃኖም ጠ/ሚንስቴር አድርጎ ለመሾም መስማማቱን ዘግበን ነበር።

አሁን ደግሞ የደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ሃይለማርያም ስልጣኑን ሲለቅ ከስልጣን ለተገለሉ ለከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የሚደረገው ጥቅምና እንክብካቤ ሊደረግለት እንደማይገባ ህወሃቶች ተስማምተውበታል፡
ለዚህም ያዘጋጁት ምክንያንያት

1ኛ. በProclamation No. 653/2009 አንቀጽ 12. Pension Rights ንኡስ ቁጥር
“1/ Notwithstanding any provision to the contrary under the relevant pension law, if a Senior Government Official who has served for at least one election term:”
አንድ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ቢያንስ የአንድ የምርጫ ዘመን ማገልገል አለበት የሚለውን እንደሚጠቅሱበትና እሱ ደግሞ ይህን ስለማያሟላ ጥቅማ ጥቅሙ አይገባውም። ዳግመኛም እንደማይመረጥ ተወስኗል፤ እንዳውም በምርጫ ጣቢያው በሌላ ተወዳዳሪ እንሚሸነፍ ይጠበቃል፡

2ኛ. ጥቅሙ የሚገባው በረሃ ለታገሉ እንጂ እዚህ ከተማ ተቀምጠው ከድል በሗላ ብቅ ለሚሉ መሆን የለበትም የሚሉ አክራሪ የህወሃት አባላት ለመቶ አለቃ ግርማ የሚደረገው እንክብካቤም ስህተት መሆኑንና እንደሚያንገበግባቸው ተገልጿል፡
ባለራዕዩ መሪ መለስ ዜናዊ በህይወት ኖሮ ያላገኘውን እንክብካቤና ክብር ሃይለማርያም ሊያገኝ አይገባም የሚሉም አሉ፡ ሃይለማርያም ስልጣን ከለቀቀ በሗላ የመለስን ስም የሚያገዝፍ የሃይለማርያምን ደግሞ የሚያቀጭጭ ዶክመንታሪ እንደሚሰራ፡ ዶክመንታሪውም የሃይለማርያም ንግግሮች እየተቀነጨቡ ምን ያህል ብቃት የለለው እንደነበርና እሱን መጀመሪያውኑ ስልጣን ላይ ማስቀመጥ ስህተት እንደነበር የሚዘረዝርና ባንጻሩ መለስ ዜናዊ ካደረጋቸው ንግግሮች ተመርጠው እንደሚካተቱና ምን ያህል ብልህና ባለራዕይ መሪ እንደነበር በንጽጽር እንደሚቀርብ ይጠበቃል።

ሰሞኑን ሃይለማርያም ላይ የተደረገው 15 ሰዓት የፈጀና ከላይ እስከታች እንዲተቹት የተደረገው በህወሃት አቀናባሪነት የዚህ እቅድ አካል እንደሆነ የውስጥ አዋቂ ምንጮት ይገልጻሉ፡ ከግምገማው በሗላ አሁንም ስህተቱን ለመቀበልና ለመማር ዝግጁ አደለም የሚሉት ትችቶች ሳጥኑ ላይ የመጨረሻው ምስማር መሆኑን ያመለክታል።

የሚቀጥለው ሳምንት ምርጫ ነው። ከምርጫው የሚጠበቅ ለዉጥ ባይኖርም መድረክ እና ሰማያዊ( የአንድነት ሰዎች በብዛት በምርጫው እንቅስቃሴ ለማድረግ ስለገቡ) በጠበበው የፖለቲካ ምህዳር ዉስጥም ሆነ ሕዝቡን ለማንቀሳቀስ ጥረት እያደረጉ ነው። በተለይም መድረክ በኦሮሚያና በትግራይ ብዙ ድጋፍ እያገኘ እንደሆነ የሚያሳዩ ምልክቶች አሉ።

መድረክን እና ሰማያዊ ወክለው ለፓርላማ ከሚወዳደሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያን መካከል እኝህ አባት ይገኙበታል። በሞያቸው ጠበቃ ናቸው። የመልካም ሴት ባላቤትና የተባረኩ ልጆች አባት ናቸው። ከእኝህ አባት ሴት ልጆች መካከል አንዷ አስተማሪ ሆና ነበር። ከደሞዟ ብዙ ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች ትረዳና ትደግፍ ነበር። እንደ ዜጋ ሕግ መንግስት በሚፈቅደው መሰረት ጻፈች፣ አስተያየቷን ሰጠች።
እነርሱ መስማትና ማንበብ ከሚፈለጉት ዉጭ እንዲጻፍና እንዲነገር የማይፈልጉት ገዢዎች፣ የአስተሳሰብ ድሆች በመሆናቸው፣ ብእሯን መመከት አልቻሉም። ወደ ጡንቻ ሄዱ። አሰሯት። በዉሸት ክስ ሽብርተኛ ናት ብለው ከሰሷት። ጠበቃ አባቷ ተከራከሩ። ሆኖም ፍርድ ቤቶች የፍትህ አካላት ሳይሆን የሕወሃት ፖሊት ቢሮ ጉዳይ አስፈጻሚዎች በመሆናቸው፣ ፍትህ ሊገኝ አልቻለም። ይች ወጣት ለአመታት በቃሊቲ ትሰቃያለች። ይች ወጣት ርዮት አለሙ ትባላለች። በዘመናችን ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ብርቅዬና ጀግና ኢትዮጵያውያን መካከል አንዷ !!!!

ጠበቃ አባቷ፣ ምን ያህል የሕግ ስርዓት እንደሌለ በመረዳታቸው፣ ፍትህ ከፍርድ ቤት እንደማይገኝ በማወቃቸው ለዚህ ደግሞ በዋናነት ምክንያቱ የተበላሻዉና የበሰበሰው የፖለትካ ስርዓቱ በመሆኑ፣ ይሄንን ስርዓት ለመለወጥ በቀድሞ ወረዳ አራት የመድረክ ተወዳዳሪ ሆነው ቀርበዋል።እኝህ አባት ጠበቃ አለሙ ጎቤቦ ይባላሉ።

ትግል የሁሉንም ተሳትፎ ይጠይቃል። ጠበቃ አለሙ በጥብቅና ሞያቸው ቀጥለው፣ ፍትህ ቢጓደልም “ ምን አገባኝ” ብለው መቀመጥ ይችሉ ነበር። ሆኖም ከራስ አልፎ ለሌላ መቆም ትልቅነት ስለሆነ፣ እኝህን አባትም ትልቅ አባት ስለሆኑ፣ ዝምታን አልመረጡም። ፖለቲካዉን ተቀላቅለው አምባገነንነትን ለመታገል ተነሱ።

የርዮት አለሙን አባት፣ የኛም የነጻነት ናፋቂዎች ሁሉ አባት የሆኑትን፣ አቶ አለሙን እንምረጥ !!!!! አገዛዙ ከአምስት አመታት በፊት እንዳደረጉት ድምጽ እንዳይሰርቁም፣ ድምጹ እስኪቆጠር ድረስ፣ ሕዝቡ በየምርጫ ጣቢያ ቁጭ ብሎ በመጠበቅ ራሱ ማስቆጠር አለበት። 3፣ 4 አጋዚ፣ ፌዴራልና ካድሬ ፣ ሺሆችን አስፈራርተው የሕዝብ ድምጽ እንዲሰርቁ ሊፈቅድላቸው አይገባም።

Minilik Salsawi – በየቦታው ትንንሽ ጦርነት የሚመስሉ ነገሮች ነበሩ፡፡ የኛ ቅስቀሳ በተሳካ ቁጥር የእነሱ ብስጭት ይግል ነበር፡፡ ካድሬው ለሆዱ፣ መንግስት ለስልጣኑ በሚገባ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ይሄ አመላካች ነው፡፡ አንዳንድ ቦታዎች ላይ ግን ካድሬው ሽጉጥ ታጥቆ፣ ጠመንጃ ይዞ እገባለሁ አትገባም የሚል ግብግብ እስከመፈጠር ደርሷል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ መኪናዎቻችን እንዳይንቀሳቀሱ ተደርገው ተወዳዳሪ እጩዎቻችን ሳይቀሩ ተደብድበዋል፡፡ በአባላቶቻችን ላይ እስር፣ ድብደባና ወከባ ተጠናክሮ ቀጥሏል:: በዘንድሮ ምርጫም ኦሮምያ ላይ እናሸንፋለን ብለዋል – ዶ/ር መረራ፡፡

በኦሮሚያ ብዙ አካባቢዎች ሰፋፊ ህዝባዊ ስብሰባዎችን አካሂደናል፡፡ ባኮ፣ አምቦ፣ ጀልዱ፣ ጊንጪ የመሳሰሉት አካባቢዎች እኔ የተገኘሁባቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች ተደርገዋል፡፡ በየስብሰባው ከ60ሺህ በላይ የሚገመት ህዝብ ነው ድጋፉን ሲገልፅልን የነበረው፡፡ በተለይ የወጣቱ ድጋፍ ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ ነው፡፡ “ከዚህ በኋላ የፀረ-ዲሞክራሲ አገዛዝ ይብቃን” የሚሉ ህብረ ዝማሬዎችን እያሰማ ነው ህዝቡ በየስብሰባው ላይ ሲታደም የነበረው፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች ሲታዩ ቅስቀሳው ስኬታማ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ክልሉን እያስተዳደረ ያለው ኦህዴድ፣ በዚህ መልኩ ወጣቱ ለኛ ድጋፍ ይሰጣል ብሎ የገመተ አይመስለንም። አሁን ታዲያ የድንጋጤ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው፡፡ በአርሲ፣ በባሌ፣ በሃረርጌ፣ በባሌ እና በሸዋ አካባቢዎች አባሎቻችንን ማሰር፣ መደብደብና ማዋከብ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የቅስቀሳ መኪናዎቻችንን መስተዋቶች በድንጋይ የመስበር፣ መኪኖችን በቡና ቤቶች አካባቢ ማሳደር እንዳንችል የማድረግ ሁኔታዎች በስፋት ተስተውለዋል፡፡ ብለዋል – ዶ/ር መረራ፡፡

በሁሉም የኦሮሚያ ዞኖችና አካባቢዎች ተመሳሳይ የሆነ አቀባበል ከህዝቡ አግኝተናል፡፡ በአጠቃላይ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በትግራይ እና በአዲስ አበባ በምርጫው እንወዳደራለን፡፡ በሁሉም ላይ ቦታ ሰፊ አቀባበል ያገኘን ቢሆንም በተለይ ኦሮሚያ ላይ ኢህአዴግ ምርጫውን ካላጭበረበረ በቀር የሚያሸንፍበት መንገድ የለውም፡፡ እኛ ሁለት ነገር ነው የምንጠብቀው፡፡ አንደኛ ኢህአዴግ ካላጭበረበረ በቀር ኦሮሚያ ላይ አያሸንፈንም፣ ሁለተኛ ደግሞ ፖለቲካውን በሚገባ እንዳሸነፍን አሳይተናል፡፡ ሰፊ ድጋፍ እንዳለን አስመስክረናል፡፡ በየትኛውም ሚዛን ከኦህዴድ እንደምንሻል አሳይተናል፡፡ በዚህ ተደናግጠው እኔ በምወዳደርበት አካባቢ ኦህዴዶች ህዝቡን በሬ አርደው ማብላት ሁሉ ጀምረዋል፡፡ የክልሉ ካድሬዎች አሁን አምቦ ከትመዋል፡፡ ሥራ ላይ ናቸው ማለት ነው፡፡ ኦህዴድና ህዝቡ ከተለያየ ቆይቷል፡፡ ያው በኢህአዴግ ጃንጥላና ጠመንጃ ስር ነው የሚንቀሳቀሰው፡፡ እነሱም እንደማያሸንፉ ያውቃሉ። እኛ በ97 እኮ አሳይተናቸዋል፡፡ በወቅቱ እነ አባዱላን ያሸነፉት እኮ የ6ኛ እና 7ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ኦህዴድ በኦሮሚያ ሊሸነፍ እንደሚችል በ97 ምርጫ ነው ያረጋገጥነው፡፡ ብለዋል – ዶ/ር መረራ፡፡

“መድረክ” አብላጫ ድምፅ ካገኘ ጥምር መንግስት ይመሰርታል:: እኛ በፕሮግራማችን ላይ በግልፅ አስቀምጠናል። በሽግግሩ ጊዜ ጥምር መንግስት ያስፈልጋል ብለናል። ብሄራዊ መግባባት ለመፍጠር፣ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድና ለመሳሰሉት ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች መልክ ማስያዣ ይሆን ዘንድ የብሄራዊ አንድነት መንግስት ያስፈልጋል፡፡ ከማን ጋር ይመስረት የሚለው በድርድር የሚከናወን ይሆናል፤ ነገር ግን አግላይ ፖለቲካ ውስጥ አንገባም፡፡አንድ ፓርቲ ሌላውን አግልሎ ኢትዮጵያን መንግስተ ሰማያት ያደርሳል የሚሉ ካሉ ወይ የፖለቲካ ሳይንስ ያልገባቸው ወይም እስከቻልን ድረስ በፈላጭ ቆራጭነት ረግጠን እንግዛ የሚሉ ናቸው፡፡ በተረፈ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲ ለማምጣት መታለፍ ያለበት አንዱ ሂደት የብሄራዊ አንድነት መንግስት ማቋቋም ነው። ብለዋል – ዶ/ር መረራ፡፡

በአጭሩ የኢትዮጵያ መንግስት ደጋግሞ እንዲያስብበት የምመክረው ምርጫውን እንዳያጭበረብር ነው፤ ውጤቱ የፈለገ ይሁን፡፡ ምርጫን አጭበርብሮ አሸንፌያለሁ የማለት ጊዜ ማብቃቱን ማወቅ አለበት። ያንን ካላደረገ ሃገሪቷንና ህዝቦቿን ለበለጠ ተስፋ መቁረጥ ነው የሚዳርገው፤ ይሄ በተግባር እየታየ ነው። ወጣቱ ከቀይ ባህር እስከ ሜዲትራኒያን ድረስ የባህር ሲሳይ የሚሆነውና በረሃ ውስጥ እንደዚያ የሚታረደው፣ ደቡብ አፍሪካ እንደዚያ የሚቃጠለው በሃገሩ ተስፋ ስላጣ ነው፡፡ ኢህአዴግ በጠራው ሰልፍ ላይ እንኳ “የስደት ዘመን ይብቃ” ብሎ ከፖሊስ ጋር እንዴት እንደተጋጨ ተመልክተናል፡፡ አጥፍቶ የመጥፋት ፖለቲካ ይብቃ! የኢህአዴግ ባለስልጣናት ደጋግመው ያስቡበት። ህዝቡንም ወጣቱንም ተስፋ ማስቆረጥ ለማንም አይጠቅምም፡፡ በተለይ ወጣቱ በሃገሬ የተሻለ ሥራ አገኛለሁ የሚል ተስፋ ሊያድርበት ይገባል፡፡ ይሄንን ወጣት ተስፋ ማስቆረጥ ለሁላችንም አይበጅም፡፡ ብለዋል – ዶ/ር መረራ፡፡ – addisadmassnews.com

Image

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ወለላዬ

PM Hailemariam Desalegn. ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ

ከስም ልጀምር፣ የዛሬ ወጣቶች በተለይ ዘፋኞች ስማቸው በመጠኑ ተቆርጦ ወይም አንሶ ሲጠሩ እየሰማን ነው፤ ቴዎድሮስ – ቴዲ ብዙ ባያስከፋም ተያይዘው የቀጠሉት ዘፋኞች ግን እስከ አባታቸው ስለሚያሳንሱት ኢትጵያዊ ስም መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ የሆነብኝ ጊዜ አለ። እስቲ አሁን ጃህ ሉድ አጥሮ ነው ወይስ ተቆርጦ ቻቺ፣ ጃኪ፣ ጂጂ፣ አቢ፣ ኢሚ፣ ዮሲ፣ ጃኪ-ጎሲ፣ ሚሊ፣ ሚኪ፣ ዮኒ፣ … ልተዋቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢትዮጵያ ለአምስተኛዉ ብሔራዊ ምርጫ መሰናዶዋን እያገባደደች ነዉ።በየማሕበረ-መገናኛዉ ዜዴዎች የምናነባቸዉ አንዳድ ፁሁፎች «ዉጤቱ አስቀድሞ የታወቀ» እያሉ ቢተቹትም ገዢዉ ፓርቲም፤ ተቃዋሚዎቹም፤ አስመራጭ መራጮችም ለምርጫዉ መዘጋጀት፤መከራከር፤መነጋገራቸዉ እንደቀጠለ ነዉ።

ከየመን የተመለሱ ስደተኛ ኢትዮጲያውያን ከቦሌ አየር ማረፊያ ተይዘው በመአከላዊ እስር ቤት ታስረዋል በየመን በቀተስተው ግጭት የተነሳ ከየመን ወደ ስአውዲ ሊሻገሩ ሲሞክሩ በስአውዲ ፖሊስ ለቀናት ከታስሩ በህዋላ አምስት የሚሆኑ ኢትዮጲያውያን ከ4 ቀናት በፊት ወደ አዲስ አበባ ቢመለሱም በቦሌ አየረ ማረፊያ በፖሊሶች ተይዘው ወደ መአከላዊ ውስር ቤት መወስዳችውን የBBN ምንጮች አረጋግጠዋል ። እስረኞቹን ቤተስቦች እስረኞቹን ለማግኘት ያደረጉት […]

“የተራቡትን መርጠን ከምንቸገር ያው የጠገበው ይሻለናል” የሚል መልክት ያላት ማዘናጊያ ሀሳብ በየፌስ ቡክ ላይ ተበትናለች። ሲጀመር በልቶ ጠገብኩ የሚሉ መቼ ነገሱብንና። በዛ ላይ ያለአባከና በሰፊው የለመደ ሆድ ለሌላ አምስት አመት ከበሉን ለመረጃ እንኳ አጥንታችንም አይጋኝም አትቀልዱ። የሚኖር አይመስለኝም እንጂ በዚህና “ድምጽ መሰረቁ ላይቀር” አይነት አንድምታ ባላቸው ምክንያቶች ተንተርሶ ለወያኔ ድምፁን የሚሰጥ ካለ በቁሙ የሞተ ነው። […]

ገዢው ፓርቲ በሰላማዊ ፓርቲዎች የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ ከፍተኛ ጫና እያደረገ ነው። የፖለቲካ መሪዎችና ጋዜጠኞች ታስረዋል። የአንድነት ፓርቲን አግዶ እንደ ሰማያዊ ያሉትን እያዋከበ ነው። ነጻ ጋዜጦች ተዘግትዋል። ትግሉ የሕዝብ ጉዳይ እንጂ የድርጅት ጉዳይ ባለመሆኑ፣ የድርጅት መሪዎችን በማሰር፣ ድርጅቶችንም በማገድ፣ የህዝብንም ሆነ የታጋዮችን የነፃነት ፍላጎት መግታት አይቻልም። የአገዝዙን አፍናና በትር ለመቋቋም፣ ህዝቡን ወደአንድ አደረጃጀት ለማምጣትና በተናጥል […]

  የማህበራዊ ጉዳይ ሀላፊ የነበረው አቶ አለነ ማህፀንቱ በትናንትና ዕለት ያለፍርድ ቤት ማዘዣ በደህንነት ኃይሎች ታፍኖ የተወሰደ ሲሆን፤ በኃይልና በድብደባ የኢሜል አድራሻውንና ፓስዎርድን ከወሰዱ በኋላ ጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ አምጥተው እንዲታሰር አድርጓል። ከዚህም በተጨማሪ የአንድነት ሊቀመንበር የነበሩት አቶ በላይ ፍቃዱ እና ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ አቶ ተክሌ በቀለ በተመሳሳይ ዕለት በደህንነት ኃይሎች ሲዋከቡ የዋሉ ሲሆን ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ […]

የግድብና የመስኖ ፕሮጀክቶች አፈጻጸማቸው ዝቅተኛ ነው ተባለ

የኢትዮጵያ የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ከውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር ውል ፈጽሞ እያከናወናቸው ያሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸማቸው ዝቅተኛ ነው ተባለ፡፡

የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ ለሚመራው የድርጅቱ ሥራ አመራር ቦርድ አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተጻፈለት፡፡ 

ለሥራ አመራር ቦርዱ የማሳሰቢያው ደብዳቤ የተጻፈው የርብ የመገጭና  የጊዳቦ ግድቦች፣ የከሰም መስኖ መሠረተ ልማት ግንባታና የተንዳሆ የኅብረተሰብና የስኳር ልማትና መጠጥ ውኃ ግንባታን ለማከናወን ውል የገባው የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት፣ ፕሮጀክቶቹን በማጓተቱና አፈጻጸሙ ዝቅተኛ በመሆኑ ምክንያት ነው ለቦርድ ማስጠንቀቂያ የተጻፈው፡፡

በውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ወንድሙ ተክሌ ሚያዝያ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. የተጻፈው ደብዳቤ ውኃ ሥራዎች ድርጅት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በገባው ውል መሠረት በአማራ ክልል የሚገኙትን የርብና የመገጭ ግድቦች ግንባታን፣ በኦሮሚያ ክልል የጊደቦ ግድብ ግንባታን፣ በአፋር ብሔራዊ ክልል የከሰም መስኖ መሠረተ ልማት ግንባታና የተንዳሆ የኅብረተሰብና የስኳር ልማትና የመጠጥ ውኃ ግንባታ ለማካሄድ ኮንትራት የወሰደ ቢሆንም፣ ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ሊጠናቅቁ አለመቻላቸው ደብዳቤው ያስረዳል፡፡ ሚኒስቴሩ በተደጋጋሚ የቀረቡለትን የማራዘሚያ ጥያቄዎችም በመቀበል የውል ጊዜን ያራዘመ ቢሆንም፣ አንዳንዶቹ ፕሮጀክቶች ወደ ኪሳራ ሊገቡ መገደዳቸውንም ያክላል፡፡

የርብ ግድብ እ.ኤ.አ. ጥቅምት 2 ቀን 2007 ተጀምሮ እ.ኤ.አ. ሚያዝያ 30 ቀን 2011 የሚጠናቀቅ ቢሆንም፣ በተያዘው ዓመት እ.ኤ.አ. 2015 አፈጻጸሙ 76.5 በመቶ ነው ተብሏል፡፡ ነገር ግን እ.ኤ.አ. ከግንቦት 2011 እስከ ሰኔ 2014 ድረስ እንዲራዘም መደረጉን ለውኃ ሥራዎች ድርጅት ሥራ አመራር ቦርድ የተላከው የማሳሰቢያ ደብዳቤ ይገልጻል፡፡ የመገጭ ግድብ ግንባታም እ.ኤ.አ. መጋቢት 22 ቀን 2012 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን፣ መጠናቀቅ ያለበት እ.ኤ.አ. ነሐሴ 30 ቀን 2016 ነው፡፡ በዚህ ዓመት ያለው የአፈጻጸም መጠን ግን 26.05 በመቶ ብቻ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የጊዳቦ ግንባታ ግንባታ የተጀመረው ጥር 3 ቀን 2002 ዓ.ም. ሲሆን፣ ይጠናቀቃል የተባለው ጥር 3 ቀን 2004 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን አራት ጊዜ ውሉ እንዲሻሻል ተደርጎ አሁን ያለበት አፈጻጸም 63.86 ብቻ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ በሌሎቹም ፕሮጀክቶች የሚታየው አፈጻጸም ተመሳሳይ መሆኑን የሚያብራራው የሚኒስቴሩ ደብዳቤ፣ ባለድርሻ አካላቱ ማለትም ሚኒስቴሩ የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅትና አማካሪው የውኃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት ተመካክረው ቦርዱ እንዲያውቀው ያደረጉ ቢሆንም ሊሻሻል አለመቻሉን ያብራራል፡፡

ሦስቱ ባለድርሻ አካላት ባደረጉት ምክክር ድርጅቱ አጠቃላይ ያለበትን ሁኔታ ቦርዱ እንዲያውቀው ተደርጎ ለማበረታታት መሞከሩን፣ ድርጅቱ ያጋጠመውን የፋይናንስ ችግር በመረዳት ከክፍያ ተመላሽ የሚደረግ 250 ሚሊዮን ብር በብድር መልክ እንዲሰጠው መደረጉን ደብዳቤው ያስረዳል፡፡

ከመንግሥት ጋርም በመነጋገር ለርብና ለመገጭ ግድቦች ግንባታ ከሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የዋጋ ማሻሻያ መደረጉን፣ እንዲሁም መንግሥት የድርጅቱ ካፒታል እንዲያድግ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በኩል የተወሰነ ክፍያ መፈጸሙንም ደብዳቤው ያብራራል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተገለጹት ድጋፎች የተደረጉለት ቢሆንም የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ሊሻሻል አለመቻሉንም ጠቁሟል፡፡ ፕሮጀክቶቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል ከማሳየት ይልቅ ዝቅተኛ አፈጻጸም ላይ መሆናቸውን ገልጾ፣ የውኃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ሥራ አመራር ቦርድ ልዩ ትኩረት በመስጠትና ችግሮቹን በመፈተሽ በቀሪው ጊዜ አፈጻጸሙ የሚሻሻልበትን  የበኩሉን ሚና እንዲጫወት የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በደብዳቤው አሳስቧል፡፡

የሥራ አመራር ቦርዱ ከሚኒስቴሩ በደረሰው ማሳሰቢያ መሠረት ምን እያደረገ እንደሚገኝ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

 

 

አስተዳደሩ የኮንዶሚኒየም ቤቶችን ዋጋ የሚያጠና ልዩ ኮሚቴ ማቋቋሙ ተሰማ

ጭማሪው በካሬ ሜትር ከ27 እስከ 45 በመቶ መሆኑ ተጠቁሟል

‹‹አስተዳደሩ ያደረገው ጭማሪ 15 በመቶ ብቻ ነው›› የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ለአሥረኛ ጊዜ ዕጣ ያወጣባቸው 41 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ሰባት ሺሕ ለልማት ተነሽዎች ናቸው)፣ በዋጋቸው ላይ ከፍተኛ ጭማሪ መደረጉን ካቢኔው ሊቀበለው ባለመቻሉ፣ ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ የዋጋ ጥናት እየተደረገ መሆኑ ተሰማ፡፡

 

የተወሰኑ የካቢኔ አባላት ሚያዝያ 26 ቀን 2007 ዓ.ም. በከንቲባው ጽሕፈት ቤት ስብሰባ አድርገው በኮንዶሚኒየሙ ወጪ ላይ መግባባት ባለመደረሱ፣ ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ የዋጋ ጥናት እንዲደረግ ስምምነት ላይ መደረሱን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ቀደም ብሎ ተቋቁሞ የነበረው ኮሚቴ ስለ ኮንዶሚኒየም ቤቶች ያጠናው ጥናት ከመጠን በላይ የተጋነነ በመሆኑ፣ ከሁሉም ዘርፍ የተወጣጣ ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ ዋጋው እንደገና መጠናት እንዳለበት ውሳኔ ላይ መደረሱን ምንጮች አስረድተዋል፡፡  አዲስ የተቋቋመው ኮሚቴ የመጀመርያ ስብሰባውን ግንቦት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. ማድረጉንም አክለዋል፡፡

የከተማ አስተዳሩ ለቤቶች ልማት ፕሮግራም ከስድስት ቢሊዮን ብር በላይ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መበደሩን የሚያስታውሱት ምንጮቹ፣ ለቤቶች ግንባታ የወጣው ወጪና በባንክ ያለው ገንዘብ ሊጣጣም ባለመቻሉ ሁለቱን አጣጥሞ ለመቀጠል በቤቶቹ ላይ ዋጋ መጨመር እንዳለበት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ እምነት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የተወሰኑ ሠራተኞች የአሥረኛው ዙር ዕድል ተጋሪ በመሆናቸው፣ ጽሕፈት ቤቱ ሥራውን እንዴት እየሠራና ምን ዓይነት ወጪ ለምንና እንዴት እየወጣ እንደሚገኝ በቅርበት ስለሚያውቁ፣ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን  ያቀረቡ መሆኑንም ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 

በቤቶቹ ላይ መደመር የሌለባቸው የተለያዩ ወጪዎች በብክነት ወይም በሌላ ወጪ መመዝገብ ሲገባቸው በቤቶቹ ላይ በመደመራቸው፣ ለግንባታና ለዲዛይን ወጪ ተገምቶ ሥራውን ለምርምር ብድር የተወሰደ ቢሆንም፣ ከባንክ ጋር የተገባውን ብድር ማፋለሱን ገልጸዋል፡፡ ካቢኔውም በተሠራው የግንባታና የዲዛይን ዋጋ መሠረት ጽሕፈት ቤቱ መሥራት ሲገባው፣ የተጋነነ ዋጋ መቅረቡ ትክክል አለመሆኑን መግለጹን  ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡ የጽፈሕት ቤቱም ሠራተኞች ወጪው ለብቻ መያዝ እንዳለበት በመግለጽ የካቢኔውን አቋም እየደገፉ መሆኑም  ተጠቁሟል፡፡ 

የካይዘን ኢንስቲትዩት ባደረገው ጥናት መሠረት በቤቶች ግንባታ ላይ 33 በመቶ ብክነት መኖሩን ለካቢኔው ማሳወቁን የገለጹት ምንጮች፣ ብክነቱን በተለያዩ ነገሮች ማወራረድ ሲቻል በቤቶቹ ዋጋ ላይ መደመር አግባብ አለመሆኑን ካቢኔውም ሆነ የዕጣው ዕድለኞች የሚስማሙበት ሐሳብ መሆኑንም ምንጮች አስረድተዋል፡፡

የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ማንኛውም ዓይነት ክትትልና ጥንቃቄ ቢደረግበት እንኳ እጅግ በጣም አስቸጋሪና ለምዝበራ የተጋለጠ መሆኑን፣ የቤቶች ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ በቅርቡ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የከተማ ልማትን በተመለከተ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ባደረጉት ክርክር ላይ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ቢሮ ኃላፊ በሚያዝያ ወር የመጀመርያ ሳምንት አካባቢ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በአሥረኛው ዙር ዕጣ በወጣባቸው ቤቶች ላይ የተደረገው ጭማሪ እንደሚባለው የተጋነነ ሳይሆን፣ 15 በመቶ ብቻ እንደሆነ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ ነገር ግን አስተዳደሩ የነባር 20/80 ባለ አንድ፣ ሁለትና ሦስት መኝታ ቤቶችና እንዲሁም የስቱዲዮ ቤቶችን ለመሸጥ ካስቀመጠው ዋጋ ላይ ከ27 እስከ 45 በመቶ ጭማሪ ማድረጉን የዋጋውን ልዩነት ያሰሉ ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡

የ10/90 ተመዝጋቢዎች ዝቅተኛ ክፍያ በካሬ ሜትር 1,310 ብር የሚከፍሉ መሆኑን በምዝገባ ወቅት የተነገረ ቢሆንም፣ በአሥረኛው ዙር ግን በካሬ ሜትር 1,910 ብር እንዲከፍሉ ተደርጓል፡፡ ልዩነቱ 600 ብር ወይም 45 በመቶ መሆኑን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ፡፡ ዝቅተኛው የስቱዲዮ ስፋት 29 ካሬ ሜትር ነበር፡፡ 

በተመሳሳይ ሁኔታ ነባር የ20/80 ባለሁለት መኝታ ቤት ተመዝጋቢ በካሬ ሜትር የሚከፍለው 3,452 ብር የነበረ ቢሆንም፣ በአሥረኛው ዙር ዕድለኛ የሆነ ግን በካሬ ሜትር 4,394 ብር ይከፍላል፡፡ ሲመዘገብ ከሚያውቀው ዋጋ ጋር ያለው ልዩነት 942 ብር ወይም 27 በመቶ መሆኑን ነዋሪዎቹ አሥልተዋል፡፡ ዝቅተኛው ባለሁለት መኝታ ቤት ስፋቱ 65 ካሬ ሜትር ነው፡፡ 

በመሆኑም የዕጣው ባለቤቶች መንግሥት መሬት በነፃ፣ ሁሉንም የግንባታ ግብዓቶች ከአገር ውስጥ ባደረገበት ጊዜ ዋጋው ይኼንን ያህል ሊጋነን እንደማይገባ እየገለጹ ባሉበት ወቅት፣ አስተዳደሩ ዋጋው በልዩ ኮሚቴ እንዲጠና ማድረጉ ተገቢና ዕድለኞቹንም ያሰበ ሊሆን ይችላል በሚል ተስፋ ላይ መሆናቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡ ነዋሪዎች የሠሩት ሥሌት ትክክል መሆን አለመሆኑንና አዲስ ስለተቋቋመው ኮሚቴም ማብራሪያ እንዲሰጡ የአስተዳደሩት ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችንና የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችን ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

 

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽ በኢትዮጵያ የመጀመርያውን የብረት ማዕድን ማውጫና ማቅለጫ ፋብሪካ ሊገነባ ነው፡፡ ፋብሪካው የሚገነባው በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምት ከተማ ሲሆን፣ የብረት ክምችቱም በምዕራብ ወለጋ ዞን ቢቅላል አካባቢ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

ለዚህ ግዙፍና ለአገሪቱ የመጀመርያ ለሆነው ፋብሪካና የብረት ማዕድን ማውጪያ ከሦስት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚደረግ፣ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. የፋብሪካው የመሠረት ድንጋይ በነቀምት ከተማ በተቀመጠበት ወቅት ተገልጿል፡፡

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርጋዴር ጄኔራል ጠና ቁሩንዴ እንደተናገሩት፣ የሚገነባው የብረታ ብረት ፋብሪካ በዓመት ከሦስት መቶ ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ የተለያዩ ብረቶችን ማምረት ያስችላል፡፡

በቀድሞው ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ባለቤትነት በኢትዮጵያ መሠረታዊ ለውጥ ማምጣት ያስችላሉ የተባሉትን የድንጋይ ከሰልና የብረት ማዕድን መገኛ ለማወቅ ጥናት ተካሂዶ ነበር፡፡ በሚኒስቴሩ በተቋቋመው ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትና የቻይና ኩባንያዎች በተሳተፉበት ጥናት፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ ኢሉአባቦራ ዞን ያዩ አካባቢ ከፍተኛ የድንጋይ ከሰል መኖሩን፣ በዚሁ ቀጣና ውስጥ ምዕራብ ወለጋ ቢቅላል አካባቢ ደግሞ የብረት ማዕድን ክምችት (አይረን ኦር) ከሌሎች ማዕድናት ጋር መኖሩን አመልክቷል፡፡

በወቅቱ እነዚህን ማዕድናት ማውጣትና ማምረት የሚያስችል ፋብሪካ ለማቋቋም የሚፈለገው ካፒታል ከፍተኛ በመሆኑ ሳይሞከር እንደቀረ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ነገር ግን ከመከላከያ ተገንጥሎ በኢትዮጵያ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ለውጥ እንዲያመጣ የተቋቋመው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ በሒደት በሁለቱም ዘርፎች በጥልቀት መግባት ችሏል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ወቅት ያዩ አካባቢ የሚገኘውን የድንጋይ ከሰል በማውጣት ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጀመረ ዓመት አስቆጥሯል፡፡ ባለፈው ሳምንት አጋማሽ ደግሞ የብረት ማዕድን አውጥቶ የሚያቀልጥበት ፋብሪካ ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ አስቀምጧል፡፡

በብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ዘርፍ ግዙፍ ኩባንያ የሆነው ስቲሊ አርኤምአይ  የኦፕሬሽንና የፖሊሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ለማ የፋብሪካውን መገንባት አስመልክተው ለሪፖርተር በሰጡት አስተያየት፣ ከውጭ ይገባ የነበረው ቢሌት (ጥቅል ፌሮ ብረት) አገር ውስጥ ማምረት መቻል ትልቅ ትርጉም አለው፡፡

አቶ ተፈራ ጨምረው እንደገለጹት፣ አገር ውስጥ ሲመረት የቆየው ብረት ከወዳደቁ ብረታ ብረት (ስክራፕ) እና ከውጭ በሚገባ ቢሌት ነው፡፡ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ወደዚህ ዘርፍ ከገባ ዩክሬን፣ ቻይናና አውስትራሊያ የሚታወቁበት የብረት ምርት በኢትዮጵያ እንዲመረት ያስችላል፡፡

‹‹ይህ ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ነው፤›› በማለት አቶ ተፈራ የፕሮጀክቱን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ አብራርተዋል፡፡

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ይኼን አዲስ ፕሮጀክት በሁለተኛው የአምስት ዓመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ ያካተተ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡

የፕሮጀክቱ ዕውን መሆን ለምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት ከመፍጠሩም ባሻገር፣ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራልም ተብሏል፡፡ 

 

የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር በሲሚንቶ ገበያ ውስጥ ችግር ፈጥሯል

የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ በገበያ ውስጥ ለተከሰተው የሲሚንቶ እጥረት ዋነኛ ምክንያት መሆኑ ታወቀ፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጡ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ሦስተኛውን መስመር ከጥቅም ውጪ ሲያደርግ፣ ደርባ ሚድሮክ

ሲሚንቶ ፋብሪካን ደግሞ የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረቱ የማምረት አቅሙን እንዳይጠቀም እንዳደረገበት ተገልጿል፡፡

ሁለቱ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች በሙሉ አቅም ማምረት ባለመቻላቸው፣ የሲሚንቶ አቅርቦት ጫና በዋነኛነት መሰቦና ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ላይ ማረፉን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከሳምንታት በፊት በዓመት 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማምረት የሚያስችለው መስመር ቁጥር ሦስት መቆጣጠርያ መሣሪያ ተቃጥሎበታል፡፡ ይኼንን መሣሪያ ከውጭ ለማስገባት ልዩ ፈቃድ የሚያስፈልግ በመሆኑ፣ በአፋጣኝ ማስገባትና ፋብሪካውን ሥራ ማስጀመር አልተቻለም ተብሏል፡፡

የኬሚካልና የኮንስትራክሽን ግብዓት ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ሀላላ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጡ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ሦስተኛውን መስመር ከጥቅሙ ውጪ ቢያደርገውም፣ ከአንድ ሳምንት በኋላ ሙገር የሚፈልገው መሣሪያ አገር ውስጥ የሚገባ በመሆኑ የፋብሪካው ቁጥር ሦስት መስመር ሥራ ይጀምራል፡፡

ደርባ ሚድሮክ ደግሞ የገጠመው ችግር የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ነው፡፡ የደርባ ሚድሮክ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኃይሌ አሰግዴ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ደርባ ሚድሮክ ሲሚንቶ ፋብሪካ በመሉ አቅሙ ለማምረት 45 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ወቅት ፋብሪካው እያገኘ ያለው ከስድስት ሜጋ ዋት አይበልጥም ብለዋል፡፡

‹‹የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረቱ በሙሉ አቅማችን ሥራ እንዳንሠራ አድርጎናል፤›› በማለት አቶ ኃይሌ የችግሩን ክብደት ይናገራሉ፡፡

የእነዚህ ሁለት ፋብሪካዎች ችግር ውስጥ መግባት የሲሚንቶ ገበያውን ችግር ውስጥ ከቶታል፡፡ በእርግጥ በሥራ ላይ ያሉት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የመሸጫ ዋጋቸው ላይ ጭማሪ ባያደርጉም ነጋዴዎች ግን በመሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ አድርገዋል፡፡

መሰቦ ሲሚንቶ ሦስት ዓይነት ሲሚንቶዎች ለገበያ ያቀርባል፡፡ የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋውም በኩንታል 250 ብር፣ 190 ብርና 165 ብር ነው፡፡ ነገር ግን በገበያ ውስጥ የመሰቦ ሲሚንቶ አንድ ኩንታል ከ350 ብር በላይ እየተሸጠ ነው፡፡

በሲሚንቶ ንግድ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንደሚሉት፣ ማንኛውም ሰው ከፋብሪካው የፈለገውን መጠን ሲሚንቶ መግዛት ይችላል፡፡ በተለይ ደላሎች ክፍያ ተፈጽሞ ሲሚንቶውን ለማግኘት እስከ ሦስት ወራት የሚወስድ በመሆኑ ወረፋቸውን በመሸጥ ብቻ ከአንድ ኩንታል እስከ አንድ መቶ ብር እያተረፉ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት በአሁኑ ጊዜ ፕሮጀክት ላለውና ንግድ ፈቃድ ላለው ቅድሚያ የሚሰጥ ባለመሆኑ የሲሚንቶ ገበያው ከፍተኛ ችግር ውስጥ እየገባ መሆኑን እየተናገሩ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት የሲሚንቶ ዋጋ በኩንታል ከ350 ብር እስከ 410 ብር ድረስ እየናረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የመሰቦ ሲሚንቶ ፕሮሞሽን ክፍል ኃላፊ አቶ ኢሳያስ ሐጎስ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በሙገርና በደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ችግር የገበያው ጫና ወደ መሰቦ ዞሯል፡፡ መሰቦ ይህ ነው የሚባል ችግር የገጠመው ባለመሆኑ ከሰባት ሺሕ እስከ ስምንት ሺሕ ሜትሪክ ቶን ሲሚንቶ በቀን ለገበያ እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የማምረት አቅም፣ ካለው ፍላጎት ከአምስት ሚሊዮን ቶን በላይ ትርፍ መሆኑ ይነገራል፡፡ ነገር ግን ፋብሪካዎቹ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት የማምረት አቅማቸውን ሙሉ በመሉ መጠቀም ባለመቻላቸው ችግር እየተፈጠረ መሆኑን ይናገራሉ፡፡

በሲሚንቶ ዘርፍ ያለውን ችግር ለመፍታት ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስብሰባ ጠርቷል፡፡ በዋንኛነት በዘርፉ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግርን ለመፍታት የተመከረ ሲሆን፣ በተለይ የደርባ ሲሚንቶ ፋብሪካን ችግር ለመፍታት በገፈርሳ ኃይል ማመንጫ የማሻሻያ ሥራዎች እየተከናወኑ በመሆናቸው፣ በአጭር ጊዜ ችግሩ እንደሚፈታ መግባባት ላይ ተደርሷል ሲሉ አቶ ሳሙኤል ተናግረዋል፡፡

ከወራት በፊት በአገሪቱ ለተከሰተው የሲሚንቶ ገበያ ችግር የትራንስፖርት እጥረት በምክንያትነት ይቀርብ ነበር፡፡ ይኼም የሆነበት ትራንስፖርት ባለሥልጣን በአገሪቱ የሚገኙ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪዎች በጂቡቲ ወደብ የተራገፉ መሠረታዊ ሸቀጦችን እንዲያነሱ በግዳጅ በማሰማራቱ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት የትራንስፖርት ችግሩ የተቃለለ ቢሆንም፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡

 

ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በሚካሄደው አምስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለማሸነፍ ተስፋ የሚያደርጉባቸውን አካባቢዎች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ 

በዚህም መሠረት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የተለያዩ ሥፍራዎችን ለማሸነፍ ተስፋ እንዳደረጉባቸው የገለጹ ሲሆን፣ ገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ግን በሁሉም ሥፍራዎች ለማሸነፍ እንደሠራ አስታውቋል፡፡ 

የኢሕአዴግ የሕዝብና የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደስታ ተስፋው፣ ‹‹በሁሉም የምርጫ ክልሎች እናሸንፋለን በሚል ነው እየሠራን ያለነው፡፡ ምርጫ ውድድር ነው፡፡ ውጤቱ የሚታወቀውም በመጨረሻ ሕዝቡ በሚሰጠው ውሳኔ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ሕዝቡ ገና ድምፁን ሳይሰጥ እዚህ አሸንፋለሁ እዚህ ደግሞ እሸነፋለሁ ማለት ትክክል አይደለም በማለት፣ ትንበያ ከምርጫ ሥነ ምግባር መርሆዎች ጋር የሚጣጣም አለመሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ 

በዚህ ሐሳብ የሚስማሙት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ፣ ‹‹ጠንካራ ቦታዎች የሚባሉትን የሚወስነው ሕዝቡ ነው፡፡ እዚህ ላይ ነው ብለን ለማለት ያስቸግረናል፤›› ብለዋል፡፡ ነገር ግን ከክልል ከተሞች ይልቅ በአዲስ አበባ ተስፋ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል፡፡ 

ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የምርምር ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ፣ ፓርቲያቸው በሦስት የተወሰኑ ቦታዎች ላይ ተስፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ 

በዚህም መሠረት የፓርቲው ፕሬዚዳንት የሚወዳደሩበት የዘንዘልማና የጢስ ዓባይ የምርጫ ክልል፣ ደብረ ማርቆስና ወላይታ ፓርቲው ለማሸነፍ ተስፋ የሚያደርግባቸው ሥፍራዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ 

አዲስ አበባ በፓርቲው ከፍተኛ የቅስቀሳ ሥራ የሚሠራበት እንደሆነ የገለጹት አቶ ዋሲሁን ‹‹ነገር ግን በከተማው 11 ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ገዢው ፓርቲ በመኖራቸው ድምፅ የመከፋፈል ዕድሉ ከፍተኛ ነው፤›› በማለት በክልል ከተሞች ያተኮሩበትን ምክንያት አብራርተዋል፡፡ 

አዲስ አበባ ላይ በእርግጠኝነት እንደሚያሸንፉ የገለጹት ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ሲሆኑ፣ በክልልም እንዲሁ ፓርቲው ተስፋ የሚያደርጋቸውን ከተሞች አስታውቀዋል፡፡ 

በዚህም መሠረት ጅማ፣ ኢሉአባቦርና የባሌ አካባቢዎች ከኦሮሚያ፣ ኮንሶና ሆሳዕና ደግሞ ከደቡብ ክልል ለማሸነፍ ተስፋ የሚያደርጉባቸው ናቸው፡፡ ከአማራ ክልል ደግሞ ባህር ዳር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደሴና ወልድያ ፓርቲው ጠንካራ እምነት አግኝቼባቸዋለሁ የሚላቸው ከተሞች ናቸው፡፡ 

‹‹ደቡብ ውስጥ በሁሉም ቦታዎች ለማሸነፍ እየሠራን የነበረ ቢሆንም፣ ባለው ሁኔታ ከፍተኛ ቅስቀሳ ማድረግ ባለመቻላችን ዕቅዳችን ሊያንስ ችሏል፤›› በማለት በደቡብ ተስፋ ያደረጉትና አሁን የሚጠብቁት የተለያዩ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ 

በአብዛኛው የኦሮሚያ ክልል በተወሰኑ የደቡብና የትግራይ ክልሎች የማሸነፍ ተስፋ እንዳለባቸው የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ዶ/ር መረራ ጉዲና ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት የትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ በሆነችው መቐለ፣ እንዲሁም ከደቡብ ከንባታና ሀድያ አካባቢዎች፣ ጋሞ ጐፋ፣ እንዲሁም ቡርጂ ዞን ውጤት የሚጠብቅባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡ 

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ፕሬዚዳንት አቶ ትዕግሥቱ አወሉ በበኩላቸው፣ በተወሰኑ የአዲስ አበባ የምርጫ ክልሎች እንዲሁም በደቡብ ሐዋሳና ዳውሮ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችና ጅማ፣ በአማራና በአፋር ክልሎች ተስፋ አለን ብለዋል፡፡

 

ሐና ላላንጐን አስገድዶ በመድፈር ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉ ተከሳሾች ጥፋተኛ ተባሉ

የጥፋተኝነት ውሳኔ የተሰጠው በልዩነት ነው 

በመስከረም ወር 2007 ዓ.ም. የ16 ዓመት ታዳጊ መሆኗ የተገለጸውን ሐና ላላንጐ፣ በታክሲ አፍነው ወደ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቀራኒዮ አካባቢ በመውሰድ፣ ተፈራርቀው በመድፈር ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ክስ

የተመሠረተባቸው አምስት ወጣቶች፣ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ጥፋተኛ ተባሉ፡፡ የጥፋተኝነት ውሳኔው የተሰጠው በልዩነት ነው፡፡

ተከሳሾቹ ሳምሶን ስለሺ፣ በዛብህ ገብረ ማርያም፣ በቃሉ ገብረ መድኅን፣ ኤፍሬም አየለና ተመስገን ዘገዬ የተባሉ ከ19 እስከ 31 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወጣቶች ሲሆኑ፣ የታክሲ ሾፌርና ረዳት መሆናቸው በክሱ መገለጹ ይታወሳል፡፡

ዓቃቤ ሕግ የወንጀል ሕግ 32(1ሀ) ማለትም በዋና ወንጀል ተካፋይነት፣ የወንጀል ሕግ 539(1ሀ)ን ማለትም ከባድ የሰው ግድያና የወንጀል ሕግ 626 (1)ን፣ ማለትም ዕድሜያቸው 13 በሆነና 18 ዓመት ባልሞላቸው ልጆች ላይ የሚፈጸም የግብረ ሥጋ ግንኙነትን በሚመለከት የተደነገገውን አዋጅ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ክስ መሥርቶ ነበር፡፡ 

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የመሠረተውን ክስ ሲመረምር የከረመው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት (የክስ ሒደቱ የተካሄደው በዝግ ችሎት ነው)፣ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ሁሉንም ተከሳሾች በልዩነት ጥፋተኛ ብሎ ለቅጣት፣ አስተያየትና የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

የተለዩት ዳኛ ከአንድ እስከ ሦስት ያሉት ተከሳሾች ላይ ከሌሎቹ ዳኞች ጋር ተመሳሳይ ሐሳብ ያላቸው ቢሆኑም፣ በአብላጫ የወንጀል ሕግ አንቀጾችን በልዩነት ያስቀመጡት፣ ተከሳሾቹ ማለትም ከአንድ እስከ ሦስት ያሉት ተከሳሾች ላይ የወንጀል ሕግ 539 (1ሀ) [ያገዳደል ሁኔታው ክብደት] እና የወንጀል ሕግ 620(3) [የአስገድዶ መድፈሩ ክብደት] ተገቢ ሆኖ ሳለ፣ በወንጀል ሕግ 620 (2መ) [ጭካኔና ስቃይ መፍጠር] ጥፋተኛ መባል የለባቸውም በሚል ነው፡፡ በአብላጫ ድምፅ በተደራቢነት የተጠቀሰውን የወንጀል ሕግ 620(4)ን [ጠለፋ] የተለዩትም ዳኛ ደግፈው፣ ነገር ግን ይኼ አንቀጽ ወደ ወንጀል ሕግ 585(1) [ከሕግ ውጭ ይዞ መቀመጥ] ስለሚወስድ በእሱ መሠረት ከአንድ እስከ ሦስተኛ ያሉት ተከሳሾች ጥፋተኛ ሊባሉ እንደሚገባ በመግለጽ ተለይተዋል፡፡ 4ኛና 5ኛ ተከሳሾች ግን በዓቃቤ ሕግ ስላልተመሰከረባቸው በነፃ ሊሰናበቱ እንደሚገባ ገልጸው ተለይተዋል፡፡

 

 

የሆላንድ ካር ባለቤት ኩባንያቸውን ለመታደግ ወደ አገር ቤት ተመለሱ

የኩባንያው ንብረት እንዳይሸጥ በድጋሚ ታገደ

በሆላንድ ካር የመኪና መገጣጠሚያ ኩባንያ በተፈጠረ ቀውስ ከሦስት ዓመት በፊት ኪሳራ በማሳወጅ አገር ጥለው የተሰደዱት ኢንጂነር ታደሰ ተሰማ፣ ኩባንያቸውን ለመታደግ ግንቦት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ኩባንያውን ለመታደግ የሚያስችል ዕቅድ ነድፈውና ለመንግሥት አቅርበው ተቀባይነት በማግኘታቸው የሕግ ከለላ ተሰጥቷቸው ወደ አገር ቤት መመለሳቸውን ተናግረዋል፡፡ 

ከ200 በላይ የሚሆኑ ደንበኞች መኪና ለመግዛት ለሆላንድ ካር ክፍያ ፈጽመው ኩባንያው መኪኖቻቸውን ለማስረከብ ሳይችል መቅረቱ ይታወሳል፡፡ ለኩባንያው ብድር የሰጠው ዘመን ባንክ በመያዣነት የያዛቸውን የኩባንያውን ንብረቶች ለመሸጥ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ መኪኖቻቸውን ያልተረከቡት ደንበኞችም በፍርድ ቤት ሲሟገቱ ቆይተዋል፡፡ 

በሆላንድ ካር መክሰር ምክንያት የኩባንያው ባለቤትና ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ታደሰ በ2004 ዓ.ም. ወደ ኔዘርላንድ ተሰደዋል፡፡ ኩባንያው በየካቲት 2005 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት መክሰሩ በይፋ ታውጇል፡፡ 

አቶ ታደሰ ኩባንያቸው ወደ ኪሳራ ሊገባ የቻለው በመሥሪያ ካፒታል እጥረት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ከሦስት ዓመት በፊት አገሬን ለቅቄ ወጥቼ ነበር፡፡ የወጣሁበት ምክንያት ሆላንድ ካር ውስጥ በተፈጠረ ችግር ምክንያት ሥራ መሥራት ስላልተቻለ ነው፡፡ ለገጠሙን ችግሮች መፍትሔ ማግኘት ስላልቻልኩኝ ምናልባት ለጊዜው ዞር ማለት ይሻላል በማለት ወጥቼ ነበር፤›› ብለዋል፡፡ 

ከአገር ከወጡ በኋላ የተቋረጠውን የኩባንያውን ሥራ ለማስቀጠል በተለይ መኪና የገዙ ደንበኞች ንብረታቸውን የሚያገኙበት ዘዴ ከመፈለግ ወደኋላ እንዳላሉ አስረድተዋል፡፡ ‹‹ብዙ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ፕሮፖዛሎች አስገብቻለሁ፤›› ያሉት ኢንጂነር ታደሰ፣ በመጨረሻ ለመንግሥት ያስገቡት ፕሮፖዛል በቤልጂየም የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቀርቦ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና በፍትሕ ሚኒስቴር በተደረገላቸው ድጋፍ የሕግ ከለላ ተሰጥቷቸው አገራቸው ገብተው እንዲሠሩ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ 

ሆላንድ ካር የከሰረበት ምክንያት ንብረት በማጣት እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ኢንጂነር ታደሰ አበዳሪያቸውን ዘመን ባንክን ወቅሰዋል፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ ባንኩ የኩባንያውን ንብረቶች የመሸጥ አቋም ነበረው፡፡ ያ ቢሆን የአንድ ቡድን ጥቅም ብቻ ነው የሚጠበቀው፡፡ ባንኩ ንብረቶቹን ሽጦ ገንዘቡን ይወስዳል፡፡ የቀሩት ደንበኞች ምንም የሚያገኙት ነገር አይኖርም፡፡ ከባንኩ ጋር ስንነጋገር የነበረው ወደ ሐራጅ ከተገባ ደንበኞች ስለሚጎዱ ወደዚያ አንግባ ብዬ ብዙ ተከራክሬያለሁ፤›› ብለዋል፡፡ 

ዘመን ባንክ በሠራው የፋይናንስ ዕቅድ ኩባንያውን ለመታደግ በወቅቱ ለሦስት ወራት 17 ሚሊዮን ብር ያስፈልግ እንደነበር ጠቁሞ፣ ከሦስት ወራት በኋላ ያለ ዕዳ መንቀሳቀስ ይችላል የሚል ነበር፡፡ ‹‹ነገር ግን ባንኩ ቶሎ ብሎ ወደ ሐራጅ ማውጣት ስለፈለገ ያንን ለመከላከል የምችለው ኪሳራ በማወጅ ብቻ ነው፡፡ ወደ ኪሳራ በማስገባበት ጊዜ ባንኩ እንደ ሌሎች ደንበኞች ተሰልፎ ይጠብቃል፡፡ እኔ ብቻ ሸጬ ልውሰድ የሚለው አይኖርም፡፡ ይህን ደግመን ደጋግመን ተናግረናል፡፡ እዚያ ውስጥ አንግባ በሚል ተነጋግረናል፡፡ እስከ መጨረሻው ቀን ጠብቄ ወደ ኪሳራ እንዲገባ አድርጌያለሁ፤›› ብለዋል፡፡ 

ሪፖርተር ዘመን ባንክን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ያደረገ ቢሆንም፣ ማኔጅመንቱ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል፡፡ ‹‹አስተያየት የለንም፤›› ብለዋል አንድ የባንኩ ከፍተኛ ኃላፊ፡፡ 

ሆላንድ ካር የዘመን ባንክ 34 ሚሊዮን ብር ዕዳ አለበት፡፡ ባንኩ የኩባንያውን ንብረቶች በ83 ሚሊዮን ብር የመነሻ ዋጋ ለጨረታ አቅርቧል፡፡ ሞጆ ከተማ የሚገኘው በ20,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ፣ መጋዘንና የቢሮ ሕንፃ 22.3 ሚሊዮን ብር የተገመተ ሲሆን፣ 236 ያልተገጣጠሙና 70 የተገጣጠሙ መኪኖች 51.7 ሚሊዮን ብር ተተምነዋል፡፡ 

ዘመን ባንክ የጨረታ ማስታወቂያውን ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ያስነገረ ሲሆን፣ የጨረታ መዝጊያው ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኢንጂነር ታደሰ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. የኩባንያው ንብረቶች እንዳይሸጡ አግዷል፡፡ እንደ ኢንጂነር ታደሰ ገለጻ ኩባንያው ያለበት የባንክ፣ የደንበኞችና የመንግሥት (ግብር) ዕዳ በአጠቃላይ 63 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ የኩባንያው ጠቅላላ ንብረት ግምት 180 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ኢንጂነር ታደሰ በአውሮፓ ቆይታቸው የገንዘብ ምንጭ ሲያፈላልጉ እንደነበር ገልጸው፣ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በቤልጂየም ከኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ተሾመ ቶጋ ጋር ረዥም ጊዜ ሲወያዩ እንደነበር፣ አምባሳደር ተሾመ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዳደረጉላቸው ተናግረዋል፡፡ 

አዲስ የነደፉትን ሆላንድ ካርን ካለበት ችግር አውጥቶ ወደፊት ሊያስኬድ የሚያስችል ያሉትን ዕቅድ፣ ቤልጂየም ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አቅርበው ኤምባሲው ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ማቅረቡን፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽንና የፍትሕ ሚኒስቴር አስተያየት እንዲሰጡበት ተጠይቀው ዕቅዱ ተቀባይነት በማግኘቱ፣ አስፈላጊው የሕግ ከለላ ተደርጎላቸው ወደ አገር ቤት ተመልሰው ችግሮቹን በውይይት እንዲፈቱ እንደተፈቀደላቸው አስረድተዋል፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ ያቀረቡት ዕቅድ በመጀመርያ በፋብሪካ ውስጥ የሚገኙትን መኪኖች ገጣጥሞ ክፍያ ለፈጸሙ ደንበኞች ማቅረብ፣ በመቀጠል የተቀሩትን መኪኖች ገጣጥሞ በመሸጥ ኩባንያው ያለበትን የባንክ ዕዳ መክፈል የሚል ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት 150 ያልተገጣጠሙ መኪኖች በፋብሪካው ውስጥ እንደሚገኙ ጠቅሰው፣ እነዚህን መኪኖች ለመገጣጠም አምስት ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡ ስድስት ሚሊዮን ብር ከአውሮፓ የገንዘብ ምንጮች ይዘው እንደመጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ሆላንድ ካር ከገባበት ማጥ ውስጥ ለማውጣት አንድ ዓመት እንደሚፈጅም ተናግረዋል፡፡ ‹‹ያልተገጣጠመ መኪና ብረት ነው፡፡ አይሸጥም፡፡ ገጣጥመን እሴት ጨምረን ብንሸጠው ሁሉም ተጠቃሚ ይሆናል፡፡ ደንበኞች ንብረታቸውን ያገኛሉ፡፡ ከዚያም ተርፎ ድርጅቱ መቀጠል የሚችልበት ሁኔታ ይኖራል፤›› ብለዋል፡፡ 

ኢንጂነር ታደሰ 115 ደንበኞች ክፍያ ፈጽመው መኪኖቻቸውን አለመረከባቸውን፣ 40 ያህል ደግሞ ቀረጥ ከፍለው መኪኖቹን መውሰዳቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የጀመሩት ጥረት ከሰመረ ወደ ሌሎች ኢንቨስትመንቶች ለመግባት ዕቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡

 ከሆላንድ ካር መኪና ከገዙ ግለሰቦች መካከል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ አንዱ ናቸው፡፡ በሆላንድ ካር ቀውስ ከተፈጠረ በኋላ መኪናቸውን የተረከቡ የመጀመርያው ደንበኛ መሆናቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

‹‹መኪናዬን ከተረከብኩ በኋላ ሌሎች ግለሰቦች መኪናቸውን እንዲያገኙ ጊዜዬንና ገንዘቤን በመሰዋት ብዙ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ ሆኖም እጃችን አመድ አፋሽ ሆነና ባልሠራነው ኃጢያት ተከሰን ጠበቃ ቀጥረን ተከራክረን ነፃ ወጥተናል፤›› በማለት በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ አስታውሰዋል፡፡ ‹‹አሁን ባለሀብቱ ያሉትን ችግሮች ፈትቼ ከባንኩ ጋር ተነጋግሬ ለደንበኞች መኪኖቹን አስረክባለሁ ካሉ በእውነቱ ይህ መልካም ዜና ነው፡፡ የሚደገፍ ተግባር ነው፤›› ብለዋል አቶ ግርማ፡፡ 

 

በምርጫው ሁከት ቢፈጠር እንኳን ከአቅም በላይ እንደማይሆን መንግሥት አስታወቀ

ምርጫውን ተጠቅመው ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ አካላትን መንግሥት የሚታገስበት ምክንያት እንደሌለና ችግር ከተፈጠረም ከአቅም በላይ ሊሆን እንደማይችል፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን አስታወቁ፡፡

ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ግንቦት 6 ቀን 2007 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ፣ አጠቃላይ የቅድመ ምርጫ ዝግጅት ከጥቃቅን ችግሮች ባሻገር ሰላማዊ እንደነበር ባለፈው ሳምንት ከምሁራንና ከፓርቲዎች ጋር በተደረገ ውይይት መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡

ቀጣዩ ምዕራፍም ተመሳሳይና ሰፋ ያለ ተሳትፎ የሚደረግበትና ምርጫው በአጠቃላይ እጅግ ሰላማዊ ሆኖ ይጠናቀቃል የሚል እምነት መያዙን ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሠረት ሁከትም ሆነ ችግር ለመፍጠር የሚያስችል ምክንያት አለመኖሩን፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆኑ ገዥው ፓርቲ በጋራ ባካሄዱት ግምገማ ከሞላ ጎደል ማረጋገጣቸውን ጠቅሰዋል፡፡

‹‹ይህ ማለት ግን ምርጫውን ተጠቅመው ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ አካላት አይኖሩም ማለት አይደለም፤›› ያሉት ሚኒስትሩ፣ ‹‹ይህንን የሚሸከም የሕዝብ ትከሻ የለም፡፡ በመንግሥት በኩልም ለፀጥታ ኃይሎች ሥልጠናና የቁሳቁስ ዝግጅት የተደረገ በመሆኑ ችግር ከተፈጠረ ከአቅም በላይ ሊሆን እንደማይችል መንግሥት እርግጠኛ ነው፤›› ብለዋል፡፡

ለፀጥታ ኃይሉ በቅርቡ የተሰጠው ሥልጠናና የአቅም ግንባታ ማዳበሪያ የተከናወነው የተለየ ሥጋት በመኖሩ እንዳልሆነም አስታውቀዋል፡፡ ከምርጫ 97 በኋላ የተደረገ ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ለፀጥታ ኃይሉ መስጠት መደበኛ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ ከቁጥጥር ውጪ የሚወጣ ነገር አይኖርም ብለዋል፡፡ የአቅም ግንባታ ሥራውም ከምርጫ በኋላ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

የግንቦት ሰባት ዋና ጸሐፊ የነበሩትና በኢትዮጵያ የደኅንነት ኃይል የመን ሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ከአዲስ አበባ አዳማ የሚወስደውን የፍጥነት መንገድ ሲጐበኙ የሚያሳይ ፎቶግራፍ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች መታየቱን አስመልክቶ የተጠየቁት አቶ ሬድዋን፣ ‹‹ምሥሉን አይቼዋለሁ፡፡ ነገር ግን ዝርዝር መረጃ አልጠየቅኩም፡፡ በመሆኑም በጉዳዩ ላይ የምሰጠው መረጃ የለም፤›› ብለዋል፡፡  

 

በካሩቱሪ ላይ ዕርምጃ ለመውሰድ ከኤጀንሲው አቅም በላይ ሆኗል

ሳዑዲ ስታር ግብርና ልማት ኩባንያ አንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት እንዲሰጠው፣ ለግብርና ሚኒስቴር አዲስ ጥያቄ ማቅረቡን መረጃዎች አመለከቱ፡፡ 

ሳዑዲ ስታር የመሬት ጥያቄውን ከሦስት ዓመት በፊት ያቀረበ ቢሆንም፣ ሚኒስቴሩ ቀደም ብሎ የወሰደውን መሬት ማልማት ባለመቻሉ፣ በፍጥነት ወደ ልማት እንዲገባ ማሳሰቢያ በመስጠት ጥያቄውን አልተቀበለም ነበር፡፡ ነገር ግን ሳዑዲ ስታር በዚህ የበጀት ዓመት ቀደም ሲል ከተሰጠው አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት ሰባት ሺሕ ሔክታሩን በማልማቱ፣ የተጨማሪ መሬት ጥያቄውን በድጋሚ ማቅረቡን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የሼክ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲ ግዙፍ የእርሻ ኩባንያ የሆነው ሳዑዲ ስታር፣ በጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት የተረከበው የሩዝ ልማት ለማካሄድ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ የኩባንያው የረጅም ጊዜ ዕቅድ በጋምቤላ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝና በአማራ ክልሎች እስከ 500 ሺሕ ሔክታር መሬት ድረስ ማልማት ነው፡፡

ኩባንያው ከዕቅዱ ውስጥ በአብዛኛው ልማት በጋምቤላ ክልል ማካሄድ እንደሚፈልግ የኩባንያው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በዚህ ዕቅድ መሠረት አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት በመረከብ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡

ሰፋፊ የገጠር መሬቶችን ከክልሎች በውክልና እየተረከበ የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ የግብርና ኢንቨስትመንትና መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ የሚመሩት አቶ አበራ ሙላት ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሳዑዲ ስታር በዚህ የበጀት ዓመት የተሻለ የሥራ አፈጻጸም አሳይቷል፡፡ ‹‹ከዚህ ቀደም የተሰጠውን አሥር ሺሕ ሔክታር መሬት ሳያለማ ተጨማሪ መሬት በመጠየቁ የቦታ ጥያቄው አልተስተናገደም፡፡ ነገር ግን ዘንድሮ ሰባት ሺሕ ሔክታር መሬት በማልማቱ የሳዑዲ ስታር ተጨማሪ መሬት ጥያቄ ሊታይ ይችላል፤›› በማለት አቶ አበራ ኩባንያው የጠየቀው መሬት ሊሰጠው እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ 

በ500 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመው ሳዑዲ ስታር፣ ከሦስት እስከ አምስት ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ በአሥር ዓመት ውስጥ በ500 ሺሕ ሔክታር መሬት ላይ ሩዝን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎችን የማልማት ዕቅድ እንዳለው ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን በተሰጠው መሬት ላይ የሚፈለገውን ልማት ባለማካሄዱ ምክንያት ዕቅዱ የይስሙላ ነው ተብሎ ሲተች ነበር፡፡

የሚያመርተውን ምርት ለአገር ውስጥ ገበያ ከማቅረብ ባሻገር በተለይ ለሳዑዲ ዓረቢያ ገበያ በስፋት እንደሚያቀርብ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ 80 ሚሊዮን ዶላር ወጭ በማድረግ ዘመናዊ የእርሻ መሣሪያዎች ገዝቶ ወደ ሥራ የገባው ሳዑዲ ስታር በቅርቡ የጠየቀው መሬት ሊሰጠው እንደሚችል የግብርና ሚኒስቴር ምንጮች ያስረዳሉ፡፡

በኢትዮጵያ ሰፋፊ እርሻ ውስጥ በመግባታቸው ድጋፍና ውግዘት ካስተናገዱ ኩባንያዎች መካከል ሳዑዲ ስታርና ካሩቱሪ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ አቶ አበራ እንዳሉት ሳዑዲ ስታርና ሌሎች የህንድ ኩባንያዎች አሁን በጥሩ ሁኔታ  ላይ የሚገኙ ቢሆንም፣ ካሩቱሪ ግን በችግር ውስጥ ይገኛል፡፡ 

አንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቦ ወደ ሥራ የገባው ካሩቱሪ እስካሁን ማልማት የቻለው 1,340 ሔክታር መሬት ብቻ መሆኑን አቶ አበራ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ኩባንያው የውስጥ ችግር ያለበት በመሆኑ መሬቱን ያለማል ብለን አንጠብቅም፡፡ መሬቱን በመንጠቅ ለሚያለማ አካል ማስተላለፍ ቢኖርብንም፣ በእኛ ደረጃ ዕርምጃ መውሰድ አንችልም፤›› በማለት የሚናገሩት አቶ አበራ ጉዳዩ በመንግሥት ደረጃ በሚወሰድ አቋም የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡

ካሩቱሪ ከአምስት ዓመት በፊት ከጋምቤላ ክልል 300 ሺሕ ሔክታር መሬት ተረክቦ ነበር፡፡ የክልሎችን ሰፋፊ መሬት የፌዴራል መንግሥት በውክልና ተረክቦ ማስተዳደር ሲጀምር ካሩቱሪ ይዞት ከነበረው መሬት ሁለት መቶ ሺሕ ሔክታር ተነጥቆ፣ አንድ መቶ ሺሕ ሔክታሩን እንዲያለማ ተወስኖ ነበር፡፡

ነገር ግን ከአንድ መቶ ሺሕ ሔክታር መሬቱም ቢሆን ማልማት የቻለው 1,340 ሔክታር ብቻ በመሆኑ፣ ለግብርና ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ተስፋ አስቆራጭ ሆኗል፡፡

ግብርና ሚኒስቴር ለ86 የአገር ውስጥና የውጭ ኩባንያዎች 2.3 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ሰጥቷል፡፡ ነገር ግን መልማት የቻለው 840 ሺሕ ሔክታር ብቻ በመሆኑ በዝቅተኛ የሥራ አፈጻጸም ተመዝግቧል፡፡  

ነገር ግን በቅርቡ በግብርና ፖሊሲ ላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረጉት የቴሌቪዥን ክርክር በውጭ ባለሀብቶች የግብርና ልማት ላይ የተጠየቁት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው፣ ‹‹የውጭ ባለሀብቶች የካፒታል እጥረታችንን በሚያቃልል፣ ቴክኖሎጂ በሚያሸጋግር፣ የገበያ ትስስር በሚፈጥር መንገድ እስከ 300,000 ሔክታር የሚደርስ መሬት ይዘው ለማልማት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡ 50 ሚሊዮን ሔክታር ገና የሚለማ መሬት አለን፤›› ብለዋል፡፡ በአገር ውስጥ ባለሀብቶች 2.2 ሚሊዮን ሔክታር መልማቱንም አክለዋል፡፡

 

መኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው የት እንደሚገኙ አላውቅም አለ

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ወደ ቢሮ አለመምጣታቸውን አስታወቀ፡፡ በአሁኑ ወቅት የት እንዳሉ አላውቅም ብሏል፡፡

በተለያዩ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ዘገባዎች ደግሞ የትጥቅ ትግል ለማድረግ ወደ ኤርትራ ማምራታቸው እየተነገረ ነው፡፡ በትክክል የት እንደሄዱ ግን አልተረጋገጠም፡፡

ካለፈው ሳምንት አጋማሽ ጀምሮ በፌስቡክ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ተስፋሁን አለምነህ የትጥቅ ትግል ለማድረግ ወደ ኤርትራ ሄደዋል የሚሉ ዘገባዎች የወጡ ቢሆንም፣ የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ ግን፣ ‹‹የት እንደሄደ አላውቅም፡፡ ጉዳዩን በተመለከተ ግን እንደ ማንኛውም ሰው በማኅበራዊ ድረ ገጽ አይቻለሁ፤›› በማለት ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ተስፋሁን ለመጨረሻ ጊዜ መኢአድ ቢሮ የታዩት ድርጅቱ ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ ለመካፈል ከሁለት ሳምንት በፊት ቅዳሜ እንደነበር ያስታወሱት አቶ አበባው፣ በመሀል የተፈጠረውን ነገርና ወዴት እንደሄዱ እንደማያውቁ ገልጸዋል፡፡

የፊታችን እሑድ በሚካሄደው አምስተኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ መኢአድን ወክለው እንደማይወዳደሩ የገለጹት አቶ አበባው፣ አቶ ተስፋሁን ፓርቲውን የተቀላቀሉት ከአሥር ዓመታት በፊት እንደነበረ አክለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ፓርቲውን የተቀላቀለው ከጐጃም ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ብሎ ደግሞ የምዕራብ ጐጃም የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ነበር፤›› ብለዋል፡፡ 

አቶ አበባው ‹‹የድርጅታዊ ጉዳይ አይደለም፡፡ የመኢአድ አባልነት መሥፈርት በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በዚህም መሠረት በፈቃደኝነት አባል ይሆናል፡፡ ለመውጣት ሲፈልግ ደግሞ ይለቃል እንጂ በግድ የሚያዝ ነገር የለም፤›› በማለት ውሳኔው ግለሰቡን ብቻ የሚመለከት እንደሆነና ከፓርቲው ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለው አስረድተዋል፡፡

አቶ ተስፋሁን በፓርቲ እንቅስቃሴ ውስጥ ጥሩ ተሳትፎ እንደነበራቸው ያስታወሱት አቶ አበባው፣ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በእንግሊዝኛ ቋንቋ መመረቃቸውንም አመልክተዋል፡፡

በኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት የተፈረጁ ድርጅቶች ኤርትራ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ፣ ከእነዚህ ድርጅቶች መካከል ግንቦት 7፣ ኦነግ እና ኦብነግ ነፍጥ አንግበው መንግሥትን ለመጣል አቅደው እንደሚሠሩ ይነገራል፡፡ 

በቅርቡ መንግሥት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ፣ ፍቅረ ማርያም አስማማውና እየሩሳሌም አስፋው ወደ ኤርትራ ሊገቡ ሲሉ በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸውና ክስ እንደመሠረተባቸው መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡  

አቶ ተስፋሁን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ የፕሮፋይል ፎቶአቸውን በመለወጥ ታጣፊ ክላሽኒኮቭ አንግተው የሚታዩ ሲሆን፣ ከሰላማዊው ትግል በመውጣት ለትጥቅ ትግል መዘጋጀታቸውን ማሳያ ነው እየተባለ ነው፡፡ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ከዚህ ቀደም የተለያዩ የፉከራና የሽለላ ግጥሞችን በማስፈር የሚታወቁት አቶ ተስፋሁን፣ ኤርትራ ወይም ሌላ ሥፍራ ለትጥቅ ትግል መሄዳቸውን ያረጋገጠ አካል የለም፡፡ 

 

ሚስቱ በይሆት ተያዘች ሚስቲቱ ሰውን በማዘዋወርና በመሽጥ አደኛ ስትሆን አቡ ስይፍ ደግሞ ሰውን ከመደል ውጭ ሌላ ሰራው ነዳጅን በመሽጥና ገንዘብ በማጠራቀም የታወቀ መሪ ነበር የአሜሪካ ኮማንዶ ሶሪያ ውስጥ ሰርጎ በመግባት አቡ ሰይፍን ሲገል ሚስቲቱን በይሆት ይዘዋታል (CNN) U.S. Special Operations forces killed a senior ISIS commander during a daring raid intended to capture him in […]