‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ እንዲሰፍን እየታገልኩ መሆኔ በክስ ማቅለያነት እንዲወሰድልኝ›› ወጣት ቴዎድሮስ አስፋው በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ ታስረው ‹‹ኢህአዴግ ሌባ ነው፣ ህገ መንግስቱ ወረቀት ነው፣ ታፍነናል፣ ታስረናል፣ መለስ የሞተው ደንግጦ ነው፣ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በቁሙ የሞተ ነው፣ ቴዎድሮስ ለህዝብ ነው የሞተው›› በሚል ብጥብጥና ሁከት ፈጥራችኋል፣ የሀሰት […]

ትላንት እሑድ ከጸሎተ ቅዳሴው ፍጻሜ በኋላ ለኹለተኛ ጊዜ ደብሩ፣ በአለቃው ‹‹የመንግሥት ያለኽ›› ጩኸት እና በምእመናን ‹‹ኃይል የእግዚአብሔር ነው፤ አንፈራም፤ አንሰጋም›› መዝሙር እና ተቃውሞ ውሏል *           *           * የቤተ ክርስቲያንን ነገር አደራ ብለው መባረኪያ መስቀላቸውን የሰጡ እንደ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ እና ብፁዕ አቡነ መልከ ጸዴቅ ያሉ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

በድርጅት ከዚያም ከፍ ብሎ በመንግስት ደረጃና በሃገር ደረጃ ግምገማ ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ ሁሉ ያምናል። የኣንድ ድርጅት ብቃትም በግምገማው ችሎታና ጥራት ሊለካ ይችላል።የኣንድ ሃገር የፖለቲካ መረጋጋት በፖለቲካ ለሂቆቹ የጠራ የሃገር የምናብ ስእልና ብስለት ሊለካም ይችላል። የፖለቲካ ቤቶች ሲኮለኮሉ፣ ፖሊሲዎች ሲቀረጹ ከፍ ያለ ግምገማን ይጠይቃል። ሃገሪቱ ያለፈችበትን የህይወት ጎዳና፣ የገጠማትን ችግር መንስዔና ውጤቶች በሰፊው መገምገም ለሚመሰረቱ […]

በክፍል አንድ፤ የሰላማዊ ትግሉ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ምን እንደሆነ ገልጫለሁ። በዚሁ ላይ፤ የሰላማዊ ትግሉ ከተወዳዳሪ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ጋር ያለውን ልዩነት አሳይቻለሁ። በተጨማሪ ደግሞ፤ የሰላማዊ ትግሉ የሚካሄደው በአንድ የሕዝባዊ ንቅናቄ ድርጅት ሥር ብቻ መሆኑንና፤ አማራጭና ተለዋጭ እንደሌለው አስምሬበታለሁ። በሂደቱ መሰባሰቢያ የሆኑትን ሀገር አቀፍ የትግል ዕሴቶች አስቀምጫለሁ። በዚህ ክፍል ሁለት ደግሞ፤ ስለተሳሳተው የሰላማዊ ትግሉ ግንዛቤያችን አስረዳለሁ። ባጠቃላይ፤ […]

ኤርትራውያን ስደተኞች አገራቸው ከአፍሪካ ኅብረት አባልነት እንድትሰረዝ ጥያቄ አቀረቡ

በኢትዮጵያ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ሰኔ 19 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በተለያዩ አገሮች ባደረጉት የተቃውሞ ሠልፍ፣ በፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሚመራውን የኤርትራ አስተዳደር በማውገዝና ሕጋዊ የሆነ መንግሥት

የማያስተዳድራት አገር የአፍሪካ ኅብረት አባል መሆን እንደማትችል በመግለጽ፣ ኤርትራ ከኅብረቱ አባልነት እንድትሰረዝ ጥያቄ አቀረቡ፡፡

በአዲስ አበባ በሚገኘው የአፍሪካ ኅብረት ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ቁጥራቸው ከ1,000 የሚበልጡ ስደተኛ ኤርትራውያን ባሰሙት ተቃውሞ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ግንቦት 28 ቀን 2007 ዓ.ም. ኤርትራን በሚመለከት ያወጣውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ ሪፖርትን ደግፈዋል፡፡ ‹‹ኢሳያስ አፈወርቂ ከሥልጣን መውረድ አለበት፤›› የሚለውንና ሌሎችንም መፈክሮች በማሰማት፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኤርትራ መንግሥት በተለይ በኤርትራውያን ወጣቶች ላይ እየፈጸመው የሚገኘውን ስቃይ፣ በደልና ሌሎች በዝርዝር ያቀረባቸውን ሪፖርቶች ኅብረቱ እንዲያፀድቀው ጠይቀዋል፡፡

ሕጋዊነት የሌለው መንግሥት የኅብረቱ አባል ሆኖ መቀጠል እንደሌለበት የጠቆሙት ኤርትራውያኑ፣ ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣናቸው እንዲወገዱ ኅብረቱ ትኩረት እንዲሰጠው ጠይቀዋል፡፡ 

ለአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ዶ/ር ንኮሳዛና ድላሚኒ ዙማ ደብዳቤ ያስገቡ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ለአውሮፓ ኅብረት ጽሕፈት ቤትም ተመሳሳይ ደብዳቤ አስገብተዋል፡፡

የቀይ ባህር አፋር ነፃ አውጭ በሚባለው ድርጅት በተዘጋጀው የተቃውሞ ሠልፍ ላይ ቁጥራቸው ከ30 ሺሕ በላይ የሆኑ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ፣ በሰመራ፣ በዱብቲ፣ በበራ ኃይሌ ካምፕ መገኘታቸው ሲታወቅ፣ በውጭ አገሮች በኒውዮርክና በጄኔቭም የተቃውሞ ሠልፉ መደረጉንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሠልፍ በማድረግ ለአፍሪካ ኅብረት ያቀረቡትን ደብዳቤ፣ የዶ/ር ድላሚኒ ዙማ ጸሐፊ ተቀብለው፣ ሊቀመንበሯ አስቸኳይ ምላሽ እንደሚሰጧቸው ነግረዋቸዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ግንቦት 28 ቀን 2007 ዓ.ም. ኤርትራን አስመልክቶ ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ፣ በእርስ በርስ ጦርነት እየወደመች ከምትገኘው ሶሪያ ቀጥላ ወጣት ዜጐቿ ወደ ስደት የሚጐርፉባት አገር መሆኗን ገልጿል፡፡

የኤርትራ ሰብዓዊ መብት አጣሪ ኮሚሽን በቀጥታ ኤርትራ ውስጥ ሆኖ በአገሪቱ ዜጐች ላይ የሚደርሰውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት መከታተልና መመራመር ባይችልም፣ ከ550 በላይ ስደተኛ ኤርትራውያንን በማነጋገርና የተለያዩ ጥናቶችን በማድረግ 484 ገጾች ያሉት ሪፖርት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ 24ኛ ዓመት የነፃነት ቀኗን በቅርቡ ያከበረችው ኤርትራ ላለፉት 24 ዓመታት ዜጐቿ የስቃይ፣ የሞትና የእስራት ሰለባ መሆናቸውን ሪፖርቱ አካቷል፡፡ የሚፈጸሙባቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም ሆን ተብሎና ታስቦበት የሚደረጉና የዘር ማጥፋትን የሚያካትቱ መሆናቸውን ሪፖርቱ እንደሚያስረዳ መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ 

 

በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የኦዲት ሪፖርት አተገባበር ላይ ትችት ቀረበ

የፓርላማው የመንግሥት ወጪ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ተሾመ እሸቱ፣ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የሚቀርብበትን የኦዲት ትችት ማስተካከል አልቻለም ሲሉ ከፍተኛ ወቀሳ ሰነዘሩ፡፡ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወቀሳውን ተቃውመዋል፡፡

የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ በከር ሻሌ የተቋማቸውን የአሥር ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሰኔ 18 ቀን 2007 ዓ.ም. አቅርበዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ በሪፖርታቸው ገጽ 19 ላይ ከተለያዩ አካላት ለመሥሪያ ቤታቸው የተሰጡ አስተያየቶች ትልቅ ጠቀሜታ እንደነበረው ገልጸዋል፡፡ ‹‹የፌዴራል ዋና ኦዲተር በተቋማችን ላይ የሚያደርገውን ኦዲት ተከትሎ የሚላክልን የኦዲት ግኝት ለሥራ አፈጻጸማችን ትልቅ መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጎልናል፤›› ብለዋል፡፡

የሪፖርት አቀራረብ ትክክል አይደለም ብለው ያመኑት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰበሳቢ አቶ ተሾመ እሸቱ፣ በአቶ በከር ላይ ትችታቸውን ሰንዝረዋል፡፡

የኦዲት ግኝትን በተመለከተ መቅረብ የነበረበት ሪፖርት በዝርዝር የተወሰደውን ዕርምጃ የሚገልጽ መሆን ነበረበት ያሉት አቶ ተሾመ፣ ይህንን ሕጋዊ ግዴታ ወደ ጎን ትቶ በደምሳሳው የኦዲት ሪፖርቱን ግብዓት አድርገነዋል ብሎ ማስቀመጥ ተገቢ አይደለም ብለዋቸዋል፡፡ 

የፌዴራሉ ዋና ኦዲተርን የሚከታተለው የፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ተሾመ፣ ‹‹ምናልባት የወሰድነውን ዕርምጃ ብንዘረዝር ከፓርላማው ክርክር ይገጥመናል ወይም ሪፖርቱ እንዳይረዝም ብዬ ነው የሚል ምላሽ ይቀርብ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ከፋኝ ተብሎ ሕግ አይጣስም፡፡ የከፋን ቀን ሕግ ጥሰን መሄድ አንችልም፤›› ብለዋል፡፡

ችግሩ ለአምስት ዓመታት መቆየቱን ጠቅሰው፣ በዚህ  የሕግ ጥሰት ላይ ምን ዕርምጃ እንደተወሰደ ጠይቀዋል፡፡ ለቀረቡላቸው ትችት አዘል ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የጀመሩት አቶ በከር፣ ‹‹ዋና ኦዲተር ያቀረበውን ሪፖርት አልካድኩም፤›› ብለዋል፡፡

ዋና ኦዲተር በትክክል ግኝት እንዳገኘ የተናገሩት አቶ በከር፣ ከዋና ኦዲተሩ ጋር በማጠቃለያ ስብሰባ ተነጋግረው ችግሮቹን ማየት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡

‹‹ነገር ግን በፖሊሲ አስተዳደር ቦታ ላይ ተቀምጦ ማየትን ይጠይቃል፡፡ ግብር የተጣለበት ከፋይ ቅሬታ አቅርቦ ሲከራከር የተጣለው ግብር ለረዥም ጊዜ ሳይሰበሰብ ይቀራል፡፡ ይህ በኦዲት ቋንቋ ያልተሰበሰ ሒሳብ ነው፤›› ብለዋል፡፡

‹‹ሌላው አምራች ኩባንያዎችን ለመደገፍ የታክስ ክፍያ ጊዜያቸውን እያሰፋንላቸው እንሄዳለን፡፡ ይኼንን በማድረጋችንም ባለሀብቶችን እየደገፍን የመንግሥትን ግብር እያስከፈልን ነው፤›› ብለዋል፡፡

በቂ መረጃ እያለ ያልተሰበሰቡ ገቢዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም  የዋና ኦዲተርን አስተያየት እንደ ግብዓት እየተጠቀሙበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለያዩ ኬላዎች የተያዙትን የውጭ ገንዘቦችና የከበሩ ማዕድናት በተመለከተ ተገቢውን የሕግ ሥርዓት አለመከተል ተገቢ ባይሆንም፣ ሕግን ባለማወቅ ሠራተኞች የፈጸሙት ስህተት ነው ብለዋል፡፡

 

ከአጋሮቹ ጋር በመሆን የፓርላማውን ወንበሮች ሙሉ በሙሉ ያሸነፈው ኢሕአዴግ፣ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አገሪቱ በምትመራበት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውይይት ላይ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን እንደሚያሳትፍ አስታወቀ፡፡ 

ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በተካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ኢሕአዴግና አጋር ፓርቲዎች ሙሉ በሙሉ ማሸነፋቸው መገለጹ ይታወሳል፡፡ በዚህ መሠረት በሕዝብ ተወካዮችም ሆነ በክልል ምክር ቤቶች ውስጥ ተቃዋሚዎች ሐሳባቸውን የሚገልጹበት ዕድል ባለመኖሩ፣ ገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲሳተፉ እንደሚመቻች፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንንና የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን አስታውቀዋል፡፡

በዚህ መሠረት በዚህ ሳምንት በመላ አገሪቱ በሚጀመረው የሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውይይት ላይ ተቃዋሚዎች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሏል፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ ከሰኔ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ለተከታታይ ስድስት ቀናት በሚካሄደው ውይይት ተቃዋሚዎች እንዲሳተፉ ባይጋበዙም፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ሁሴን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለዕቅዱ ግብዓት ወይም ሐሳብ የሚሰጡበት ራሱን የቻለ መድረክ ይዘጋጃል፡፡ 

‹‹ተቃዋሚዎች ከሕዝብ ጋር ተቀላቅለው ለውይይት ቢቀርቡ ሐሳባቸው ሊዋጥና በሚገባ ላይስተናገዱ ይችላሉ፤›› በማለት አቶ ሬድዋን ተቃዋሚዎች ለብቻቸው መድረክ እንደሚዘጋጅላቸው ገልጸዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ሁለት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የተለያዩ ሐሳቦችን አራምደዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ጉዳዩን አጣጥለውታል፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ችግር በእንደዚህ ዓይነት መንገድ አይፈታም፡፡ ሥር የሰደደ ችግር አለ ከተባለ ሥር የሰደደ መፍትሔ ነው መቅረብ ያለበት፡፡ ለብ ለብ ሊሆን አይችልም፤›› በማለት በውይይቱ መሳተፍ ኢሕአዴግን እንደማጀብ አድርገው ገልጸዋል፡፡ 

የኢዴፓ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ወንድወሰን ተሾመ በበኩላቸው፣ መንግሥት በዕቅድ ሰነዱ ላይ ለመወያየት ይፋዊ ጥያቄ ያላቀረበ ቢሆንም ኢዴፓ ከመኢአድና ከኢራፓ ጋር በመሆን ሰላማዊ ትግሉ በሚቀጥልበት መንገድ ላይ መምከር መጀመራቸውንና በቅርቡም መግለጫ እንደሚሰጡበት አስታውቀዋል፡፡ በኢዴፓ በኩል መንግሥት ጥያቄ ካቀረበ በሥራ አስፈጻሚው በኩል ውይይት ተደርጎ እንደሚወሰን አቶ ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡ 

በአቶ መኮንን ማንያዘዋል በሚመራው ብሔራዊ ፕላን ኮሚሽንና በከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በሚመሩ ኮሚቴዎች የተዘጋጀው ሁለተኛው የአምስት ዓመት ዕቅድ ሰነድ በዘርፍ፣ በዘርፍ ተከፍሎ ለውይይት ይቀርባል፡፡ 

በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁት አምስት መድረኮች አቶ ሬድዋን፣ ከንቲባ ድሪባ ኩማና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ዓባይ ፀሐዬ ውይይቱን ይመራሉ፡፡ 

በክልሎች የሚካሄዱትን የውይይት መድረኮች በተለይ በትግራይ ክልል የሚካሄደውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል፣ በአማራ ክልል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ በኦሮሚያ ክልል በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደርና ሲቪል ሰርቪስ ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትሯ ወ/ሮ አስቴር ማሞና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር ከድር፣ በደቡብ ክልል የትምህርት ሚኒስትሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣ በሐረሪ ክልል የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ መመደባቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ 

ሁለተኛው የአምስት ዓመት ዕቅድ ሰነድ ውይይት የሚካሄደው በዘርፍ በዘርፍ ተከፋፍሎ ሲሆን፣ ጥሪ ከተደረገላቸው መካከል ወጣቶችና ሴቶች ለየብቻ፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮች፣ የመንግሥት ሠራተኞችና ምሁራን፣ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችና የአካባቢ ልማት ኮሚቴ ተወካዮች ይገኙበታል፡፡ 

አቶ ሬድዋን እንደገለጹት፣ ከፋፍሎ ማወያየቱ አስፈላጊ የሆነው ሁሉም በተሰማራበት መስክ በቂ ጊዜ ወስዶ ለመነጋገርና ስትራቴጂውን ለማሳካት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡ 

ጥሪ የተደረገላቸው ተወያዮችም በኢሕአዴግ መዋቅር ውስጥ ያሉ ብቻ ሳይሆኑ፣ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል የሚወክሉ እንደሆኑ አቶ ሬድዋን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

 

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የፌዴራልና የክልል የጋራ ገቢ ተብሎ ከሚሰበሰበው ገቢ ውስጥ ድርሻው እንዲከፈለው ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያቀረበው ጥያቄ፣ የክልል መንግሥትነት ዕውቅና የሌለው በመሆኑ ውድቅ ተደረገ፡፡

የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 98 የፌዴራሉ መንግሥትንና የክልሎችን የጋራ ታክስና የግብር ሥልጣንን ይደነግጋል፡፡

በዚህም መሠረት የፌዴራል መንግሥትና ክልሎች በጋራ በሚያቋቁሟቸው የልማት ድርጅቶች ላይ የንግድ ትርፍ ግብር፣ የሥራ ግብር፣ የሽያጭና የኤክሳይስ ታክስ በጋራ እንደሚጥሉና እንደሚሰበስቡ ይገልጻል፡፡ በተጨማሪም በድርጅቶች የንግድ ትርፍ ላይና በባለአክሲዮኖች የትርፍ ድርሻ ላይ የግብርና የሽያጭ ታክስ በጋራ እንደሚጥሉና እንደሚሰበስቡ፣ በመጨረሻም በከፍተኛ የማዕድን ሥራዎች፣ በማናቸውም የፔትሮሊየምና የጋዝ ሥራዎች ላይ የገቢ ግብርና የሮያሊቲ ክፍያዎች በጋራ እንደሚጥሉና እንደሚሰበሰቡ ይደነግጋል፡፡ 

ይህንኑ ድንጋጌ መሠረት በማድረግ ከሚሰበሰበው የጋራ ገቢ ክልሎች ድርሻቸውን በመውሰድ ለልማት እያዋሉ የሚገኙ መሆኑን፣ በዚሁ አግባብም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የጋራ ገቢ ክፍፍል ድርሻውን እየወሰደ እስከ 2001 ዓ.ም. ድረስ ለልማት ሲያውል መቆየቱን፣ አስተዳደሩ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ከ2001 ዓ.ም. በኋላ ግን የገቢ ድርሻው መቋረጡን በመጥቀስ እንዲለቀቅለት ጥያቄውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ የአስተዳደሩን ጥያቄ ለበጀት ድጐማና የጋራ ገቢዎች ድልድል ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመራው የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ ቋሚ ኮሚቴው ያቀረበለትን የውሳኔ ሐሳብ ሰኔ 17 ቀን 2007 ዓ.ም. አዳምጧል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የትምህርት ሚኒስትሩና የደቡብ ክልል ምክር ቤት ተወካዩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት፣ ቋሚ ኮሚቴው በድሬዳዋ አስተዳደር ጥያቄ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም የሚያስፈልገው መሆኑ ስለታመነበት፣ ለሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ እንዲመራ በማድረግ ምላሽ ማግኘቱን አስታውቀዋል፡፡

የሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባዔው ባደረገው ምርመራ ‹‹የኢፌዴሪ መንግሥት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 46(1) መሠረት በክልል መንግሥትነት ዕውቀና የተሰጣቸው ዘጠኙ ክልሎች መሆናቸውን፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 49(1) የፌዴራል መንግሥቱ አካል ተደርጐ የሚወሰደው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ነው፤›› በማለት መግለጹን አቶ ሽፈራው ገልጸዋል፡፡

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በፌዴራል መንግሥት በወጣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/1996 መሠረት ለጊዜው የፌዴራል መንግሥት አስተዳደራዊ አካል ቢሆንም፣ በሕገ መንግሥቱ በክልልነትም ሆነ በፌዴራል መንግሥት የአስተዳደር መዋቅር ውስጥ የሌለ በመሆኑ የሕገ መንግሥት ትርጉም የሚያስፈልገው ጥያቄ አይደለም በማለት ጉባዔው እንደወሰነ ተናግረዋል፡፡

በዚሁ መሠረትም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ውሳኔውን እንዲያውቀው መደረጉን አቶ ሽፈራው ለምክር ቤቱ አስረድተዋል፡፡

‹‹በሌላ በኩል ግን ከኅብረተሰቡ የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት አንፃር የከተማ አስተዳደሩ ያቀረበው ጥያቄ አግባብነት ያለው መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ያምናል፤›› ሲሉ አቶ ሽፈራው ተናግረዋል፡፡ 

ጉዳዩን በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የድሬዳዋ ከተማ የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ፈቃዱ በየነ የከተማው አስተዳደር በውሳኔው ደስተኛ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ ‹‹የድሬዳዋ ከተማ በሕገ መንግሥቱ የክልል መንግሥትነት ዕውቅና እንደሌላት የታወቀ ነው፡፡ ነገር ግን የፌዴራል መንግሥት ከከተማው የሚሰበሰበው ገቢ ተቋዳሽ መሆን አለበት፡፡ ከተማዋ ወደ ኢንዱስትሪ መንደርነት እየተቀየረች ነው፡፡ መሠረተ ልማት ማሟላት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ተጨማሪ ገቢ የከተማው አስተዳደር ሊያገኝ ይገባል፤›› ብለዋል፡፡

ከከተማው የሚሰበሰውን ገቢ የፌዴራል መንግሥት ብቻ እየወሰደ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ወይም አሁን በሚፈጠሩት ኢንዱስትሪዎች የሚለቀቅ ጢስና የአካባቢ ጉዳት ገፈት ቀማሽ ብቻ መሆን የለባቸውም ብለዋል፡፡ አስተዳደሩ በካቢኔ ደረጃ ተነጋግሮ ምላሽ የሚሰጥ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ 

የኦሮሚያ ክልልና የሶማሌ ክልል በድሬዳዋ ላይ ባነሱት የይገባኛል ጥያቄ የፌዴራሉ መንግሥት ባወጣው አዋጅ፣ ድሬዳዋ በጊዜያዊነት የፌዴራሉ መንግሥት መዋቅር አካል እንድትሆን መደረጉ ይታወሳል፡፡  

 

ግንባታው በመገባደድ ላይ ባለው የአዲስ አበባ-ሜኤሶ የባቡር መስመር ላይ በሐዲዶችና በመጋዘን የተከማቹ ንብረተቶች ላይ ተደጋጋሚ የዘረፍ ሙከራ እየተካሄደበት መሆኑ ተጠቆመ፡፡ ፖሊስ መሠረተ ልማቱንም ሆነ በግንባታ የሚሳተፉ

ሠራተኞች ደኅንነት ለማስጠበቅ የተጠናከረ ጥበቃ ማድረጉንና ዘራፊዎችንም ለሕግ ማቅረቡን ገልጿል፡፡

በተለይ በአዳማ ከተማ አካባቢ በመገንባት ላይ ባለው ጣቢያ ተደጋጋሚ ዘረፋ እንደሚፈጽም ተነግሯል፡፡ የጥበቃ ሠራተኞችና ቻይናዊያን ባለሙያዎችም በዘራፊዎች ተኩስ ተከፍቶባቸው እንደነበር ሪፖርተር ሥፍራው ድረስ በመሄድ ለመገንዘብ ችሏል፡፡

በግንባታ ላይ የተሰማሩ ሠራተኞች ዘራፊዎች በጦር መሣሪያ ጭምር በሌሊት ካምፑን ሰብረው በመግባት በመጋዘን የሚገኙ ብረታ ብረቶችንና የግንባታ ግብዓቶችን ለመስረቅ ሙከራ እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡

ከአዲስ አበባ-ሜኤሶ ባለው አጠቃላይ መስመር ላይ አንድ ሻምበል የተጠናከረ ፌዴራል የፖሊስ ኃይል የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በአዳማ መጋዘኖች በሚገኙ ቦታዎች ግን ዘራፊዎች ከሠራተኞች ጋር በመመሳጠርም ዘረፋ ለማድረግ መሞከራቸው ተገልጿል፡፡

ግንባታውን እያካሄደ ከሚገኘው የቻይናው ሲአርሲሲ የተገኘ መረጃ፣ ባለፉት ሦስት ዓመታት ከ100 ጊዜ በላይ የዘረፋ ሙከራዎች መፈጸማቸውን ያሳያል፡፡

የአዳማ 03 ቀበሌ አስተዳደር ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ ተጠርጣሪ ዘራፊዎችን አድነው በመያዝ ለሕግ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን እስካሁን ድረስ ምን ያህል የዘረፋ ሙከራ እንደተካሄደ ባይገልጹም፣ ሁለት ተጠርጣሪዎች ተይዘው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ መሆኑን አንድ የአዳማ ከተማ አስተዳደር ኃላፊ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ሪፖርተር ከፖሊስ መረዳት እንደቻለው፣ ዘራፊዎች በምርመራ ወቅት ሲጠየቁ የዘረፉት ንብረት የአገሪቱ ሳይሆን የቻይና እንደሆነም አድርገው ይቆጥሩታል፡፡

የጥበቃ ሥራውን እያስተባበሩ የሚገኙት ምክትል ኢንስፔክተር እንግዳው ባዬ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአብዛኛው ሕዝብ ዘንድ የመሠረተ ልማቱን በተመለከተ የተሻለ ግንዛቤ ያለ ቢሆንም፣ በጥቂቶች ዘንድ ያለው ግንዛቤ በተቃራኒው ስለሆነ ሰፊ የግንዛቤ ትምህርት መሰጠት አለበት፡፡

ኩባንያው በበኩሉ በቡድን የተደራጁና የጦር መሣሪያ የታጠቁ ዘራፊዎች በኢትዮጵያውያንና በቻይናውያን ሠራተኞች ላይ በተደጋጋሚ ማስፈራሪያ ሲፈጽሙ፣ በተለያዩ ካምፖች ግንባታ የሚቆምበት ጊዜ እንደነበር ገልጿል፡፡ 

የአገር አቀፍ የባቡር ትስስር አካል የሆነው የሰበታ-ሚኤሶ የባቡር መስመር  ግንባታው በቻይናው ሲአርሲሲ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ 329 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ይኼ ፕሮጀክት በቅርቡ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ለግንባታው 1.8 ቢሊዮን ዶላር በጀት እንደወጣበት ይነገራል፡፡ 

 

ድርጅታቸውን ለመታደግ አገር ቤት የተመለሱት የሆላንድ ካር ባለቤት ያቀረቡት ሐሳብ ውድቅ ተደረገ

በኪሳራ የተዘጋውን ሆላንድ ካር የመኪና መገጣጠሚያ ኩባንያቸውን ለመታደግ፣ ከሦስት ዓመታት ቆይታ በኋላ ግንቦት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት ኢንጂነር ታደሰ ተሰማ፣ ኩባንያውን እንዴት ሊታደጉት እንደሚችሉ

ያቀረቡትን ሐሳብ 201 የሚሆኑ ገንዘብ ጠያቂዎች ውድቅ አደረጉት፡፡

ኩባንያውን ከጨረታ ሽያጭ ያድናል ያሉትን ዕቅድ ነድፈውና ለመንግሥት አቅርበው ተቀባይነት በማግኘታቸው ወደ አገር ቤት የተመለሱት ኢንጂነር ታደሰ፣ ስድስት ሚሊዮን ብር ይዘው መምጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

201 የሚሆኑት የኩባንያው ደንበኞች መኪና ለመግዛት ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ የፈጸሙ ቢሆንም፣ ኩባንያው በገባው ቃል መሠረት ሊፈጽም ባለመቻሉ ኪሳራ አሳውጆ ነበር፡፡

ቁጥራቸው 201 መሆናቸው የተጠቀሰው ገንዘብ ጠያቂዎች፣ ሰኔ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. የኩባንያው ባለቤት፣ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሬጅስትራርና የተለያዩ ኮሚቴዎች ተሰብስበው በኩባንያው ባለቤት ሐሳብ ላይ ውሳኔ አስተላልፈዋል፡፡

በጠበቃቸው አቶ ጥላሁን ምትኩ አማካይነት የኩባንያው ባለቤት ሐሳብ ተገልጿል፡፡ በዚህም መሠረት ኩባንያው ከኪሳራ ወጥቶ የባለገንዘቦቹን መብት እንደሚያስጠብቅ፣ በመገጣጠሚያ ፋብሪካው ውስጥ ያሉ 174 መኪኖችን ገጣጥሞ ለገበያ ለማቅረብ ስድስት ሚሊዮን ብር እንደተዘጋጀ፣ ተሽከርካሪዎቹ ተገጣጥመው እስከሚሸጡ ድረስ ንብረቶቹ በሙሉ በንብረት ጠባቂና መርማሪ ዳኛ ሥር እንደሚቆዩ ተናግረው፣ በሐራጅ ቢሸጡ ግን የሚገኘው ገንዘብ ከመንግሥት ግብር፣ ከባንክ ዕዳ፣ ከሠራተኞች ክፍያና ከንብረት ዕዳ ማጣሪያ ክፍያ እንደማይተርፍ በመግለጽ፣ በኢንጂነሩ ሐሳብ መስማማት ምርጫ የሌለው መሆኑን ጠበቃው አብራርተዋል፡፡ 

ገንዘብ ጠያቂዎቹ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ እንዳብራሩት፣ ኢንጂነር ታደሰ ያቀረቡት ሐሳብ ቀደም ብሎ በእንግሊዝኛ ካቀረቡላቸው የሚለየው በአማርኛ መቅረቡ ነው፡፡ የቀረበው የአፈጻጸም ዕቅድ ተዓማኒ እንዳልሆነና ለገንዘብ ጠያቂዎቹ ገንዘባቸው እንዴት እንደሚመለስና ምን ያህል ወለድ እንደሚያካትት አይገልጽም፡፡ ለ174 መኪናዎች መገጣጠሚያ ብለው ያቀረቡት ገንዘብ፣ ባለአንድ ፎቅ የሆነ ቤት እንኳን መግዛት አይችልም ብለዋል፡፡ ኩባንያው ሐሳብ ሲያቀርብ ስለዕዳው አከፋፈል በቅድሚያ የገንዘብ ዋስትና ማቅረብ ቢኖርበትም አለማቅረቡን፣ የከሰረው ኩባንያ ከፍተኛ ዕዳ ቢኖርበትም ከባንክና ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ግብር ከፋዮች መሥሪያ ቤቶች ጋር ምን ዓይነት ስምምነት ላይ እንደደረሰ ባለማሳወቁ፣ ሐሳቡን ለመቀበል እንደማይችሉ አስረድተዋል፡፡

የከሰረው ኩባንያ ንብረት ጥበቃ ሹም አቶ ግርማ ዓለሙ የሚባሉት ግለሰብ ደግሞ፣ የኢንጂነር ታደሰን ሐሳብ ሌላ ጊዜ ጽፈው ከሚያቀርቡት የተለየ አለመሆኑን ተናግረው፣ የመክሰር ሥርዓት ሒደቱን ለማቋረጥና በስምምነት ሐሳቡ ለመቀጠል የሚያስችል፣ በንግድ ሕጉ ያሉ አስገዳጅ ሁኔታዎችን አሟልተው አለመቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡ ስድስት ሚሊዮን ብር እንዳቀረቡ ኢንጂነሩ ቢናገሩም፣ በቅድሚያ መፍትሔ ማግኘት ያለባቸው የቀድሞ ሠራተኞች ክፍያ፣ የፎርክሎዠር (በሐራጅ የመሸጥ) መብት ያለው ዘመን ባንክ ብድር ጉዳይና ለሌሎች የመንግሥት ክፍያዎች የሚበቃ ገንዘብ ስለመኖሩ ተጨባጭ ማረጋገጫ እንደሌለ ገልጸዋል፡፡

በንግድ ሕግ ቁጥር 1064(3) መሠረት የስምምነት ሐሳቡ በኩባንያው ሥልጣኑ በተሰጠው አስተዳዳሪ የፈረመበት ሆኖ ባለመገኘቱ፣ የኢንጂነር ታደሰ ውክልና ሥልጣን የተሰጣቸው ስለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ ስላልቻሉ፣ ሐሳቡ ተቀባይነት እንደሌለውም ተናግረዋል፡፡

በሕግ መሟላት የሚገባቸው ነገሮች ሳይሟሉ ስምምነት ላይ ቢደረስና ሥራ ቢጀመር፣ ንብረቶች ሊሸሹና ሊጠፉ ስለሚችሉ ሊመለስ የማይችል ጉዳት ሊደርስ እንደሚችልም አክለዋል፡፡

በመጨረሻም በውይይቱ ላይ የተለያዩ አስተያየቶች በመቅረባቸው ድምፅ እንዲሰጥበት ተደርጐ፣ በዕለቱ የተመዘገቡ 201 ግለሰቦች ወይም 62,516,068 ብር ካላቸው ገንዘብ ጠያቂዎች ውስጥ 54,982,120 ብር ያላቸው 134 ሰዎች ሐሳቡን ውድቅ አድርገውታል፡፡ በመሆኑም በንግድ ሕግ ቁጥር 1084 (1) መሠረት የስምምነት ሐሳቡ ተቀባይነት አለማግኘቱን፣ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዋና ሬጅስትራር አቶ መሠረት አያሌው በፊርማቸው አረጋግጠዋል፡፡    

 

የዛይ ሕዝብ የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ አቅርቧል

የአማራ ክልል ምክር ቤት የቅማንት ሕዝብ ላነሳቸው ተጨማሪ የማንነትና ራስን የማስተዳደር ጥያቄ፣ ከዚህ ቀደም ዋናውን ችግር ለመፍታት በሄደበት መንገድ እንዲፈታ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የመጨረሻ የሥልጣን ዘመኑን ማጠቃለያ ጉባዔ ሰኔ 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ባካሄደበት ወቅት፣ የምክር ቤቱ የሕገ መንግሥትና ክልሎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በቅማንት ሕዝቦች የማንነትና የራስ አስተዳደር ጥያቄ ላይ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ነው ውሳኔውን ያሳለፈው፡፡ 

በአማራ ክልል የሚኖሩ የቅማንት ሕዝቦች የማንነትና ራስን የማስተዳደር ሕገ መንግሥታዊ ጥያቄያቸውን በመጀመርያ ያቀረቡት ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ነው፡፡ ምክር ቤቱም ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የሕገ መንግሥትና የክልል ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ኃላፊነቱን እንዲወስድ ማድረጉን የቋሚ ኮሚቴው ሪፖርት ያስታውሳል፡፡ 

ቋሚ ኮሚቴው የጥናት ቡድን አቋቁሞ ከአማራ ክልል፣ ከሰሜን ጎንደርና በየደረጃው ከሚገኙ የወረዳና የቀበሌ አመራሮችና ከአቤቱታ አቅራቢ ኮሚቴ ጋር በመተባበር ጥናት ማካሄዱን ይገልጻል፡፡ በዚሁ ጥናት በላይ አርማጭሆ፣ በጭልጋና በመተማ ወረዳዎች የወረዳ አመራሮችና የጥያቄ አቅራቢው ሕዝብ አስተባባሪ ኮሚቴ በመስማማት በመረጧቸው ናሙና ቀበሌዎች ባደረገው ጥናት ዕድሜ ጠገብ አዛውንቶች፣ አልፎ አልፎም ወጣቶች ቋንቋውን እንደሚናገሩና ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ሕፃናት ቋንቋውን ለመማር ከፍተኛ ጉጉት እንዳላቸው የጥናት ቡድኑ ማረጋገጡን የኮሚቴው ሪፖርት ይገልጻል፡፡ 

በጥናቱ ያልተሸፈነ ነው ያለውን ማኅበረሰቡ በተያያዘ መልከዓ ምድር መኖር ያለመኖራቸውን ያካተተ ጥናት ተጠንቶ እንዲቀርብለት ቋሚ ኮሚቴው ለጥናት ቡድኑ ውሳኔ ማሳለፉን አስታውሷል፡፡ 

የጥናት ቡድኑ ከላይ በተገለጸው መሠረት ጥናቱን ለመቀጠል በተንቀሳቀሰበት ወቅት፣ የክልሉ መንግሥት በራሱ ተነሳሽነት ለጥያቄው ምላሽ ለመስጠት ኮሚቴ አቋቁሞ ሥራ መጀመሩን ገልጿል፡፡ በቋሚ ኮሚቴው የተላኩ አጥኚዎች ተልዕኮ ለጊዜው እንዲቆይና የክልሉ መንግሥት በራሱ ጥያቄውን ለመመለስ የጀመረው እንቅስቃሴ ውጤት እንዲጠበቅ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት፣ ጥያቄውን ቋሚ ኮሚቴው እንደተቀበለው ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ 

ክልሉ ባካሄደው ጥናት የራስ አስተዳደር ጥያቄውን ዕውቅና ሰጥቶ የቅማንት ሕዝብ ራሱን ችሎ በኩታ ገጠም በሚኖርባቸው የጭልጋና የላይ አርማጭሆ ወረዳዎችን ማዕከል በማድረግ፣ ከሐምሌ 1 ቀን 2007 ጀምሮ የአስተዳደር በጀት ለመመደብና ሌሎች አስፈላጊ ሥራዎችን ለመሥራት የአማራ ክልል ምክር ቤት በ14ኛ መደበኛ ጉባዔው ውሳኔ ማሳለፉን በመግለጽ፣ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ሪፖርት ማድረጉን ቋሚ ኮሚቴው ገልጿል፡፡ የክልሉ መንግሥት ችግሩን ለመፍታት በተነሳሽነት ያሳየው ትብብርና ቁርጠኝነትን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አድንቆታል፡፡ 

ይሁን እንጂ የማኅበረሰቡ ተወካዮች የክልሉ ምክር ቤት የሰጠው ውሳኔ ሁሉንም ቀበሌዎች ያላካተተና የተሸራረፈ ውሳኔ ነው በማለት ተቃውሟቸውን በድጋሚ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ማቅረባቸውን፣ የሕገ መንግሥትና የክልል ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሪፖርት ይገልጻል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው በጥያቄው ላይ ውይይት በማድረግ የቀረበውን ተጨማሪ ጥያቄ ክልሉ ከዚህ በፊት ከፈታው ችግር በላይ ሊሆን እንደማይችል ግንዛቤ በመውሰድ፣ የክልሉ መንግሥት በጀመረው አግባብ ተጨማሪ ጥያቄውን እንዲፈታ የሚል አቋም በመያዙ የፌዴሬሽን ምክር ቤትም ይህንን ውሳኔ በመቀበል ለክልሉ ኃላፊነቱን በመስጠት እንዲወስን ሲል ጠይቋል፡፡ በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ በመወያየትም ምክር ቤቱ ውሳኔውን ተቀብሎ አፅድቆታል፡፡ 

የቅማንት ሕዝብ በአማራ ክልል በስምንት ወረዳዎች በሚገኙ 126 ቀበሌዎች ውስጥ የራስ አስተዳደር ጥያቄ ያነሰ ቢሆንም፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት ግን ባካሄደው ጥናት ላይ ተመሥርቶ መጋቢት 2 ቀን 2007 ዓ.ም. የሰጠው ውሳኔ በሁለት ወረዳዎች በሚገኙ 42 ቀበሌዎች ላይ ነው፡፡ የቅማንት ሕዝብ ተወካዮች ለሪፖርተር በጽሑፍ እንደገለጹት፣ የክልሉ መንግሥት ጥያቄያቸውን እየሸራረፈና ተጨማሪ ጥያቄዎችን እያነሱ ባሉት ተወካዮች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው፡፡ 

‹‹ከዚህ ሁሉ የችግር ጫና ውስጥ የቅማንት ሕዝብ እየገባ ያለው ጥያቄው በይግባኙ መሠረት በፌዴሬሽን ምክር ቤት መመለስ ባለመቻሉ ነው፡፡ ይግባኝ የቀረበለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 251/1993 በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የማያዳግም ውሳኔ ቢያስተላልፍ ይህ ሁሉ ችግር ውስጥ አይገባም ነበር፡፡ አሁንም በቀረበለት ይግባኝ መሠረት ውሳኔ እንዲያስተላለፍ አቤቱታችንን እናሰማለን፤›› ሲሉ ሰኔ 9 ቀን 2007 በጻፉት ደብዳቤ ፌዴሬሽን ምክር ቤትን ጠይቀዋል፡፡ 

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥትና የክልል ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ግን በአዋጁ መሠረት ኃላፊነት ቢኖረውም፣ ለክልል መንግሥታት ቀርበው ውሳኔ በተሰጠባቸው የማንነት ጥያቄዎች ቅር በመሰኘት ለፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በመመርመር፣ በምክር ቤቱ የውሳኔ ሐሳብ እንደሚያቀርብ በተሻሻለው የምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ ምግባር ደንብ ቁጥር 1/1999 ኃላፊነት የተሰጠው በመሆኑ የክልሉን ውሳኔ በመመርመር እንደተቀበለው ገልጿል፡፡ 

ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ኃላፊነት በመውሰድ ጥናት ጀምሮ የነበረው አጥኚ ቡድንና የክልሉ ምክር ቤት ባካሄደው ጥናት ላይ በመመሥረት ያሳለፈው ውሳኔ ተመሳሳይነት ያላቸው በመሆኑ፣ ተጨማሪ ጥያቄውን የክልሉ መንግሥት በቀደመው አግባብ ቢመልሰው ችግር እንደማይኖረውም ቋሚ ኮሚቴው እምነቱ እንደሆነ ገልጿል፡፡ 

ይህ በእንዲህ እንዳለ በኦሮሚያ ክልል ዝዋይ ሐይቅ ደሴት ላይ የሚኖሩት የዛይ ማኅበረሰብ የማንነትና ራስን የማስተዳደር ጥያቄ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡ የምክር ቤቱ የሕገ መንግሥትና የክልሎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባዔ፣ የክልሉ መንግሥትና ምክር ቤት የዛይ ማኅበረሰብ ጥያቄን በተመለከተ ውይይት እያደረጉ መሆኑን በመጥቀሳቸው ጉዳዩ ለክልሉ ተትቷል፡፡ 

 

በደቡብ ክልል በጋብቻ ምክንያት በሐዲቾና በወላቢቾ ጎሳዎች መካከል የተቀሰቀሰውን ከፍተኛ ግጭት፣ የክልሉ ፖሊስ በአስቸኳይ እንዲቀርፍና ጥፋተኞችን ለሕግ እንዲያቀርብ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አሳሰበ፡፡ 

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሰኔ 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ፣ የፌዴራል ፖሊስን ወደ አካባቢው ማሰማራት አግባብነት እንደሌለው፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ሰላምና ፀጥታ ለማስፈን በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት ኅብረተሰቡ ተረጋግቶና ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲኖር ለማድረግ የሕዝብ አደራና ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስቧል፡፡ 

በዚህ የጎሳ ግጭት ተሳታፊ የሆኑት ሕገወጥ ድርጊት ፈጻሚዎች ላይ ምርመራው ተጣርቶ ለሕግ እንዲቀርቡ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችም ወደ ቀድሞ መኖሪያ ቤታቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ አሳስቧል፡፡ 

በሒዲቾና በወላቢቾ ጎሳዎች መካከል ግጭቱ የተቀሰቀሰው ከግንቦት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ወዲህ ሲሆን፣ ምክንያቱ ደግሞ የሐዲቾ ጎሳ አባል የሆነ ግለሰብ ከወላቢቾ ጎሳ አባል ከሆነች አንዲት ግለሰብ ጋር በመጋባቱ ነው፡፡ 

ይህንን ጋብቻ ያልተቀበሉ የወላቢቾ ጎሳ አባላት፣ ‹‹እንዴት አናሳ ዘር ከእኛ ዘር ይጋባል?›› በማለት በአንድ ላይ በመነሳት በሐዲቾ ጎሳ አባላት ላይ ጥቃትና የንብረት ውድመት መፈጸማቸውን ከአካባቢው ለፌዴራል መንግሥት ተቋማት አቤት ለማለት ተወክለው የመጡ ግለሰቦች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

የወላቢቾ ነዋሪዎችን ቤቶችና ንብረቶች በማቃጠልና ያገኙትን በመደብደብ፣ በበርካታ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት ከማድረሳቸው በተጨማሪ ሰዎችን መግደላቸውን ተወካዮቹ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

ጉዳዩን በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የወንዶ ገነት ወረዳ ፖሊስ ኃላፊ የተፈጠረው ግጭት በአሁኑ ወቅት መቀረፉን ገልጸው፣ የሞተ ሰው አለ መባሉን አስተባብለዋል፡፡ 

የፖሊስ ኃላፊው ይህንን ይበሉ እንጂ፣ የሐዲቾ ጎሳ አባላት በርካቶቹ እስካሁን ወደ መኖሪያቸው እንዳልተመለሱና አሁንም ሥጋት ውስጥ መሆናቸውን ተወካዮቹ ይናገራሉ፡፡  

 

በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ተገንብተው አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ ተብለው የሚጠበቁ ስምንት የዓለም አቀፍ ብራንድ ሆቴሎች መምጣትን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ ከአሥር ዋና ዋና የአፍሪካ አገሮች ውስጥ አንዷ

ለመሆን እንደቻለች ታወቀ፡፡ በአፍሪካ በሆቴል ኢንቨስትመንት ውስጥ ስማቸው ከሚጠቀስ ኩባንያዎች መካከል ሒልተን ዓለም አቀፍ፣ በአዳዲስ ሆቴሎች ግንባታና በመኝታ ክፍሎች ብዛት ቀዳሚውን ሥፍራ መያዙን ጥናቶች ጠቁመዋል፡፡ 

ላለፉት አራት ዓመታት ‘አፍሪካ ሆቴል ኢንቨስትመንት ፎረም’ በሚል ርዕስ ዓመታዊ ጉባዔ በማካሄድ ላይ የሚገኘው የእንግሊዙ ቤንች ኤቨንትስ ይፋ ባደረገው ጋዜጣዊ መግለጫ መሠረት፣ በኢትዮጵያ የሚገነቡት ስምንት ሆቴሎች በጠቅላላው ከ1,300 በላይ ክፍሎች እንደሚኖሯቸው ይጠበቃል፡፡ በአንፃሩ በአፍሪካ ከ270 በላይ ሆቴሎች እንደሚገነቡ ሲጠበቅ፣ ከ30 ሺሕ ያላነሱ ክፍሎች እንደሚይዙም ቤንች ኤቨንትስ ጥናቶችን ጠቅሶ ያሠራጨው መግለጫ ያመለክታል፡፡ 

በአፍሪካ ግብፅ በ18 አዳዲስ ሆቴሎች ግንባታ የመጀመሪያውን ረድፍ በመያዝ እየመራች ትገኛለች፡፡ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዝያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሊቢያ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሩዋንዳ በቅደም ተከተል ከአንድ እስከ አሥር ያለውን ደረጃ በመያዝ ግብፅን ይከተላሉ፡፡ በእነዚህ የሆቴል ግንባታዎች ላይ ትልቁን ድርሻ የያዘው ሒልተን ዓለም አቀፍ መሆኑም ታውቋል፡፡ በክፍሎች ብዛት ቀዳሚነቱን የያዘው ሒልተን ከ7,200 በላይ ክፍሎች ያሏቸውን 29 ሆቴሎች በአፍሪካ እየገነባ እንደሚገኝ ሲገለጽ፣ ማሪዮት ሆቴል በበኩሉ በ36 ሆቴሎች እየመራ ቢሆንም፣ በክፍሎች ብዛት ግን 6,412 ላይ በመወሰኑ ከሒልተን ባሻገር በካርልሰን ሬዚዶር ተቀድሟል፡፡ 

በሌላ በኩል ከወራት በፊት በአዲስ አበባ ተካሂዶ ዓለም አቀፍ ትኩረትን ስቦ የነበረው የአፍሪካ ሆቴል ኢንቨስትመንት ፎረም፣ በመጪው ዓመት መጀመሪያ ላይ በድጋሚ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ መዘገባችን ይታወሳል፡፡

የፎረሙ አዘጋጆች ከወራት በፊት ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ ለአራተኛ ጊዜ ተካሂዶ በነበረው ፎረም ሪከርድ የሰበረ ተሳትፎና ያልተጠበቀ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ሽፋን ማግኘቱ በአዲስ አበባ በድጋሚ እንዲካሄድ ለመወሰን ምክንያት ሆኗል፡፡ ከዚህም ባሻገር በሆቴልና በሌሎች የኢንቨስትመንት መስኮች የተሰማሩ ትልልቅ ኩባንያዎች ያሳዩት ፍላጎትና ተሳትፎም ጉባዔው በድጋሚ አዲስ አበባ እንዲካሄድ ማስገደዱን፣ ፎረሙን የሚያዘጋጀውና መገኛው እንግሊዝ የሆነው ቤንች ኤቨንትስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ማቲው ዌይስ ገልጸው ነበር፡፡ 

ከአምስት ዓመት በፊት ጀምሮ የአፍሪካ ሆቴሎች ኢንቨስትመንት ፎረም በአዲስ አበባ እንዲካሄድ ለማድረግ ሲንቀሳቀስ የቆየው አገር በቀሉ ካሊብራ ሆስፒታሊቲ ኮንሰልታንሲ ኤንድ ቢዝነስ ኩባንያ መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡ ስለፎረሙ በድጋሚ መምጣት ከሪፖርተር ጥያቄ የቀረበላቸው የካሊብራ አማካሪ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ነዋይ ብርሃኑ፣ በመጪው ዓመት መስከረም ወር አጋማሽ ላይ እንዲካሄድ ቀነ ቀጠሮ የተያዘለት ፎረም እንዲመጣ መወሰኑ እንደማይቀር ከዚህ ቀደም የታየው ስኬታማ ዝግጅት ጠቋሚ እንደነበር መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡

ከሆቴሎች ባሻገር በካሊብራ አማካሪ ኩባንያ በኩል ድርድር እያደረጉ ከሚገኙ መካከል ሦስት ተጨማሪ ሆቴሎች፣ ቀጣዩ ፎረም ከመካሄዱ በፊት ስምምነት ይፈጽማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ነዋይ ለሪፖርተር መግለጻቸውን በመጥቀስ መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ለሁለተኛ ጊዜ በሸራተን አዲስ ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው ፎረም፣ በቅርቡ ሥራ የጀመረው የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅትና የኢትዮጵያ ቱሪዝም ምክር ቤት እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተሰምቷል፡፡ ቤንች ኤቨትንስ ኩባንያም ለእነዚህ መንግሥታዊ ተቋማት ፎረሙ በድጋሚ በአዲስ አበባ እንዲካሄድ የኩባንያው ቦርድ መወሰኑን በደብዳቤ እንዳሳወቃቸው ታውቋል፡፡

በዚህ ቀደም የተካሄዱትን የአፍሪካ ሆቴል ኢንቨስትመንት ፎረሞችን ሞሮኮ አንድ ጊዜ፣ ኬንያ ሁለት ጊዜ ያስተናገዱ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ መጪውን ጨምሮ ለሁለተኛ ጊዜ በማስተናገድ ኬንያን ትስተካከላለች፡፡ ከስድስት መቶ በላይ ተሳታፊዎች፣ በርካታ የአገር ውስጥና የውጭ ዓለም አቀፍ ሆቴሎችና አማካሪዎች፣ እንዲሁም የሆቴል አስተዳዳሪዎች በስፖንሰርነት የታሰተፉበት ከፍተኛው ፎረም በአዲስ አበባ መካሄዱን ቤንች ኤቨንትስ አስታውቋል፡፡ በመጪው ፎረም በስፖንሰርነት ለመሳተፍ ከወዲሁ ከተመዘገቡት መካከል ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኩባንያ ግንባር ቀደምት ሆኗል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ብራንድ ያላቸው ሆቴሎች ቁጥር ሦስት ብቻ መሆናቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት አገሪቱ ይኖራታል ተብሎ የሚጠበቀው ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን የሚያሟሉ ብራንድ ሆቴሎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እንደሚጨምር ትንበያዎች ይጠቁማሉ፡፡ በአገሪቱ ያሉ ጠቅላላ ባለ ኮከብ ሆቴሎች ቁጥር 120 ሲሆን፣ ያሏቸው የመኝታ ክፍሎች ብዛትም ከአንድ ሺሕ በታች ነው፡፡ 

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከግንቦት 1988 እስከ ሚያዝያ 1997 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ጊዜያት በሕገወጥ መንገድ የተያዙ ይዞታዎችን ሕጋዊ ለማድረግ ባወጣው መመርያ ለመስተናገድ ከቀረቡ 91 ሺሕ ጥያቄዎች፣ ለተወሰኑት ሕጋዊ ካርታ ተሰጠ፡፡ 

የአዲስ አበባ ይዞታ አስተዳደር ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት የቀረቡለት ጥያቄዎች ላይ ባካሄደው ማጣራት 32 ሺሕ የሚጠጉት ጥያቄዎች ቦታውን የያዙት ከ1997 ዓ.ም. በኋላ በመሆኑ ውድቅ ሲያደርግ፣ በበጀት ዓመቱ ለአምስት ሺሕ ሕገወጥ ባለይዞታዎች ሕጋዊ ካርታ መስጠቱ ታውቋል፡፡  

የአዲስ አበባ ከተማ ይዞታ አስተዳደር ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ደረጀ ላቀው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ የተያዙ ቦታዎች 44,547 ናቸው፡፡ ነገር ግን ምዝገባ በሚካሄድበት ወቅት ከ91 ሺሕ በላይ ጥያቄዎች መቅረባቸውን አቶ ደረጀ ገልጸው፣ 32 ሺሕ ያህሉ በመመርያው መሠረት ሊስተናገዱ የማይችሉ ናቸው ብለዋል፡፡

በዚህ ወር መጨረሻ በሚጠናቀቀው የበጀት ዓመት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ አምስት ሺሕ ቦታዎች ሕጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ሰጥቷል፡፡ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ አጠቃላይ ሥራውን በዚህ በጀት ዓመት የማጠናቀቅ ዕቅድ ቢኖረውም፣ የማጣራት ሥራው በመብዛቱ በሚቀጥለው በጀት ዓመት ቀጣይ ሥራዎች እንደሚኖሩ አቶ ደረጀ አስረድተዋል፡፡

ከ1988 እስከ 1997 ዓ.ም. ባለው ጊዜ የተያዙ ይዞታዎች ቢሆኑም፣ ከማስተር ፕላኑ ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው 2,346 ባለይዞታዎች ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸው ለመሬት ባንክና ማስተላለፍ ኤጀንሲ መላካቸውን አቶ ደረጀ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ከሕጋዊ ይዞታ ውጪ አስፋፍተው መሬት ከያዙና የይጠቃለልኝ ጥያቄ ካቀረቡ 14 ሺሕ ባለይዞታዎች ውስጥ፣ 3,160 የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንደታተመላቸው፣ ከሁለት ሺሕ በላይ የሚሆኑት ከማስተር ፕላኑ ተቃርኖ ያለው ይዞታ አጠቃለው በመያዛቸው ጥያቄዎቻቸው ተቀባይነት እንዳላገኙ አስታውቀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ1988 ዓ.ም. በፊት የተያዙ 65 ሺሕ ሰነድ አልባ ይዞታዎች ጥያቄ ማስተናገዱም ይታወቃል፡፡ ከዚህ በኋላ ከ1988 እስከ 1997 ዓ.ም. ድረስ የተያዙ ቦታዎች ከማስተር ፕላኑ ጋር ተቃርኖ የሌላቸው መሆኑ ከተረጋገጠ እንዲያስተናግዱ መወሰኑ ይታወሳል፡፡

ነገር ግን አሁንም ቢሆን ከ1997 ዓ.ም. በኋላ በሕገወጥ መንገድ ይዞታ የያዙ ግለሰቦች መንግሥት እንዲያስተናግዳቸው በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

በነ ዘመነ ካሴ መዝገብ የተከሰሱት 5 የመኢአድ አባሎች ናቸው አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርብላቸው ነው የጠየቁት የተከሰሱት የግንቦት 7 አባል ናችሁ ተብለው ነው በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ስልጠና ተሰጥቷችሁ የሽብር ተግባር ለመፈጸም ስትንቀሳቀሱ ነበር ተብለው ላለፉት ሁለት አመታት በእስር የሚገኙት እነዚህ ተከሳሾች አንዳርጋቸው ፅጌ የሚባል ሰው አናውቅም አንዳርጋቸው አሱ አውቃቸዋለሁ አሰልጥኛቸዋለሁ የሚል ከሆነም በናንተ ቁጥጥር ስር […]

ምርጫው ወያኔ በሚፈልገው እንደውም ባቀደው መንገድ አጠናቋል። “እረጭ ያለ ምርጫ”። እስከቅርብ ጊዜ እንዲደርሰን የተደረገው መረጃ ምርጫውን በመቶ ፐርሰንት ማሸነፋቸውን ነበር። አሁን ለይቶለታል። በመቶ ፐርሰንት ማሸነፋቸውን ብቻ ሳይሆን በተወሰኑት ምርጫ ጣቢያዎች ላይ አገኘንም የሚሉት ድምጽም በተመሳሳይ መቶ ፐርሰንት እንደሆነም ነው። ሌብነቱ እንዳለ ሆኖ ምርጫውን ከዚህ በተሻለና በሚመስል መንገድ ከውኖ በመንግስትነት ለመቀጠል መሞከሩን የሚያውቁት ነበር። አልፈለጉትም እንጂ […]

ብቻውን ሆኖ ከጥግ ቆሞ ይቆዝማል። ጸጉሩን እየፈተለ ይናደዳል . . . ብቻውን ያልጎመጉማል። ትንሽ ቆይቶ ያለቅሳል። ለጉድ! ያነባዋል። ሰው እንዳለ እንደሌለ አካባቢውን ይቃኛል። ገና ወደዚህ አካባቢ እንደመጣ ሲብስበት በሰው ፊት ያለቅስ ነበር። አሁን አሁን ግን ሲያለቅስ ሰው ሲያየው አይወድም። መጀመሪያ አካባቢ ጎረቤቶቹ ሲያለቅስ ሲመለከቱ ያጽናኑት ነበር። በኋላ ግን ቀውሷል ብለው ደመደሙ። እንዲያው በደፈናው ግማሾቹ ፍቅር […]

‹‹ደቀ መዛሙርቱ ከየአህጉረ ስብከቱ ተመርጠው ሲላኩ የቤተ ክርስቲያን ልጆች መኾናቸው እና የሃይማኖታቸው ጥንካሬ ታይቶ እንዲመለመሉ አህጉረ ስብከት ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል፡፡›› ‹‹ወደ ኮሌጅ የሚገቡ ተማሪዎች እና የሚያስተምሩ መምህራን መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ዕውቀታቸው እና መንፈሳዊ ሕይወታቸው እየታየ ወደ ኮሌጁ ገብተው እንዲማሩ እና እንዲያስተምሩ  ይደረግ፡፡›› /የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የጥቅምት ፳፻፬ ዓ.ም. ውሳኔ/ ‹‹የቤተ ክርስቲያን ከፍተኛየትምህርት ተቋማት እና …

መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ ቆይተው እንዲፈቱ ተወስኖላቸው ከእስር ቤት ሲወጡ እንደገና በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለወርቅ ላይ ፖሊስ አዲስ ክስ አቀረበ፡፡ እነ ወይንሸት ሰኔ 18/2007 ዓ.ም ቀደም ብለው ተከሰውበት በነበረው ተመሳሳይ ‹ወንጀል› ፖሊስ የምርመራ መዝገብ ይዞ ቀደም ብለው ውሳኔ ባገኙበት በተመሳሳይ ቄራ ፍርድ ቤት ቀርበው ዳኞቹ ‹‹እኛ ፈርደናል፤ እንዲለቀቁም […]

“ለቤተመጻህፍታቸው ጥሩ ፎቶዎች ያገኛሉ” ዳግም የመመረጥ ጭንቀት በማይኖርበት በሁለተኛው የአስተዳደር ዘመን ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ እንደታየው የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች አፍሪካን ለዕረፍት ይጎበኛሉ፤ ይዝናናሉ፡፡ የዱር እንስሳትን ያያሉ፤ “የአገራቸውን ባህል ልብስ” ከለበሱ የአፍሪካ ሹመኞች ጋር ጥሩ ፎቶዎችን ይነሳሉ፤ የሥልጣን ዘመናቸው ካለቀ በኋላ ለሚመሠርቱት ቤተመጻህፍት ማስዋቢያ የሚሆን ለየት ያሉ ፎቶዎችን ይሰበስባሉ፡፡ መጪው ወር (July) መገባደጃ አካባቢ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ […]

The post ኦባማ “የዕረፍት ጊዜ ለማሳለፍ” ወደ ኢትዮጵያ ይጓዛሉ appeared first on ሳተናው .

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-“በኢትዮጵያ ያሉ ሚንስትር ድኤታዎች ድምፅ አልባ እና ተሳትፎ የሌላቸው ደካማዎች ናቸው” ሲል የኢህአዴግ ጽ/ቤት የአመራር ግንባታ የመለስ ዜናዊ የአመራር ግንባታ ክፍል ያወጣው ደብዳቤ አመለከተ። ደብዳቤው ዝቅተኛ እና መካከለኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ያላቸውን ሚኒስትር ድኤታዎች ዘርዝሮ አስቀምጧል። በአቶ አዲሱ ለገሰ የሚመራው እና ከፍተኛ የኢህአዴግ አባላትን ብቻ የሚያሰለጥነው …

ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምንጮች እንደገለጹት የሮመዳንን ጾም ተከትሎ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቃውሞ እንደገና ሊያገረሽ ይችላል በሚል ስጋት፣ 53 ሚሊየን ብር በጀት በመመደብ የመስጊድ ኢማሞችን በአክራሪነት ዙሪያ የማሰልጠን እና የማግባባት ስራውን እያከናወነ ነው፡፡ አንዴ ሞቅ ሌላ ጊዜ ቀዝቀዝ ሲል የሚታየው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ አሁንም መንግስትን እንቅልፍ እንደነሳው ነው፡፡ በሁሉም ክልልች ለሚገኙ …

ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በብዙ መቶ ሚሊዮኖች ብር ወጪ ይሰራል የተባለውን የመለስ ፋውንዴሽን ለማስገንባት ህዝቡ በፈቃደኝነት ገንዘብ ያዋጣል ተብሎ ሲጠበቅ፣ የህዝቡ መልስ አስደንጋጭ መሆኑን የተረዳው በወ/ሮ አዜብ መስፍን የሚመራው ፋውንዴሽን፣ የመንግስት ስልጣንን በመጠቀም የመንግስት ደሞዝ ተከፋይ ሁሉ ገንዘብ እንዲያዋጣ ለማስገደድ ሞክረዋል። ግምገማ በመፍራትና በግዳጅ ገንዘብ እንዲያዋጡ ከተደረጉት መካከል የመከላከያ ሰራዊት …

ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ወጣት ተመስገን ታፈሰ ተሰማ ዕድሜው 22 ዓመት ሲሆን በትምህርት ደረጃውም በማኔጅመንት የመጀመሪያ ድግሪ ያገኘ ወጣት ነው፡፡ ትውልዱና ዕድገቱ በደቡብ ክልላዊ መንግስት በቡርጂ ወረዳ ውስጥ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የኢማዴ-ደህአፓ/መድረክ አባል ሆኖ ለመታገል የወሰነና በመድረክ አባልነታቸው ምክንያት በሀገራቸው ሠርተው የመኖር የዜግነት መብታቸውን እየተነፈጉ አስተዳደራዊ ግፍ እየተፈጸመባቸው ካሉ …

ኢሳት ዜና (ሰኔ 18፥ 2007) በኢትዮጵያ አየር ሀይል ውስጥ ባለው ዘረኝነትና አስተዳደራዊ በደል በመንገፍገፍ ከሰራቱ የሚለዩት የበረራ ባለሙያዎች ቁጥር እየጨመረ መገኘቱን እንዲሁም ሙስና በከፍተኛ ደረጃ መስፋፋቱን የአየር ሀይል ምንጮች ለኢሳት ገለጹ።  በህገ-ወጥ የሰው ዘውውር የአየር ሀይል አባላት የታሰሩ መሆናቸውንም  ለመረዳት ተችሏል። በ2007 አ/ም ብቻ አስር የበረራ ባለሙያዎች ስርአቱን በመክዳትና ወደ እስር ቤት በመጋዝ ከአየር ሀይሉ …

የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 18/2007 ዓም በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ ባወጣው መግለጫ የኢህአዴግ/ወያኔን መንግስትን ማስጠንቀቁን ሮይተርስ ዘገበ አቶ አንዳርጋቸው የህግ ድጋፍ በማያገኙበትና ይግባኝ ሊጠይቁ በማይችሉበት ሁኔታ በአስከፊ ሁኔታ መታሰራቸውን የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሀሞንድ አውግዘዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ እና ደህንነት እንደሚያሳስበን በተደጋጋሚ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም ብንገልጽም ከቃል ያለፈ መልስ አለገኘንም፣ […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ሰኔ ፲፰ (አስራ ሰምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምንም አይነት መረጃ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ከፍተኛ ቁጥጥርና ክትትል የሚደረግበት ከሰኔ አንድ ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አዘጋጅነት የተጀመረው ግምገማ ፈታኝ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል። ግምገማውን ተከትሎ አንዳንድ ፖሊሶች በደህንነቶች ተደብድበዋል። በጉለሌ ክፍለከተማ መምሪያ ስር የሚገኙ አንድ የሳጅን ማእረግ ያለውና አንድ ተራ ፖሊስ የአቶ …

ሰኔ ፲፰ (አስራ ሰምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸው የህግ ድጋፍ በማያገኙበትና ይግባኝ ሊጠይቁ በማይችሉበት ሁኔታ በአስከፊ ሁኔታ መታሰራቸውን የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ፊሊፕ ሀሞንድ አውግዘዋል። የአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ እና ደህንነት እንደሚያሳስበን በተደጋጋሚ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም ብንገልጽም ከቃል ያለፈ መልስ አለገኘንም፣ የምክር እና ራሳቸውን መከላከል የሚችሉበት መብትም አላገኙም ሲሉ የገለጹት …

ሰኔ ፲፰ (አስራ ሰምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤትን በመጥቀስ ሪፖርተር እንደዘገበው በማዕድን ሚኒስቴር ላይ በ2006 ዓ.ም. አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ላይ ባደረገው የክዋኔ ኦዲት አገሪቱ ከፍተኛ ገንዘብ ማጣቷን አረጋግጧል፡፡ የማዕድን ሥራ አዋጅ ቁጥር 678/2002 የከበሩ ማዕድናት ላይ ስምንት በመቶ ፣ያልከበሩ ማዕድናት ላይ ደግሞ ስድስት በመቶ የሮያሊቲ ክፍያ መጣሉን ሪፖርቱ …

እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለትግሬዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦሮሞዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአማራዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሶማሌዎች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአፋሮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለኦጋዴኖች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለአኙዋኮች ጥብቅና እቆማለሁ፣ እኔ ከያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የበለጠ ለሲዳማዎች ጥብቅና […]

‘የአፍሪቃ ድሃ ባይጠግብም እንኳ ቀምሶ ካደረ ይበቃዋል’ አይነት ንቀት የተሞላው የምዕራቡ አለም ምልከታ ከመቼውም ጊዜ በከፋ መልኩ አፍጦና አግጦ እየታየ ነው፡፡ በርሃባችንና በእርስ በእርስ መናቆራችን ለዘመናት ሲነግዱበትም ሲማረሩበትም ቆይተዋል፡፡ ዛሬ ዛሬ የመጫወቻው ካርድ ተቀይሮ ለአፍሪቃ አንባገነኖች አንድ ቃል ተለጥፎላቸው ካሳላፍነው ታሪክ ምናልባትም በከፋ መልኩ ጉዟችንን ቀጥለናል፤ የኋሊት ይሁን ወደፊት እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ነገር ግን የምዕራቡ አለም […]

ኢትዮጵያዊያን፤ ተከታታይ አምባገነን መሪዎችን ከነአገልጋዮቻቸው ለማስወገድና የሕዝቡን የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ የምናደርገው ትግል፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ ነው። በ ፲፱፻፷፮ ዓመተ ምህረት ሕዝቡ የተነሳባቸው የመብትና የመሬት ባለቤትነት ጥያቄዎች አሁንም አልተመለሱም። ይኼው ሃምሳ ዓመት አለፈው። ይባስ ብሎ ሕዝቡን የመንግሥት አገልጋይ አድርጎ የሚጠቀም ጠባብ አምባገነን ገዢ፤ በሀገራችን ነግሷል። ይኼን መንግሥት ለማስወገድ የሚደረገው ትግል ማዕከል የለውም። በሀገር ቤት ከፍተኛውን […]

በሕብረተሰባች ውስጥ ንዝህላልነት ወይም ዳተኛነት ጎልቶ ይታያል፤ ራሱን፣ ትውልዱን ፣ሀገሩን ጭምር፣ለዘለቄታው ለሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ያለው ተሣትፎ የቀዘቀዘ ነው። መንስዔውን ለመግለጽ በተረጋገጠ እውነት ላይ የተመሠረተ ማስረጃ የለኝም። ሆኖም በጋራም ሆነ በተናጠል ለሚመራበት፣ የፖለቲካ ሥርዐት በአሉታም ሆነ በአዎንታ ፍላጎቱን በነፃነት መግልጽ አይችልም፤ ላለፉት ሁለተ አሥርት ዓመታት በቁርጥኝነት ራሱን ገልፆ ለራሴም ለሀገሬም ይጠቅማሉ በሎ ያመነበትን ይዞ የቀጠለበት ሁኔታ […]

ወጣቱ ፖለቲከኛ ዳዊት አስራደ የሚወዳቸውን ቤተሰቡንና ልጁን ትቶ ከሀገር መሰደዱ ተሰምቷል፡፡ ዳዊት ከ13ቱ የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የስራ አስፈጻሚ እንዲሁም የብሄራዊ ምክር ቤት አባልና የአንድነትን የአምስት አመት ስትራቴጂክ እቅድም ከሌሎች የፓርቲው አመራሮች ጋር በመሆን የነደፈ ሙሉ ማንነቱን ለሀገር ትግል የሰጠ ቁርጥ ኢትዮጵያዊ ልጅ ነው፡፡ በ2002 ዓ.ም በአማራ ክልል ምርጫ ቅስቀሳ ላይ እያለ በመኪና ተገጭቶ ለ6 […]

ከሀገር ውጭም በስደት በሕውሓት ሰላዮች ክትትል ይደረግባቸው የነበሩ ኢትዮጵያውያኖች ከሰዳን ወደሊቢያ ገዞ ላይ እንዳሉ የሕውሓት ሰው ከሱዳን አቻው ጋር በመሆን በሱዳን ወታደራዊ ተሽከርካሪ ስደተኞቹ የተሳፈሩበትን ተሽከርካሪ በመግጨት አና እንዲገለበጥ በማድረግ አዳጋ ከደረሰባቸው መካከል የሥርዓቱ ሰው የነበረን ቁስለኛ ከሌሎች ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል ፎቶ ከኪሱ በማውጣት ከፎቶው ካስተያየ በኋ በያዘው ሽጉጥ እንደረሸነው የአይን ምስክር ከሞት በተረፉት ሊጋለጥ […]