በአሁኑ ወቅት 30 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀውና በሦስት ዓመታት ውስጥ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመለከተ፣ ‹‹ቴክኒካዊ›› በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ድርድሮች እየተደረጉ ነው፡፡

በእያንዳንዱ ድርድር ከሚስተዋሉ አቋሞች ግን ለዘመናት የቆዩ ሴራዎች መልካቸውን ቀይረው እየመጡ ይመስላል፡፡

በታላቁ የዓባይ ግድብ ላይ የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ቡድን ጥናት ውጤት የያዘው ሪፖርት አሁን እየተደረጉ ላሉት ድርድሮች መሠረት የሚጥል ነው፡፡ ሪፖርቱ እንደሚለው፣ የግድቡ ግንባታ እንዲቋረጥ ምንም መሠረታዊ ምክንያት ባለመኖሩ፣ በተቻለ መጠን በታችኛው የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ላይ ሊያስከትለው የሚችለው የውኃ ፍሰት መጠን መቀነስና ቴክኒካዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሦስቱም አገሮች ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን በጋራ ተቀራርበው መሥራት እንዳለባቸው ነው፡፡ በተረፈ የግድቡ ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን ሪፖርቱ አጽንኦት ይሰጣል፡፡

የግብፅ ዥንጉርጉር አቋሞች

ኢትዮጵያና ሱዳን ሪፖርቱን በፀጋ የተቀበሉት በመሆናቸው ሚስጥርነቱ እንደተጠበቀ እንዲቆይም የሚቻላቸውን ጥረት አድርገዋል፡፡ በሌላ በኩል ግብፅ በሪፖርቱ ላይ የተዘበራረቀ አቋም እያንፀባረቀች በመሆንዋ ሪፖርቱ ይፋ በሆነበት ወቅት በተጠራው ብሔራዊ ምክክር፣ በተለይ የግብፅ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በኢትዮጵያ ላይ ጦር ኃይሉ እንዲዘምት ድምፃቸው ተሰምቷል፡፡ ግብፅ ባጋጠማት ቀውስ ምክንያት እየተደረጉ ያሉት የባለሥልጣናት መቀያየር የግብፅ መንግሥት አቋም ለትንተና የማይመች ቢሆንም፣ አንዱ የሌላውን ስህተት እየደገመ ይመስላል፡፡ አንዱ ከሌላው ስህተት እየተማረ አይመስልም፡፡ አሁን ሥልጣን ላይ ያለው የሽግግር መንግሥት ከአንድ ዓመት የሥልጣን ቆይታ ጊዜ በኋላ የተባረረውን የፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ መንግሥት በኢትዮጵያና በዓባይ ግድብ ላይ የተለሳለሰ አቋም መያዙ ለውድቀቱ ምክንያት መሆኑን እየተናገረ ነው፡፡

ሁለተኛ ከላይ ከተጠቀሰው ምክንያት ጋር ተያያዥነት ያለው ቢሆንም፣ ግብፅ በአንድ በኩል የባለሙያዎቹ ሪፖርትን አለመቀበልዋና በሌላ በኩል የቡድኑን ምክረ ሐሳብ ለመተግበር ድርድር እንዲደረግ መስማማቷ እርስ በርስ የሚጣረሱ አካሄዶች ናቸው፡፡

ሦስተኛ ሪፖርቱን በተመለከተ በሚስጥር ተይዞ መቀመጥ በነበረበት ጊዜ አንዳንድ ተፅዕኖ ያሳርፋሉ ተብለው ለሚገመቱ አገሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተላልፎ እንዲሰጥ ማድረጓ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ዋሽንግተን ፖስትን ጨምሮ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሪፖርቱን ድምዳሜ በተሳሳተ መንገድ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይህ እንግዲህ በአገር ውስጥ የሚደረገውን አሉታዊ የሚዲያ ቅስቀሳን ጨምሮ ማለት ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ ግብፅ የሪፖርቱን ውጤት መቀበሏን በግልጽ ባታሳውቅም፣ የባለሙያዎች የቡድንን ምክረ ሐሳብ ለመተግበር በቅርቡ ያለውጤት የተበተነውን ጨምሮ ሦስት ጊዜ ድርድር ተቀምጣ ነበር፡፡

ከኢትዮጵያ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የባለሙያዎች ቡድን ያቀረበውን ምክረ ሐሳብ ተግባራዊ ለማድረግና ይህንን ተግባራዊ የሚያደርግ ኮሚቴ ለማቋቋም በሁለቱም የመጀመርያ ድርድሮች ግብፅ ተስማምታ ነበር፡፡

በኮሚቴው አወቃቀር ላይ አንዳንድ ውዝግቦች የነበሩ ቢሆንም፣ በመጨረሻ በኮሚቴው ውስጥ ሦስቱን አገሮች የሚወክሉ ዜጐች ብቻ እንዲካተቱ ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር፡፡ ይህ የኢትዮጵያ አቋም ነበር፡፡ ኮሚቴውም ምክረ ሐሳቡን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ የውጭ አማካሪ ድርጅትን የመቅጠርን ሥራ ጨምሮ አማካሪው የሚያቀርበውን ሐሳብ ይገመግማል ይላል፡፡

ባለፈው ሳምንት በካርቱም በተደረገው ሦስተኛው የድርድር ዙር ግን የግብፅ ተወካዮች ዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት እንዲቀጠር ይጠይቃሉ፡፡ የውኃ፣ የመስኖና የኢነርጂ ሚኒስቴር የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅ አህመድ ግብፆች እንዲቀጠር የፈለጉት የውጭ አማካሪ ድርጅት ቀደም ሲል ስምምነት ከተደረሰበት መንፈስ ውጪ የሚቋቋመውን ኮሚቴ በበላይነት የመቆጣጠር ኃላፊነት እንዲኖረው የሚል ድብቅ አጀንዳ የያዘ መሆኑን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ድርድሩ ያለውጤት ሲበተን በቀጣይነት ግን ለመነጋገር ቀጣሮ ተይዟል፡፡

የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን አባል የሆኑት በዓባይ ወንዝ ፖለቲካ ላይ ግንባር ቀደሙ ተመራማሪው ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በግብፅ የቀረበው የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ቡድን እንዲመሠረት ብትቀበልም በሁለት ነገሮች አለመግባባት ተፈጥሯል፡፡ አንደኛው የባለሙያዎቹ ቡድን በሦስቱ አገሮች የጋራ መግባባት (ሙሉ በሙሉ) መመሥረት አለበት የሚል የኢትዮጵያ አቋምን ግብፅ መቀበል አለመቻሏ ነው፡፡

ሁለተኛው የባለሙያዎቹ ቡድን የሚመሠረተው ከሦስቱም አገሮች የተውጣጡ አባላትን ያቀፈው የምክረ ሐሳቡን አስፈጻሚ ኮሚቴ ባለሙያዎች ቀጥሮ ሥራውን ሲያስፈጽም ድንገት አለመግባባት ከተፈጠረ እንጂ፣ አሁን የሚመሠረትበት አመክንዮ የለም የሚለው የኢትዮጵያ አቋም ነው፡፡

ሌላው ስብሰባው ያለ ውጤት እንዲበተን ምክንያት የሆነው ሦስቱም አገሮች የጋራ መግባባት እንዲኖራቸው ግብፆች ሰባት መርሆች ይዘው መቅረባቸው ነበር፡፡ የመግባባት ሰነድ መፈራረም የዚሁ ስብሰባ አጀንዳ ካለመሆኑም ባሻገር፣ ቀደም ሲል በተለይ የውኃ አጠቃላይ የስምምነት ማዕቀፍ ላይ ሲፈራረሙ፣ ከአሥር ዓመት በላይ ከቆዩ በኋላ አሁን እንዲህ ዓይነት አጀንዳ ላይ መነጋገር ዋናውን ጉዳይ ወደ ጐን ለመግፋት ያለመ በመሆኑ ኢትዮጵያ ያልተቀበለች ምክንያት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ እንደ ዶ/ር ያዕቆብ እምነት፣ ጥያቄው ሒደቱን ወደ ኋላ የሚመልስ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የተደረገውን የሚቃረን መርህ ነው፡፡

ዴይሊ ኒውስ የተባለ ጋዜጣን ጨምሮ አብዛኞቹ የግብፅ ሚዲያዎች ግን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸውን ዋቢ አድርገው የዘገቡት ከዚህ በተቃራኒ ነው፡፡ ‹‹ከሦስቱም አገሮች የተውጣጣ አንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም ግብፅ ያቀረበችው ሐሳብ በኢትዮጵያ ተቀባይነት አላገኘም፤›› በሚል፡፡

ምን ማለት ነው?

ዓለም አቀፍ የውኃ ኤክስፐርቶች ያሉበት ቡድን ግድቡን አጥንቶ ሪፖርቱን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ ያቀረበውን የምክረ ሐሳብ ለመተግበር ተደጋጋሚ ድርድር እየተደረገ ቆይቷል፡፡ አሁን ግን ድርድሩ እንከን እያጋጠመው ይመስላል፡፡

ዶ/ር ያዕቆብ፣ ‹‹ወደፊት ድርድሩ ምን የሚሆን ይመስልዎታል?›› በማለት ከሪፖርተር ለቀረብላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ‹‹አሁን እየተሠራ ያለው ሥራ በባለሙያዎች ደረጃ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ጥናት እንዲደረግ ነው፡፡ በቁጥር ተለክቶ ተወስኖ የሚገለጽ ነገር ነው፡፡ ግብፆች ያንን ነገር መቀበል አይፈልጉም፤›› ብለዋል፡፡

እንደተደራዳሪም እንደ የፖለቲካል ሳይንስ ተመራማሪም የጀመሩትን ምላሽ በመቀጠል፣ ‹‹በቴክኒክ ደረጃ ያለውን ነገር ወደ ላይ ወደ መሪዎች ግብፆች ተመልሶ እንዲሄድና ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ይፈልጋሉ፡፡ እስካሁን የተሠራውንና የተለፋበትን መና የሚያስቀር ነው፡፡ እንዳልተሠራ ሆኖ ወደ ኋላ የሚመለስ ከመሆኑም በላይ፣ በዚያውም ግብፆች የፖለቲካ ውዝግቡን ለሚዲያ ቀልብና ትችት ይዳርጋሉ፤›› ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ በኩል እያንዳንዷ እንቅስቃሴ በጥንቃቄ የምትታይ መሆኗን፣ ድርድሩ በዝርዝርና በቴክኒክ አፈጻጸም ጉዳዮች ላይ እንጂ ወደ ፖለቲካ ተመልሶ የሚሄድበት መንገድ በሩ ዝግ ነው ብለዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህርና በዓባይ ውኃ ውዝግብ ላይ ጥናት ያካሄዱት አቶ ዘሪሁን አበበ በበኩላቸው፣ በአብዛኛው የኢትዮጵያ ተደራዳሪውን ዶ/ር ያዕቆብ ሐሳብ ይደግፋሉ፡፡ ‹‹በግብፅ በኩል ለማድረግ የሚፈለገው አንድና አንድ ነው፡፡ የግድቡ ሥራ እንዲቋረጥ ወይም በጣም ትንሽ ሆኖ እንዲገነባ ነው፡፡ ያ እስካልተሳካላቸው ድረስ ጉዳዩ ሁሌም ፖለቲካዊ መልክ ይዞ በሚዲያ እንዲራገብና ኢትዮጵያን ለማስተቸት ይፈልጋሉ፤›› ብለዋል፡፡ ዞሮ ዞሮ ፍላጐታቸው ቀደም ሲል በብቸኝነት የተፈረመውን እ.ኤ.አ. የ1959 ‹‹ውል›› ማሽከርከር እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ እንደ አቶ ዘሪሁን ገለጻ፣ ግብፆች በአንድ በኩል የተፋሰሱን አገሮች የውኃ ትብብር ማዕቀፉን በጀርባ እየመጡበት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት የያዘው መንገድ እንዳለ ሆኖ፣ በዓባይ ተፋሰስ አገሮች ሥራ ላይ የዋለውንና ሕግ ሆኖ የፀደቀውን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በፈራሚ አገሮች ፓርላማ እንዳይፀድቅ ጥረት ያደርጋሉ፡፡

የተመናመነው የመደራደር አቅም

በዓባይ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች በሦስት አገሮች መካከል ብቻ የሚደረጉ የሦስትዮሽ ድርድር ሆነዋል፡፡ ቀደም ሲል በግድቡ መገንባት ተቃውሞ ቢጤ አሰምታ የነበረችው ሱዳን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አቋሟን ለመከለስ ተገዳለች፡፡ በመሆኑም አሁን በጉዳዩ ላይ በሚደረጉ ድርድሮች ጐልተው እየወጡ ያሉት ጫፍ የረገጡ ውዝግቦች በሁለቱ አገሮች ማለትም በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ሆነዋል፡፡ ይኼውም ከ80 በመቶ በላይ የዓባይን ውኃ ጥቅም ላይ በምታውለው ግብፅና ለዓባይ ውኃ 86 በመቶ አስተዋጽኦ በምታደርገው ኢትዮጵያ መካከል ነው፡፡ ውዝግቡ በተለያዩ መንገዶች የሚገለጽ ሲሆን፣ የሱዳን አቋም መለወጥ የግብፅን የመደራደር አቅም እየተመናመነ እንዲመጣ ምክንያት መሆኑን አንድ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ስማቸው እንዲገለጽ የማይፈልጉ የውኃ ዲፕሎማሲ ተመራማሪ ተናግረዋል፡፡ እሳቸው እንደሚሉት፣ የግብፅ የመደራደር አቅም የተመናመነው ግብፅ ውስጥ ባለው ቀውስ ምክንያት ብቻም አይደለም፡፡ እንዲያውም ሚዲያዎቻቸው ከሚዘግቡት ማስተዋል እንደሚቻለው፣ የግብፅ ፖለቲከኞች አገራቸው ከገባችበት ቀውስ መውጣት የምትችለው አንድ ትልቅ ውጫዊ የሆነ አጀንዳ በመፍጠር መሆኑን የተስማሙ ይመስላሉ፡፡ እሱም የዓባይን ጉዳይ በማቀንቀን ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የተባለችውን ‹‹ነባር ጠላት›› ማስቀደምና የውስጥ ጉዳያቸው በድርድር እንዲቆይ ማድረግ ነው፡፡ እንደ ዲፕሎማቱ እምነት ሱዳን በግድቡ ላይ የነበራት አቋም ሲለወጥ በግብፅ ላይ ከፍተኛ መደናገጥ ነበር የፈጠረው፡፡

የዓባይን ግድብ በተመለከተ የሱዳን አቋም መለወጥ ብቻ ሳይሆን፣ የግድቡን ተፅዕኖ ያጠኑት የውኃ ባለሙያዎች ቡድን ሪፖርት የግብፅ ፖለቲከኞች በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠሩትን ሴራ አክሽፎባቸዋል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ግብፆች በኢትዮጵያ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያደርጉት ጉትጐታ ተቀባይነት እንዳይኖረው አድርጐታል፡፡ በተቃራኒው የኢትዮጵያን አቋም በይፋ ሙሉ ለሙሉ ተሰሚነት አገኘ ባይባልም፣ አንዳንድ ትልልቅ መገናኛ ብዙኃን ሚዛኑን በጠበቀ አኳኋን መዘገብ ጀምረዋል፡፡ አሁን ቴክኒካዊ የሆነ ድርድር ወደ ፖለቲካ ደረጃ ከፍ ብሎ ውዝግብ እንዲፈጥር የሚፈለግበት ምክንያት ይኸው ነው፡፡

ቀደም ሲል ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ የምታራምደውን የማዳከም ስትራቴጂ የተገነዘበው የኢትዮጵያ መንግሥት ግድቡን ሙሉ ለሙሉ በራሱ ወጪ ለመገንባት ነበር ያቀደው፡፡ በመሆኑም በፕሮጀክቱ ተፈጥሮም ሆነ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የወጣው ዓለም አቀፍ ሪፖርት ግብፅ በውጭው ዓለም ልታሳርፍ የነበረውን ተፅዕኖ በእጅጉ ቀንሶታል፡፡

‹‹በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ›› እንዲሉ፣ በቅርቡ ለግብፅ የውጭ ፖሊሲ ማስፈጸሚያ እንዳትውል ትሰጋ የነበረችው ሱዳን አቋም መለወጥ ብዙ ነገሮችን በግብፆች ላይ ያወሳሰባቸው ይመስላል፡፡ እዚህ ላይ ሁለት ነገሮች ማስታወስ ግድ ይላል፡፡

አንደኛው ከሁለት ዓመት በፊት የአሜሪካ አንድ የደኅንነት ድርጅት (Stratford) እና ዊኪሊክስ ይፋ እንዳደረጉት፣ ግብፅንና ሱዳን ኢትዮጵያንና ታላቁን ግድብ ለማጥቃት ሐሳብ ነበራቸው ተብሎ ነበር፡፡

ሁለተኛው ሱዳን ሥጋት በሚፈጥረው የሁለቱ አገሮች ጦርነት ውስጥ በቀጥታ ትሳተፋለች የሚል ግምት ያልነበረ ቢሆንም፣ ግብፅ ኢትዮጵያን ለማጥቃት የቅርብ ጐረቤት የሆነችው የሱዳንን ግዛት እንደ መንደርደርያ ልትጠቀምበት ትችላለች የሚል ግምት ነበር፡፡

ግብፅ የዓባይን ውኃ በብቸኝነት ለመጠቀም ታዋቂና በአብዛኛው የውኃው ባለቤት ከሆነችው ኢትዮጵያ ውጪ የተደረጉት እ.ኤ.አ. የ1929ና የ1959 አሮጌ ስምምነቶች በአዲሱ ሁለገብ የውኃ አጠቃቀም ማዕቀፍ (CFA) በስድስት አገሮች ፈራሚነት መተካታቸውና ሕግ ሆነው መፅደቃቸው ይታወሳል፡፡

ሪፖርተር

በሃገራችን ውስጥ እየተከሰተ ያለው የሰብኣዊ መብት ጥሰት እኛ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን የአለም ህዝብ ትኩረት በመሳብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በገሃድ እየታየ ነው:: ይህ የሰብኣዊ መብት ጥሰት የሚፈጸመው ቁልፍ ባለስልጣናት የፖሊስ መኮንኖችን በመጠቀም የህዝብን ሰላም ማደፍረስ እና ሽብር መንዛት የእለት ተግባራቸው አድርገው ተያይዘውታል::

ብልሃት በሌለው መልካም አስተዳደር የፖሊስ ባለስልጣናት የሚፈጽሙት ኢሰብኣዊ ተግባራት የህዝብን የመኖር ሁኔታ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከቶታል::ከጥያቄ ምልክትም አልፎ ከባባድ ወንጀሎች በህዝብ የእለት ተለት ሂደት ውስጥ ራሱን መንግስት ያሰኛው ሕወሓት እየፈጸመ ነው::የኢትዮጵያ ህዝቦች ሃይማኖት እና የፖለቲካ አስተሳሰብ ሳይለያቸው በጋራ የሚያቀርቡትን ጥያቄ
ላይ መልስ መስጠት እየተቻለ በጉልበት እና በማስፈራራት በመግደል እና በማሰር የሚመጣ ለውጥ የለም:; የህዝቦች ትግል በየፈርጁ እየቀጠለ ይሄዳል::ማንኛውም ህዝብ ለለውጥ እስከተነሳ ድረስ የሚሞትለት አላማ እንዳለውም ማሰብ ያስፈልጋል::

ባለስልጣናት ህጋዊ የሆኑ ዜጎች እንዲታሰሩ እንዲገላቱ የሚያደርጉት ከተጠያቂነት አያድናቸውም:; ህገመንግስታዊ መብቶችን በመጣስ ዜጎችን በአገራቸው እና ህጋዊ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማዋከብ ስልጣን ላይ ያለው ጁንታ ህግን እንደማያከብር ፍንትው አድርጎ ያሳየበት ህገወጥ ተግባር በተደጋጋሚ እያየን ነው:: ራሳቹህ ያወጣችሁትን ህግ ያላከበራችሁ እኛ እንዴት እናክብርላችሁ?? መጀመሪያ አንድ መንግስት ባለስልጣኖቹ ህግን አክብረው ለህዝቡ አርኣያ መሆን አለባቸው:: እያየን ያለነው ግን ሕግ አውጪው እና አስፈጻሚው አካል ህግን እየጣሰ መሆኑን ነው:: ስለዚህ ብልሃት አልባ ዲሞክራሲ በሞላባቸው እና የሰውን ልጅ መብት ትርጉም በማያቁ ባለስልጣናት ከመመራት ሞትን መርጦ መታገል አማራጭ እየሆነ ያለበት ዘመን ላይ ደርሰናል::

ከማናችንም ኢትዮጵያውያን በፊት ባለስልጣናት ህግ አውጪዎች ህግ አስፈጻሚዎች እና የጸጥታ ሃይሎች ለህግ ተገዢ ይሁኑልን::ለእኛም አርኣያ ይሁኑ::በጉልበት እና በሃይል በብልሃት አልባ ዲሞክራሲ ሽብር እየነዙ ሃገር አይመራም!!!ምንሊክ ሳልሳዊ

በወያኔ ዘርኝነት፤ ጎጠኝነትና ወደር የለሽ ጭቆና ከሁለት አስርተ አመታት በላይ ጀርባዉ የጎበጠዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ሁለት ወራት ዉስጥ በሁለት እጅግ አስቀያሚና ዘግናኝ በሆኑ የታሪክ ምዕራፎች ዉስጥ አልፏል። ለወትሮዉ በወርሃ ህዳርና ታህሳስ፤ ህዳር ሚካኤልንና የገና በዐልን እያከበረ አጆቹን ወደ ፈጣሪዉ የሚዘረጋዉ የኢትዮጵያ ህዝብ፤ ዘንድሮ ከእነዚህ ሁለት የቆዩ ባህሎቹና ወጎቹ ፈቀቅ ብሎ በሁለት ክብሩን ባዋረዱና ማንነቱን ጥያቄ ዉስጥ በከተቱ ከስተቶች ልቡ ቆስሎ ከራሱ ጋር ሲነታረክ ሰንብቷል። የፈጠረዉን አምላክ መለምን እንጂ በፈጣሪዉ አማርሮ የማያዉቀዉ የኢትዮጵያ ህዝብ . . . የሚያስብልኝ መንግስት እንደለሌለኝ አዉቃለሁ፤ አምላኬ ግን በፍጹም አይረሳኝም። ምነዉ ቅዱስ ሚካኤል አንተና ሰይፍህ እያላችሁ እንዴት እንዲህ ይደረጋል አንዴ . . . እያለ በምድራዊዉም በሰማያዊዉም መንግስታት ላይ የመረረ ጩኸቱን አሰምቷል።
በህዳር 2006 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ አገራቸዉ ዉስጥ የስራ ዕድል ተነፍገዉ ስራ ፍለጋ ወደ ሳዑዲ የተሰደዱ ወገኖቹ በሳዑዲ ፖሊስና ህዝብ ከፍተኛ በደል ሲፈጸምባቸዉ ተመልክቶ በኃዘንና በቁጭት ልቡ በግኗል። በተለይ ወንዶች ልጆቹ ፈለጊ እንደሌለዉ እንስሳ በየአደባባዩ ሲረገጡና ሲደበደቡ፤ ሴቶች ልጆቹ ደግሞ በየማጀቱ ሲደፈሩ ተመልክቶ ለህዝብና ለአገር ለሚያስቡ አስተዋይና ጨዋ መሪዎች ባለመታደሉ በባዕድ አገር ዉስጥ በደረሰበት ዉርደትና መከራ በአለም አቀፍ ደረጃ ጩኸቱን አሰምቷል።በዚሁ በ2006 ዓም በታህሳሰ ወር አጋማሽ ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ብርድ ልብስ ተጠቅልሎ የተጣለ የሰዉ ልጅ አጽም ቀርቶ በስመአብ ተብሎ የታረደ በሬ ስጋም ማየት በማይፈልግበት በገና ፆም ወቅት የገዛ ወገኖቹ አጽም በመንገድ ቆፋሪዎች ከመሬት ዉስጥ እየተጎተተ ሲወጣ አይቶ በቆሰለ ልብና በነደደ አንደበት “እባክህ ፈጠሪ ወይ ዉረድ ወይ ፍረድ” እያለ ከወያኔ ጋር ከመኖር የፈጣሪን ፍርዱን አለዚያም ዳግም ምጽአቱን ተመኝቷል።
ባለፉት ሁለት ወራት ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ድፍን ህዳርንና ታህሳስን በአለም ዙሪያ በአራቱም ማዕዘን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንን ያሰባሰበ፤ ያነጋገረ፤ ያበሳጨ፤ ያስቆጨና አንጀት ያሳረረ ጉዳይ ነበር። አዎ የ2006 ህዳርና ታህሳስ አገር ዉስጥም ካገር ዉጭም ለምን መጡ የሚያሰኙ የቀን ጎደሎዎች ነበሩ። የወገኖቹ በባዕድ አገር አላግባብ መታሰር፤መደብደብና መገደል ያበሳጨዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ ሀዘኑና ብስጭቱ ሳይላቀቅ ነበር ባለፈዉ ታህሳስ 18ትና 19 ቀን ሌላ አሳዛኝና አስደንጋጭ ዜና የጭንቅና የመከራ ጓዳ የሆነችዉን መዲናችን ከአዲስ አበባን አንደ ሐምሌ ጨለማ የከበባት። ደርግን አሸንፈዉ ስልጣን ሲይዙ ደርግ ገድሎ የቀበረዉን አስከሬን መቃብር እየቆፈሩ ያወጡት የወያኔ መሪዎች እነሱም በተራቸዉ በጅምላ ገድለዉ በብርድ ልብስ እየጠቀለሉ የቀበሯቸዉን ኢትዮጵያዉያን አስከሬን ዬት እንደቀበሩት እንኳን ሰለማያዉቁ እነሱ እራሳቸዉ እየቆፈሩ አዉጥተዉ ወንድሞቹና እህቶቹ እንደወጡ የቀሩበትን የኢትዮጵያን ህዝብ አንጀት እንደገና አቁስለዋል።
እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም ሊያሳስበንና ሊያስጨንቀን የሚገባ ነገር ቢኖር ባለፈዉ ሳምንት ከስድት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የጃንሜዳ ጦር ካምፕ አካባቢ በብርድ ልብስ እንደተጠቀለለ የተገኘዉ የ6 ሰዎች አጽም ሊገኝ የቻለዉ ሆን ተብሎ የጅምላ መቃብር ለማግኘት በተደረገ ቁፋሮ ሳይሆን በአጋጣሚ ነዉ። ይህ የሚያሳየን አዲስ አበባን ጨምሮ በብዙ የአገራችን አካባቢዎች ዉስጥ መረጃ የተሰበሰባበቸዉንና የሚጠረጠሩ ቦታዎችን የኢትዮጵያ ህዝብ ከአለም አቀፉ ህብረተሰብ ጋር ተባብሮ እየቆፈረ መፈተሽ ቢጀምር ወያኔ ጭካኔዉን ሊያሳየን ከሞከረዉ ከደርግ ስርዐት ጋር ምንም የማይለያይ ጨካኝና አረመኔ ስርዐት ለመሆኑ ማንም ማስተባበል የማይችለዉ ተጨባጭ ማስረጃ ይገኛል ብለን እናምናለን።
የወያኔ ዘረኞች አዲስ አበባን በተቆጣጠሩ ማግስት ስራችን ብለዉ የጀመሩት ደርግ የሰለበዉን የኢትዮጵያን ህዝብ ሞራል ማደስ ወይም በሶሻሊዝም ስም የደቀቀዉን የአገራችንን ኤኮኖሚ መገንባት አልነበረም። የደርግ ሰርዐት አንደ ገለባ ሲበተን አብሮት የተበተነዉ የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያሰራዊትም ቢሆን እንደጠላት የሚመለከቱት ኃይል ስለነበር ይህ ለእናት አገሩ ዳር ድንበር መከበር ደሙን ያፈሰሰ ሰራዊት የሚበላና የሚቀመስ አጥቶ ወደ መንገድ ላይ ለማኝነት ሲቀየር ሌላ ቢቀር ጡረታዉን እንኳን ለማስከበር ያደረጉለት ምንም ነገር አልነበረም። ወያኔዎች ስልጣን እንደጨበጡ የደረጉት አቢይ ነገር ቢኖር ከክፍለ ሀገር ክፍለ ሀገረ እየዞሩ ደርግ በቀይ ሽብርና በሌላም ሌላ ግዜ ገድሎ የቀበራቸዉን ሰዎች መቃብር እየቆፈሩ አጽም መሰብሰብ ነበር። በወቅቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተከታታይ እንደተመለከትነዉ የወያኔ ጉድጓድ ቆፋሪዎች የሰነበተ መቃብር እየከፈቱና አጽም እየሰበሰቡ ደርግ ምን አይነት ጨካኝ ነብሰ ገዳይ እንደሆነ ለአመታት የምናዉቀዉን እዉነት እንደገና እንድናዉቀዉ አድርገዉናል። በዚህ ከአንድ አመት ከመንፈቅ በላይ በዘለቀዉ የወያኔ መቃብር ቁፋሮ ወያኔ የቀድሞዉን ንጉስ የቀዳማዊ ኃ/ስላሤን ጨምሮ የብዙ ሰዎችን የመቃብር ቦታ እየቆፈረ እሱ ለፖለቲካ ፍጆታዉ የሚፈልጋቸዉንና በተለይ ደግሞ የኔ ናቸዉ የሚላቸዉን ሰዎች አጽም እየለቀመ አንደገና በክብር እንዲቀበሩ ሲያደርግ ሌሎቹን የደርግ ሰለባዎች ደግሞ ምሶ ያወጣዉን አፈር አንደገና መልሶባቸዋል። እንደዚህ አይነት ጉድ የተመለከትነዉ ከሃያ ሁለት አመታት በፊት ወያኔ ኢትየጵያን ሲቆጣጠር ነበር።
ባለፈዉ ሳምንት አዲስ አበባ ዉስጥ መንገድ የሚሰሩ ሰዎች ለራሳቸዉ ጉዳይ መሬት ሲቆፍሩ ከተጠቀለሉበት የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስ ዉስጥ እየዘለሉ ወጥተዉ “የፍትህ ያለህ” እያሉ ሲጮኹ የሰማናቸዉ አጽሞች ወያኔ በእኔ ዘመነ መንግስት ሰዉ በሰዉነቱ ይከበራል እንጂ እየተጎተተ አየገደልም ብሎ ከማለ በኋላ በራሱ በወያኔ በግፍ እየተጎተቱ ተገድለዉ የተጣሉ ዜጎች አጽም ነዉ። ይህንን በታሪካችን ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ጉድ በስፍራዉ ተገኝተዉ የተመለከቱ የአይን ምስክሮች እንደተናገሩት ቦታዉ ዘመናዊ የመቆፈሪያ ማሽኖች በመቆፈር ላይ እያለ በመጀመሪያ አራት አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተንከባለዉ ወደላይ ሲወጡ የታዩ ሲሆን፤ በሁኔታዉ የተደናገጡት ቆፋሪዎች ስራቸዉን አቋርጠዉ ወደ ቤታቸዉ ከሄዱ በኋላ በነጋታው ረፋዱ ላይ በሌላ አቅጣጫ ሌላ ቁፋሮ ሲያደርጉ አሁንም እንደገና በተመሳሳይ ሁኔታ በብርድ ልብስ የተጠቀለሉ ስድስት አስከሬኖች አግኝተዋል።
አንድ አስከሬኖቹ በተገኙበት አካባቢ በብዛት ተገኝቶ ሁኔታዉን ይመለከት የነበረዉን ህዝብ ለማባረር ወታደሮቹን አስከትሎ የመጣ ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንን “ይህ ግቢ ሶስት ስርዓቶችን ያገለገለ በመሆኑ የማናቸው እንደሆነ ለማወቅ አይቻልም፤ ሆኖም ሰዎች በመሆናቸው ክቡር ናቸውና አፈር አልብሷቸው” በማለት የዘረኞቹን የወያኔ መሪዎች አይን ያወጣ ወንጀል ለመደበቅ ሲሞክር ተደምጧል። ሆኖም ሁኔታዉን በቅርብ ሆኖ የተከታተለዉም ሆነ በርቀት ሆኖ በምስል የተመለከተ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወንጀሉ የሌሎቹ መንግስታት ሳይሆን የወያኔ መሆኑን ለመገንዘብ ግዜ አልወሰደበትም። አስከሬኖቹ በጅምላ የተጠቀለሉበት የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስም ቢሆን እንኳን መሬት ዉስጥ ተቀብሮ ምስጥ፤ እርጥበትና ዘመን ተፈራርቀዉበት፤ አልጋ ላይ ህያዉ ሰዉ ለብሶትም ቢሆን ሃያ አመት ቀርቶ አምስት አመትም የሚቆየዉ የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ለብሰዉት አንደመጡት ቁምጣ በመርፌ ከተጠቋቆመ ብቻ ነዉ። ባለፈዉ ሳምንት አርብና ቅዳሜ አስር አስከሬኖችን እንዳቀፈ ከመሬት ዉስጥ ሲወጣ ያየነነዉ ብርድል ልብስ የሚያሳየን ነገር ቢኖር ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ኢትዮጵያዉያንን በሚስጢር እየገደለ እንደ ቆሻሻ ዕቃ ዬትም ቦታ መጣሉን እንዳማያቆም ነዉ።
የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ለሀይማኖት የሚሰጠዉ ቦታ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። በእስልምናዉ፤ በክርስትናዉም ሆነ በአይሁድ ሀይማኖቶች አስተምህሮ በሀይማኖት ዉስጥ ሁለቱ ዋና ዋና አካሎች እግዚአብሄርና ሰዉ ናቸዉ፤ ይህ የሚያሳየን ሰዉ ክቡር ፍጡር መሆኑን ነዉ። ወደዚህ አለም ሲመጣም ሆነ ይህችን አለም ሲለይ በከብር መጥቶ በክብር የሚሸኝ የሰዉ ልጅ ብቻ ነዉ። የኢትዮጵያ ክርስትና እምነት መሰረት ከሆነችዉ ከትግራይ ክልል የመጡት የዛሬዎቹ የኢትዮጵያ መሪዎች ግን ክርስትናዉን ብቻ ሳይሆን የራሳቸዉንም ሰዉ መሆን የረሱ ይመስላል። ሰዉን የመሰለ ክቡር ፍጡር በጅምላ ተገድሎ፤ በጅምላ ከተቀበረበት ቦታ በኮንስትራክሺን ሠራተኞች ከመሬት ዉስጥ እየተጎተተ መዉጣቱን የሰሙ የወያኔ መሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ አንድም ትንፍሽ ያሉት ቃል የለም። እነሱ ብቻ ሳይሆኑ በእነሱ ቁጥጥር ስር ያሉት የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥንም እነማን እንደሆኑ፤ መቼ እንደሞቱና ማን እንደገደላቸዉ የማይታወቅ ሰዎች አስከሬን በብርድልብስ ተጠቅልሎ ሲገኝ ያንን ለስድብና ህዝብን ለመኮነን ቀኑን ሙሉ የሚከፍቱትን አፋቹዉን መክፈት አልፈለጉም። የሚገርመዉ እንደ አለባሌ ነገር ከተጣሉበት ቦታ ተጎትተዉ የወጡት አስከሬኖች ሁኔታና የተጠቀለሉበት ብርድልብስ ሙሉ በሙሉ ወንጀሉን ወያኔ ላይ ስለሚያመለክት ነዉ እንጂ የእነሱ እጅ የሌለበት ወንጀል ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሳምንት ሙሉ ሌላ ዜና አይሰማም ነበር።
አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ አገሮች የሚኖረዉ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ባለፈዉ ሳምንት እንደ ዋዛ ከመሬት ዉስጥ እየተጎተቱ የወጡ ወገኖቹን አስከሬን ጉዳይ በቀላሉ መመልከት የለበትም። ወያኔ ስልጣን እጁ ከገባ ጀምሮ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያንን እያፈነ በየማጎሪያ ቤቱ አጉሯቸዋል። ከሰሞኑ ጃንሜዳ አካባቢ ያየነዉ ዘግናኝ ክስተት ስለእነዚህ ወያኔ በየድብቅ አስር ቤቶች አስሮ አድራሻቸዉ ስለጠፋ ዜጎቻችን ብዙ የሚለዉ ነገር ያለ ይመስለናል። እኛ ነን አድራሻቸዉ የጠፋ ሰዎች እያልን የምንጨነቀዉ እንጂ እነዚህ ወያኔ አስሯቸዉ አድራሻቸዉ የጠፋ ሰዎች ዬት እንዳሉ ጃንሜዳ አፉን ከፍቶ ነግሮናል። አዲስ አበባና በየከተማዉ የሚኖረዉ ህዝብ ስለወያኔ የጅምላ ግድያ የሚያዉቀዉ ብዙ ሚስጢር ይኖራል፤ በጅምላ ተገድለዉ በጅምላ የሚቀበሩ ሰዎችንም ጉዳይ በተመለከተ ማንም ሰዉ ሳያየዉና ሳያዉቀዉ የሚፈጸም ነገር አይመስለንምና ከአሁን በኋላ ጥረታቻን ሁሉ የወያኔ የጅምላ ግድያዎች በብሄራዊና በአለም አቀፍ አካላት እንዲመረመሩና ወንጀለኞቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ መሆን አለበት። በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃ ያላቸዉ ዜጎች መረጃዎቻቸዉን ማሰባሰብ፤ማደራጀትና ለሚመለከተቸዉ አካላት መስጠት ይኖርባቸዋል። ዬት እንደደረሱ ሳናዉቅ ባለፈዉ ሳምንት ሳይተሳብ በደብረህርሃን ብርድ ልብስ እንደተጠቀለሉ ከመሬት ዉስጥ የወጡ ዜጎቻችን ፍትህ ሳያገኙ ማንም ኢትዮጵያዊ እንቅልፍ ሊወስደዉ አይገባም።

ካለመታደል ሀገራችን ዛሬም ሰላም ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት በልማትና በእድገት ጎዳና የምትራመድ ሀገር አልሆነችም። ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም እንደ ዓቢይ ምክንያት ተደርጎ የሚቀርበው የህዝብን ይሁንታን ያገኘ፡ ህዝብን በእኩልነት የሚዳኝ፡ ህዝባዊና ዲሞክራሲያዊ የሆነ መንግሥት አለመመስረቱ፡ አገርና ህዝብ የሚተዳደሩበት ዲሞክራሲያዊ ህገ መንግሥት አለመኖሩ ነው።

እስከዛሬ በተጨባጭ እንደታየው በ ኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተፈራረቁበት ገዥዎቹ በየበኩላቸው አንዱ ከሌላው የሚለዩባቸው ባህርያት ቢኖራቸውም ሁሉንም ግን አንድ የሚያስመስሏቸው ባህርያትም አሏቸው። እነሱም ሁሉም በኃይል ሥልጣን መያዛቸው፡ አምባገነንነታቸው፡ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ማራመዳቸው፡ በህዝብ መካከል የጋራ መተማመንና ከበሬታን ለመፍጠር፡ ሁሉም ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን በሀገሪቱ ለማስፈን አለመቻላቸው ደግሞ ዛሬ ለሁሉም በግልጥ እየታየ ያለ ነው። በዚህም የተነሳ በሀገራችን ለብሔራዊ ክብርና ነፃነት፡ ለዲሞክራሲ፡ ለማህበራዊ ፍትህ፡ ለሰላምና ለእኩልነት የሚታገሉ ኃይሎች የሰላማዊ ለውጥ በሮች ስለተዘጉባቸው የአ መፅን ጎዳና እንዲከተሉ የሚጋብዝ በር ተቀዶ ይገኛል።

በሌላ በኩል ደግሞ በሀገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ መረጋጋት ንእዲፈጠር፡ ሕዝቡም አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ አግኝቶ ያለስጋት ለመኖር እንዲችል፡ የዳኝነት ተቋሞች ነፃ ሆነው የሚሠሩበት፡ የህግ የበላይነት የተረጋገጠበት ሁኔታ እንዲፈጠርና፡ ህዝቡም በህግና ሥርዓት መኖር ላይ እምነት እንዲያድርበት ለማድረግ እንዲቻል፡ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊ ተቃዋሚ ኃይሎች በተናጠልም ሆነ በኅብረት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል። ሆኖም እስከዛሬ የተደረጉት ጥረቶችን ሁሉ በማምከን ወያኔ የሰላምና የእርቅ መሰናከል ከመሆኑም ባሻገር በንፁሃን ዜጎች ደም ሰላምን አጠልሽቶታል። ወያኔ ስለ ሰላምና እርቅ ሊሰማም ሊነጋገርም እማይችልበት የደም ስካር ላይ ደርሷል።

ብአዴን ቢመጣ ኦህዴድ ቢመጣ ደህዴን ቢመጣ የሚለወጥ ነገር አይኖርም። ጠንከር ያለ ለለውጥ የተዘጋጀ – አስከ ሞት የቆረጠ -ጠቅላይ ሚኒስተር ስልጣን አገኘ ማለት የህወሃት የበላይነት እና ፈላጭ ቆራጭነት ፍላጎት ፈተና ይገጥመዋል ማለት ስለሆነ! ህወህት የበላይነቱን ለማሰጠበቅ የፈጠራቸው የመንግስት ስልጣን አደረጃጀት አና ተቋማት ዛሬም በሙሉ ሃይላቸው አሉ። የህወሃት ፈላጭ ቆራጭነት ሳይዳከም ለውጥ አይመጣም። የህወሃት ፈላጭ ቆራጭነት መሰረቱ ደሞ ከምንም በላይ ወታደራዊ ሃይሉ ላይ የተመሰረተ አንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው። በደህነንት ቢሮ ያሉትን የህወሃት አመራሮች ከታች ያሉት ማዳክም የሚችሉበትን አጋጣሚ አና ሁኔታ ተጠቅመው አስካላዳከሙት ደረስ የህወሃት የስልጣን የበላይነት ትርጉም ባለው ሁኔታ እክል ሊገጥመው አይችልም።

ሌላ ሌላውን ትተን መሰረታዊ የሆነ ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ ያስፈልጋል፣ የፍትህ ስርዕቱ የፍትህ ስርእት መመስልም መሆንም አለበት፣ የነጻው ፕሬስና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ህዳሴ አንመራለን አየተባለ በመካከለኛው ዘመን አና ከዛ በፊት ከነበረው አንደነበረው በሰይፍ አና በሰደፍ መያዝ የለበትም። አነኚህ ወሳኝ ርምጃዎች በአዝጋሚ ለውጥ ይመጣሉ ብየ አላስብም። የአዝጋሚ ለውጥ ዲስኩር (ፍላጎት ካለ ፍላጎትም) ጭራሽ ወደማይቀልበስ የባርነት ዓለም አና ዘመን የመውሰጃ ከፓለቲካ ዘዴ ሊሆን ይችላል። ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓለቲካ መሪዎች ዘብጥያ ሲጣሉ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፈጠሩትን ዓይነት ጫና መፍጠር ስላልተቻለ አንኳን መሰረታዊ የፕሬስ ነጻነት አና በነጻነት ያለገደብ የመደራጀት መብት የሚከበርበት ፍንጭ ሊገኝ ቀርቶ የታሰሩትን ጋዜጠኞች አና የፓለቲካ መሪዎች ማስፈታት አንኳን አልተቻለም። ጭራሽ መብታቸው ተረግጦ ያላግባብ አስር ቤት የተጣሉ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ድረስ “አሸባሪ” አየተባሉ አየተፌዘባቸው ነው ያለው። አቶ ኃይለማርያምም ፌዙን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ አያስተጋቡት ነው።

ከበቀለበት የተጋጋበት አንዲሉ የ”በሳሉ መሪ ራዕይ” ዜማ ከህወሃት አባላት በእህት ድርጂቶች የፓለቲካ አላዋቂዎች አና መሪዎች ይበልጥ ተዜመ! በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝም ተሰማ። ችግሩ የለውጥ ጥያቄ ማድበስበሻ ሆኖ ለረዢም ጊዜ ሊቆይ አይችልም። በውሽት ላይ የተመሰረተ ፐሮፓጋንዳ ስር ሊይዝ አይችልም።አንዴት ይሄን ማየት አቃታቸው?!የሕዝባችን መከራና ሰቆቃ እየከፋ ሄደ። የተጨቆነዉ ሕዝብ ተነሳስቶ ለመብቱ ሲታገል ጨቋኝ መንግሥታት ለዉጥ እንዲያደርጉ ይገደዳሉ፤ ካለዚያ በተባበረዉ የሕዝብ ኃይል ተንኮታኩተዉ ይወድቃሉ። የታገለዉ ለዉጥ ያመጣል፤ ያልታገለዉ ቁጭ ብሎ በባርነት ሲገዛ ይኖራል፤ ቁጭም ባለበት ይሞታል ማለት ነው። የለዉጥ ባለቤት ሁሌ ሕዝብ መሆን አለበት። ህዝቡ ትግሉን በሚገባ እንዲያቀናጅ የትግል መሪ ይፈልጋል።

ስለዚህ የተቃዋሚ የፖሊቲካ መሪዎች ታላቅ ኃላፊነት ይጠበቅባቸዋል። ያገራችንን ጭብጥ ሁኔታ ስንመረምር ግን በሁለቱም በኩል ታላላቅና ተደጋጋሚ ድክመቶች ታይተዋል። አምባገነን መንግሥታት ለዘለዓለም ካልገዛን ሲሉ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኅብረታቸዉን ማጠናከር ስላልቻሉ የጨቋኝ መንግሥታትን ዘመናት ሲያራዝሙ ቆይተዋል።ወያኔ/ኢሕአደግ ለዘለዓለም ሊገዛ አይችልም፤ ለሁሉም ጊዜ አለዉና።ትግሉ ይበልጥ መፋፋም፡ ይበልጥ መጨስ፡ መጋጋም፡ መንደድ ይጠበቅበታል። ትግሉን ለማፈንና አቅጣጫውን ለማሳት የወያኔ መንጋ እየተሯሯጠ ነው። በውጭ ያለውንም የሕዝብና የድርጅቶችን ተቃውሞ ቢቻለው ለማዳፈን፡ ካልሆነለት ደግሞ ለማዳከም፡ በአሁኑ ወቅት የወያኔ ከፋፋይ ቡድን በየቦታው በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ እያየን ነው። ይህ ቡድንም፡ ምሁር ነን፡ አስታራቂ ነን፡ ሽማግሌ ነን ወይም ታጋይ ነን በሚሉ መሰሪዎችም እየተደገፈ ነው።

የሕዝብ ክንድ ይላላ፡ ይደክም ዘንድ፡ በከፋፋይ ሴራ የተሰማሩትን ነቅቶ መጠበቅ፡ ትግሉን መከላከል ብቻ ሳይሆን ወያኔ ለባሾችን፡ ሰላዮችን ሳንፈራ እየመነጠርን ማጋለጥ ይኖርብናል። ዘረኛው ቡድንና ጭፍሮቹ የሕዝቡን ትግል ለመከፋፈል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየጣሩ ናቸውና። ሕዝብ አንድነቱን ጠብቆ፡ የወያኔን ቡድን ለአንዴም ለሁሌም ለማስወገድ አስፈላጊውን መስዋእ ትነት እየከፈለ ባለበት ወቅት የፖለቲካ ድርጅቶችን እገዛና አመራር ይጠይቃል። የሕዝብ አሸናፊነት አጠራጣሪ ባይሆንም፡ አሸናፊ ለመሆን ግን መታገል መቅደም እንዳለበት ምን ጊዜም መረሳት የለበትም። ለዚህ መሠረቱ ግን ከራስ ጋር እየታረቁ፡ ከወገን ጋር እየተስማሙ በጋራ ዓላማና ብሔራዊ እጅንዳ ዙሪያ ተሰባስቦ በጋራ መታገል ብቻ ነው።

በዓለም ታላቅ ዝና ያተረፉት የግ/ቀ/ኃ/ሥና በአፍሪቃ አህጉር መሬትን ያንቀጠቀጠዉ የደርግ መንግሥት ቀናቸዉ ሲደርስ እንዴት እንደመነመኑና እንደከሰሙ መዘርዘር አይኖርብኝም፤ በታሪክ ፊት ተቀምጧልና። በሩቁም በእነ አሜሪካ ለረዥም ዓመታት ሲረዱና ሲደገፉ በነበሩት በእነ ሞቡቱ፤ የሻህ ንጉሥ፤ ሆስኒ ሙባረክ፤ ወዘተ ላይ በመጨረሻ የደረሰዉን ዉርደት መገንዘብ ያስፈልጋል። ተቃዋሚ የፖሊቲካ ድርጅቶች ነን የሚሉትና በተግባር ግን የጭቆናን ዘመን የሚያራዝሙ በሙሉ ካለፉት ስህተቶች ገና ሊማሩ አልቻሉም፤ ・ድር ቢያብር እንበሳ ያስር・ የተባለዉን ቅዱስ አሳብ ደጋግመዉ መናቃቸዉ ያስተዛዝባል። ቁርጥ ያለ አቋም ያስፈልጋል፤ ከዛፍ ዛፍ መዝለል ዬትም አያደርስም። ለጊዜያዊ ጥቅማ ጥቅሞች በርካሽ መገዛትና አገርን መሸጥ በሰማይም በምድርም ያስጠይቃል። ቀኑ ሲደርስ ራቆታችንን ወደምድር እነደመጣን ሁሉ ራቆታችንን ወደዚያዉ እነደምንመለስ አንርሳ!!!

ነገርግን በህብረት ለሀገር ታሪክ ሰርቶ ማለፍ ዘላለማዊ የትዉልድና የሀገር ክብር ነዉ!!!

ከጎልጉል የተወሰደ

ኢትዮጵያዊነት የሚለው ቃል እኮ የኢያንዳንዳችን መከበሪያ እና መኩሪያ እንጂ ማፈሪያ አይደለም::ለአመታት ታገልን የሚሉ ከወያኔ ጎን እየፈሉም ያሉ እና የከሰሙ የብሄር ድርጅቶች በታገሉባቸው አመታቶች ከወሬ ውጭ ለሃገሪቱም ይሁን ለሚጠሩት ብሄር ምንም የፈየዱት ነገር የለም:: ያመጡትም ነጻነት የለም ይብሱኑ እርስ በእርስ ከማጨፋጨፍ ውጪ እና ህዝብን ለእልቂት ከመዳረክ ውጪ ምንም ያመጡት ውጤት የለም:: በብሄር ስም መታገል እና ዘረኝነት ማራመድ ለብሄራዊ ጭቆና በር መክፈት ነው :: ገዢው ፓርቲን ሕወሓትን እንኳን ብትመለከቱት ለትግራይ ህዝብ የፈጠረው አዲስ ነገር የለም:: የትግራይ ህዝብ በዘመናዊ ጭቆና ፍዳውን እያየ ነው::

እኛ በጋራ እስካልታገልን ድረስ ለውጥ አይመጣም:: ከሃገር ሲወጡ የወያኔን ጽዋ ጠጥተው እዚህ ከመጡ በኋላ የሚከረበቱ አስመሳይ ተለጣፊ ፖለቲከኞችን ማስወገድ ግዴታችን ነው:: ኢትዮጵያዊነት የሚለው ቃል እኮ የኢያንዳንዳችን መከበሪያ እና መኩሪያ እንጂ ማፈሪያ አይደለም:: ከሌላው አለም የምንወስደው ትምህርት ምንድን ነው??ሌላው ዜጋ ሃገሩን እና ሌላውን ወገኑን እንዴት ነው የሚወደው?? የዘር እና የቀለም ልዩነት እየተወገደ በሚሄድበት በዚህ በሰለጠነው አለም ላይ ትላንትን እያሰብን የምንኖር ሰዎች ግንዛቤያችንን ማስፋት ይጠበቅብናል::

ኢትዮጵያ ምን አደረገችልኝ የሚል አነጋገር የሚናገሩ ጠባብ ብሄርተኞች አላማቸው የት ላይ እንደሚያርፍ ራሳቸው አያውቁትም::ኢትዮጵያ እኮ አንዲት ግኡዝ አካል ነች :: ተንቀሳቅሳ ላንተ ላንቺ እና ለእናንተ የምትፈይደው ነገር የለም ምድሯን እየረገጥን እየተማርን እየኖርን ያለነው እኛ ነን ::የእኛ ስራ ደሞ አገርን ከክፉ ገዢዎች አድነን ራሳችንን ነጻ በማውጣት የወገንን እምባ ማበስ እንጂ በወገን እንባ እና ደም መነገድ አላስፈላጊ ኪሳራ ያስከትልብናል ለኢትዮጵያ ምን ሰራሁላት ለወገኔ ምን አደረኩለት ብለህ ጠይቅ እንጂ እንደ ከብት አታጓራ:: በህዝብ ጥያቄ ስም ተደብቆ ጠባብነትን ማራመድ ክሽፈትን ያመጣል እና እንጠንቀቅ:: በየትኛውም አገር ያለን ኢትዮጵያውያን በጡት ነካሾች የታሰበውን ጸረ ኢትዮጵያ ዘመቻ ልንቃወም ይገባል::ምንሊክ ሳልሳዊ

አምስተኛው ዙር አገር አቀፍ ‹‹ምርጫ›› እንደወትሮው ሁሉ በቀጣዩ ዓመት ሊደረግ በዕቅድ ተይዟል፤ ወሬውም ከወዲሁ ለፖለቲካ ፍጆታነት እየዋለ ነው፤ ኢህአዴግም በበኩሉ ‹አውራ ፓርቲ›ነቱን ከቀደመው በበለጠ አጠናክሮ የሚቀጥልበትን ሴራ ፈትሎ በመግመድ ውሎ ማደሩን ገና በማለዳ እያቀላጠፈው መሆኑን እየታዘብን ነው፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ (ከልቡ ባይሆንም) በ1996 ዓ.ም ወርሃ ሐምሌ ላይ በተደረገ የግንባሩ ጉባኤ ‹‹የሚቀጥለው ምርጫ እንከን-አልባ ይሆናል›› ሲል ‹ቃል› ገብቶ የነበር ቢሆንም፣ ከስድስት ዓመት በኋላ በተካሄደው አራተኛው ዙር ‹‹ምርጫ›› በግላጭ ‹እንከን-አልባ ድል› በሚል ሲቀይረው ቅንጣት ታህል ሀፍረት

አልተሰማውም ነበር፡፡ ግና! ‹አንድ ለእናቱ› እንዲል አቤ ጎበኛ፣ የተቃውሞውን ስብስብ የምትወክል አንዲት ወንበር ሾልካ ወደ ምክር ቤቱ በመግባቷ፣ ፓርቲው ዛሬም ድረስ እንደ እግር እሳት እያንገበገበችው መሆኑን በተለያየ መንገድ እያሳየን ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ኢህአዴግ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ በሚቀጥለው ዓመት በሚደረግው ‹‹ምርጫ›› እንዲህ አይነት ‹እንዝህላልነትን› ለማረም በከፍተኛ ዝግጅት መጠመዱን የሚጠቁሙ መረጃዎች እያፈተለኩ ነው፡፡ መቼም የጉዳዩ እውነትነት ከተረጋገጠ፣ ምናልባትም በ2012 ዓ.ም ልክ እንደ ኤርትራ ወይም እንደ ቻይና ‹ልማታዊ መንግስት እንጂ ምርጫ የሚባል ነገር አያስፈልግም! የምርጫ ፖለቲካ የኒዎ-ሊበራሊስቶች አጀንዳ ነውና!!› ከማለት የሚመለስ አይመስለኝም፡፡ ማን ያውቃል? …እንዲህ እንደዛሬው የሶስት ሺ ዓመት ታሪክ ያላትን እና የዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ አገርን ፍርሃት በመንዛት አሸንፎ ከቆየ የምናየው ይሆናል፡፡

ከዚህ ባለፈ ቀጣዩን ‹‹ምርጫ›› በፍፁማዊ ጠቅላይነት ለመጨረስ እያደረገ ያለው መሰናዶ በሶስት የተከፈለ ነው፤ የመጀመሪያው ለመላው የድርጅቱ አባላት (የመንግስታዊ ተቋማት ኃላፊዎችን ጨምሮ) የተዘጋጀው ፓኬጅ ነው (ሰሞኑን በተለያዩ ከተሞች ስለ ‹አውራ ፓርቲ› አስፈላጊነት እና የ‹ልማታዊ መንግስት›ን ጠቀሜታ በተመለከተ እየተሰጠ ያለው ሥልጠናም የዚሁ አካል እንደሆነ ሰምቻለሁ)፤ ሁለተኛው መራጩ ሕዝብ ላይ በተናጥል አተኩሮ ለመተግበር እየተሞከረ ካለው ቀመር ጋር የሚያያዝ ሲሆን፤ ይህም እንደ ቀድሞው ሁሉ ለአቅመ-ምርጫ የደረሰውን ህዝብ በኮንዶሚንየም፣ በመልካም አስተዳደር እና በማይጨበጡ የተስፋ ፕሮፓጋንዳዎች ማማለልን የሚያካትት ነው፤ የመጨረሻው ደግሞ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና የግሉ የህትመት ሚዲያ ላይ ያነጣጥራል፤ በዚህ ፅሁፍም አጀንዳ የምናደርገው አገዛዙ በዚህኛው ግንባር ከሚያስወነጭፋቸው የ‹ጦር መሳሪያዎች› በዋነኛነት በዘጋቢ ወይም በዶክመንተሪ መልክ የሚያዘጋጃቸው ፊልሞችን የተመለከተ ነው፡፡

ስውሩ አጀንዳ…
በርግጥ ይህ አይነቱ አሰራር ዛሬ የተጀመረ አይደለም፤ ባለፉት ሃያ ዓመታት በሙሉ ሲተገበር የነበረ ነው፡፡ በተለይ ሕዝባዊ ተቃውሞን

የመሰለ ለሥልጣን የሚያሰጋ ድንገቴ አጋጣሚ ሲከሰት የሚመረቱት ፊልሞች ቁጥርም እንዲሁ ይጨምራል፤ እንደ ምሳሌም የ1993ቱን የህወሓት ክፍፍልን ተከትሎ በየአካባቢው የሕዝብ ማጉረምረም በበረታበት ወቅት፣ የሰሜን አፍሪካ አብዮት በጋመበት ማግስት እና የእስልምና እምነት ተከታዮች ሕገ-መንግስታዊው የኃይማኖት ነፃነት እንዲከበርላቸው በአደባባይ በጠየቁባቸው ጊዜያት በ‹‹ዘጋቢ ትዕይንት›› ስም የተሰራጩትን ብቻ መመልከቱ በቂ ነው ብዬ አስባለሁ (በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት ጭብጥ ያላቸው ፊልሞች ደራሲያን፣ የስርዓቱ ዋነኞች ‹ኤጲስ-ቆጶሳት› እንጂ ተቋሙ የሰበሰባቸው ብላቴና ልማታውያን ጋዜጠኞች አይደሉም)

ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የመረጃ ምንጮቼ እንዳረጋገጥኩት ‹ዶክመንተሪ ፊልሞች› የሚዘጋጁት በሁለት መንገድ ነው፤ የመጀመሪያው በኢቲቪ ባልደረቦች ሃሳብ አመንጪነት በፕሮፓጋንዳ ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣ በሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ይሁንታን ሲያገኝ እንዲተላለፍ የሚደረግ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ፣ በጉምቱ የፓርቲው መሪዎች የጭብጥ አሰናጅነት ሙሉ ድራማው አልቆለት በቀጥታ አየር ላይ እንዲውል ወደ ጣቢያው የሚላከው ነው፡፡ በዚህ ዘውግ የሚመደቡት አብዛኛዎቹ ፊልሞች ተቃዋሚ ፓርቲዎችን፣ በግል ሚዲያ ላይ የተሰማሩ ጋዜጠኞችን፣ የኃይማኖት መሪዎችን እና ዓለም-አቀፍ ተቋማትን በመወንጀልና በመዝለፍ ላይ የሚያውጠነጥኑ ናቸው (የቅርቦቹን እንኳ ለማስታውስ ያህል ብንጠቅሳቸው ይህንኑ ያስረግጣሉ፡- ‹አዲስ አበባን እንደ ባግዳድ›፣ ‹አኬልዳማ›፣ ‹ጀሀዳዊ ሀረካት›፣ ‹ሽብርተኝነት በኢትዮጵያ› እና የመሳሰሉት)

በጥቅሉ እስከ 2004 ዓ.ም መገባደጃ ድረስ የእነዚህ ፊልሞች ደራሲ አቶ መለስ ዜናዊ የነበረ ሲሆን፤ ከእርሱ ህልፈት በኋላ የኮሚኒኬሽን መ/ቤት (ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር አማካሪዎች) በደህንነት እና ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል ስም

እንደሚያዘጋጁት ውስጥ-አወቅ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ኢቲቪ በእንዲህ አይነት ጭብጥ ዙሪያ በሚያውጠነጥኑ ፊልሞች ላይ ምንም አይነት ተሳትፎ አያደርግም፤ ሳይቀንስና ሳይጨምር ለሕዝብ ማስተላለፍ አማራጭ ያልተተወለት ብቸኛ ግዴታው ነው፤ የህወሓቱ ሰው ገራገሩ የተቋሙ ስራ አስኪያጅ ዘርዓይ አስግዶምም ቢሆን ይህ ኃላፊነት ሲሰጠው ትጉህ አገልጋይነቱ ለማን እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቀዋልና፣

በፍፁም ፈቃደኝነት ሥራውን ከማሳለጥ በቀር የሚቃወምበት ወይም የኤዲቶሪያል ነፃነቴን አላስገፋም ብሎ የሚቀብጥበት አንዳች ምክንያት የለውም፡፡ በግልባጩ ውዳሴ መለስ፣ ስደት፣ የአባይ ቁጭት፣ የኮንዶሚንየም ቤቶችንና መሰል ጉዳዮችን በተመለከተ ደግሞ ሩቅ አላሚዎቹ ‹‹ልማታዊ ጋዜጠኞች››፣ እንቅልፍ አጥተው የሚጨነቁበትና እርስ በእርስ ለመቀዳደም የሚተጉበት አጀንዳ ስለመሆኑ ራሱ በረከት ስምዖንም ገና ድሮ የገባው ይመስለኛል (በነገራችን ላይ በየጊዜው ጥቂት የጣቢያው የተለያዩ ፕሮግራም አዘጋጆች እና የዘጋቢ ፊልም ባለሙያዎች የቻይናን የሚዲያ ተሞክሮ አጥንተው እንዲመጡ እንደሚደረግ ይታወቃል)

ለዚህ ፅሁፍም እንደ ማሳያ የምጠቅሰው፣ ባለፈው ሳምንት ‹‹ሽብርተኝነት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ ለተመልካች የቀረበው ዘጋቢ ፊልም፣ ሙሉ በሙሉ በብሔራዊ መረጃ መ/ቤት ስም የተዘጋጀ ሲሆን፣ በንባብ የተሳተፉት ሁለቱ ‹‹ጋዜጠኞች››ም የኢቲቪ መደበኛ

ባልደረቦች እንዳልሆኑ ከምንጮቼ አረጋግጫለሁ፡፡ ምንም እንኳ የፊልሙ ‹ባለቤት› የሆነው የደህንነት ቢሮ በሽብርተኝነት ዙሪያ የሚያውጠነጥን ነው ቢለንም፣ እንዲተላለፍ የተፈለገው ዋነኛ መልዕክት በቀጥታ ከቀጣዩ ምርጫ ጋር የተያየዘ ነው ወደሚል ጠርዝ የሚገፉንን ማሳያዎች መምዘዝ የሚቻል ይመስለኛል፡፡ እንዴት ሆኖ? የሚለውን ጥያቄ በአዲስ ርዕስ ሥር እናፍታታው፡፡

ከፍርሃት ጋር ወደፊት!

በዚህ ፊልም ላይ ዋነኛ አጋፋሪ ሆነው የቀረቡት ሶስት ሰዎች ናቸው፤ የኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ ሽመልስ ከማል (ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በእንዲህ አይነት ፊልሞች ላይ የመሪ-ተዋናይነትን ገፀ-ባህሪ ወክሎ መጫወቱን እየተካነው እንደሆነ እኔም ራሴ እመሰክርለታለሁ¡)፣ የፌደራሉ ዋና ዓቃቢ-ሕግ ብርሃኑ ወንድማገኝ እና አቶ ዘሪሁን ተሾመ (ይህ ሰው ደግሞ አሉባልታና ጠቀሜታቸው ረብ-የለሽ የሆነ ወሬዎችን በማቅረብ የሚታወቀው የ‹ዛሚ-90.7› ሬዲዮ ባለቤት ሚሚ ስብሃቱ የትዳር አጋር ነው) ከትዕይንቱ መካከል የሚታወሱ ፊቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ድራማው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ተሰፍሮ የተሰጣቸውንና በፈጠራ ታሪክ የተሞላውን ‹ስክሪፕት› ቃል-በቃል ሸምድደው መምጣታቸውን በግልፅ በሚያሳይ መልኩ ሲያነበንቡ ላስተዋላቸው ተመልካች ‹‹ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች›› የጣሉባቸውን ግዴታ በቁርጠኝነት ለማስፈፀም ‹ቀራኒዮ› ድረስ የሚጓዙ ሊመስለው ቢችል አይፈረድበትም¡ መቼም አገዛዙ ዓለማዊ ፍላጎታቸውን እስካሟላላቸው ድረስ ሀገር፣ ሕገ-መንግስት፣ ሕሊና… ደንታ ሳይሰጧቸው ሕዝብን በማሸበር የስርዓቱ ዕድሜ ይረዝም ዘንድ ‹ከፍርሃት ጋር ወደፊት!!› ለማለት የማያመነቱ ሰዎችን በዙሪያው የኮለኮለው ለእንዲህ አይነቱ ጊዜ ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ፊልሙ ከቀድሞዎቹ አንፃር እንኳ ሲመዘን የወረደና አሰልቺ ቢሆንም፣ ያን ያህል ከተደሰኮረለት የ‹‹ሽብርተኝነት ጉዳይ›› ባሻገር ሁለት ያደፈጡ ስውር ዓላማዎች ያሉት ይመስለኛልና፣ እነርሱን ነጣጥለን እንመልከት፡፡

የቀደሙ ልምዶችን ተንተርሰን ስናብሰለስለው፣ የዘጋቢ ትዕይንቱ ድብቅ ዓላማ ተደርጎ ሊጠቀስ የሚችለው የመጀመሪያው የቢሆን ሃሳብ፣ ኢህአዴግ ከምርጫው መዳረሻ በፊት በተቃውሞ ፖለቲካው ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ ያሉ የተወሰኑ የአመራር አባላትን እና ጥቂት ጋዜጠኞችን እንደተለመደው ከግንቦት 7 ጋር አቆራኝቶ ለማሰር እየተዘጋጀ ነው የሚል ይሆናል፡፡ በርግጥም ይህንን መከራከሪያ ከመቀበል ሌላ አማራጭ የሚያሳጡ ሁለት ገፊ ምክንያቶች አሉ፤ አንዱ ፓርቲው ቀጣዩን ምርጫ ከትግል ዘመኑ ጀምሮ ይመራው ከነበረው ጉልበታሙ አቶ መለስ ውጪ የሚያደርገው መሆኑ ያሳደረበት ስጋት ወደ ጭፍን አምባገነንት እንዲቀየር ከማስገደድ አልፎ፣ ይህንኑ የሰውየውን ህልፈት ተከትሎ የተከሰተው የኃይል መከፋፈል ያነበረው የመሳሳት ተፅእኖ ይመስለኛል፤ እነዚህ ኩነቶችም ስርዓቱ ህልውናውን ካፀናበት አምባገነናዊ ባህሪው አኳያ ድንገቴ እርምጃ እንዲወስድ መግፋታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ካደረ ተሞክሮው የሚነሳ ነው፤ ይኸውም በ2002ቱ ምርጫ ዋዜማ በተልካሻ ምክንያት የአንድነት ለፍትሕና ዴሞክራሲ ሊቀ-መንበር የነበረችውን ብርቱካን ሚደቅሳን እስር ቤት በመክተት ፓርቲውን እና የተቃውሞ ደጋፊ ኃይሉን እስረኛ በማስፈታት አጀንዳ እንዲጠመድ ያደረገበት ስልት እና ሁነቱ የፈጠረው ማሕበረሰባዊ የፍርሃት ድባብ ያስገኘለት ጠቀሜታን ሊከልሰው መሞከሩ አይቀሬ መሆኑ ነው፡፡ በአናቱም በወቅቱ ከፍተኛ ተነባቢነት የነበራትን የ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ አዘጋጆች ምርጫው አራት ወር ብቻ ሲቀረው በግልፅና ስውር ጫና ጋዜጣውን ዘግተው ከሀገር እንዲሰደዱ ያደረገበት መንገድም የዚሁ አፈና ጉትያ እንደነበረ አለመዘንጋቱ፣ በቅርብ ከሚፈጠሩ ተመሳሳይ ክስተቶች ጋር ለማያያዝ ያስችላል፡፡

ሌላኛው የዘጋቢ ፊልሙ ዓላማ በቀጣዩ ምርጫ ለውጥ ፈላጊውን የህብረተሰብ ክፍል ወደ ተቃውሞ ጎራ ሊያሰባስብና መነቃቃት ሊፈጥር ይችላል የሚል ብርቱ ጥርጣሬ ያሳደረበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጣቢያን በመርገም (በሽመልስ ከማል አነጋገር ‹‹ውጉዝ ከመአርዮስ›› በማለት) የተቀናቃኝ ድምፆች በተከበበላቸው ሞገድ ብቻ እንዲሰሙ ማስገደድ ነው፡፡ ይህ ሁናቴ አገር ውስጥ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እና ጋዜጠኞች ለጣቢያው ቃለ-ምልልስ እንዳይሰጡ በፍርሃት ቆፈን መሸበብንም ያከተተ ነው፡፡ አስደንጋጩ ጉዳይ ደግሞ መከራከሪያ ሆኖ የቀረበው ሕገ-መንግስታዊው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ሳይሆን፣ ለሚዲያ ተቋሙ የብሶት መግለጫዎችን መስጠትም ሆነ ኢ-ፍትሀዊ አሰራርን ማጋለጥ በሽብርተኝነት እንደሚያስከስስ የሚተርክ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም››

መሆኑ ነው፡፡ በርግጥ ለዚህ ማስፈራሪያ እንደ መደገፊያ የተጠቀሙት ፀረ-ሽብር ሕጉ በግብረ-አበርነት ተጠያቂ የሚያደርግበትን የተለጣጭነት ባህሪውን አፅንኦት በመስጠት እንደነበረ ታዝበናል፡፡

በፊልሙ ላይ አቶ ዘሪሁን ምሬት በዋጠው ድምፅ ‹‹ኢሳት የግንቦት 7 ወፍጮ ነው!›› የሚል መፈክር ሲያሰማ፣ ሽመልስ ከማል ደግሞ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ከዚህ ቀደም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ‹አሸባሪ› ተብለው ከተፈረጁት ድርጅቶች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳይኖር ለማድረግ እንደሆነ ምሎ-እየተገዘተ ተመልካቹን በፍርሃት ለማንበድበድ ሲሞክር ተስተውሏል፡፡ ይሁንና የአቶ
ሽመልስን እርግጠኛነት ለማመን አመክንዮ መጠቀም የግድ ይሆናል፤ እናም ኢሳት የእነዚህ ድርጅቶች ዓላማ አራማጅ መሆኑን ለማሳየት ምን ተጨባጭ ማስረጃ አቀረባችሁ? ለሚለው ጥያቄ እየነገሩን ካለው እንቶ-ፈንቶ ባለፈ በማስረጃ የተደገፈ መልስ መስጠት የሚኖርባቸው ይመስለኛል፡፡ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የኤርትራ መንግስት ከሰጠው አምስት መቶ ሺህ ዶላር ውስጥ ሁለት መቶ ሺውን ለኢሳት ሥራ ማኪያሄጃ እንዲውል መወሰኑን በስልክ ሲናገር ከማሰማት በዘለለ ማለቴ ነው፡፡

እግረ-መንገድ ለመጥቀስ ያህል የዚህ ፅሁፍ ዓላማ ኢሳትን መንግስት ለምን ወነጀለው በሚል ግብረ-መልስ መስጠት አለመሆኑን ማስገንዘቡ አስፈላጊ ይመስለኛል፤ መነሻ ምክንያቴ እንደ ሚዲያ ተቋምነቱ ከእኔ ሞያ ጋር በቀጥታ መገናኘቱ ሲሆን፤ ለምን ይህ ሆነ? ያልኩበት ተጠየቅም የሕግ የበላይነት ጉዳይ ብቻ በመሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም የተመለከትነው ፕሮግራም ኢሳት እስከ ዛሬ ባሰራጨው ዘገባ ላይ ‹አሸባሪ› ሊያስብለው የሚያስችል ትዕዛዝ ያስተላለፈበትን ወይም ንፁሃን ኢትዮጵያውያንን በተጠመደ ፈንጂ ዶግ-አምድ እንዲሆኑ መቀስቀሱን የሚያጋልጥ ሳይሆን፣ በሰላማዊም ሆነ በትጥቅ ትግል ከተደራጁ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት ጋር ያደረገውን ቃለ- መጠይቅ ብቻ በመደጋገም ነው፡፡ ለዚህም ይመስለኛል የዘጋቢ ፊልሙ ድብቅ ዓላማ ስርዓቱ በሀገር ውስጥ ያሉትን ጥቂት የግል የሕትመት ሚዲያዎች በፈርጣማ የፖለቲካና ቢሮክራሲ ክንዱ ደቁሶ ካኮሰመነ በኋላ፣ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ድምፅ ላጡት ድምፅ መሆን እየቻለ የመጣውን እና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች አማራጭ የሚዲያ ምህዳር የፈጠረውን የቴሌቪዥን ጣቢያ ከተለመደው የአፈና መንገድ /ጃሚንግ/ በተለየ ስልት ከጨዋታ ውጪ ለማድረግና በቀጣዩ ምርጫ ‹አውራ ፓርቲ›ነቱን ለማስጠበቅ የሚያደርገው ዝግጅት ነው እንድንል የተገደድነው፡፡

ከዚህ ቀደም እነ እስክንድር ነጋ በግንቦታ 7 አባልነት ተወንጅለው በታሰሩበት ወቅት አቶ መለስ ዜናዊ ለፓርላማው ‹‹ክምር ማስረጃ አለን›› ቢልም፣ ጉዳዩ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ግን በጨበጣ እንደገባበት ማየታችን አደባባይ የወጣ ሀቅ ነበር፤ በርግጥም ማስረጃ ሆኖ የተቆጠረው ራሱ ያዘጋጀው ‹‹አኬልዳማ›› የሚል ‹‹ዘገቢ ፊልም›› እንደነበረ ስንመለከት፣ ይህ ስርዓት አስቀድሞ የተናገረበት ጉዳይ ስህተት መሆኑ እንዳይጋለጥ ምንም ነገር ከማድረግ እንደማይመለስ እንታዘባለን (በነገራችን ላይ በወቅቱ በፍትህ ጋዜጣ ‹‹አኬልዳማው! የአይሁድ ወይስ የኢህአዴግ?›› በሚል ርዕስ የዘገባውን ፈጠራነት በተጠናከረ ማስረጃ ለማጋለጥ ከተሞከረ በኋላ እንዲህ የሚል ምክር አዘል ቁም-ነገር ተላልፎ እንደ ነበር አይዘነጋም፡-

‹‹ሆሊውድ የሚሰሩ አስፈሪ (ሆረር) ፊልሞች እንኳ ቢያንስ ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች እንዳያዩአቸው የሚከለክል ሕግ አለ፣ ኢቲቪ ግን የተበጠሰ አንገት፣ የተገነጠለ ክንድ፣ የተቆረጠ እጅ፣ የተፈረከሰ ጭንቅላት… እያሳየ፣ ‹13 ዓመት የሞላው ሕፃን በሙሉ ሊያየው ይችላል› ማለቱ ኃላፊነት የጎደለው አሰራር ነው››

ባለፈው ሳምንት በቀረበው ፊልም ላይ ቢያንስ ይህ ሁኔታ ታርሞ ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች ሊያዩት እንደማይገባ ከሚያስጠነቅቅ መልዕክት ጋር መተላለፉ ስርዓቱ ምክር መስማት ጀመረ እንዴ? እንድንል የሚያጭር ነው፡፡ በርግጥም በሌሎች ጉዳዮችም እንዲህ ቢያዳምጡን ኖሮ፣ እየዋጣቸው ካለው ጥልቅ ጨለማ ራሳቸውን መታደግ የሚችሉበት በርካታ ዕድል ነበር፡፡)

የሆነው ሆኖ በዚህና መሰል ፊልሞች ላይ የሚነሳው ሌላው ለትዝብት የሚያጋልጠው ጉዳይ የደህንነት ተቋሙ ሁሉንም ዜጋ አብጠርጥሬ አውቃለሁ የሚለው ማንአህሎኝነቱ ነው፡፡ አስቂኙ ጉዳይ ግን በአዋጅ የተቋቋሙት የመረጃው መስሪያ ቤት እና የፀረ-ሽብር ግብረ-ኃይል፣ ያሻቸውን ዜጋ ቤት (በስውርም በግልፅም) መበርበር፣ ስልክ መጥለፍ፣ የኢ-ሜል እና የማሕበራዊ ሚዲያዎችን አካውንት ‹የሚስጥር ቁልፍ ቃላት› ሰብሮ መፈተሽ… ከሚያስችል ያልተገደበ ሥልጣን ጋር የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፣ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እንደ አዋጭ መፍትሄ የወሰዱት ‹ዶክመንተሪ ፊልም›ን እስኪመስል ድረስ በሳምንት አንዴ መመልከቱ የተለመደ መሆኑ ነው፡፡ ርግጥ እንዲህ አይነት ትዕይንቶች ተጨማሪ ስርዓታዊ ጠቀሜታቸው ማህበራዊ ተቀባይነታቸው የጎላ ዜጎችን በስቅየት (ቶርቸር) እያንበረከኩ በቴሌቭዥን መስኮት አንገት አስደፍተው በማቅረብ ትውልዱ ተጠራጣሪና ድንጉጥ እንዲሆን ያላቸው አስተዋፆኦ አንዱ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ይህው ቃል በሚከሰሱት ንፁሀን ላይ ተመልሶ እንደ ማስረጃ ተቆጥሮ፣ ከአስር ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ የሚደርስ ቅጣት በ‹ካንጋሮው› ፍርድ ቤት እንዲጣልባቸው የሚያደርገው ግፈኝነት ነው፡፡ ለዚህም ቅጥ ያጣ አምባገነንነት አይደፈሬ ሥልጣኑ የሰጠውና ገና ሲረቅቅ ጀምሮ ጠንካራ ተቃውሞ ሲቀርብበት የነበረውን የፀረ-ሽብር አዋጅን የሕጋዊነት ከለላ አድርጎ እየተባባሰ በመጣ መልኩ መጠቀሙን መቀጠሉ ነው፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የታተመው ‹‹ኒውስ ዊክ›› መፅሄት ‹‹Ethiopia declares war on [deleted] men›› በሚል ርዕስ ባስነበበው አደገኛ መጣጥፍ አዋጁን ያብጠለጠለበት ሀረግ የትችቶቹን ሙሉ መንፈስ የሚጠቀልል ይመስለኛልና እዚህ ጋር ልጥቀሰው፡-

‹‹የፀረ-ሽብር ሕጉ መንግስት ሽብርተኝነት ብሎ የሚያስበውን ጉዳይ በ‹መፃፍ፣ ማቀናበር፣ ማተም ወይም ማሰራጨት› የሚከሰውን ዜጋ በሃያ ዓመታት እስር እንዲቀጣ ፈቅዶለታል፡፡››

እነዚህን ነገሮች ጠቅልለን ስንመለከት ገዥው ፓርቲ ለሀገሪቱ ስጋት እንደሆነ የሚነግረንን ሽብርተኝነት ራሱ ባዘጋጀው ሕገ-መንግስት ሳይሆን፣ በዶክመንተሪ ፊልም ጎርፍ ለመግታት ነው የተዘጋጀው ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ በርግጥ የፓርቲው አላማ ሥልጣኑን መጠበቅ ነውና ሕገ-መንግስቱን ወዲያ ጥሎ ዘጋቢ ፊልሞች ላይ ቢንጠለጠል እንዴት ልንገረም እንችላለን?!

ወደ የፍርሃት ‹ሪፐብሊክ›

ይህች መከረኛ ሀገር በደርግና በኢህአዴግ ከተሠጣት ቅጥያዎች አንዱ ‹‹ሪፐብሊክ›› የሚል እንደሆነ ይታወቃል (የደርጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሲል፤ ይህኛው ደግሞ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ነች ይለናል)፡፡ ዝርዝር ሃተታውን

ትተን ከዚህ ፅሁፍ አውድ አንፃር የሪፐብሊክን ብያኔ ሕዝባዊ መንግስትነት የሚል ትርጓሜ ሰጥተን ማለፍ ይበቃል፡፡ ይሁንና የተሻገርናቸው ሁለት አስርታት የሚያስረግጡት ብቸኛ እውነት ቢኖር ሀገሪቱ ከዚህ የተጠያቂ መንግስት ምስረታ ተፃራሪ የሆነውን መንገድ መምረጧን ነው፡፡ ከላይ ለማሳያነት የጠቀስኩት ዶክመንተሪ ፊልምም ሆነ ተያያዥ አፋኝ ሕጎቹ እና ፖለቲካዊ አተገባበራቸው በፍርሃት የሚርድ ማሕበረሰብ በመፍጠር፣ ቀጣይ አስርታቱን ካለአንዳች መደነቃቀፍ ረግጦ መግዛትን ዋነኛ ግብ ያደረጉ ናቸው፡፡ ይህን ተቋማዊነትን ተደግፎ የሚካሄደው መንግስታዊ ሽብር፣ በአንዳች ክስተት ብርክ በሚያናውጣቸው ዜጎች ማሕበረሰቡ እየተሞላ እንደሚሄድ ግልፅ ነው፤ ከፌደራላዊ ወደ ፍርሃት ሪፐብሊክ እየተደረገ ባለው በዚህ ጉዞ፣ ሀገሪቱን ከዝግመታዊ ሞት ለመታደግ የበረቱ መዳረሻቸውን ስርዓቱ አዘጋጅቷል፡፡ እናም ዋጋው ምንም ቢሆንም በአደባባዩ ላይ የሚደረግ የተቃውሞን እንቅስቃሴ፣ ኢህአዴግን ከሥልጣን የማውረድ ብቻ ከመሆን መታለፉን በሚገባ ልናስብበት እንደምንገደድ ይሰማኛል፡፡ እነርሱ ከሚቀጥለው ምርጫ በፊትም ሆነ በኋላ ሕዝባዊ ምህዳሩን ምንም አይነት የተቃውሞ ድምፅ የማይሰማበት ምድረ-በዳ ለማድረግ ይህን ያህል ርቀት መጓዛቸውን ስንመለከት ምርጫችን ሁለት ብቻ ይሆናል፡፡ ቀጣዩን ትውልድ በፍርሃት ሪፐብሊክ ውስጥ ትቶ ማለፍ፣ አሊያም አደባባዩን በጨኸት መሙላት፡፡

ኢትዮሚድያ

ይሄ አደጋ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ የግዲያ ሙከራ ይሁን አሊያም በአጋጣሚ የተፈጠረ የእሳት ቃጠሎ ይሁን ማወቅ አልተቻለም።

የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት እና የዓረና ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የውብማር አስፋው ጋር በመሆን በመኪና እየሄዱ እያለ ድንገት መኪናቸው በእሳት መያያዟን የተመለከቱ ሰዎች ባደረጉላቸው ጥቆማና ርብርብ ከእሳቱ ቃጠሎ ለጥቂት መትረፋቸውን ማወቅ ተችሏል። በመኪናዋን ግን እዚያ የነበረው ሰው ሁሉ ብዙ ርብርብ ቢያደርግም ከቃጠለው ማተረፍ አልተቻለም። በእውነቱ ይህን መረጃ እንደደረሰኝ አላመንኩም ነበር፤

በመሆኑም ወዲያው ወደ አቶ ገብሩ አስራት ስልክ ደውዬ እውነት መሆኑን ማረጋገጥ ችያለሁ። ነገር ግን የአቶ ገብሩ ባለቤት ወ/ሮ የውብማር አስፋው ህወሃት ባካሄደው የትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም ሚና ከነበራቸው ጥቂት ሴት ታጋዮች ውስጥ የሚመደቡ እና “ፊኒክስዋ ሞታም ተነሳለች፥ ያልተቋጨው የትግራይ ሴቶች ትግል” የሚለውን መፅሐፍ የፃፉ ናቸው።
ለማነኛውም ለአቶ ገብሩ አስራት እና ለባለቤታቸው ወ/ሮ የውብማር አስፋው እንኳን በህይወት አተረፋችሁ ለማለት እፈልጋለሁ።

ግርማይ ገብሩ የቀድሞ የህወሓት ታጋይና የአሁን የቪኦኤ (VOA) ዘጋቢና ደራሲ ነው። ዓላማዬ ስለ ግርማይ ገብሩ ለመፃፍ አይደለም፤ ግርማይ በፌስቡክ ገፁ ስላሰፈረው መረጃ ለመዋስ እንጂ። መረጃው ከዚህ በፊትም አውቀው ነበር። ግን ለማስረጃ ያህል ግርማይን ልጥቀስ: ምክንያቱም ግርማይ የህወሓት ታጋይ ነበርና።

ግርማይ በ1969 ዓም የህወሓት (ተሓህት) ሦስቱ መፈክሮች ሲጠቅስ የመጀመርያውና ዋነኛው አድርጎ የፃፈው “አፄነት፣ መስፍንነትና የአማራ የበላይነት ይወድማሉ” ይላል።
በትግርኛ “ካብ ጭርሖታት ህወሓት 1969 ዓም: ሃፀይነት፣ መስፍንነትን ናይ አምሓራ ዕብለላን ዓነውቲ እዮም!” ይላል። ግርማይ ገብሩ አልተሳሳተም። ከህወሓቶች ጋር የማልስማማበት ግን ነጥብ አለኝ።

እርግጥ ነው። እኔም አፄነትና መስፍንነትን እንደ ስርዓት አልቀበልም። ምክንያቱም አፄነትና መስፍንነት (እንደ ስርዓት) ላሁኗ ኢትዮጵያ አይመጥኑም። የአፄነትና መስፍንነት ስርዓት በኢትዮጵያ ታሪክ እዚ ግባ የሚባል ለውጥ አላመጣም። ስለዚህ እኛ የሚያስፈልገን ዘመናዊ (ከዘመኑ ንቃተ ህሊናችን ጋር አብሮ የሚሄድ) የህዝብ አስተዳደር (ዴሞክራሲ) እንጂ ንጉስነት (የሰው ገዢነት) አይደለም። የምንፈልገው የሕግ የበላይነት እንጂ የንጉስ የበላይነት አይደለም።

ግን አፄነትና መስፍንነት እንደ ስርዓት ባልቀበለውም የንጉሳውያን ቤተሰቦችና መሳፍንቶች መጥፋት አለባቸው ብዬ ግን አላምንም። እኔ ብሆን እነኚህ የንጉስ ቤተሰቦችና መሳፍንት ቁልፍ የመንግስት ስልጣን አልሰጣቸውም ነበር። በሀገራቸው በሰላም እንዲኖሩ ግን እፈቅድላቸው ነበር። ምክንያቱም እንደማንኛውም ሰው ዜጎች ናቸው፤ ለሀገራቸው በተቻላቸው መጠን አስትዋፅዖ አድርገዋል። ስለዚህ ንጉሳዊ ቤተሰብና መሳፍንት ስለሆኑ ብቻ መጥፋት አለባቸው ብዬ አልፈርድም። እንደ ጠላትም አላያቸውም፣ እንደ ዜጎች እንጂ።

ህወሓት ግን በመፈክር ደረጃ በጠላትነት ፈረጃቸው። በተግባርም አጠፋቸው፣ ገደላቸው። በንጉሳዊ ቤተሰብና መስፍንነት ዝንባሌዎች ሰበብ ብዙ የተምቤን፣ ዓጋመ፣ እንደርታ፣ ዓድዋ፣ ሽረ፣ አክሱም ወዘተ መሳፍንቶች እንዲጠፉ ተደረገ። ‘ትግራይ ከመሳፍንቶች ነፃ ወጣች’ ተባለ። እውነታው ግን ‘ትግራይ ተገደለች’ መባል ነበረበት። መሳፍንቶች ከስልጣን ማውረድ እየተቻለ መግደል ምን አመጣው (ህወሓቶች ከስልጣን ማውረድ እየተቻለ መግደል ለምን ያስፈልጋል)?

ባጠቃላይ መሳፍንቶቹ ሲወድሙ ትግራይ ወደመች። አሁን በትግራይ የተቃውሞ መንፈሱ የተዳከመው በመስፍንነት ሰበብ ብዙ ብቁ ሰው ስለተፈጀብን ነው የሚል እምነት አለኝ። በህወሓት የተገደሉብንን ያህን በሌላ ስርዓት አልተገደሉብንም። ስለዚህ መሳፍንቶች ከስልጣን በማውረድ (መሳፍንቶችን ሳይሆን መስፍናዊ ስርዓቱ) ከህወሓቶች ጋር እስማማለሁ። መስፍናዊ ስርዓቱ ለማጥፋት መሳፍንቶቹ ማጥፋት ከሚል የህወሓት መፈክር ወይ መርህ ግን አልስማማም።

ሌላውና መሰረታዊ የህወሓት ችግር “የአማራ የበላይነት ይውደም!” የሚል መፈክር ነው። እኔም ብሆን የማንም ሰው ወይ ብሄር ወይ ሌላ አካል የበላይነት አልቀበለም። የቴድሮስ ወይ ዮሃንስ ወይ ምኒሊክ ወይ ኃይለስላሴ ወይ መንግስቱ ወይ መለስ ወይ ኃይለማርያም ወይ አማራ ህዝብ ወይ ትግራይ ህዝብ ወይ ኦሮሞ ህዝብ ወይ ሌላ … የበላይነት አልቀበልም። እኔ የምቀበለው የበላይነት ‘የሕግ የበላይነት’ ብቻ ነው። የሌላ የማንም የበላይነት አልቀበልም።

እንደ ፖለቲካ ድርጅት አንድን ህዝብ ዒላማ አድርጎ መነሳት ግን ስህተት ብቻ ሳይሆን በሽታ ነው። ህወሓት (ተሓህት) የአማራን ህዝብ ዒላማ አድርጎ ሲነሳ፣ ሌሎች የህወሓት ተቃዋሚዎች ደግሞ በህወሓት ምክንያት የትግራይን ህዝብ ዒላማ ሲያደርጉ ዉጤቱ ምን ይሆናል? አንድን ህዝብ ከሌላ ህዝብ ጋር የማጣላት ስትራተጂ የፖለቲካ ዕብደት ነው። ህዝብና ገዢው መደብ አለመለያየት (አንድ እንደሆኑ አድርጎ ማሰብ) የፖለቲካ እውቀት ማነስ ዉጤት ነው። ስርዓቱ መቃወምና መታገል እየተቻለ ህዝብን ዒላማ አድርጎ በህዝቦች ላይ መተማመን እንዳይኖር መትጋትና በህዝቦች መካከል ጥላቻ እንዲነግስ መስራት ጠባብነት ነው።

አንድን ህዝብ የበላይነት ሊይዝ አይችልም። አንድን ቡድን ግን በአንድን ህዝብ ስም በመነገድ ሌሎችን ሊበድል ይችላል። የሰው የበላይነት (በህዝቦች ላይ) ሊተገብር ይችላል። ህዝብ እንደ ህዝብ ግን ሌላውን ህዝብ ሊበድል አይችልም። ህወሓት የትግራይን ህዝብ እንደሚወክል ይነግረናል። የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ እያለ ሌሎች ህዝቦች (የትግራይን ጨምሮ) ይበድላል። ሌሎች ህዝቦች (የትግራይ ዉጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን) ደግሞ በህወሓት ስርዓት ሲበደሉ በትግራይ ህዝብ የተበደሉ አድርገው ያስባሉ። ግን ስህተት ነው። መታረም አለበት። የትግራይ ህዝብ ለራሱ በህወሓት አገዛዝ የሚበደል ነውና።

“የአማራ የበላይነት” የሚባለው የህወሓት በሽታ እስካሁን ፈውስ አላገኘም። በመርህ ደረጃ ህዝብን ዒላማ አድርጎ ህዝብን ለመታገል መነሳት ስህተት ነው ብያለሁ። በፖለቲካ ህዝብን ዒላማ አይደረግም። ምክንያቱም የፖለቲካ ዓላማ ህዝብን ማገልገል እንጂ ህዝብን መጨቆን አይደለም። ስለዚህ ህዝብን የመበደል ዓላማ መያዝም መተግበርም የህሊና ወንጀል ነው። ህወሓቶች ይህን በሽታ (“የአማራ የበላይነት” መፈክር) አልተዋቸውም። አሁንም “ፀረ አማራ” እንቅስቃሴዎች አሉ። የህወሓት የአሁኑ ስትራተጂ “እኛ ከስልጣን የምንወርድ ከሆነ ከአማራ ጋር አብረን አንቀጥልም” የሚል ገንጣይ አስተሳሰብ እያራመዱ ይገኛሉ። “እኔ ከሌለሁ ሠርዶ አይብቀል …” ዓይነት ስትራተጂ መሆኑ ነው። በጣም የሚገርመው ነገር ፀረ ብአዴንም መነሳታቸው ነው። ለነሱ ከስልጣን ከሚወርዱ ኢትዮጵያ ብትበታተንና ትግራይን አስገንጥለው ትግራይን እየጨቆኑ ቢገዙ ይመርጣሉ።

ግን ይህን “አማራ” የሚባል ህዝብ መቼ ይሆን የበላይነት ይዞ ሌሎች ህዝቦችን የበደለው? አንድን ህዝብ እንዴት ሌላውን ህዝብ ይበድላል? ህዝብ ህዝብን ሊበድል አይችልም። ምክንያቱም አንድን ህዝብ ሌላውን ህዝብ መበደል ከጀመረ (ከቻለ) ህዝብ መሆኑ ቀርቶ ገዢ መደብ (elite) ሁነዋል ማለት ነው። ገዢ መደብ ከሆነ ደግሞ ህዝብ አይደለም። ገዢ መደብ ስርዓት ነው። ህዝብና ስርዓት ደግሞ ይለያያሉ።

ምናልባት የህዝብ የበላይነት አለ የምንለው ህዝብን የሚያስተዳደር (የሚገዛ) ስርዓት ከህዝቡ የወጣ ሲሆን ይሆን? ይህም አሳማኝ አይደለም። ምክንያቱም ገዢ ሁሌ ከህዝቡ ነው የሚወጣው (የቅኝ ግዛት ካልሆነ በስተቀየር)፤ ገዢ ከህዝቡ እንጂ ከማርስ አይመጣም። የኢትዮጵያ መሪ ከኢትዮጵያ ህዝብ ይወጣል። በኢትዮጵያ ብዙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሉ። ስርዓቱ ከሁሉም ህዝቦች ሰዎች ይኖሩታል። መሪ ግን አንድ ነው የሚሆነው። ያ አንድ ሰው (መሪው) ከአንድ ብሄር ሊሆን ይችላል። ያ አንድ ሰው ስልጣኑ ተጠቅሞ ሌሎች ህዝቦችን ሊበደል (ወይ ሊጠቅም) ይችላል። ሰውየው የፈጠረው ስርዓት ለህዝቡ ቢጎዳም ቢጠምም ከስርዓቱ ይገናኛል እንጂ መሪው ከመጣበት ብሄር ጋር አይገናኝም። ስለዚህ ገዢዎች የሚወክሉት የፈጠሩትን ስርዓት እንጂ የመጡበትን ብሄር አይደለም።

የደርግ ስርዓት ሲበድለን፣ “አማራ በድሎናል” ይሉናል። የኃይለስላሴ ስርዓት ሲበድለን “አማራ በድሎናል” ይሉናል። የምኒሊክ ስርዓት ሲበድለን “አማራ በድሎናል” አሉን። የህወሓት ስርዓት ሲበድለንስ ማን በደለን ሊሉን ነው? የትግራይ ህዝብ? አይሆንም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ የትግራይን ህዝብ ይበድላል? አንድን ህዝብ ራሱን ይበድላል? በደል ሁሉ ወደ አማራ ህዝብ ለምን? ስርዓትና ህዝብ ማገናኘት የፖለቲካ ኪሳራ ያስከትላል።

ግን እስቲ ይሁን፤ መሪዎች የመጡበትን ብሄር ይወክላሉ እንበል (ስህተት ቢሆንም)። እነሱ (መሪዎቹ) ሲበድሉ የመጡበት ብሄር በበዳይነት ተፈርጆ እንደ ጠላት ይቆጠር እንበል። የአማራ ህዝብ መቼ ይሆን በመሪዎቹ አድርጎ ሌሎች ህዝቦችን የገዛ (የበደለ)? ያለፉ ጨቋኝ ስርዓቶች አማራ ነበሩ ያለው ማነው? አማርኛ የተናገረ ሁሉ አማራ አይደለም። እስቲ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ መሪዎች እንመልከት።

ብዙ ግዜ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ የሚጀምረው ከአፄ ቴድሮስ ነው (ወይም ከዚሁ እንጀምር! ምክንያቱም ከአፄ ቴድሮስ በፊት ኢትዮጵያ በመሳፍንቶች ነበር የምትተዳደረው። በዘመነ መሳፍንት መሳፍንቶች የራሳቸውን ህዝብ (ብሄር) ይገዙና ይበድሉ ነበር)። “አማራ” ተብሎ ከተሰየመው አከባቢ የሚወለድ ገዢ ቴድሮስ ነው። አፄ ቴድሮስ ኢትዮጵያ አንድ ለማድረግ በዛን ግዜ የነበሩ መሳፍንቶች ተዋጉ። አፄ ቴድሮስ ዉግያው የጀመሩት በአማራ መሳፍንቶች (የጎጃም፣ ወሎና ጎንደር) ነበር። ቴድሮስ “ከአማራ ስለመጣሁ፣ አማራ ስለምወክል፣ የአማራ መሳፍንቶች ማጥፋት የለብኝም” አላሉም። (ህወሓት ለትግራይ መሳፍንቶች እንዳደረገው ሁሉ)። ስለዚህ አፄ ቴድሮስ አማራን ወክለው ሌላው ኢትዮጵያዊ አልበደሉም (ከበደሉም ለሁሉም ነው)። ስለዚህ “በአማራ ህዝብ ተገዛን” የሚለው ክስ “በአፄ ቴድሮስ ተገዛን” የሚል እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ።

የአማራ ተወላጅ የሆነ የኢትዮጵያ ገዢ ቴድሮስ ብቻ ነው ብዬ አስባለሁ (ጉዳዩ ለታሪክ ተመራማሪዎች ልተወው እንዳልሳሳት፤ ከተሳሳትኩ እታረማለሁ)። ዮሃንስ አማራ አልነበረም፣ ምኒሊክ አማራ አልነበረም፣ ኃይለስላሴ አማራ አልነበረም፣ መንግስቱ አማራ አልነበረም፣ መለስ አማራ አልነበረም፣ ኃይለማርያም አማራ አይደለም። ማነው አማራ?

ምናልባት “የአማራ ገዢዎች” የምንለው ግለሰቦቹ (ንጉሶቹና መሪዎቹ) ሳይሆን ስርዓቱ ነው ካልን ያው ስርዓቱማ ከሁሉም ህዝቦች ተወካዮች አሉበት። አማራ ለብቻው ገዥ ነበር ማለት አንችልም። ምናልባት ገዢዎቹ አማርኛ ስለሚናገሩ ነው ካልን ደግሞ አማርኛ የተናገረ ሁሉ አማራ አይደለም። አቶ መለስም አማርኛ ይናገር ነበር። አፄ ዮሃንስም አማርኛ ይናገሩ ነበር (አማርኛ የኢትዮጵያ ኦፊሽየላዊ የስራ ቋንቋ እንዲሆን የወሰኑት አፄ ዮሃንስ ናቸው የሚል መረጃ አለኝ፤ ‘መረጃ’ እንጂ ‘ማስረጃ’ አላልኩም)።

የአማራ ህዝብ እንደ ማንኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በኢትዮጵያ ገዢዎች ሲሰቃይ የነበረ ነው። ባልበላበት በልተሃል፣ ባልገዛበት ገዝተሃል ሲባል ይገርማል፤ ልክ እንደ ትግራይ ህዝብ። የትግራይ ህዝብ ሳይበላ በልተሃል፣ ሳይገዛ ገዝተሃል ይባላል፤ ህወሓት በበላው፣ ህወሓት በገዛው። ህወሓት ትግርኛ ተናጋሪ ስለሆነ ከትግራይ ህዝብ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም (በፖለቲካ መልኩ)። ያለፉ ገዢዎች አማርኛ ስለሚናገሩ ከአማራ ህዝብ ጋር የሚያገናኛቸው ነገር የለም። ህዝብ ሌላ ገዢ ሌላ።

ባጭሩ ፀረ ህዝብ አቋም መያዝ ተገቢ አይደለም (ለማንኛውም ህዝብ)። ሰው የፈለገውን የፖለቲካ አመለካከት መያዝ ይችላል። “የቀድሞ ስርዓት አባላት …” ምናምን እያልን አንፈርጅ። የህወሓት አባላት ለሌሎች ሰዎች የቀድሞ ስርዓት አባላት፣ ናፋቂዎች ወዘተ እያላቹ ስትፈርጁ እናንተም ራሳችሁ ከህወሓት ስርዓት በኋላ “የቀድሞ ስርዓት አባላት ..” ምናምን እየተባላቹ ስማቹ ይጠፋል፣ የፈለጋችሁን የፖለቲካ ፓርቲ አባል የመሆን መብታቹ ይገደባል። አሁን በሌሎች ላይ የምትፈፅሙትን ስም የማጥፋት ተግባር በናንተ (በራሳቹ) ይፈፀማል።

ስለዚህ እናስተውል። ከጥላቻ ፍቅር ይሻለናል። ጥላቻ ይውደም። አሜን!

It is so!!!

እ ጎ አ ከ 2001 – 2006 የእሥራኤል ጠ/ሚንስትር የነበሩትና ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ የአልጋ ቁራኛ ሆነው የቆዩት አሪዬል ሻሮን ፤ በዛሬው ዕለት በደቡብ እሥራኤል በነጌቭ በረሃ በራሳቸው የአርሻ ቦታ በወታደራዊ ሥነ ሥርዓት ግብዓተ መሬት ተፈጽሞላቸዋል።

አርየል ሻሮን።ሞቱ እንዳይባሉ ይተነፍሳሉ።አሉ እንዳይባሉ አይሰሙም፣ አይለሙም።ስምንት አመት።ሐኪሞች «ከስቃይ መገላገያ» በሚሉት ደንብ እንዳይረዷቸዉ «አይሁድ ነብስ አያጠፋም» የሚለዉ ሕግ አገዳቸዉ።እሳቸዉን ግን በነብስ አጥፊነት የሚወነጅሏቸዉ ብዙ ናቸዉ

የአንድነት ፓርቲ አዲሱ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ ዲሲ ከሚገኘዉ የአንድነት ሬዲዮ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገዋል። በቃለ መጠይቁ፣ ወጣቶች በድርጅቱ ዉስጥ ስለሚኖራቸው ድርሻ፣ ስለመድረክ፣ ከኢሕአዴግ ጋር ሊኖር ስለሚገባው ብሄራዊ መግባባት፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ለመዋሃድ እየተደረገ ሳላለው ጥረት፣ በቅርቡ ይታወጃል ተብል ስለሚጠበቀዉ የሁለተኛ ዙር የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ዘመቻና ሌሎች ጉዳዮች ተዳሰዋል። ወጣቶችን በተመለከተ ለማዳመጥ መድረክን በተመለከተ ለማዳመጥ […]

ጥናቱን የማስቆም አልያም የማዘግየት ፍላጎት ያላቸው ሙሰኛና ጎጠኛ ‹ተቃዋሚዎች› የመናፍቃንን ሤራ በውስጥ አርበኝነት የማስፈጸም ተልእኮ ሊኖራቸው እንደሚችል በማስጠንቀቅ ሕጋዊና የሥነ ሥርዐት ርምጃዎች እንዲወሰዱባቸው አመልክተዋል *                *                *   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን  ጥር 5 ቀን 2006 ዓ.ም  ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ …

A couple of years ago, a Canadian writer came to Addis to give a short training for amateur writers including myself. This trainer gave us an assignment of short writing on the first day of the training and we came up with different very short stories from which he chose a few to show some basics.

Among the stories chosen by him, there was one which has a girl character who is managing to attend in a party thrown for her friend’s birthday. The writer of this story, in her narration, explained the ambition of the girl to go to the party and how her mother said “No” angrily as soon as her daughter popped the question.

The trainer wasn’t comfortable of this statement because he thought mothers just don’t say ‘No’ whenever their daughters (and sons) ask them to go to parties. He said the girl’s mother had to ask what kind of party it is before she had to rush to deny permission.

One thing this Canadian didn’t know is the contextual meaning of ‘party’ in Ethiopia. It definitely means that it is an event where alcoholic drinks, smokes are presented accompanied by music and where girls and boys go wrong. It occurs in no Ethiopian’s mind that a party could be like an event or a place where freinds gather and have fun without getting wasted. Even night clubs are referred as ‘party bet’ (party house) colloquially.

So, any healthy mother, who knows the meaning of party in Ethiopia doesn’t let her daughter go to the parties.

What caught my attention since then and throughout is that how wronged our concept of having fun is. The most famous recreation means in Ethiopian cities, next to watching football especially for men, is drinking. Alcohol. (Of course I am talking about the urban life, which I know.)

It starts traditionally. Most type of ‘digis’ (can we call them parties?) have alcoholic drinks like ‘tella’ and ‘tej’. In our bigger cities, beer and other alcohols are joining them. Children who see this want to experience the feeling of getting drunk but aren’t usually allowed to by their parents. They would do it anyway without the knowledge of their parents.

Many youngsters tell their parents they want to crush at their cousin’s place (or friends house, let’s say, to do school assignment) and at the same time the same cousin/friend asks their parents permission to crush on the former’s place and both go to the clubs. If this doesn’t work, there are many people who are making a living out of the youngsters wish to party.

Many self-appointed DJs are always busy throwing day parties for students who never had chance to party in clubs at night. The day parties are usually thrown on weekdays so as to make sure the students parents have no way to know where their children are. The youngsters manage to convince their teachers that wether they are sick or one of their siblings are dead to be absent from school. They party and get wasted, in the real sense of getting wasted.

However the audience of day-parties are mostly highschool students, there are no restrictions on the kind of drinks offered as long as they can afford it. Places are usually reserved for privacy where one can be able to smoke weed, kiss one another and at times have sex. There are also parties where everyone has the right to kiss anyone – and they do that to raise money for another event.

Money isn’t a factor for many of the youngsters. Many parents who send their children to private schools, also give their children much pocket money in competition with other children’s parents without having any idea how it will be spent.

This becomes a habit and many youths have already lost their ways forever. Yet, their parents don’t know what is going on; their school leaders are reluctant about it; and, most of all, the government covered its ears not to hear the defeaning voices of the dying generation.

የሳውዲ ዓረቢያ መንግስት ሕገ ወጥ ስራ ፈላጊዎች ያላቸው የውጪ ዜጎች እንዲወጡ ካዘዘ በኋላ የኢትዮጵያ መንግሥት ካለፈው ህዳር ወር እስካሁን በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች ይኖሩ የነበሩ ከ140,000 የሚበልጡ ዜጎችን ወደ ሀገር መልሶዋል።

ምንሊክ ሳልሳዊ:-የትርፍ ሰአት ፖለቲካ በህዝብ ላይ የሚሴር ያልታወቀ እና ያልተነቃበት ሴራ ነው::ይህ ማለት ፖለቲከኞቹ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በሃሊዮ ወላ በገቢር የህዝብን የመኖር ደህንነት አደፍርሰዋል ::ራሳቸውንም ኢእውቀታዊ ወደሆነ የፖለቲካ ኪሳራ አዘቅት ልከውታል:: ታዲያ ለእነዚህ የትርፍ ሰኣት ፖለቲከኞች ወይም ሴረኞች እንበላቸው ጸረ ህዝብ እና ጸረ ሰላም የሚል ታርጋ ይነሳቸው = ወያኔን አሸባሪ ማፊያ አድፍጦ ገዳይ አፋኝ ወዘተ ስንለው እነዚህን ታቃዋሚ እና ታማኝ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን ሂደታቸው ላይ ያልነቁ ደበኞች ብንላቸው ሲያንሳቸው ነው::

ተቃዋሚ ፖለቲከኝነት በብዛት የትርፍ ሰአት ስራ የሆነባት ኢትዮጵያ አንድም ከወያኔ ቅጥረኝነት ሌላም ከፖለቲካ ከሚገኘው ጥቅም የተትረፈረፈ የህይወት ስኬት ለማግኘት የሚደረግ ሩጫ አስመስሎታል::ያለፉት 22 አመታት መለስ ብለን ስናስበው የሽግግር ወቅት እንዲመሰረት ወያኔ ከፈጠራቸው የአናሳ ድርጅቶች እና በኋላም በተቃዋሚ ስም እንዲንቀሳቀሱ ተደርገው የምክር ቤት ወንበር እስከመያዝ የደረሱት ፖለቲከኞች አንድም የዩንቨርስቲ መምህር ናቸው አሊያም የግል ስራቸውን የሚያሯሩጡ እና በትርፍ ሰኣታቸው ገንዘብ ላለማጥፋት ወደ ፖለቲካው ያዘነበሉ አሊያም ከገዢው ፓርቲ ዳጎስ ያለ ጉርሻ አግኝተው የሚኖሩ ግለሰቦች ናቸው::

የትርፍ ሰአት ፖለቲካ የሚመነጨው ከግለኝነት ስለሆነ በሃገር ላይ የሚደረጉ ህዝባዊ አብዮቶችን እና ለውጦችን በምናገባኝነት ስሜት(አስመሳይነት) እንዲመለከቱት ያደርጋል;ፕሮፓጋንዳን ብቻ ለፖልቲካ ፍጆታነት የመጠቀም ስልት ማለትም ነው::ግለኝነት ስንል ፖለቲከኛው በፖለቲካው ረገድ መጫወት ያለበትን ሚና ረስቶ ከፖለቲካው ከሚገኘው ጥቅም ላይ ስለሚያተኩር ሲሆን ህዝባዊነትን ገደል ይከተዋል:: ወያኔዎች እያንዳንዳቸው ፖለቲካውን ስራዬ ብለው ስለያዙት በፖለቲካው መስክ ያላቸው ስኬት በዲሞክራሲ ስም ወደ አምባገነንነት አድጓል::

የትርፍ ስራ ፖለቲካ ሌላ ያዋጣቸው ለታማኝ ተቃዋሚዎች ነው::ታማኝ ተቃዋሚዎች ከተቃሚነት ሌላ የፖለቲካ ስለላ ያካሂዳሉ:: የፈለጉትን የትምህርት ዘርፍ ይማራሉ::አስፈላጊው የውስጥ እና የቅርብ ርቀት ጥበቃ ይደረግላቸዋል::በዚህ ላይ በስልጣን እርከን እንደመምሪያ ሃላፊ የመሳሰሉትን ስልጣኖች ይሰጣቸዋል:: ከዛም ስልጣን ሰበብ ለማስመሰል ይባረራሉ::አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የህዝብ ጥያቄ ሲነሳ ከትርፍ ስራ ተቃዋሚነት ወደ ቋሚ ፖለቲከኝነት በጊዜያዊነት ተመሳስለው ገብተው እንዲያከሽፉት ይደረጋል:: አቤት ታማኝ ተቃዋሚዎች የመንግስትን ወንበር ከያዙት ይልቅ እኮ እነሱ የተመቻቸው ናቸው::

የትርፍ ሰአት ፖለቲካ እያራመዱ ሃገርን እና ህዝብን የፖለቲካ ኪሳራ ላይ የጣሉ የ22 አመታት የፈጠራቸው ተቃዋሚ ፖለቲከኞች አሁን አሁንማ የኪሳራቸው ውጤት ስድብ ብቻ ሆነ::የትም ላይደርሱ እየተፈራገጡ:: ባለፉት 22 አመታት ጫካ ገብተው ቢሆን እስካሁን የመንግስትን ስልጣን ይዘው ባናፉብን ነበር::በጎረሩብን ነበር:: እኛም ወያኔ ጭራቁን አስወገዱ ብለን ባከበርናቸው ነበር:: እነ ሽማግሌዎቹ ጡረተኛ ፖለቲከኞችም ቢሆኑ በቋሚነት ስላለባቸው ደምብዛት እና ሰኳር ማስታመም ጋዜጣ ማንበብ እና መጻፍ በትርፍ ሰኣታቸው ህዝቡ ትዝ ሲላቸው ተነስተው ይህችኑ ፖለቲካቸውን ይተነፍሱብናል::

ገና በጠዋቱ “ዓሰብን ማስመለስ አለብን የምትለው እንዴት ነው? ወደ አላስፈላጊ ጦርነትና ደም ማፋሰስ ልታስገቡን ፈለጋቹ?” የሚል አስተያየት አዘል ጥያቄ አገኘሁ።

መጀመርያ ወደ ጭንቅላታችን መምጣት ያለበት ጉዳይ ‘የዓሰብ ወደብ የማነው?’ የሚል ነው። ዓሰብ የኢትዮጵያ ልአላዊ ግዛት (ንብረት) ስለመሆኑ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ሕጋዊ (በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት) ማረጋገጫዎች አሉን። ዓሰብ የኛ ስለመሆኑ የሚያጠራጥር ምንም ምክንያት የለም። ማስረጃዎቹ (ማረጋገጫዎቹ) እዚሁ ፌስቡክ ላይ ባልፅፋቸውም በወደቡ ባለቤትነታችን ጥርጣሬ አይግባቹ። ስለዚህ ጥያቂያችን ፍትሐብሄር ነው።
ሁለተኛ ጉዳይ ዓሰብ የኛ ቢሆንም አሁን ያለው ግን በኤርትራ ቁጥጥር ስር ነው። ንብረት ሃብታችን ተነጥቀናል ማለት ነው። ጥያቄው መሆን ያለበት ‘ዓሰብ ወደብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል?’ የሚል ነው። መልሱ: ‘አዎ! ያስፈልጋታል’ ነው። የባህር በሯን የተነጠቀች ብቸኛዋ ትልቅ ሀገር ኢትዮጵያ ናት። በአሁኑ ግዜ የባህር በር የአንድ ሀገር የህልውና በር ነው። የህልውና በሩ መዘጋት የለበትም። ስለዚህ ኢትዮጵያ ንብረቷ (ወደቧ) የማስመለስ መብትም ታሪካዊ ግዴታም አለባት።

ሦስተኛ ‘እንዴት ነው ወደቡን ማስመለስ የምንችለው?’ የሚል ጥያቄ ማየት ተገቢ ነው። ምክንያቱም ዓሰብ የኢትዮጵያ ቢሆንም በመሪዎቻችን ሐላፊነት የጎደለው ዉሳኔ ምክንያት ለኤርትራ ተሰጥቶ ይገኛል። ‘ወደባችን አለ አግባብ ለኤርትራ በመሰጠቱ ምክንያት ዓሰብን የማስመለስ ጉዳይ ከባድ ሊያደርገው ይችላል’ የሚል ሐሳብ ቢነሳ አግባብነት አለው። ጦርነትም ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ሊቀቅ ይችላል።
ግን ማትኮር ያለብን ስለ ጦርነት አይደለም፤ ስለ ዓሰብ ንብረትነት እንጂ። ዓሰብ የኛ መሆኑ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ማረጋገጥ (ማሳመን) ይኖርብናል። በዓሰብ ጉዳይ ፅኑ አቋም ይዘን የኢትዮጵያም የኤርትራም ህዝብ እንዲገነዘበው መጣር አለብን። የዓለም ህዝብ ይሁን መንግስትታት ይደግፉናል። ምክንያቱም የባለቤትነት መከራከርያ ነጥባችን ጠንካራ ነው። የዓለም አቀፍ ሕግም ይደግፈናል። ዓሰብ የኢትዮጵያ ስለ መሆኑ የሚመሰክግሩ የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ ስምምነቶችም አሉ።
አራተኛ ዓሰብ የኛ መሆኑ ቢናረጋግጥና ለዓለም መንግስታትና ማህበረሰብ ቢናሳውቅ እንኳ እንዴት ዓሰብን መመለስ እንችላለን? የኤርትራ መንግስትኮ ፍቃደኛ አይሆንም፣ ጦርነት ሊነሳ ይችላል … ወዘተ የሚሉ ጉዳዮች መነሳታቸው አይቀርም። ግን ችግር የለውም። ዓሰብ የኛ መሆኑ ካረጋገጥን ‘ንብረታችን መልስልን’ ብለን የመጠየቅ መብት አለን። የኤርትራ መንግስት ፍቃደኛ ላይሆን ይችላል። ጦርነትም ሊከፍት ይችላል።
እኛ ጦርነት አንፈልግም። ሕጋዊ ንብረታችን (ወደባችን) በሰለማዊ መንገድ እንዲሰጠን ነው የምንጠይቀው። አዎ! ጦርነት አንፈልግም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ግን ጦርነት ከፍተን በሃይል የሌላ ሀገርና ህዝብ ንብረት አንወርም ማለት እንጂ ጦርነት ፈርተን ልአላዊ ግዛታችን (ሃብታችን) ለሌሎች ሃይሎች አሳልፈን እንሰጣለን ማለት አይደለም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ጦርነት እንፈራለን ማለት አይደለም። አዎ! ጦርነት ስለማንፈልግ ሌሎች ህዝቦችን አንወርም። ጦርነት ፈርተን ግን እናት ሀገራችን አናስደፍርም።
ጦርነት ስለማንፈልግ ዓሰብን በሰለማዊ መንገድ የምንረከብበት መንገድ እናመቻቻለን። የኤርትራ መንግስት ጦርነት ሊከፍትብን ይችላል ብለን ግን ሃብት ንብረታችን ከመጠየቅ ወደኋላ አንልም። ጦርነት ተፈርቶኮ የሀገር ግዛት አሳልፎ አይሰጥም። ጦርነት ተፈርቶኮ ልአላዊ ግዛትን ከማስከበር ወደኋላ አይባልም። በባድመ ጉዳይ ጦርነት ዉስጥ የገባነው ጦርነት ስለምንፈልግ ሳይሆን ልአላዊ ግዛታችን የማስከበር፣ ሀገራችን ከወራሪዎች የመከላከል ሀገራዊ ግዴታ ስላለብን ነው። ጦርነት ፈርተን እጃችንና እግራችን አጣጥፈን የባድመን መሬት ለሻዕቢያ ወራሪዎች አሳልፈን አልሰጠንም።
(በኋላ በፖለቲካዊ ዉሳኔ፣ በመሪዎቻችን ግድየለሽነት ምክንያት ባድመን መስዋእት ከፍለን በደም አስመልሰን ሲናበቃ በእስክርቢቶ ለወራሪዎች ተላልፎ ተሰጠ እንጂ። በጦርነት የተመለሰ ንብረት በድርድር ሲከሽፍ በታሪክ ለመጀመርያ ግዜ ነው። የባድመ ጉዳይ …!)
ምንም እንኳ ጦርነት ባንፈልግም ሃብት ንብረታችን ግን አሳልፈን አንሰጥም። ጦርነት መስዋእት ይጠይቃል። ግን ለሀገራችን መስዋእት ብንከፍል ችግሩ ምንድነው? ለሀገራችንኮ መሞት አለብን። በምንክያት መስዋእት መሆን እንቻላለን። ደግሞኮ ኢህአዴጎች የዓሰብን ጉዳይ ስናነሳባቸው ‘ጦርነት ናፋቂዎች’ ይሉናል። እኔ ግን ለሀገር መስዋእት ብንከፍል ጉዳት የለውም ባይ ነኝ። እንኳንም ለሀገራችን ኢትዮጵያ ለሶማሊያም እየሞትን ነው። ይቅርታ ለሶማሊያም እየሞትን አይደለንም። ምክንያቱ ላልታወቀ ጉዳይ ነው በሶማሊያ እየሞትን ያለነው። ወታደሮቻችን በሀገረ ሶማሊያ እየሞቱ ያሉ ለምን ዓላማ ነው? ዜጎቻችን ዓላማው ለማይታወቅ ጉዳይ በሶማሊያ ከሚሞቱ ለሀገራችን ቢሞቱ አይሻልም ነበር? ኢህአዴጎች ‘ጦርነት ጥሩ አይደለም’ ይሉናል። ጦርነት ጥሩ አለመሆኑ ቢያውቁ ኑሮ ለምን በሶማሊያ ያሉ ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው አያስገቡም?
አዎ! ጦርነት ጥሩ አይደለም። በተቻለ መጠን ጦርነትን ማስወገድ አለብን። ጦርነት ፈርተን ግን ሀገራችንን አሳልፈን አንሰጥም።
አሜን!

/መስፍንወልደማርያም

በአሁኑ ጊዜ ወያኔ ሰውን እያፈረሰ፣ ማህበረሰብን እያፈረሰ ሰማይ-ጠቀስ ሕንጻዎችን በሚሠራበት ጊዜ፣ ከትናንት ወዲያ የሰዎችን ቤቶች አፍርሶ ትናንት የመኪና መንገድ ከሠራ በኋላ ዛሬ መንገዱን አፍርሶ የባቡር መንገድ እየተሠራ አዲስ አበባ በትራፊክ መጨናነቅ መኪና መንዳት አደገኛ በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ባለሥልጣኖች የሚሠሩት ጠፍቶአቸው የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ የሚባለውን በአማካሪዎች ከሞሉት በኋላ ለሚኒስትሮችም አማካሪ መሾም በተጀመረበት ጊዜ፣ ዛሬ በሳኡዲ አረብያ ኢትዮጵያውያን እንደአደገኛ አውሬ እየታደኑ በሚደበደቡበት፣ በሚታሰሩበት፣ በሚደፈሩበትና በሚገደሉበት ጊዜ፣…

ሙሉውን አስነብበኝ …

እስራኤልን ለአምስት ዓመታት መርተዋል
አርኤል ሻሮን  Ariel SharonEthiopia Zare (ቅዳሜ ጥር 3 ቀን 2006 ዓ.ም. Jan 11, 2014)፦ የእስራኤል የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር የነበሩትና ሀገሪቷን ለአምስት ዓመታት ያህል የመሩት አርኤል ሻሮን በሰማንያ አምስት ዓመታቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

‹‹ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት አስተዳደር በቤተ ክርስቲያን ለመዘርጋት የተረቀቀው ሕግ ወደ ኋላ አይመለስም፤ መሥመሩን አይለቅም›› /ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/ (አዲስ አድማስ፤ ጥር 3 ቀን 2006 ዓ.ም.) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለመዋቅርና አሠራር ለውጥ በባለሞያ ያካሔደውን የአደረጃጀትና የአሠራር ጥናት እንቃወማለን የሚሉ ውስን አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች አይወክሉንም ሲሉ የሀገረ ስብከቱ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎች፣ የሰበካ ጉባኤያት …

በደቡብ ሱዳን ካለፈው ታህሣሥስድስት ወዲህ የቀጠለውን እና ከአንድ ሺ በላይ ህዝብ ያጠፋውን፤ ከ 200,000 በላይ ህዝብ ውጊያ ለማስቆም በተፋላሚ ዎቹ ወገኖች ተወካዮችመካከል በኢጋድ ሸምጋይነት በአዲስ አበባ

የእስራኤል መንግሥት አዲስ ያወጣውን የስደተኞች ሕግ እና በስደተኞች ላይ የሚያደርሰዉን በደል በመቃወም በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪቃዉያን ሰሞኑን በተከታታይ የአደባባይ ሠልፍ ሲያካሂዱ ሰነበቱ።

Image

በአሁኑ ጊዜ ወያኔ ሰውን እያፈረሰ፣ ማህበረሰብን እያፈረሰ ሰማይ-ጠቀስ ሕንጻዎችን በሚሠራበት ጊዜ፣ ከትናንት ወዲያ የሰዎችን ቤቶች አፍርሶ ትናንት የመኪና መንገድ ከሠራ በኋላ ዛሬ መንገዱን አፍርሶ የባቡር መንገድ እየተሠራ አዲስ አበባ በትራፊክ መጨናነቅ መኪና መንዳት አደገኛ በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ባለሥልጣኖች የሚሠሩት ጠፍቶአቸው የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ የሚባለውን በአማካሪዎች ከሞሉት በኋላ ለሚኒስትሮችም አማካሪ መሾም በተጀመረበት ጊዜ፣ ዛሬ በሳኡዲ አረብያ ኢትዮጵያውያን እንደአደገኛ አውሬ እየታደኑ በሚደበደቡበት፣ በሚታሰሩበት፣ በሚደፈሩበትና በሚገደሉበት ጊዜ፣ ዛሬ በኬንያና በዩጋንዳ እንዲሁም በእሥራኤል ኢትዮጵያውያንን የማንገላታት ዝንባሌዎች በሚታዩበት ጊዜ፣ ዛሬ ኢትዮጵያውያን ከስዊድን እስከአውስትራልያ እየተሰበሰቡ በመጮህ ለማይሰሟቸው ሁሉ አቤቱታቸውን በሚያቀርቡበት ጊዜ፣ ዛሬ በተለያዩ አገሮች በኢትዮጵያውያን ላይ በሚፈጸመው ጥቃትና በደል፣ አለሁላችሁ የሚል መንግሥት በሌለበት ጊዜ —- ዛሬ ታሪካዊትዋ ኢትዮጵያ፣ ራሳቸውን የሚያከብሩና ኩራት ራታችን የሚሉት ኢትዮጵያውያን አልቀው ለሆድ በየሰው አገር መሰደድ ባህል በሆነበት ጊዜ፣ ዛሬ ዶር. በድሉ ዋቅጅራ ስለኢትዮጵያና ስለኢትዮጵያውያን ውርደት ደጋግሞ የነፍሱን ኡኡታ ባሰማበት ጊዜ በድንገት አንገታችንን ቀና አድርጎ ኩራታችንን ሊያስጎነጨን የሞከረ ሰው ተገኘ! ኢትዮጵያ ሁሌም የተአምር አገር ነች።
በታላቁ ሰው በኔልሰን ማንዴላ እረፍት ምክንያት አንድ ተደብቆ የኖረ ክቡር ኢትዮጵያዊ ብቅ አለ፤ ማንዴላ ለሥልጠና በኢትዮጵያ በነበረበት ጊዜ ምናልባትም እንግሊዞች ማንዴላን ሊያስገድሉ ከጠባቂዎቹ አንዱ የነበረውን ወታደር በገንዘብ ገዝተው ዓላማቸውን ለመፈጸም አቅደው ነበር፤ ወታደሩ ገንዘቡን ከተቀበለ በኋላ ሀሳቡን ለውጦ ገንዘቡን ለአለቃው ሰጠ፤ ማንዴላ ከሞት ተረፈ፤ አንድ ተራ ኢትዮጵያዊ ራሱንና አገሩን የሚያስከብር ሥራ ሲሠራ የሚኮሰኩሳቸው ባለሥልጣኖች ለእነሱ የማይተላለፍ ክብር በመሆኑ ተዳፍኖ እንዲኖር አደረጉት፤ እነሱ ሞተው ወይም ተሰድደው ሲያልቁ የተዳፈነው ምሥጢር ብቅ አለ፤ ባለሥልጣኖቹ ሸልመውት ይሆናል፤ ግን አላከበሩትም፤ ሻምበል ጉታን ያከበረው የማንዴላ ሞት ነው፤ የሚያሳዝነው ማንዴላ ይህንን የሱን ሕይወት ለማትረፍ ሁለት ሺህ ፓውንድ ያጣውን ኢትዮጵያዊ ወታደር ሳያውቀው መሞቱ ነው።
የኢትዮጵያ አርበኞች ታሪካቸው ተቀብሮ የቀረው እንዲህ እየሆነ ነው፤ ታዴዎስ ታንቱ ሥራዬ ብሎ የተረሱ አርበኞችን ከመቃብር እያወጣ ያስተዋውቀናል፤ በሌሎች አገሮች እንደዚህ ለአገር ትልቅ ፋይዳ ያለው ሥራ በአንድ ሰው በበጎ ፈቃድ የሚሠራ ሳይሆን ዋና የመንግሥት ተግባር ነው።
ሻምበል ጉታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ባይሆንም ራሱን ችሎ ለኔልሰን ማንዴላ መቃብር ደርሶአል፤ በአገር ደረጃ በሥልጣን ወንበሮቹ ላይ ለአገር የሚያስቡ ሰዎች አለመኖራቸውን ለማወቅ ግሩም ማስረጃ ነው፤ ለቀብር የሄደው ባለሥልጣን ሻምበል ጉታን ይዞ ቢሄድ ኖሮ ለራሱም ሆነ ለአገሩ ክብርና ጌጥ ይሆንለት ነበር፤ ለደቡብ አፍሪካ ሕዝብም ሆነ ለዓለም በመላ አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር አልሸጥም-አልለወጥም ብሎ የኔልሰን ማንዴላን ሕይወት ማትረፉን በማስታወቅ አገሪቱን ያስከብር ነበር፤ የታፈነው ታሪክ አፈትልኮ ሲወጣ ከስደተኞች ጋር ተያይዞ መሆኑ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የአደባባይ መክሸፍ የሚያሳይ ነው፤ ባለቤት ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳ ተቀበለው፤ መንግሥት ያፈነውን ክብር ስደተኞች አጌጡበት!
ለእኔ አሁን አንድ ጥያቄ ይቀራል፤ ሻምበል ጉታ የአገሩን ክብር ከራሱ ጥቅም በላይ በማድረጉ፣ የተቀበለውን አደራ በመጠበቁ ቢያንስ ሁለት ሺህ ፓውንድ አጥቷል፤ እንዳጣ ሊቀር ነው? ቢያንስ የከፈለውን ሁለት ሺህ ፓውንድ ወይስ ያንን አሥር እጥፍ አድርገን እንከፍለዋለን? ሻምበል ጉታን የምናመሰግነው በርጥቡ ነው በደረቁ? እኛ ያለጥርጥር ኮርተንበታል፤ ሁላችንም በኢትዮጵያዊነታችን የሱን ክብር በመጋራት ራሳችንን አክብረናል፤ ሻምበል ጉታም በእኛ እንዲኮራና በእኛ እንዲከበር ማድረግ ያለብን ይመስለኛል፤ ስለዚህ ምን እናድርግ? ለራሱ ክብር፣ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ክብር ሲል የከፈለውን እስቲ ከወሬ ያለፈ ነገር እናስብና ለዚህ ጀግና የምንችለውን አድርገንለት እግዚአብሔር ዕድሜ ይስጥህ እንበለው።

ሕወሓት መራሹ ገዢ መደብ ኢሕኣዴግ በድርጅቱ ውስጥ ባደረገው ውስጣዊ ጥናት እና ግምገማ መሰረት ከተቃዋሚው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ቁርኝት አላቸው ግንኙነት ፈጥረዋል ለዲሞክራሲያዊ ስርኣቱ እንቅፋት ሆነዋል የድርጅቱን መረጃ አቀብለዋል ያላቸውን አባሎቹን ሊያባርር መሆኑን ከአዲስ አበባ የኢሕኣዴግ ጽ/ቤት የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል::

በዚሁም መሰረት የተደረገው ውስጣዊ ጥናት እና ግምገማ እንዲሁም ከብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ቢሮ የተገኘ ማስረጃን መሰረት በማድረግ የሚባረሩትን አባላት እና ከተባረሩ በኋላ ሊወሰድባቸው የሚገባ እርምጃ እየተጠና መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ጦር ሰራዊቱ የከፍተኛ መኮንኖች ግምገማ ሊያደርግ መሆኑ ታውቋል::ከሻለቃ ማእረግ ጀምሮ ወደላይ እስከ ጄኔራሎች ድረስ የሚደረገው ግምገማ አጀንዳው ሙስናን ያጠቃል/አያጠቃል ባይታወቅም በዚህ ሰሞን በሕወሓቱ ጄኔራል ሳሞራ ቢሮ የተሰበሰቡት ጄኔራሎች በከፍተኛ መኮንኖች ላይ ግምገማ እንዲደረግ መወሰናቸው ሲታወቅ በግምገማው ላይ የሚገመገሙ መኮንኖች ስም ዝርዝር እንዲዘጋጅ ለወታደራዊ ደህንነት ክፍል ትእዛዝ የተሰጠ ሲሆን ስም ዝርዝራቸው ያልተጠቀሱ መኮንኖች እንደማይገመገሙ ሆኖም እንደሚገመግሙ ታውቋል::ምኒልክ ሳልሳዊ

‹‹በቤተ ክርስቲያን ልጅነት በግብረ ገብነት መነጋገር ነው እንጂ ሕገ ወጥ ንግግር ተቀባይነት የለውም፤ ይኼ የአሁኑ የእናንተ የረጋ አቀራረብ ነው፤ ያስመሰግናል፤ ቤተ ክርስቲያን ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለው አስተዳደር እንዲኖራት ነው የኹላችን ጥረት፤ ወደኋላ የምንመለስበት ምንም ምክንያት አይኖርም፤ መሥመሩን አይለቅም›› /ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ/ ‹‹የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ያስጠናውን ተወያይተንበታል፤ የታሰበው የአደረጃጀትና የአሠራር ማሻሻያ የሚያነቃቃ ነው፤ ቤተ ክርስቲያናችን መልካም …

የደቡብ ሱዳን አማጺያንና መንግሥት በጠብ ያለመፈላለጉን ስምምነት ያለምንም ቅደመ ሁኔታ እንዲፈራረሙ ዩናይትድ ስቴትስ ጠይቃለች፡፡

ፕሬዚደንት ሳልቫ ኪርም ታሣሪዎቹን የሱዳን ሕዝብ አርነት ንቅናቄ – ኤስፒኤልኤም አመራር አባላት እንዲፈቱም ጥሪ አቅርባለች።

ሁለቱ የደቡብ ሱዳን ወገኖች ዛሬም ለሦስተኛ ቀን ፊት ለፊት አልተወያዩም።

የተያያዘው የእስክንድር ፍሬው ዘገባ ዝርዝሩን ይዟል፤ ያዳምጡት

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ዘጋቢዎች ከጎንደር እንደገለጹት ኮማንደር አለባቸው የተባሉት የሰሜን ጎንደር ዞን የወይኔ ቤት አዛዥ የተገደሉት ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ ነው። ኮማንደሩ በጥይት መመታታቸው ቢገለጽም ዘጋቢያችን ማን እንደገደላቸው ለማወቅ ያደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። የግለሰቡ አስከሬን ወደ ተወለዱበት በየዳ ወረዳ መላኩ ታውቋል። አወጋን እየተባለ የሚጠራው ድርጅት ግድያውን መፈጸሙን ገልጿል። ድርጅቱ በማህበራዊ …

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በወልድያ የሚገኙ ነጋዴዎች፣ ለኢሳት እንደገለጹት  ፈቃድ ለማሳደስ በሚሄዱበት ጊዜ ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ቦንድ ካልገዛችሁ አይታደስላችሁም ተብለዋል። የግል ክሊኒኮችን ከፍተው የሚሰሩ ነጋዴዎች ለኢሳት እንደገለጹት፣ ፈቃዳቸውን ለማሳደስ በሚሄዱበት ጊዜ ከ2ሺ ብር ጀምሮ ቦንድ እንዲገዙ ተገደዋል። የኢህአዴግ ካድሬዎች በየቀበሌው እየዞሩ ነጋዴዎች ቦንድ እንዲገዙ ያለበለዚያ የንግድ ፈቃዳቸው እንደማይታደስላቸው እያስጠነቀቁ ነው። እድሮችና  …

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሚያ የአካባቢ ጥበቃ የአካባቢ ተፅዕኖና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ አቶ አሕመድ ሁሴን በኦሮሚያ ክልል አካባቢን ለመጠበቅ እየተደረጉ ስላሉ እንቅስቃሴዎችና አካባቢን በማይጠብቁት ላይ ምን ዓይነት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት እንዲሁም ስለተወሰዱ እርምጃዎች እንደገለጹት፣  በኦሮሚያ ክልል ከአካባቢ ተፅዕኖ ጋር የሚነሱ ችግሮች በክልሉ በሚካሄዱ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የተነሳ በአካባቢ ላይ ጉዳት ይደርሳሉ፡፡ ይህንን …

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ2003-2005 ዓ.ም መንግስት መንደር ማሰባሰብ በሚል በሚጠራው የሠፈራ ፕሮግራም በጋምቤላ በ12 ወረዳዎች 38 ሺ፣በቤንሻንጉል ጉሙዝ በ18 ወረዳዎች 77 ሺ ፣በአፋር በ8 ወረዳዎች 10ሺ፣ በሶማሌ በ21 ወረዳዎች 150 ሺ አባወራና እማወራዎች በድምሩ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሕዝብ እንዲሰፍር ተደርጓል፡፡ እስከ2007 የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ማጠናቀቂያ ድረስ 85ሺ ቤተሰብ ለማሰባሰብ …

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአገሪቱ ጦር ሀይሎች ቃል አቀባይ እንደገለጹት አማጽያኑ የነዳጅ ማውጫ ጉድጓዶች የሚገኙባትን ቤንቲዩን ለቀው የወጡት እኩለ ቀን ላይ ነው። የደቡብ ሱዳን መንግስት አካባቢውን መቆጣጠሩን ቢገልጽም፣ በአማጽያኑ በኩል የተሰጠ ምንም አይነት ምላሽ የለም። መንግስት የነዳጅ ከተማዋን መቆጣጠሩ አማጽያን በመንግስት የቀረበውን ቅድመ ሁኔታ ለመቀበል ይገደዱ ይሆናል የሚል አስተያየቶች ቀርበዋል። በኢትዮጵያ …

በሕዋ ሣይንስ ዘርፍ የሚሠራው የሥነ ፈለክ ኅብረት አሥራ አራት አገሮችን የሚያስተባብር ፅሕፈት ቤት አዲስ አበባ ላይ ለመክፈት ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

የፅሕፈት ቤቱ አዲስ አበባ ላይ መከፈት ኢትዮጵያን ይበልጥ ተጠቃሚ ሊያደርግ እንደሚችል የኢትዮጵያ የጠፈር ሣይንስ ማኅበረሰብ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተፈራ ዋልዋ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

በደቡብ ምዕራብ ወሎ፥ ቦረና ውስጥ ካሁን ቀደም የማይታወቁ ጥንታዊ የድንጋይ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናትን ማግኘታቸውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች አስታወቁ።

አብያተ ክርስቲያናቱ ለአደጋ የተጋለጡ መሆናቸውንም ባለሞያዎቹ አክለው አስረድተዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የመለስካቸው አምሃ ዘገባ ያዳምጡ፡፡