ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ከጎንዬሽ ጉዳዬች ውጪ ለ25ተኛ ጊዜ (በአጠቃላይ ለ27ተኛ ጊዜ) የተሰየመው ችሎት ዛሬም የደረጃ ምስክሮችን ሲያሰማ ውሏል፡። ከሳምነትት በፌት የተሰየመው ችሎት አቃቤ ህግ 41 ምስክሮች አሉኝ ነገር ግን ላገኛቸው ስላልቻልኩ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ቆይተው ተጨማሪ ማፈላለጊያ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ጠይቆ ለዛሬ የተቀጠረ ቢሆንም ዛሬም “የሽብር ተግባሩ “ ዋና ምስክሮች ባለመገኘታቸው ፍተሻ ላይ ተገኝተናል ያሉ አምስት ምስክሮች ተሰምተዋል፡። የምስክሮቸን ቁጥርም 35 ነው በማለት ቀይሮታል፡፡
ባለፈው የተሰሙት 13 ምስክሮች ሲሆኑ በዛሬው ችሎት ባልተካደ ነገር ላይ ሲመሰክሩ የዋሉት የደረጃ ምስክሮች
14ተኛ ምስክር ተወዳጅ ኃ/ማርያም ይባላሉ፡፡ እድሜያቸው 34 ሲሆን የመንግስት ሰራተኛ ናቸው፡፡ የምስክርነት ቃላቸውም ‹‹የመጣሁበት ኬዝ ግንቦት 7/2006 ዓ.ም በምኖርበት ልደታ 5ኛ አካባቢ የፌደራል ፖሊስ ታዛቢ ሁነኝ ብሎ ጠይቆኝ በታዛቢነት ያየሁትን ለመመስከር ነው፡፡ ማህሌት ጤና ጥበቃ ሚ/ር ትሰራለች መሰለኝ፣ እዚያ መስሪያ ቤት ፖሊስ ማህሌት ኮምፒውተርና ጠረጴዛ ላይ ያለውን ሲበረብር አይቻለሁ፡፡ መንግስት መስሪያ ቤት የምትጠቀምበት ኮምፒውተር ላይ የተገኙ ሰነዶች ላይ ማህሌት ስትፈርም እኛ ታዛቢዎችም ፈርመናል፡፡ የፈረምነው ግንቦት 7/2007 ዓ.ም ነበር፡፡ የገጹን ብዛት አሁን አላስታውስም፤ ወደ 40 ገጽ ይሆናል፡፡ እንግሊዝኛና አማርኛ ጽሁፎች አሉበት፡፡ የተወሰነ የፖለቲካ ይዘት የነበረው አለ፡፡ የፖለቲካ ፕሮግራም ማኒፌስቶ አይቻለሁ፡፡ ፖሊስ ማህሌትን ሲጠይቃት ከኦነግ የወጣው የሌንጮ ፓርቲ ፕሮግራም ነው ብላለች፡፡ ጎስፕ ንግግሮችም አሉ›› ብሏል፡፡ ዳኛው ጎሲፕ በአማርኛ ምንድነው ሲላቸው ምስክሩ ‹‹ሽሙጥ ንግግር ነው›› ብለው መልሰዋል፡፡ ምስክሩ የተገኙ ሰነዶች ላይ ፌደራል ፖሊስ ሄደው እንደፈረሙና ይሄን ያደረጉትም ግንቦት 9/2006 ዓ.ም ነው ብለዋል፡
15ተኛ ምስክር ፀሐይ ብርሃኔ እድሜያቸው 33 የሆኑ የመንግስት ሰራተኛ ናቸው፡፡ የምስክርነት ቃላቸውም ‹‹ግንቦት 7/2006 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፖሊስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አሳይቶ ቢሮ ሲፈተሽ ታዘብ ተብዬ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሲ.ዲ እና ዲክሜንት ሲወሰድ አይቻለሁ፡፡ ከዚያ ፖሊስ በ9/2006 ዓ.ም ሄጄ በሶፍት ኮፒ የነበሩት ሰነዶች ፕሪንት ተደርገው ማህሌት የፈረመችባቸው ላይ ፈርሜያለሁ፡፡ በእንግሊዝኛና አማርኛ የተጻፉ ናቸው፡፡ በግምት ወደ 40 ገጽ ይሆናል፡፡ አብዛኛው የፖለቲካ ነክ ጽሑፎች ናቸው፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጽሑፎች አሉበት፡፡ ያየናቸው መረጃዎች ከእሷ ኮምፒውተር ላይ ስለመገኘታቸው አይተን ፈርመናል፡፡››
ለእኒህ ምስክር መስቀለኛ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ነበር፡፡
የጠበቆቹ መስቀለኛ ጥያቄ፡- ሲዲውን ማን እንዳመጣው
ታውቃለህ…ውስጡ ምን ነበረበት…
የምስክሩ መልስ፡- እኛ ራሳችን ቼክ አድርገናል፤ ባዶ ሲ.ዲ ነው፡፡
ጥያቄ፡- የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ብለሃል….ስንት ናቸው
መልስ፡- አንድ ብቻ አይደሉም
ጥያቄ፡- የተለያዩ ፓርቲዎች ሰነዶች ብለዋል እኮ….እነዚህ ላይ ሁሉ ፈርመዋል
መልስ፡- አሁን በትክክል የማስታውሰው የሌንጮ ፓርቲ ሰነድ ላይ መፈረሜን ነው፡፡ ሌሎች ላይ አልፈረምኩም፡፡
(አንድ ሰነድ ቀርቦላቸው ፊርማው የእሳቸው ስለመሆኑ እንዲለዩ ተደርገው የእሳቸው መሆኑን አረጋግጠው የፈረሙበትን ሰነድ ይዘት ግን እንደማያውቁ አስረድተዋል፡፡)
ፍርድ ቤቱ ‹‹40 ገጽ ማየትህን ተናግረሃል፤ 40 ገጽ ላይ ፍርመሃል፣ ይዘቱንስ ታውቃለህ›› ብሎ ጠይቋቸው ምስክሩ ‹‹እያንዳንዱ ሰነድ ላይ ፍረሜያለሁ፤ ግን አላነበብኩትም፡፡ ክፍት የስራ ማስታወቂያ የሚል ግን አይቻለሁ›› ብለዋል፡፡ በተለየ የትኛውን ነው ያነበብከው ለተባሉት ደግሞ ‹‹አሁን አላስታውስም፤ የሌንጮ ሰነድ ላይ ፈርሜያለሁ፡፡ ማህሌት ፖሊስ ሲጠይቃት ሌንጮ የራሳቸውን አዲስ ፓርቲ እያቋቋሙ እንደሆነ ስትናገር ሰምቻለሁ›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡
16ተኛ ምስክር ዳግማዊ እንዳለ 25 ዓመታቸው ሲሆን የመንግስት ሰራተኛና የአ.አ ከተማ የካ ክ/ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ በ5ኛ ተከሳሽ አጥናፍ ላይ ለመመስከር እንደመጡ ተናግረው የአባቱን ስም አላስታውስም ብለዋል፡፡
“ሚያዝያ 17/2006 ዓ.ም 11፡00 ገደማ ከስራ ወደ ቤት ስሄድ 22 ትራፊክ ፖሊስ ጀርባ ፌደራል ፖሊስ የፍርድ ቤት ወረቀት አሳይቶ ታዛቢ ሁነኝ ብሎኝ ተገኝቻለሁ፡፡ አጥናፍ ቤት ገብተን ሰነዶች ሲገኙ አይቻለሁ፡፡ ፍላሽ፣ ሴኪዩሪቲ ኢን ኤ ቦክስ የሚል መጽሐፍ፣ ሲ.ዲ ተገኝተዋል፡፡ ሌሎች ታዛቢዎችም ነበሩ፡፡ ሰነዶቹ ላይ አጥናፍ ሲፈርም እኛም ፈርመናል፡፡›› ብለዋል፡፡
17ኛ ምስክር፡- ሳምሶን ሲሳይ ይባላሉ፤ 29 ዓመታቸው ሲሆን በግል ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡ አድራሻቸው አ.አ የካ ክ/ከተማ ነው፡፡ አጥናፍ ላይ ለመመስከር መምጣታቸውን ተናግረዋል ‹‹ሚያዝያ 17/2006 ዓ.ም 11፡00 አካባቢ ትራፊክ ጽ/ቤት ጀርባ ፖሊሶች ታዘብልን ስላሉኝ ታዝቤያለሁ፡፡ ሲ.ዲ፣ ፍላሽ፣ የተለያዩ ዶክሜንቶች፣ ላፕቶፕ፣ ማስታወሻ ደብተሮች መገኘታቸውን አይቻለሁ፡፡ በዝርዝር አላስታውስም፡፡ ግን 150 አካባቢ መጽሐፍ ቆጥረናል፡፡ ፋክት መጽሔት ተገኝቷል፡፡ መጽሐፎቹ በእንግሊዝኛና አማርኛ የተጻፉ ናቸው፡፡ አጥናፍ የፈረመባቸው ላይ እኛም ፈርመናል፡፡›› ብለዋል፡፡
18ኛ ምስክር፡- እኒህ ምስክር ደግሞ በረከት ብርሃኔ የሚባሉ ሲሆን እድሜያው 29 ነው፡፡ በግል ስራ ላይ የተሰማሩና የአ.አ አራዳ ክ/ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ 6ኛ ተከሳሽ ዘላለም ላይ ለመመስከር እንደመጡ በመግለጽ ዘላለምን በአካል ለይተው አሳይተዋል፡፡ ‹‹ግንቦት 16/2006 ዓ.ም ማዕከላዊ ለግል ጉዳይ ሄጄ ፖሊስ በጠየቀኝ መሰረት ታዝቤያለሁ፡፡ ሰነዶች ልናይ ስለሆነ እይልን አሉኝ፡፡ እሺ ብዬ ወደ ቢሮ ገባሁ፡፡ ከቀኑ 8፡00 ይሆናል፡፡ እኛ ከገባን በኋላ ዘላለም ተጠርቶ መጣ፡፡ ላፕቶፑን ራሱ ፓስወርዱን ከፈተው፡፡ ከዚያ ከላፕቶፑ የወጡ ሰነዶች ፕሪንት ተደርገው ፈረምንባቸው፡፡ እንግሊዝኛም አማርኛም ነበር፡፡ ደሞ ምሳ ተጋብዘናል፡፡ ዘላለም ብላ ሲባል አልበላም አለ፡፡ አሁን ሰነዶቹ ምን እንደሆኑ አላውቅም፡፡ ዘላለም የፈረመበት ላይ ነው እኔ የፈረምኩት፡፡ ለማንበብ ግን ጊዜ አልነበረኝም፡፡ ስለዚህ ይዘቱን አላውቀውም፤ እሱ የፈረመበት ስለሆነ ብቻ ፈርሜያለሁ፡፡ አልፈርምም ያለው ሰነድ አልነበረም፡፡ ሌሎች ታዛቢዎችም ነበሩ፡፡ እነሱም ፈርመዋል›› ብለዋል፡፡
ምስክሮች ከመሰማታቸው አስቀድሞ አቃቤ ህግ ባለፈው የተሰጠው ቀጠሮ አጭር በመሆኑ ሌሎቹን ምሰክሮች ለማግኘት ረዘም ያለ ጊዜ ቀጠሮ አንዲሰጠው አንዲሁም አስመዝግቤያለው ካላቸው ሲዲዊች ውስጥ 7ቱ አንዲሰሙለት የጠየቀ ሲሆን የቀሩት ግን ሲዲውን የያዘው ባለሞያ ከአገር ውጪ በመሆኑ ማቅረብ አልቻልንም ብሏል፡፡ የተከሳሾች ጠበቆች ተከሳሾች ከታሰሩ አንድ አመት ሊሞላ ጥቂት አንደቀረ ምስክሮቸን ማዘጋጀት ቀደም ብሎ መሰራት የነበረበት የአቃቤ ህግ ስራ መሆኑን ነገር ግን በተደጋጋሚ እድል እየተሰጠው አንዳልተጠቀመበት በመጥቀስ ዛሬ የቀረቡት የሰው ምስክሮች መጨረሻ አንዲሆኑ እና የቀሩ ማስረጃዎቸን ለመስማት አጭር ቀጠሮ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ “ፍርድ ቤቱ” የአቃቤ ህግን ክርክር በመደገፍ የሚቀጥለውን ቀጠሮ ከአንድ ወር በላይ በማራዘም ግንቦት 18-21 2007 አም ድረስ እንዲሆን አንዲሁም የሲዲ ማስረጃዎቹ በወቅቱ ተሟልተው አንዲቀርቡና ቀሪ ምስክሮቹም በዚያው ቀን ወስኖ ችሎቱ ተጠናቋል፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
አንደሁልጊዜው ሁሉ የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ክስ ፓለቲካዊ ነው ያልተሰራ ወንጀል ምስክር አይገኝለትምና ፈጣን ፍትህን የማግኘት መብትን መቀለጃ ላደረገው ፍርድ ቤትም ሆነ የመንግስት ስራ አስፈጻሚ ጓደኞቻችንን ለመፍታት አሁንም ጊዜው አልረፈደም የሚለውን መልእክት ለማስተላለፍ አንወዳለን፡፡

መጋቢት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለስልጣኖቹ በባህርዳር ከተማ በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ የተመላሽ ሰራዊት አባላትን ሰብስበው ስርአቱ አደጋ ውስጥ በመግባቱ እንዲታደጉት ጥሪ ቀርቦላቸዋል። ከምርጫው ጋር ተያይዞ ልማቱን ለማስቀጠል አደጋ ውስጥ ገብተናል ያሉት ባለስልጣናቱ፣ የተቀናሽ ሰራዊት አባላት በምርጫው ንቁ ተሳተፎ በማድረግ ስርአቱን እንዲታደጉ ተማጽነዋል። የሰራዊቱ አባላት “የቦታ ባለቤት እናደርጋችሁዋለን” ተብሎ ቃል የተገባላቸው ሲሆን፣ የፊታችን ቅዳሜ  …

መጋቢት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ9 ፓርቲዎች ትብብር ስር የሚንቀሳቀሰው የከምባታ ህዝቦች ኮንግረስ  ሊ/መንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርዴሎ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ ወደ ትውልድ ቀያቸው አንገቻ ወረዳ ቢያቀኑም፣ የወረዳው አመራሮች ከፍተኛ ችግር እንደፈጠሩባቸው ለኢሳት ተናግረዋል። ወደ ወረዳው በመሄድ የምርጫ ፖስተሮችን ሲለጥፉ እንደተቀደደባቸው፣ የተከራዩትን ቤት እንዲለቁ መገደዳቸውን የገለጹት አቶ ኤርጫፎ ይባስ ብሎ ከተማው ውስጥ ሆቴል ለመያዝ …

የየመንን ዋና ከተማ ሰንአን በመቆጣጠር ሁለተኛዋን ታላቋን ከተማ ኤደንን ለመቆጣጠር ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በመፋለም ላይ የሚገኙት የሃውቲ ሚሊሺያዎች፣ ከሳውድ አረቢያ የሚደርስባቸውን የአየር ጥቃት ተቋቁመው ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር መቃረባቸውን መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ነው። አማጽያኑ በሚደርስባቸው የአየር ጥቃት ሳይበገሩ፣ የቀድሞውን ፕሬዚዳንት ታማኝ ወታደሮች በመፋለም ላይ ናቸው።አሜሪካ ለሳውድ አረቢያ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን በማቅረብ ላይ መሆኗን ገልጻለች። ኢራን በበኩሉዋ …

ፒያሳ አካባቢ ያየነው ትንሽ ለየት ይላል፡፡ መርካቶን አሊያም ከዛም አለፍ ያሉትን የአዲስ አበባ ክፍሎች በቁጥጥር ስራቸው አውለው ወደ አራት ኪሎ እየገሰገሱ የሚመስሉ ፈርጣማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፒያሳ ላይ ገዥ መሬት ይዘዋል፡፡ መኪና አይቀርባቸውም እንጅ መኪና መንገዱን ግማሹን እነሱ እየተንፈላሰሱበት ነው፡፡ ተቆጣጥረውታል! ደግሞ ኮዳና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሳቸውን ግጥም አድርገው ታጥቀዋል፡፡ አንድ ሁለት እርምጃ እንዳለፉ የሚተኩሱ በሚመስል ሁኔታ መሳሪያቸውን ዘቅዝቀው ይዘውታል፡፡ በተጠንቀቅ! በቃ ፒያሳን የጦር ቀጠና አስመስለዋታል፡፡

ከሶስቱ መካከል አንዱ የሁለቱን ደህንነት ለመጠበቅ በሚመስል መልኩ ወደኋላ ይቀራል፡፡ ሰውንም፣ ወርቅ ቤቶቹንም፣ መኪናዎችንም ዘወር ዘወር ብሎ ያያል፡፡ እንደገና ፈጠን ፈጠን ብሎ ይቀላቀላቸውና በአንድ ላይ ወደቀኝና ግራ እያማተሩ መሳሪያቸውን ዘቅዝቀው ይነጉዳሉ፡፡

ሌላ ሶስት አባላት ያሉት ‹‹ጋንታ›› ይከተላል፡፡ እነዚህም በተመሳሳይ ሶማሊያ አሊያም ኤርትራ ድንበር ያሉ ነው የሚመስሉት፡፡ ቀኝና ግራ፣ ወደኋና ወደፊት ይቅበዘበዛሉ፡፡ የቆሙ መኪናዎችን ጠጋ ብለው ያያሉ፡፡ አላፊ አግዳሚው ላይ ያፈጣሉ፡፡ ከእነሱ በኋላ ደግሞ ጯፉ እሳት የተቆሰቀሰበት የሚመስለውን ዱላ ከአጋማሹ ላይ የያዙ አራት ‹‹ተራ አስከባሪዎች›› (ካልሲ አባራሪዎች) ይከተሏቸዋል፡፡ ደጀን ጦር መሆናቸውን ነው፡፡
በዛሬው እለት Getachew Shiferaw አዲስ አበባን እንዲህ ቃኛት::
ማሳሰቢያ፡- አብረውኝ ከነበሩት ሁለት ጓደኞቼ ጋር ፎቶ የማንሳት ፅኑ ፍላጎት የነበረን ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች ፎቶ ማንሳት ሳይቻለን ቀርቷል!
Image

በእስራኤል ፓርላማ ሲገቡ የመጀመሪዋ ሴት ትውልደ ኢትዮጵዊት አይሁድ የሆኑት የሽአዲስ ታመኑ ሽታ ዘረኝነትን እንደሚዋጉ ተናገሩ፡፡ ሴትየዋ ባገባደድነው ወር በእስራኤል ተካሂዶ በነበረው የፓርላማ ምርጫ በጥቂት ድምጾች ተሸንፈው ከፓርላማ እንደራሴነት ውጪ ቢሆኑም እንኳን ዘረኝነትን በየትም ቦታ ሆነው ለመዋጋት ነው ቃል የገቡት፡፡ የምሰራው ብዙ ስራ አለኝ ያሉት ወይዘሮዋ “የኔና የወገኖቼ የፊት ገጽ በዘረኝነት ወላፈን በሚገረፍበት ሀገር ውስጥ መኖር […]

The post ኢትዮጵያዊቷ አይሁድ በእስራኤል የሰፈነውን ዘረኝነት እዋጋለሁ አሉ appeared first on ሳተናው .

ኅዳሴ ግድብን የቴክኒክ ጥናት ሂደት እንዲመራ የተሰየመው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የጋራ ኮሚቴ ዛሬና ነገን (ረቡዕና ሐሙስ) ለሚዘልቅ ስብሰባ አዲስ አበባ ላይ ተቀምጧል፡፡ ኮሚቴው በዚህ አምስተኛ ስብሰባው ወቅት የቴክኒክ ጥናቱን የሚያካሂድ ዓለምአቀፍ ድርጅት ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በስብሰባው ላይ የሦስቱ ሃገሮች የውኃ፣ ኢነርጂና መስኖ ጉዳዮች ሚኒስትሮች፣ ኤክስፐርቶች፣ የዲፕሎማሲ ባለሙያዎችና ሌሎችም እየተሣተፉ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የድርጅቱ ምርጫ የሚካሄደው ቀደም ሲል […]

The post ለኅዳሴ ግድብ ዓለምአቀፍ የቴክኒክ አማካሪ ድርጅት ለመምረጥ ሃገሮቹ ስብሰባ ተቀምጠዋል – VOA appeared first on ሳተናው .

 

የኅዳሴ ግድብን የቴክኒክ ጥናት ሂደት እንዲመራ የተሰየመው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የጋራ ኮሚቴ ዛሬና ነገን (ረቡዕና ሐሙስ) ለሚዘልቅ ስብሰባ አዲስ አበባ ላይ ተቀምጧል፡፡

ኮሚቴው በዚህ አምስተኛ ስብሰባው ወቅት የቴክኒክ ጥናቱን የሚያካሂድ ዓለምአቀፍ ድርጅት ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በስብሰባው ላይ የሦስቱ ሃገሮች የውኃ፣ ኢነርጂና መስኖ ጉዳዮች ሚኒስትሮች፣ ኤክስፐርቶች፣ የዲፕሎማሲ ባለሙያዎችና ሌሎችም እየተሣተፉ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የድርጅቱ ምርጫ የሚካሄደው ቀደም ሲል በመጣ አጭር ዝርዝር ላይ ከቀሩ አራት አማካሪ ኩባንያዎች መካከል መሆኑንና መራጮቹ የሚመለከቱት የቴክኒክና የበጀት ሰነዶችን እንደሚሆን የምሥራቅ ናይል ተፋሰስ ዞን ፅ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈቅአሕመድ ነጋሽ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

ከአቶ…

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ከጎንዬሽ ጉዳዬች ውጪ ለ25ተኛ ጊዜ (በአጠቃላይ ለ27ተኛ ጊዜ) የተሰየመው ችሎት ዛሬም የደረጃ ምስክሮችን ሲያሰማ ውሏል፡። ከሳምነትት በፌት የተሰየመው ችሎት አቃቤ ህግ 41 ምስክሮች አሉኝ ነገር ግን ላገኛቸው ስላልቻልኩ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ቆይተው ተጨማሪ ማፈላለጊያ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ጠይቆ ለዛሬ የተቀጠረ ቢሆንም ዛሬም “የሽብር ተግባሩ “ ዋና ምስክሮች ባለመገኘታቸው ፍተሻ ላይ ተገኝተናል […]

The post ” ምስክር ፈላጊው ችሎት ” – 27ተኛ የፍርድ ቤት ውሎ -የዞን9 ማስታወሻ appeared first on ሳተናው .

ፍቅር ለይኩን

ጎልጎታ Golgota by Geberekirstos Desta
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሳምንቱ ሰሙነ ሕማማት በሚል ሲጠራ የዛሬዋ ዕለት አርብ ደግሞ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መከራው፣ ሕማሙና ስቅለቱ በፍቅርና በትሕትና የሚታሰብበትና በተለያዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓቶች የሚዘከርበት ታላቅ ዕለት ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንቶች ዘንድ “ደረቅ ሐዲስን ተናጋሪ” ተብሎ የሚጠራው ነቢዩ ኢሳይያስ አስቀድሞ በትንቢቱ፡-

ሙሉውን አስነብበኝ …

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ከጎንዬሽ ጉዳዬች ውጪ ለ25ተኛ ጊዜ (በአጠቃላይ ለ27ተኛ ጊዜ) የተሰየመው ችሎት ዛሬም የደረጃ ምስክሮችን ሲያሰማ ውሏል፡። ከሳምነትት በፌት የተሰየመው ችሎት አቃቤ ህግ 41 ምስክሮች አሉኝ ነገር ግን ላገኛቸው ስላልቻልኩ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ቆይተው ተጨማሪ ማፈላለጊያ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ጠይቆ ለዛሬ የተቀጠረ ቢሆንም ዛሬም “የሽብር ተግባሩ “ ዋና ምስክሮች ባለመገኘታቸው ፍተሻ ላይ ተገኝተናል […]

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ “ግድቡን መገንባት ወይም ደግሞ እርግፍ አድርጎ መተው” የሚለው የመለስ ጥያቄ ነበር፡፡ ከዛሬ አራት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2/2011 አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ በምዕራብ ኢትዮጵያ በሚገኘው ቤንሻንጉል ጉሙዝ እየተባለ በሚጠራው “ክልል” ልዩ ስሙ ጉባ በሚባለው ቦታ በመገኘት በዚያን ወቅት የሚሊኒየሙ ግድብ/Millennium Dam እያለ ይጠራው የነበረውን እና እንደገና በኋላ ደግሞ በደቀ መዛሙርቶቹ አማካይነት […]

The post የመለስ ግድብ ሕዳሴ ከንቱ ዉዳሴ? – ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም appeared first on ሳተናው .

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሰው ለምን በአይሮፕላን መብረርን ይፈራል? በእንግሊዝኛ «አቪፎቢያ» ወይም «ኤይሮፎቢያ» የሚባለው ለምን ያድርበታል? ከሚነቀሳቀስበት የብስ ራቅ ባለና አንዳች ሊቆጣጠረው ፣ ሊይዘው- ሊጨብጠው በማይችልበት ሁኔታ ስለሚገኝ? ሰው በሠራው የሥነ ቴክኒክ

(በቴክኖሎጅስት ዳንኤል አማረ)
ምግብ ከተመገቡ በኃላ በፍጽም ሊያደርጓቸው የማይገቡ ተግባሮች

1. ትኩስ ሻይ መውሰድ

ሻይ የበላነውን ምግብ እንዳይዋሀድ ያደርጋል። ሻይ በውስጡ ያለው ቁስ ነገር ብረት(iron) የተሰኝውን ንጥረ ነገር ከሰውነታችን ውስጥ በማስወገድ ለብረት እጥረት እና ለደም ማነስ ችግር ያጋልጣል። በተጨማሪም ሻይ (Tannin) የ

በምዕራብ አፍሪቃ ባለፈው ዓመት የተከሰተውን የኤቦላ ወረርሽኝ ለመታገል ዓ/አቀፉ ማህበረሰብ የወሰደው ርምጃ ንዑስና አዝጋሚ ነበር ሲሉ የርዳታ ድርጅቶች ወቀሳ ሰንዝረዋል። ተላላፊ በሽታ በሚከሰትበት ጊዜ ተመሳሳይ ዝግመት እንዳይታይም፣ የጀርመን መንግሥት አስቸኳይ የህክምና ርዳታ የሚሰጥ ሁሌ ዝግጁ የሚሆን የጦር ግብረ ኃይል ለማቋቋም አቅዷል።

ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም በነዚህ እጩዎች ላይ የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ ከእጩነት ቢያገላቸውም ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስዶ እንዲወዳደሩ እንደተበየነለት ሰማያዊ ፓርቲ አስታውቋል ።

የማምነው ነገር፣ የሀገሪቷ ችግር ሲፈታ፤ እስክንድርም አብሮ እንደሚፈታ ነው”

የስደት ህይወት ሁሉንም ነገር ከዜሮ ያስጀምርሃል

የእስክንድር ፅናት እና ብርታት ከፈጣሪ የተሰጠው ፀጋ አድርጌ እመለከተዋለሁ

በሀገራችን ጉዳይ ላይ ለመሳተፍ የግድ ፖለቲከኛ መሆን አይጠበቅብንም” ሰርካለም ፋሲል (ጋዜጠኛ)

Eskinder Nega, Serkalem Fasil and Nafkot Eskinder
በአንባቢያን ዘንድ ታዋቂ የነበሩት “አስኳል”፣ “ሚኒሊክ”ና “ሳተናው” ጋዜጦች አንዷ አሳታሚ ነበረች። የ97 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረ ግርግር ለእስር ከተዳረጉት ጋዜጠኞች እና አሳታሚዎች መካከልም አንዷ ነች – ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል። በሀገራችን የግል ፕሬስን በመጀመር ፈር ቀዳጅ የሆነው የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ሰርካለም ልጃቸው ናፍቆትን የወለደችው በቃሊቲ እስር ቤት መሆኑ ይታወቃል። 

ሙሉውን አስነብበኝ …

‹‹የማምነው ነገር፣ የሀገሪቷ ችግር ሲፈታ፤ እስክንድርም አብሮ እንደሚፈታ ነው›

‹‹የስደት ህይወት ሁሉንም ነገር ከዜሮ ያስጀምርሃል››

‹‹የእስክንድር ፅናት እና ብርታት ከፈጣሪ የተሰጠው ፀጋ አድርጌ እመለከተዋለሁ››

‹‹በሀገራችን ጉዳይ ላይ ለመሳተፍ የግድ ፖለቲከኛ መሆን አይጠበቅብንም››
ሰርካለም ፋሲል (ጋዜጠኛ)
—————–
በአንባቢያን ዘንድ ታዋቂ የነበሩት ‹‹አስኳል››፣ ‹‹ሚኒሊክ‹‹ና ‹‹ሳተናው›› ጋዜጦች አንዷ አሳታሚ ነበረች፡፡ የ97 ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረ ግርግር ለእስር ከተዳረጉት ጋዜጠኞች እና አሳታሚዎች መካከልም አንዷ ነች – ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል፡፡ በሀገራችን የግል ፕሬስን በመጀመር ፈር ቀዳጅ የሆነው የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ሰርካለም ልጃቸው ናፍቆትን የወለደችው በቃሊቲ እስር ቤት መሆኑ ይታወቃል፡፡ index.jpg
ከእስር ከተለቀቁም በኋላ እስክንድር የጋዜጣ ፍቃድ ቢከለከልም ሀገሬን ጥዬ አልመሄድም በሚል አቋሙ በመጽናቱ ጽሑፎቹን በተለያዩ በውጭ ሀገር ባሉ ድረ-ገጾች ላይ ማቅረብ ቀጠለ፡፡ በሀገር ውስጥ የግል ጋዜጦች ላይም ቃለ-ምልልስ በማድረግ የግል ሀሳቡን በድፍረት በማቅረብ ላይ ሳለ ነበር በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥሮ መስከረም 03 ቀን 2004 ዓ.ም ለእስር የተዳረገው፡፡ በፍርድ ሂደትም 18 ዓመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ በዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ ውስጥ ባለቤቱ ሰርካለም ከጎኑ ነበረች፡፡
ሰርካለም በአሁኑ ወቅት በስደት አሜሪካ ሀገር ትገኛለች፡፡ የዚህ ሳምንት የ‹‹ፍቱን›› እንግዳ የሆነችው እ.አ.አ በ2007 ዓ.ም ከዓለምአቀፍ የሴቶች ሚዲያ ፋውንዴሽን “Courage in Journalism Award” የሚል ሽልማት ካገኘች በኋላ የሽልማት ገንዘቡን ለአምነስቲ ኢንተርሽናል ተቋም ድጋፍ እንዲውል ያደረገችው ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ነች፡፡ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የተወሰኑ ጥያቄዎችን (ስደትን፣ እስክንድርን፣ ልጃቸው ናፍቆትን በተመለከተ) በማንሳት እንዲህ አነጋግሯታል፡፡

በቅድሚያ ለቃለ-መልልሱ ፈቃደኛ በመሆንሽ በ‹‹ፍቱን›› መጽሔት ስም እናመሰግናለን፡፡
——

እኔም ለቃለ-ምልልሱ ዕድሉን ስለሰጣችሁኝ በአንባቢዎቻችሁ እና በራሴ ሥም አመሰግናለሁ።

ሰርካለም፣ ከሀገር ከወጣሽ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ? ለምን እንደወጣሽም በአጭሩ ንገሪን?
—————

ከሀገር ከወጣሁ አንድ ዓመት ከስድስት ወር አካባቢ ሆኖኛል። ከሀገር የወጣሁትም በግሌ ወስኜ ሳይሆን፣ ከእስክንድር ጋር ለረጅም ጊዜ ተነጋግረንበት፣ በጋራ በደረስነው ውሳኔ መሰረት ከሀገር ልወጣ ችያለሁ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ፣ ማንም እንደሚያውቀው ልጃችን ናፍቆት የተወለደው እኔ እስር ውስጥ ሆኜ ነው። በ1998 ዓ.ም የአንድ ወር ተኩል ነብሰ ጡር ሆኜ ነበር የታሰርኩት። የወለድኩትን ልጅ ማቀፍም ሆነ ማጥባት ሳልችል ነው ከልጄ ጋር የተለያየሁት። ከእስር ስንፈታ፣ ልጃችን አንድ ዓመት ሊሆነው የአንድ ወር ዕድሜ ሲቀረው ነበር ዳግም የተገናኘነው። በአጠቃላይ የልጃችን ታሪክ ከእስር እና ከመከራ ጋር የተያያዘ ነው። በአሁኑ ሰዓት ካለአንዳች ወንጀል፣ በሀሰት ክስ እስክንድር በግፍ 18 ዓመት ተፈርዶበት ቃሊቲ ይገኛል። ትላንት ቃሊቲ የተወለደው ናፍቆት ዛሬ ነብስ አውቆ፣ የልጅነት መቦረቂያ ጊዜውን አባቱ ጋር እየተመላለሰ ማሳለፍ ዕጣ ፈንታው ሆኖ ነበር። እስክንድርም ከእስሩ በላይ የልጁ መንከራተትና ስቃይ በየዕለቱ እረፍት እንደነሳው በተደጋጋሚ ይገልጽልኝ ነበር። ከዚህም ባሻገር ‹‹ይህ ህፃን ጥላቻ ይዞ ማደግ የለበትም፣ ቂም ይዞ ማደግ የለበትም›› በሚል መነሻ ናፍቆትን ይዤ ከሀገር ለመውጣት ተገድጃለሁ።

የስደት ሕይወትን እንዴት አገኘሽው?
————–

የስደትን ህይወት እንዲህ በቀላሉ መግለጽ እቸገራለሁ። የስደት ህይወት ሁሉንም ነገር ከዜሮ ያስጀምርሃል። የእውነት ሀገርህ የሚናፍቅህ፣ የእውነት መንደርህ የሚናፍቀው በስደት ዓለም ውስጥ ነው፤ በተለይ እንደእኔ በማኅበራዊ ህይወት ትስስር ቁርኝት ላደገ ሰው።
አሜሪካ በርህን ዘግተህ ጎረቤት አታውቅ፣ ጎረቤትህ አያውቅህ፣ መንገድ ላይ ረጅም መንገድ ብቻህን ብትሄድ አንድም ሰው ላታይ በምትችልበት ሀገር፣ ራስን ከዚያ ጋር ማላመዱ ትንሽ ያስቸግራል። ሀገርህ ላይ ያለው ማኅበራዊ ህይወት ቢናፍቅህም፣ በሌላ ጎኑ ያለው ነፃነት ደግሞ እጅግ ያሥገርማል። የሰውን መብት እስካልነካህ፣ ያሻህን ብትሆን ቀና ብሎ የሚመለከትህ እና የሚያስፈራራህ አንዳችም ሀይል የለም። ‹‹ስጋት ውስጥ ይጥለኛል›› ብለህ የምትጠነቀቀው ወይም የምታስበው አይኖርም። አሜሪካ የሁሉም ነች፡፡ ሁሉም እኩል ይስተናገድበታል። ሁሉም እኩል መብት አለው። …ይህ ግን የሥደትን ህይወት ጣፋጭ አያደርገውም። …ከነምናምኗ ሀገርን የመሰለ ምንም ነገር የለም።

ባለቤትሽ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በሽብርተኝነት ወንጀል 18 ዓመት ተፈርዶበት በቃሊቲ እስር ቤት ይገኛል፡፡ አንቺም ከማዕከላዊ እስከ ቃሊቲ በነበረው እስሩ በጥየቃ አብረሽው ነበርሽ፡፡ አሁን ከልጃችሁ ናፍቆት ጋር በአሜሪካ ቨርጂኒያ ትገኛላችሁ፡፡ ባለቤትን ከጎን አጥቶ ሕይወትን መኖር እና ልጅን ለብቻ ማሳደግ እጅግ ከባድ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እስኪ በዚህ ጉዳይ ላይ ያለሽን ስሜት አጋሪን?
—————————-

እስክንድር “አሸባሪ” የሚል የሀሰት ታርጋ ተለጥፎበት ከታሰረ አራት ዓመት ሊሞላው ትንሽ ወራቶች ይቀሩታል። እስክንድር ሀገሩን እና ወገኑን የሚወድ ኢትዮጵያዊ እንጂ፣ ተሸባሪዎቹ እንደሚገልጹት “አሸባሪ” ወይም ህዝብና ሀገርን የሚጎዳ አንዳችም ነገር አድርጎ እንደማያውቅ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን፣ እነጆን ኬሪ በአደባባይ የመሰከሩለት ሀቅ ነው። የኢህአዴግ መንግሥት በግፍ፣ ማዕከላዊ ውስጥ (ለጊዜው ስማቸው ይቆየን) በሃላፊዎች ደረጃ ንፅህናው እየተነገረው ግን ‹‹ከአቅማችን በላይ ነው››፣ ‹‹ይታሰር ተብሏል፣ ትዕዛዝ ነው›› እየተባለ የታሰረ የግፍ እሥረኛ ነው። እስክንድር ላመነበት ነገር የሚያስከፍለውን ሁሉ ለመቀበል የተዘጋጀ ጠንካራ ሰው በመሆኑ፣ እኔም ለብቻዬ ልጃችንን ለማሳደግ በብዙ ማይልሶች ርቀት ላይ ብገኝም፣ ከሁለታችንም በኩል ጥንካሬ ብቻ እንደሚጠበቅብን አምናለሁ። በተለይ የእኛ ጥንካሬ፣ ለእስክንድር ሞራል እንደሚሆነው ስለማውቅ ልጅን ለብቻ ማሳደጉንም ሆነ ተለያይቶ በመኖሩ ጊዜያዊ አድርጌ ነው የምቆጥረው። ደግሞም እግዚያብሄር ይችላል!

በስደት ዓለም ሆናችሁ፣ ሰዎች ስለእስክንድር እና ስለእናንተ ያላቸው ያላቸው ቦታ …
————————-
….ከእኔ ልጀምር፣ ‹‹በእጅ የያዙት ወርቅ እንደመዳብ ነው›› ይላል የሀገሬ ሰው። እስክንድር በውጪ ዓለም በዚህ ደረጃ አድናቂ እና ተከታይ እንዳለው በጭራሽ አላውቅም። በተጓዝንበት ሥፍራ ሁሉ፣ ለእስክንድር ያላቸውን ክብር የሚገልጹ ሥደተኛ ወገኖቼ፣ ለእኔ እና ለናፍቆት የተለየ እንክብካቤና ፍቅር እያደረጉልን ይገኛሉ። ሁልጊዜ አዲስ ነው የምንሆንባቸው።

እስክንድር በእስር ላይም ሆኖ፣ መንፈሰ ጠንካራነቱ ወደር አይገኝለትም፡፡ ጠያቂ ሊያበረታታው ሄዶ ጠያቂውን አበረታቶ የሚመልስ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ስለእስክንድር የዓላማ ጽናት፣ ውስጣዊ ጥንካሬና ብርታት እሱን ለምታውቂው አንጻር ይህ ብትታቱ እነና ጽናቱ ከምን የመነጨ ነው?
———————-
የእስክንድር ፅናትና ብርታት ከምን የመነጨ እንደሆነ ለመግለፅ፣ ለመናገር ከቃላት በላይ ነው። በአጭሩ ማለት የምችለው፣ ከላይ (ከፈጣሪ) የተሰጠው ፀጋ አድርጌ ነው የምመለከተው። ምክንያቱም የሰው ልጅ የሆነ ቦታ ላይ ሲደክመው ወይም ተስፋ ሊቆርጥ ይችላል። እስክንድር ግን ብዙ መከራና ግፍ፣ እንግልት፣ በየጊዜው ቢደርስበትም፣ ለአንዲትም ቀን ‹‹አሁንስ ደከመኝ›› የሚል ነገር አስቦ አያውቅም። አካላዊ ስጋው ቢጎዳም መንፈሱ ግን ሁልጊዜ አዲስ፣ ሁልጊዜ ጠንካራ፣ ከራሱ አልፎ ሌላውን የሚያበረታታ ምርጥ የኢትዮጵያ ልጅ ነው። የእሱ መከራ መቀበል ከቆመለት ዓላማ ትንሽም እንደማያነቃንቀው በተግባር ያሳየ የዘመኑ ጀግና ነው። ሞራሉን ለመግደል በሀሰት ተወንጅሎ 18 ዓመት ቢፈረድበትም፣ ‹‹ለዴሞክራሲ መከፈል ያለበት ዋጋ ነው›› ብሎ ውስጡ ፀፀት እንደሌለበት አውቃለሁ። ውስጡ ትልቅ ሰላም እንዳለውም አውቃለሁ። ላመነበት ነገር የሚከፍለው ዋጋ ጥንካሬ እንጂ፣ ቁጭትን እንደማይፈጥርበት አውቃለሁ። ከምንም በላይ በሀሰት የተፈረደበት በመሆኑ፣ ለአሳሪዎቹን እንጂ የእሱ ጭንቅላት ነጻ በመሆኑ የጥንካሬው ምንጭም ሊሆን ይችላል – የሚፀፀትበትን ነገር ባለመፈፀሙ።

በባለሽበት ስቴት፣ በቅርብሽ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከልጇ ሃሌይ ጋር አሉ፡፡ በ1997 ዓ.ም ምርጫን ተከትሎ በተፈጠረው ችግር፣ ከሁለቱም ጋር በቃሊቲ አብራችሁ ታስራችሁ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በስደት ዓለም አብራችሁ ትገኛላችሁ፡፡ አጋጣሚውን እንዴት ታይዋለሽ?
——————————-

እንዳጋጣሚ ሆኖ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ንግሥት ገብረህይወት (የቅንጅት ማዕከላዊ ኮሚቴ) …አሁን ደግሞ የቀድሞው የመንግሥት ጉዳዮች ኮሙኑኬሽን ሚኒስትር ደኤታ የነበሩት አቶ ኤርምያስ ለገሰ በአንድ አካባቢ እንገኛለን። ይህ ደግሞ፣ ቅርበታችንን ከጓደኝነት አልፎ ቤተሰብ እስከመሆን አድርሶናል። አንዳችን ሌላኛችን ቤት ለመድረስ ከአምስት ደቂቃ በላይ አይጠበቅብንም። በስደት ሀገር እንደዚህ ከምታውቀው እና ከምትግባባው ሰው ጋር አንድ አካባቢ መኖር፣ ውስጥህ ያለውን ብቸኝነት በትልቁ የሚቀርፍ ነው። በአጋጣሚ በአንድ አካባቢ መገኘታችን ለእኔ ትልቅ ደስታ ሰጥቶኛል።

በማኅበራዊ ድረ-ገጽ ላይ በንቁ በመሳተፍ እመለከትሻለሁ፡፡ ብዙ ጊዜ መረር ያሉ የቁጭት፣ የሀዘንና ልብን የሚነኩ ጽሑፎችን ትጽፊያለሽ፡፡ የጠቀስኳቸውን ስሜቶች ምን ፈጠራቸው?
————————-

በማኅበራዊ ድረ-ገፅ ላይ የሚጠበቅብኝን ወይም በምፈልገው መጠን እየተንቀሳቀስኩ እንዳልሆነ ይታወቀኛል። የዚህም ምክንያቱ፣ ልጄን በብቸኝነት ለማሳደግ የምሮጠው የህይወት ሩጫ በመጠኑም ቢሆን ገድቦኛል። ልጅ ትምህርት ቤት ማመላለስ፣ የልጄን ትምህርት በአግባቡ መከታተል እንዲሁም ለመኖር የሚያስችለንን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ መከወን በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው። ይህ ማለት ግን፣ ተሳትፎዬ ይቀንስ እንጂ፣ የሀገሬን ማንኛውንም ነገር ከመከታተል ወደ ኋላ ብዬ አላውቅም። ለተጠየኩት ጥያቄ መልሴ ግን፣ ባለችኝ ጊዜ የምፅፋት ነገር ምሬት እንደሚበዛባት አውቃለሁ። የዚህ ምሬት ምክንያት ደግሞ፣ ከሀገሬ መራቄ አንዱ ምክንያት ነው። ከሀገርህ ርቀህ ዜጎች ላይ የሚደርሰውን ጭቆና ማድመጥ በጣም ያማል። ምናልባትም ከመላመድ ብዛት፣ ውስጡ ሆነህ (ሀገርህ ላይ) እምብዛም አይታወቅም፡፡ ራቅ ስትል ግን፣ ‹‹እንደዚህ ለምን ይሆናል?››፣ ‹‹..እስከመቼ?›› የሚለው ነገርን ነገር በተደጋጋሚ እንድታስበው ያደርግሃል። በትንሹም ቢሆን የእኔም መረር ያለ ፅሁፍ ከዚህ የመነጨ ነው ብዬ አስባለሁ።

በአሜሪካ ሆነሽ፣ እስክንድርን በተመለከተ ምን እያደረግሽ ነው?
————————–

ባለሁበት ሀገር፣ እስክንድርን በተመለከተ፣ ከተለያዩ አካላት ጋር እገናኛለሁ። ስቴት ዲፓርትመንት ከጎንግረስ ማኖች (Congress man)፣ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት ስለእስክንድር የማያውቁት ነገር ባይኖርም፣ በተጨማሪ እኔም ስለሚገኝበት ሁኔታ እና በእስር ቤት ውስጥ ስለሚደርስበት የሰብዓዊ መብት ጥሰት አሳውቃቸዋለሁ። የሚገርመው ነገር በየሄድኩበት ትላልቅ ተቋማት በእስክንድር ጉዳይ ላይ ከበቂ በላይ መረጃ ያላቸው መሆኑን ነው። ‹‹እስክንድር አሸባሪ ነው›› የሚለውን የሀሰት ፍረጃ ጠንቅቀው እንደሚያውቁ በተደጋጋሚ በአንደበታቸው ሲገልፁ ይሰማል። ከኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በተጨማሪ፣ በትልቅ የኃላፊነት ቦታ ላይ የሚገኙ ባለሥልጣኖች ለእስክንድር ያላቸውን ክብር መስማት የተለመደ ነው። …ገፍተው ሌላ ነገር ማድረግ ባይችሉም እስክንድርን የሚመለከቱት በተለየ መነፅር ነው። ለጊዜው በዚህ እንቅስቃሴ ላይ እገኛለሁ። ወደፊት ግን እስክንድርን በተመለከተ ለመስራት የታሰበ ሰፊ ሥራ አለ። ጊዜው ሲደርስ የምገልጸው ይሆናል።

በግልሽ እስክንድር ከእስር ወጥቶ በቅርቡ እንገናኛለን የሚል እምነት አለሽ?
—————————
እስክንድር የጊዜ ጉዳይ እንጂ ከእስር እንደሚፈታ ጥርጣሬ የለኝም። መቼ? ለሚለው ግን እስክንድር ከዚህ በፊት እንደገለጸው ጊዜው ሊያጥርም ሊረዝምም ይችላል። ነገ ይፈታል፣ ከነገወዲያ ይፈታል ብዬ የቀን ስሌት አላስቀመጥኩም። አንድ የማምነው ነገር፣ የሀገሪቷ ችግር ሲፈታ፣ እስክንድርም አብሮ እንደሚፈታ ነው። እስከዚያው ከጨለማው ስር የሚወጣውን ብርሃን እጠብቃለሁ።

በሀገር ጉዳይ ላይ፣ ከሴት እህቶቻችን ምን ይጠበቃል?
———————-

በሀገሬ ጉዳይ ላይ ከሴት እህቶቻችን ብቻ ሳይሆን ሁሉም ሀገር ወዳድ ወገኖቻችን ንቁ ተሳትፎ በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ማድረግ አለባቸው እላለሁ። በሀገራችን ጉዳይ ላይ ለመሳተፍ የግድ ፖለቲከኛ መሆን አይጠበቅብንም። ከዚህ ባለፈ ሩቅ ሆኜ፣ እንዲህ ቢደረግ፣ እንዲያ ቢደረግ የሚል ነገር ለማስተላለፍ የሞራል ብቃቱ የለኝም። ‹‹እንዲህ አድርጉ›› ለማለት ከህዝብ ጋር ሆነህ በሀገር ላይ ተቀምጠህ እንጂ፣ በርቀት ሆኜ የምናገረው አንዳችም ነገር የለም።

በሀገር ውስጥ ለሚገኙ (ለሚያውቁሽና ለማያውቁሽ) ወገኖችሽ ያለሽ መልዕክት …
———————-
በመጨረሻ… ለሚያውቁኝ ወገኖቼ የማስተላልፈው መልዕክት፣ እስክንድር ከታሰረ ጀምሮ በሞራልም በገንዘብም ከጎናችን ላልተለያችሁን ወገኖቼ በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ የሚል ነው፡፡

አቡበከር አህመድ እንደዘገበው:- መንግስት በሴኩላሪዝም ስም ህብረተሰቡን በተለይ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከእምነቱ ለማስወጣት የሚያደርጋቸውን ጥረቶች አጠናከሮ የቀጠለ ሲሆን የዚህ እቅድ አንደ አካል የሆነውን ድርጊቱን ማንኛዉም አይነት የእምነት አዲስ ተቋማት በአዲስ አበባ ከተማ ዉስጥ እንዳይገነቡ በሚል መመሪያ ማዉጣቱን ምንጮች አስታዉቀዋል። በየትኛዉ እምነት አማኞች ፈጣሪያቸውን በአንድነት የሚያመልኩበት ቦታና የእምነቶቻቸውን ጥሪ የሚያደርጉበት ቦታ የእምነት የእምነት ተቋማቸዉ ሆኖ እያለ ከተማዋ […]

The post በአዲስ አበባ ከተማ ዉስጥ ማንኛዉም አዲስ የእምነት ተቋም እንዳይገነባ መመርያ ወጣ appeared first on ሳተናው .

በሕወሓት መሪነት የሚዘወረው የደህንነት ተቋሙ በኢሕአዴግ ውስጥ የዘለቀውን የመበስበስ አደጋ ተከትሎ በስልጣናችን ላይ ችግር ይፈጥራሉ ለድርጅቱ ሳይሆን ለሕዝብ እያደሉ ነው::ከተቃዋሚ ሃይላት መረጃ አምጡ ሲባሉ የሚዘናጉ እና አላስፈላጊ መረጃ ይሰጣሉ::ከአውሮፓ ዲፕሎማቶች ጋር ለምን አላማ እንደሆነ በማይታወቅ መልኩ ግንኙነት ፈጥረዋል ወዘተ ያላቸውን አስራ ስምንት አባላቱን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ከደህንነት ቢሮ የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል:: በሙስና እና የዘረፋ ቡድን […]

The post በደህንነት ቢሮ ውስጥ የተጀመረው ማጥራት ቀጥሏል::18 አባላቱ በቁጥጥር ስር ውለዋል:: appeared first on ሳተናው .

የዘንድሮ ምርጫ ኣሸንፎ ለመውጣት የህወሓት መንግስት ኣርባው ሲያስወጣ “…ከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ ፈጥሬ ድጋፍ ኣገኛለው…” ብሎ ኣስቦ ነበር። ይሁን እንጂ ከድጋፍ በላይ ተቃውሞ በመውለድ ያሁሉ ጥረቱ መና ሁኖ መቅረቱ ህወሓት ተረድተዋል። ድሮም በወከባ የሚገኝ ህዝባዊ ድጋፍ እንደሌለ የሚታወቅ ነው። ህወሓት ጥረቱ ከንቱ ሲቀር የዘየደው መላ በትግራይና የሚያዋስኑት የኢትዮ ኤርትራ ድንበር ኤርትራ የጦርነት ድባብ በመፍጠር የምርጫው ኣቅጣጫ […]

ተጻፈ በ  ደረጀ ጠገናው የእግር ኳስ ቤተሰቡ እምብዛም በዝርዝር እንደማያውቀው የሚነገርለት የቴክኒክ ኮሚቴና ቴክኒክ ዲፓርትመንት ሚናና አደረጃጀት ለአገሪቱ እግር ኳስ ቁልፍ ከሚባሉት ኃይሎች አንዱና ዋናው ነው፡፡ ይህ የሙያ ዘርፍ አሠልጣኞችንና ተጫዋቾችን ከመገምገምና የቡድን ግንባታው ላይ እሴት ከመጨመር ጀምሮ በትልልቅ ውሳኔዎች ላይ ተሳታፊና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አመንጪ ሊሆን እንደሚገባውም ይታመናል፡፡ ይሁንና በፌዴሬሽኑ ይህንን ሥልጣንና ኃላፊነት የተጣለበት ተቋም […]

The post እግር ኳስ ፌዴሬሽን ‹‹በጭቃ›› የተሸፈነውን እሾህ ቢያጠራ? appeared first on ሳተናው .

ከሁለት ዓመታት በኋላ ከቆዩበት የሕግ ከለላ በማግኘት ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ (ዱባይ) በቅርቡ የተመለሱት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣ በቅርቡ የአክሰስ ሪል ስቴት አክሲዮን ማኅበር የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መመረጣቸው ታወቀ፡፡ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ባደረገው ድርድር ከ2,000 በላይ ከሚሆኑ ከአክሰስ ሪል ስቴት ቤት ገዢዎች ጋር በተደረሰ ስምምነት ከየካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በሪል ስቴቱ ውስጥ ሥራ የጀመሩት አቶ […]

The post አክሰስ ሪል ስቴት አቶ ኤርሚያስ አመልጋን የቦርድ ሰብሳቢ አድርጐ ሰየመ appeared first on ሳተናው .

ተጻፈ በ  ታምሩ ጽጌ -ከ30 ሺሕ በላይ ዜጐችን በሕገወጥ መንገድ ማዘዋወራቸው ተጠቁሟል በኬንያ በማድረግ በታንዛኒያ በማቆራረጥ ወደ ደቡብ አፍሪካ በሕገወጥ መንገድ በኮንቴይነር ውስጥ አሽገው ሲያስተላልፉ፣ ታንዛኒያ ውስጥ እንዳሉ ሕይወታቸው ላለፉት 47 ኢትዮጵያውያን ተጠያቂ ናቸው የተባሉ ሁለት ኢትዮጵያዊያት ፍርድ ቤት ቀርበው፣ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው፡፡ አስካለ ዴዴሳ ዴዴቦ በቅጽል ስሟ ‹‹ቤቲ›› እና ሰሚራ ሐሰን ዓሊ የተባሉት […]

The post በታንዛኒያ በ47 ኢትዮጵያውያን ግድያ የተጠረጠሩ ፍርድ ቤት ቀረቡ appeared first on ሳተናው .

ከኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ነባር አመራሮች አንዱ የነበሩት አቶ መስፍን መንግሥቱ ተንሸራተው በመውደቃቸው ሳቢያ ሕይወታቸው በማለፉ፣ መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ተፈጸመ፡፡ አቶ መስፍን በተለያዩ ርዕስ ጉዳዮች ላይ ሪፖርተርን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች ሐሳባቸውን በማካፈል የሚታወቁ ፖለቲከኛ የነበሩ ሲሆን፣ ከ1995 ዓ.ም. ጀምሮ የኢዴፓ አባል በመሆን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሠርተዋል፡፡ ለአምስት ዓመታት ያህል የኢዴፓ […]

The post የኢዴፓ ነባር አመራር የነበሩት አቶ መስፍን መንግሥቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ appeared first on ሳተናው .

ከኢትዮጵያ ጋር ረዘም ላለ ጊዜ የዘለቀ ወዳጅነት የነበራቸው ዕውቁ አሜሪካዊው የፖለቲካ ሶስዮሎጂስት ፕሮፌሰር ዶናልድ ናታን ሌቪን፣ መጋቢት 26 ቀን 2007 ዓ.ም. አረፉ፡፡ ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን ስለኢትዮጵያ በጻፏቸው “Greater Ethiopia” (‹ታላቋ ኢትዮጵያ› በሚል ርዕስ አቶ ሚሊዮን ነቅንቅ ወደ አማርኛ መልሰውታል)፣ “Wax and Gold” እና “Interpreting Ethiopia” በተሰኙ መጽሐፎቻቸው የሚታወቁ ሲሆን፣ ለአምስት አሥር ዓመታት በኢትዮጵያ ላይ ትኩረት […]

The post የኢትዮጵያ ወዳጅ የነበሩት ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን አረፉ appeared first on ሳተናው .

ሆያሆዬ ሳይደርስ ሆያሆዬ .. ዉሮሸባዬ ሳይከፈት እስክስታ..ካለጊዜ ያውራዶሮ ገደል ማሚቱ ከመሆን አንድም ይሰውረን አንድም ያድነን::ምርቃት የማይደርስበት እርግማን እንደክፋት ላይገን ያደባበት የጊዜ ጀግንነት ለመደረብ የምንራወጥበትን ሰከን ብለን በሰውነት ጀግንነት የምንለካ ያድርገን::ጊዜን በአግባቡ እንደ ወርቅ ለመድመቅ ልንጠቀምበት የሚገባዉን ከአንዱ ይህ እይታውን ያደላዋል::የሚገባው በሚገባው ዘመን ላይ የማይገባው በሚያላዝንበት መደድ ላይ መሆናችንን መዘንጋት የለብንም:: በማንኛውም ደረጃ ላይ ቢሆን በትክክል […]

Semayawi Party in Stockholm, Sweden. በስዊድን የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር ራሱን አስተዋወቀEthiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. April 7, 2015)፡- ቅዳሜ አፕሪል 4 ቀን 2015 ዓ.ም. (ግንቦት 26 ቀን 2007 ዓ.ም.) የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር በስዊድን ተመስርቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በመግለጽ፤ የድጋፍ ማኅበሩ ራሱን አስተዋውቋል። በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ዓላማና ተግባርን ጥሪ ለተደረገላቸው ተሰብሳቢዎች ያስረዱት አቶ ሰለሞን ጌታነህ የድጋፍ ማኅበሩ ሰብሳቢ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

(በቴክኖሎጂስት ዳንኤል አማረ)

ማር ስኳር እስከተገኝበት 16ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ተፈጥሯዊ ማጣፈጫ በመሆን ያገለግል ነበር የአሰራር ሂደቱ በጣም አስደናቂ ከመሆኑም ባሻገር በብዙ ሰዎች ተወዳጅና ተመራጭ የምግብ ዓይነት ነው። በፍሩክቶስ(fructose) ይዘቱ በጣም የበለፀገ ስለሆነ ብዙ የህክምና ጥቅሞች አሉት እነሱም እንደሚከተለው ይቀርባሉ።

1. የካንሰርና የልብ ህመም ይከላከላል
የተፈጥሮ ማር ፍላቮንድና አንቲ ኦክሲዳንት(antioxidant) በውስጡ ይዟል እነዚህ ነገሮች በካንሰርና የልብ ህመም የመጠቃት እድልን ይቀንሳሉ።…

  በቨርጂኒያ ሀገረ ግዛት ፣ በሬገን ብሄራዊ የአየር ማረፊያ ተርሚናል ውስጥ አብርሀም ዘመድአገኘሁ የተባለ፣ መስማት የተሳነው እና የጎዳና ተዳደሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ወንድማችን ምንም በማያውቀው እና ባልፈፀመው ወንጀል አይፓድ ሰርቀሀል በሚል በፖሊስ ተይዞ ለስድስ ሳምንታት በወይህኒ ቤት አሳልፏል። አሰግድ ታመነ  

The post መስማት የተሳነው ኢትዮጵያዊ በቨርጂኒያ ፖሊስ ታሰረ appeared first on ሳተናው .

የሰውነት ቃጠሎን በቤት ውስጥ እንዴት ማከም እንችላለን?

(በቴክኖሎጂስት ዳንኤል አማረ)

አነስተኛ የሰውነት ቃጠሎዎችን በቀላሉ በቤት ውስጥ በፍጥነት የመጀመሪያ እርዳታ ህክምና መስጠት ሲቻል ከበድ ያሉ ቃጠሎዎች ሲሆኑ ግን ወደ ህክምና መስጫ ተቋሞች መሄድ ተገቢ ነው።
በሙቅ ውሀ ወይም ዘይት ቃጠሎ ሲደርስብን ቤታችን ውስጥ በሚገኙ ነገሮች እንዴት የመጀመሪያ ህክምና እንደምንሰጥ በዝርዝር እንመልከት

1. ማር
ማር በፀረ-ባክቴሪያ ባህሪውና ቁስል በፍጥነት እንዲያገግም በማድረግ ወደር አይገኝለትም። ይህም…

መጋቢት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመድረክ አባል የሆነው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊ/መንበር አቶ በቀለ  እንደተናገሩት በመጪው ምርጫ ለመሳተፍ ድርጅታቸው በኦሮምያ የተለያዩ አካባቢዎች እጩዎችን ቢያሰማራም፣ እጩዎቹ እየታሰሩና እየተደበደቡ በመሆናቸው መድረክ ቀጣዩን ሂደት ለመወሰን እየተነጋገረ ነው። አቶ በቀለ በሆድሩ ጉድሮ አባሎቻቸው ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መከልከላቸውን፣ በሜታ ሮቢ  ከ50 ያላነሱ ወጣቶች መታሰራቸውን፣ በግንደበረት የወረዳው አስተዳደር ሽጉጥ …