ደቀ መዛሙርቱ ጽ/ቤቱ ከመንግሥት በመነጋገር የደኅንነት ጥበቃ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል የልዩ ጽ/ቤቱን ለቃችኹ ውጡ ትእዛዝ ‹‹ሕግን የጣሰና ለከሳሽ ያደላ›› በሚል ተቃውመውታል የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ እና የጠ/ቤ/ክህነቱ ዋ/ሥራ አስኪያጅ ደቀ መዛሙርቱን እያረጋጉ ነው የፓትርያሪኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ አቡነ እስጢፋኖስ ከደቀ መዛሙርቱ ጎን ቆመዋል ተብሏል ኹኔታው ያሳሰባቸው የማታ ተማሪዎች ተወካዮች ከቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት ጋራ ተወያይተዋል የኮሌጁ መምህራን አቡነ ጢሞቴዎስ …

ሐምሌ ፱( ዘጠኝ )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰሜን ሺዋ ዞን የደብረ ብርሃን ከተማ ኗሪዎች የመንግስት ሹማምንት የሚያደርሱባቸውን በደሎች በመዘርዝር ለመንግስት አቅርበዋል። ክልሉ በቅርቡ በጀመረው የህዝብ ብሶቶችን መስሚያ መድረኮች ላይ ነዋሪዎች ” በአደባባይ እንደበደባለን ፤እንታሰራለን፤ በአገራችን በሰላም ለመኖር አልቻልንም” ሲሉ ምሬታቸውን ገልጸዋል፡፡በተደጋማሚ በሚደርስባቸው በደል አገር ጥለው የሚሰደዱ ዜጎች መበራከታቸውንም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። ሹመት የሚሰጠው በዘመድ ዝማድ …

ሐምሌ ፱( ዘጠኝ )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በያዝነው ወር ብቻ 500 ሲቪሎች፣ ከጅጅጋ፣ ደገሀቡር፣ ዋርዴር እና ጎዴ በደህንነት ሀይሎች ተወስደው እስር ቤት ገብተዋል። አዲሱ የእስር ዘመቻ የተከፈተው በቅርቡ በርካታ የመንግስት ባለስልጣናትና ወታደሮች ከድተው እጃውን ለኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት ከሰጡ በሁዋላ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል። ከታሰሩት መካከል በርካታ ህጻናትና ሴቶች ሲገኙበት፣ አብዛኞቹም ጅጅጋ አካባቢ በሚገኝ ወታደራዊ …

ሐምሌ ፱( ዘጠኝ )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 11 ሺ 93 ስዎች ከነፍስ ግድያ ሙከራ ተደርጎባቸው ተርፈዋል፡፡ የክልሉ አሰተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ባካሄደው  የዳሰሳ ጥናት በ10 አመታት ውስጥ ከነፍስ ግድያ ጋር በተያያዘ 13 ሺ 64 ሰዎች ሲገደሉ ፣ 11 ሺ 93 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። በጥናቱ ውስጥ እንደተመለከተው ድብደባ መፈጸም ቀዳሚነቱን ሲይዝ  አካል ማጉደል እና …

ሐምሌ ፱( ዘጠኝ )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአፍሪካ ህብረት በጤና ጉዳይ ላይ ለመመካከር በናይጀሪያ ባዘጋጀው ስብሰባ ላይ የተገኙት የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር ሰብሰባቸውን ሳይጨርሱ ወደ አገራቸው የተመለሱት ፣ አለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የናይጀሪያ መንግስት ይዞ እንዲያስራቸው አቤቱታውን ለፍርድ ቤት ካቀረበ በሁዋላ ነው። ፕሬዚዳንቱ ሰኞ እለት ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ በድንገት አገሪቱን ለቀው መውጣታቸው …

ብሔርተኝነትን መግለፅ ለኤርትራዉያን ወጣቶች የሚመጣ ችግርን መከላከያ ጥሩ ሥልት ነዉ።ሌላ ቢሎ መዘዙ ሌላ ነዉ።አምስት ሚሊዮን ሕዝብ ያላት ትንሽ ሐገር እራሷን ከተቀረዉ ዓለም ዘግታለች።ከሠላሳ ዓመት ጦርነት በሕዋላ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ድጋፍ ነፃነትዋን በይፋ ያወጀችዉ በ1985 ነዉ።

ከዛሬ አምስት ዓመት ተኩል ወዲህ ደግሞ ጋንዲ በሲና በረሃ በግብፅ በሊቢያና በቱኒዝያ እስር ቤቶች የሚሰቃዩ ባመዛኙ ኤርትራውያን ስደተኞችን እየረዳ ነው ። ጋንዲ ሲና በረሃ የታገቱ በርካታ ስደተኞችን ከአፋኞቻቸው ነፃ ለማውጣት በቅቷል ።

በኢጣልያ የሊጋ ኖርድ ፓርቲ እንደራሴ እና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚደንት ሮቤርቶ ካልዴሮሊ በሀገሪቱ የመጀመሪያዋ ጥቁር ሚንስትር ዶክተር ሴሲል ኪዬንጌ ላይ አሳፋሪ አስተያየት የሰነዘሩበት አነጋገር ከተለያዩት የሀገሪቱ ፓርቲዎች እና ከሕዝቡ ብዙ ተቃውሞ ቀስቀሰ።

መጾም መራብ ሳይሆን ተፈጥሯዊ የሆነ የአኗኗር ስልት ነዉ ይላሉ የዚህ ሃሳብ አራማጆች። ዓላማቸዉ በየደረጃዉ ተዘጋጅተዉ ለገበያ በሚቀርቡት የተለያዩ የኢንዱስትሪ ምግቦች ምክንያት ወደአካላችን ገብቷል የሚሉት አላስፈላጊ ንጥረ ነገር እነሱ መርዝ የሚሉትን በተፈጥሯዊ ስልት ከሰዉነት ለማስወገድ ነዉ።

እስራኤል በምድሯ የሚገኙ ጥገኝነት ጠያቂ አፍሪቃዉያንን ወደየመጡበት አስገድዳ መመለሷን የመብት ተሟጋቾች አወገዙ። ከትናንት በስተያ እስር ላይ ካቆየቻቸዉ ሁለት ሺህ ኤርትራዉያንና ሱዳናዉያን መካከል 14 ኤርትራዉያንን ወደአስመራ መላኳን አንድ የእስራኤል የመብት ተሟጋች ድርጅትና ሂዉማን ራይትስ ዎች ይፋ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) ዕሁድ ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ. ም በጎንደርና በደሴ ከተሞች የተካሄዱትን ትዕይንተ-ሕዝቦች ይደግፋል። ”የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት!” በሚል መሪ ሃሳብ ሥር በአንድነት ፓርቲ አቀነባባሪነት የተጀመረው የሕዝብ እንቅስቃሴ፤ የተጋረጠበትን እንቅፋት ሁሉ አልፎ እነሆ በደሴና በጎንደር ከተሞች በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ በሕዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ የፍራቻ ድባብን ሰብሮ በይፋ ለመግልጥ መቻሉ ሁሉንም […]

ሃብትና ስልጣን አስክሮአቸው፣ በዚህች ደሃ ሃገርና ሕዝብ ላይ ተፈናጠው ሁለት አስርተ አመታት ያስቆጠሩ አምባገነን መሪዎቻችን የሃገርና የሕዝበ ፍቅር አጥተው በምዝበራ ለመክበር ብቻ፣ ሕዝብንም በሃገሩ በሰላም የመኖር መብቱን ቀምተው ተደላድለው ለመቀመጥ ዘንድሮም እንደ አምናው በሽብር ስም በጫኑብን የአፈና መረብ ሸብበው ሕዝቡን ከዳር እዳር ማስጨነቃቸው ሳያንስ አሁን ደግሞ ለዚህ እኩይ ተልኳቸው ላሰለጠኑዋቸው የስርዓቱ ሰዎች (ደህንነቶች) በዴሞክራሲና በመልካም […]

ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2005 ዓ.ም መንግስት የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን የወረዳ አመራሮችንና አባላትን በዘመቻ ማሰር ጀምሯል፡፡ እስከአሁኗ ሰዓትም 42 የሚሆኑ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት በፖሊሲ ቁጥጥር ስር ይገኛሉ፡፡ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጠኞች ተዘዋውረው እንደዘገቡት 42 የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላት በፖሊስ እንዲታሰሩ ተደርጓል፡፡ የአንድነት ፓርቲ በአዲስ አበባ እያሰራጨ ያለውን ህጋዊ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በማደላቸው […]

የኮሌጁ የቀን መርሐ ግብር እስከ መስከረም አጋማሽ ፳፻፮ ዓ.ም ድረስ እንዲቋረጥ ተወስኗል ደቀ መዛሙርቱ በቀጣይ ርምጃዎቻቸው ላይ እየመከሩ ነው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ኮሌጁን ‹‹በሰላማዊ መንገድ›› ለቀው እንዲወጡ የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት በይፋ አዘዘ፡፡ ልዩ ጽ/ቤቱ ዛሬ፣ ሐምሌ ፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ከቀትር በኋላ በኮሌጁ የለጠፈው ማስታወቂያ፣ የኮሌጁ ደቀ መዛሙርት ማስታወቂያው ከወጣበት ከዛሬ ሐምሌ …

የተቃዉሞ ሠልፍ መደረጉን፥ አንዳዶች ገዢዉ ፓርቲ ላለፉት ስምንት ዓመታት ይከተለዉ ከነበረዉ መርኹ የመለሳለሱ ምልክት ይሉታል።ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመጠናከራቸዉ ማሳያ ነዉ-ባዮችም አሉ። ሌሎች ደግሞ ቢያንስ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን የሚደግፈዉ ሕዝብ ተቃዉሞዉን ለማሰማት ዶክተር ነጋሶ እንዳሉት የመቁረጡ አብነት ነዉ።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ ፤«የሚሊዮኖች ድምፅ ለነጻነት »በሚል መሪ ቃል ለ 3 ወራት ያወጣውን የህዝብ ንቅናቄ እቅድ ትናንት በጎንደርና ደሴ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ እንዲከናወን በማድረግ ጀመረ። ከትናንቱ ሰልፍ በፊት ፣ ህዝብ ለሰልፍ እንዲወጣ

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አርብ ፣ ሀምሌ 6 2005 ዓም በእነ አቶ ተሻለ ኮርኔ መዝገብ የተከሰሱ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ፍርድ ቤት የሚወስዳቸው ፖሊስ ያጣሉ። በቅጽል ስሙ ሻእቢያ እየተባለ የሚጠራውን የእስር ቤቱን ሀላፊ ሲጠይቁት ቀጠሮአቸው ለ4 ወር መራዘሙን ይነግራቸዋል። እስረኞቹም ” ከ2 አመታት በላይ የላፍትህ ታስረን በመጨረሻ …

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው በደሴና እና በጎንደር የተሳኩ የተቃውሞ ሰልፎችን ባካሄደ ማግስት ከ30 በላይ አባሎቹ በዋና ከተማዋ የተቃውሞ ፊርማ ሲያሰባስቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ባለፉት ሳምንታትትም በተመሳሳይ መንገድ የታሰሩ እና የፍርድ ቤት ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ያሉ አባላት አሉ። አንድነት ፓርቲ ለ3 ወራት በሚቆየው የተቃውሞ እንቅስቃሴ  በዋና ዋና ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን …

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ሕዝበ ክርስቲያኑ ከጎናቸው እንዲቆም በመጠየቅ ትናንት በአመታዊ የሥላሴ ክብረ በዓል ላይ  መፈክሮችን ሲያሰሙ ውለዋል። ተማሪዎቹ ሲያሰሙዋቸው ከነበሩት መፈክሮች መካከል፦የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን መዝጋት ታሪክን ማጥፋት/ማበላሸት ነው!፣የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ችግራችንን ይመልከት!፣ሙስናንና ኑፋቄን የሚያደቅ ክንድ አለን!የምንማረው በምእመናን ብር ነው፡፡ ሌቦች ሆይ፣ እጃችኹ ይሰብሰብ! …

ሐምሌ ፰( ስምንት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል የሥነምግባርና የጸረ ሙስና ኮምሽን በቅርቡ ባካሄደው የአሰራር ሥርዓት ጥናት በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የግዥ አፈፃፀም ለሙስና እና ብልሹ አሠራር የተጋለጠ ነው ብሎአል፡፡ በፖሊስ ኮምሽኑ የተጠና የጠቀሜታ ዝርዝር /ስፔስፊኬሽን/ አዘገጃጀት አሰራር አለመኖር፣ ግዥዎችን በዕቅድና በፕሮግራም አለመፈፀም፣ በጀት መኖሩ ሳይረጋገጥ የግዥ ሂደቶችንማከናወን፣ በግዥ መመሪያው ከተቀመጠው የገንዘብ መጠን በላይ ግዥ …

በነገው ዕለት በመንበረ ፓትርያሪኩ በሚያካሂዱት ከፍተኛ የተቃውሞ ትዕይንት ምእመኑ ከጎናቸው እንዲሰለፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል አቡነ ጢሞቴዎስ ደቀ መዛሙርቱን በፖሊቲከኝነት መወንጀል ጀምረዋል የተማሪዎች መማክርት የኮሌጁን አስተዳደር በሕግ ለመጠየቅ እየተዘጋጀ ነው ምእመናን ቤተ ክርስቲያን ከመሳለምና ገንዘብ ከመስጠት/ከመመጽወት ባሻገር ስለ ቤተ ክርስቲያናቸው ጉዳይ በመጠየቅ ቀጥተኛ ተሳታፊ መኾን እንደሚገባቸው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት አሳሰቡ፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ማሳሰቢያውን ያስተላለፉት፣ …

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን መዝጋት ታሪክን ማጥፋት/ማበላሸት ነው! የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ችግራችንን ይመልከት! ልጆቹን የማይጠይቅ አባት አለን? ሙስናንና ኑፋቄን የሚያደቅ ክንድ አለን! የምንማረው በምእመናን ብር ነው፡፡ ሌቦች ሆይ፣ እጃችኹ ይሰብሰብ! ጢሞቴዎስ ሆይ፣ አደራህን ጠብቅ፡፡ (፩ኛጢሞ. ፬÷፳) ችግራችንን የሚሰማንና መፍትሔ የሚሰጠን አባት ዐጣን! የቅ/ሲኖዶሱ አባላት ትኩረት ይስጡን! ሙስናን በቃል ሳይኾን በተግባር እንዋጋ! ተማሪዎች ሙስናን በመዋጋታቸው […]

ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም የጎንደር ከተማ የገዢዉ ፓርቲ ካድሬዎችን ታላቅ አሳፋሪ አፈና ጥሶ በመሄድ ድምጹ በታላቅ ጀግንነት አሳምቷል። የአንድነት ድህረ ገጽ ላይ የወጣ በኦዶዮ የታጀበ ዝርዝር ሸገባ እንደ እንደሚከተለዉ አቅርበናል። እዚህ ይጫኑ !

አንድ ቢሊዮን ገደማ ህዝብ ባለው ክፍለ ዓለም 54 አባል ሃገራትን ያቀፈውና ዘንድሮ 50 ኛ ዓመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የአፍሪቃ ኅብረት በየጊዜው በሚከሠቱ የአህጉሩ ችግሮች መፈተኑ አልቀረም ። የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ወይዘሮ እንኮሳዛና ድላማኒ

ክልሉ የፍትሕና ጸጥታ ዘርፍ እንዲሁም የፖሊስ ሓላፊዎች ለሁከት ፈጣሪዎቹ ወግነዋል

ደቀ መዛሙርቱ ለሦስተኛ ተከታታይ ቀን የኮሌጁን የምግብ ቤት አገልግሎት ተከልክለዋል የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ደቀ መዛሙርቱ ወደ ክረምት ዕረፍት ከመሄዳቸው በፊት የማጠቃለያ ፈተና እንዲወስዱና ተመራቂዎቹ እንዲሸኙ ጥረት እያደረገ ነው፤ በፓትርያሪኩ የመወሰን አቅም ላይ ጥርጣሬ የገባቸው የሚኒስቴሩ ሓላፊዎች ልዩ ጽ/ቤቱ ደቀ መዛሙርቱን በኀይል ከኮሌጁ ለማስወጣት ያቀረበውን የድጋፍ ጥያቄ ውድቅ ባደረጉበት አቋማቸው ጸንተዋል ፓትርያሪኩ በሚይዟቸው አቋሞች ረዳት ሊቀ ጳጳሱ …

የነገው አበባ ለምን ለፌደራል ፖሊስ ይሰጣል? ዳዊት ሰለሞን (ፍኖት ዘጋቢ) ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም አበባ የሰው ልጆች በአንድ ድምጽ «ፍቅራችንን ወክልልን» በማለት የመረጡት ይመስል የፍቅርን አደራ ተሸክሟል፡፡ከሶስተኛው አለም እስከ አንደኛው የሚገኙ የአዳም ልጆች «አበባን» የፍቅር ስጦታ በማድረግ ለሚወዱት ይቸሩታል፡፡የሚወዱት ሲሞትባቸውም ፍቅራቸውን ለሟቹ ለመግለጽ አስከሬኑ ላይ አበባ ያኖሩለታል፡፡ ወደ ደሴና ጎንደር እንምጣ፣ ነገ ከሌላው ጊዜ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም “ህገ መንግስት ተጥሷል !” ካልክ ድምጽህን በሰላማዊ ተቃውሞ አሰማ ! ይድረስ ትናንተም ሆነ ዛሬ ግፍ በነገሰባት ምድር፣ ኑሮን በመከራ ለምትገፋው ወገኔ ! ይድረስ መልካም አስተዳደር ጠፍቶ በደል ለተጫነብህ ፣ ፍትህ ርትዕ ተዛብቶ የአስተዳደር ሚዛኑ ኑሮህን ላጨለመው ወገኔ ! ይድረስ ከዲስኩር ባላለፈ “የእድገት ስላጣኔ መንገድ እየተጓዝክ ነው ” ለሚሉህ ፣ ይድረስ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም በደሴ አካባቢ ከሚገኙ ከተሞች(ከወረባቡና ሐይቅ)፣ በነገው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ለመገኘት ወደ ከተማይቱ ለመምጣት ትራንስፖርት ያስፈልጋቸው የነበሩ ዜጎች፣ በከተማው አስተዳደር ስውር ትዕዛዝ መሰረት፣ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ የትራንስፖርት መኪኖቹ ከአገልግሎት ውጪ እንዲሆኑ መታዘዛቸውን የየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ለሰልፉ አዘጋጆች በመደወል እየገለጹ ነው፡፡ ሁኔታው ያሳዘናቸው ሰዎች በቻሉት መንገድ ሁሉ ወደ ሰልፉ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” የሚል መሪ ቃል በማንገብ ዕሁድ በሚካሄደዉ ህዝባዊ የተቃዉሞ ሰልፍ ላይ ሁሉም ተሳታፊ የሚከተሉትን ተግባራት ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ 1. ሰልፉን ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማካሄድ፡፡ የተለያዩ ትንኮሳዎች ቢፈታተኑንም እንኳን ሰልፉ ስነ-ስርዓቱን በጠበቀ እና ጨዋነት በተሞላበት መልኩ ማካሄድ ይገባል፡፡ አንድ ጠጠር እንኳን ፍፁም መወርወር የለበትም፡፡ 2. የተመረጡ መፈክሮችን ብቻ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም የአገዛዙ ካድሬዎች ላለፉት በርካታ ሳምንታት የአንድነት ፓርቲ እያደረገ ያለዉን ሰላማዊና ሕዝባዊ ቅስቃሳ ከግቡ እንዳይደርስ ለማድረግ፣ በአለቆቻቸው ታዘው የተለያዩ የአፈና እንቅስቃሴዎችን ሲያደርጉ እንደነበረ በሰፊት ተዘግቧል። በርካታ ታሰረዋል፤ ወከባና እንግልትም ደርሶባቸዋል። ነገር ግን የአንድነት አባላትን ደጋፊዎች እንደዉም ሕዝቡ እግዚአብሄር የሰጣቸውን የዜግነት መብት ለማረጋገጥ ቀርተዉ የተነሱ ይመስላል። አፈናዉ የበለጠ እየጨመረ በመጣ ቁጥር የሕዝቡን […]

ሐምሌ 7 በጎንደርና በደሴ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ተሳተፉ!! ድምፃችሁንም በአደባባይ አሰሙ!! ————————————————————– ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ ————————————————————– ፓርቲያችን አንድነት ህጋዊና ሰላማዊ መንገድ የሚታገል ፓርቲ በመሆኑ የሚያደርጋቸውን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ኃላፊነት በተሞላበት ህጋዊ አግባብ ሲተገብር ቆይቷል፡፡ ፓርቲያችን “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት/Millions of voices for freedom” በሚል መሪ ቃል የጀመረውም ህዝባዊ ንቅናቄ የህዝባችንን መሰረታዊ ጥያቄዎችን ያነገበ […]

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም ነገ እሁድ ጠዋት ሐምሌ 7 ቀን 2005 ዓ.ም. በጎንደር እና ደሴ ከተሞች ለሚደረገው ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተፈቅዶ ከፖስተር መለጠፍ፣ በራሪ ወረቀት ከመበተን በተጨማሪ በድምፅ ማጉያ ሰልፉን ያዘጋጀው አንድነት ፓርቲ ቅስቀሳውን እያደረገ ይገኛል፡፡ ይንንም ተከትሎ በተመሳሳይ ጊዜ በደሴ ከተማ አራዳ ገበያ ህንፃ አንድነት ፓርቲ ተከራይቶ ያለውን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አከራዩ እንዲያስለቅቁ […]

በማዕከላይ አፍሪቃዊቱ ሬፓብሊክ ያማፅያን ቡድኖች የተሰባሰቡበት የየሰሌካ ህብረት የቀድሞውን ፕሬዚደንት ፍራንስዋ ቦዚዜን በመፈንቅለ መንግሥት አስወግዶ ሥልጣን ከያዘ ወዲህ ሀገሪቱ አሳሳቢ ሰብዓዊ ቀውስ ገጥሞዋታል።

በአምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት የሐሰት ዉንጀላ ለእስር የተዳረገዉ ታዋቂዉና ተወዳጁ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ዲያስፖራዉ በሀገር ዉስጥ እየተካሄደ ባለዉ ሠላማዊ ትግል ላይ በአካል ተገኝቶ እንዲሳተፍ መልዕክት አስተላለፈ፡፡ የፖለቲካና የህሊና እስረኞችን በአካል ለመጠየቅ ቃሊቲ ለተገኙ ጋዜጠኞች እና የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሕዝባዊ ንቅናቄ የግብር ሃይል አባላት አደራ ሲል ባስተላለፈዉ መልዕክቱ ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ቀጣይ በሚካሄዱ […]

ጎንደሮች በሰልፉ ለመገኘት የትኛውንም ዋጋ እንከፍላለን እያሉ ነው! ሐምሌ 5 ቀን 2005 ዓ.ም በጎንደር የአንድነት አመራሮች ፖሊስ ካሜራ እየነጠቀ ነዉ ! ‹‹እኛ ሰላማዊ ታጋዮች ነን። የያዝነው ጥያቄ እንጂ መሳሪያ አይደለም» አቶ ዘካሪያስ የማነአብ ፣ የአንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ ———————————————————– በ30/10/2005 በጎንደር ሰላማዊ ሰልፍ ለማከናወን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ያቀረበውን ጥያቄ የከተማው አስተዳደር ባቀረቡት ጥያቄ […]