የዩናይትድ ስቴይትስ የብድር ጣራ መነሳትና አለመነሳት የሰሞኑ የመገናኛ ብዙሃን ትኩረት ሆኖ ነው የሰነበተው። የፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ አስተዳደር በበጀት መጓደል የገጠሙትን እክሎች ሊያስተካክል፤ የመንግስቱን ወጭ በመቀነስ ላይ ባለበት ወቅት፤ አገሪቱ ተጨማሪ ብድር የምታገኝበትና፤ ከዚህ ቀደመ የቆዩ ብድሮቿን ለመክፈል እንድትችል፤ ተጨማሪ ብድር …

የዩናይትድ ስቴይትስ የብድር ጣራ በዴሞክራቶችና በሪፐብሊካኖች መካከል ያስነሳው ውዝግብ ቀጥሏል Read more »

በአፍሪቃ ቀንድ ግማሽ ሚሊዮን የሚደርሱ ሕፃናት ከተመጣጠነ ምግብ እጦት ጋር በተያያዘ ለማይቀር የሞት አደጋ ተጋልጠዋል፤ ሲል የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት UNICEF ሪፖርት አደረገ። ድርጅቱ፥ ሌሎች ተጨማሪ አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ ሕፃናትም ተመሳሳይ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ብሏል። አሁን በቅርቡ ከኢትዮጵያና …

በአፍሪካ ቀንድ ለምግብ ዕጥረት የተጋለጡ ከሚልዮን በላይ ህፃናት የሞት አደጋ እንዳዣበበባቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሳሰበ Read more »

በኢትዮጵያ በተከሰተው ድርቅ በእጅጉ የተጎዱት በተከታታይ ዓመታት ለድርቅ አደጋ የተጋለጡ የአርብቶ አደሩ አካባቢዎች መሆናቸው ተገለጠ። የአልሚ ምግብ ዕርዳታ የሚሹ ህፃናትና እናቶች ቁጥር እስከ 700 ሺህ ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል። ከአዲስ አበባ የተጠናቀረውን የዚህን ዘገባ ዝርዝር ቀጥሎ ያድምጡ፤

መሃል ከተማ የሚገኙ መናኸሪያዎች ወደ አዲስ አበባ መውጫዎች መዛዎራቸው ለከፍተኛ መንገላታትና ወጪ አጋልጦናል በማለት ተገልጋዮች አማረሩ። የከተማዋ ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ችግሩ ጊዜያዊ ነው ይላሉ። ከመሃል ከተማ ታክሲና ሚኒባስ ይዘው ለሚሄዱ ሰዎች ደብረዘይት ናዝሬት አዋሳ የመሳሰሉ ከተሞች ቅርብ ሁንው ቆይተዋል። …

መናኽሪያዎች ከመሃል አዲስ አበባ በመውጣታቸው ለተጨማሪ ወጪና እንግልት ተዳረግን ሲሉ ተገልጋዮች አማረሩ Read more »

ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን በሚል ይታወቅ የነበረውና ከኀዳር 20 ቀን 2003 ዓ.ም ጀምሮ ኢትዮ-ቴሌኮም እየተባለ መጠራት የጀመረው የመንግሥት የልማት ድርጅት የሠራተኞች ማኅበር ክሡን ያቀረበው ሰኔ 27 ቀን 2003 ዓ.ም ነበር፡፡ የክሥ መዝገቡ የቀረበለት በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ …

የኢትዮ-ቴሌኮም እና የሠራተኞቹ ውዝግብ Read more »

የአፍሪቃ ህብረት ከሁለት ሳምንትት በፊት ባካሄደው ጉባኤ አለም አቀፍ የወንጀል ችሎት በሙዐማር ጋዳፊ ላይ ያወጣውን የእስራት ማዘዣ እንደማይቀብልና ከችሎቱ ጋር እንደማይተባበር ማስታወቁ ይታወቃል። የሊብያ ችግር በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታም እቅድ አቅርቧል። ስለ ጉዳዩ እንዲያብራሩልን ዶክተር መሰረት ቸኮልንና ዶክተር አየለ በከሬን አነጋግረናል። …

የወንጀል ችሎት በጋዳፊ ላይ ያወጣውን የእስራት ማዘዣ የአፍሪቃ ህብረት አንቀበልም አለ Read more »

«ባህላችን የሁለንተናዊ ማንነታችን መሠረት ነውና እሱን ይዘን እንከኖቹን ነቅሰን ማሻሻልና ማጎትበት እንችላለን፤» የሚለውን መከራከሪያ የያዘ ተከራካሪ በአንድ ወገን «የለም ባህላችን፤ ይልቁንም ደግሞ የፖለቲካ ባህላችን መሠረታዊ ለውጥ ይሻል፤ ዛሬ ላሉን ችግሮችም የአንዳንዱ መነሻ ነውና ከሥር መሠረቱ መቀየር አለበት፤» የሚለውን የያዘው ደግሞ …

ክርክር፥ ባህላችን በፖለቲካችን ላይ ያለው አንድምታ Read more »

  የዛሬው «ኢትዮጵያ በጋዜጦች» ፕሮግራማችን – ኢትዮጵያ የ $398 ሚልዮን ዶላር የምግብ እርዳታ ያስፈልጋታል ተባለ -በኢትዮጵያ የጎርፍ መጥለቅለ ሊኖር እንደሚችል ተገለጸ -ኩፍኝ በኢትዮጵያና በኬንያ ሰውዎችን ገደለ -ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የአገር ውስጥ ጉዳይ ለግሽበት አስተውጽዖ ማድረጉን አመኑ -የኢትዮጵያ ወታደሮች አብየ መግባት …

ኢትዮጵያ $398 ሚልዮን ዶላር የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች Read more »

የደቡብ ሱዳን አስተዳድር ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት መንግስቱ ኃይለማርያም ዘመናዊ የመኖሪያ ቤት ሰርቷል በሚል የተሰራጩ ዘገባዎችን አስተባበለ። የደቡብ ሱዳን መንግስት ለቪኦኤ በሰጠው ቃል ዘገባዎቹን አስተባብሎ፤ እንዲህ መሰል የሃሰት ወሬዎችን የሚያሰራጩት በኢትዮጵያና በደቡብ ሱዳን በኩል ቅራኔ እንዲኖር የሚፈልጉ ሃይሎች ናቸው ብሏል። ቅዳሜለት …

ደቡብ ሱዳን ለመንግስቱ ኃይለማርያም ቤት ሰርታለች የሚሉ ዘገባዎችን አስተባበለች Read more »

የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት በ60 አመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ድርቅ ተመትተዋል፡፡ በዚህም መሰረት በኬንያ 3.5 ሚሊዮን ፥በኢትዮጵያ 4.5 ሚሊዮን እንዲሁም በሶማሊያ 2.9 ሚሊዮን ህዝብ ለዚሁ አደጋ ተጋልጧል፡፡ በአደጋው የተጋለጠውን ህዝብ ለመታደግ ከፍተኛ እርዳታ እንደሚያስፈልግ WFP ገልጿል። በአፍሪቃ ቀንድ በተከሰተው ድርቅ ለከፋ …

በደቡብና ምስራቅ ኢትዮጵያ ከተራቡ ሰዎች በተጨማሪ ሶማሊያዊያን ስደተኞች እርዳታ ይሻሉ Read more »

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በአሸባሪነት ተከሰው በእስር የሚገኙ ዜጎች ህገ-መንግስታዊ መብታቸው እንዲጠበቅ ጠየቀ። የጸረ ሽብርተኝነት አዋጁም ከአገሪቱ ህገ-መንግስት ጋር የሚጋጭ ነው አለ። አንድነት ይህን ያለው ዛሬ ባወጣው መግለጫ ነው። እንድ የመንግስት ባለስልጣን በበኩላቸው ክሱ ትርጉም የለሽ ነው ብለዋል። የአንድት ለዲሞክራሲና …

አንድነት ፓርቲ በአሸባሪነት የተከሰሱት ዜጎች ህገ-መንግስታዊ መብታቸው ይከበር አለ Read more »

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በአገሪቱ አንዳንድ አከባቢዎች የተከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም መንግስታቸው በራሱ አቅምና ከውጭ በሚገኝ እርዳታ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። የሁለት ሺህ አራት አም ባጀት ትላንት በፓርላማው ሲጸድቅ የተናገሩት አቶ መለስ በምክር ቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎችም ማብራርያ ሰጥተዋል። ለድርቁ ረድኤት የተጠየቀው …

ኢትዮጵያ ለድርቅ ከጠየቀቸው እርዳታ 25 ከመቶውን ብቻ እንዳገኘች ታወቀ Read more »

ሰኔ 23 ቀን ኢትዮጵያን በሚያዋስነው የፑንትላንድ  ድንበር በጋልቃዮ በኩል ሁለቱ ስዊድናዊ ጋዜጠኞች ከከኦጋዴን ብሄራዊ ነጻአውጭ ግንባር (ኦብነግ) ታጣቂዎችና ሌሎች አጋዦቻቸው ጋር ሲጓዙ ነበር የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች በደረሳቸው መረጃ መሰረት ተከታትለው ያገኟቸው። ወዲያውኑ ተኩስ ተከፈተ። የኢትዮጵያ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ በረከት …

ሁለት ስዊድናዊ ጋዜጠኞች በወያኔ የጸጥታ ሃይሎች ቆስለው ታሰሩ Read more »

የኢትዮጵያ መንግሥት በሽብር ሤራ ተሳትፈዋል ያላቸውን ሁለት ጋዜጠኞች ማሠሩን ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች ደኅንነት ተሟጋች ቡድን (ሲፒጄ) አስታወቀ። እርምጃው መታየት ያለበት መንግሥት ትችት የሚያቀርቡበትን የነፃውን ፕሬስ ጋዜጠኞች ለማፈንና ለማሠር የተጋነኑ ክሦችን እየተጠቀመ ካለበት የቆየ አሠራሩ ጋር ነው ሲልም ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል …

የሽብር ክስ በጋዜጠኞች ላይ ተመሠረተ Read more »

በሶማሊ ክልል የሚንቀሳቀሰው የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻአውጭ ግንባር (ኦብነግ) ሰኞለት ሁለቱን ሰራተኞች ለWFP ማስረከቡን ያስረከበው ሰኞለት ነበር። የአለም የምግብ ድርጅት በዛሬውለት ሁለቱ ታጋቾች በአዲስ አበባ ከቤተሰባቸው ጋር መቀላቀላቸውን ይፋ አድርጓል። ከስድስት ሳምንታት በፊት በሶማሊ ክልል አንድ የአለም የምግብ ድርጅት WFP ሰራተኛ …

ለ6 ሳምንታት በሶማሊ ክልል ታግተው የነበሩት የWFP ሰራተኞች ተለቀቁ Read more »

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ባለፈው ቅዳሜ አምስተኛውን ጠቅላላ ጉባዔውን ባካሄደበት ወቅት አገሪቱ እንድትለማ መሠረታዊ የመዋቅር ለውጥ እንዲደረግ ጠይቋል። በኢትዮጵያ የህግ የበላይነት የለም፣ ታላላቅ ባለሥልጣናት በሙስና ተዘፍቀዋል፣ በተከሰተው የኑሮ ውድነት ድሆች የባሰ ደኅይተዋል የሚሉ ትችቶች በጉባዔው ላይ ተደምጠዋል። መድረክ በቅዳሜው …

መድረክ መሠረታዊ ለውጥ ጠየቀ Read more »

ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት (አይኦኤም) ከትናንት በስተያ ባወጣው የፕሬስ መግለጫ በየመንና በሣዑዲ አረቢያ አዋሣኝ አካባቢዎች ላይ ከ1 ሺህ 900 በላይ ኢትዮጵያዊያን መንቀሣቀሻ አጥተው እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡ ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት ሰሞኑን ባካሄደው የመመለሱ ሥራ የመጀመሪያ በረራ ከመካከላቸው 115ቱ ሕፃናትና ታዳጊዎች እንዲሁም 34ቱ ሴቶች …

ዓለምአቀፉ የፍልሰት ድርጅት ኢትዮጵያዊያንን ከየመን እየመለሰ ነው Read more »

ሳምንታዊው «ኢትዮጵያ በጋዜጦች» ፕሮግራማችን ዛሬ የካተታቸው ርዕሶች – የኢትዮጵያ የምግብ ዋጋ መናር -ዝናብ በኢትዮጵያ እፎይታ ቢያስገኝም አደጋም ደቀነ -የኢትዮጵያ ሰላም ጠባቂዎች አብየ እንዲገቡ ይጠበቃል -ኢትዮጵያ ለሱዳንም የኤለክትሪክ መብራት ሀይል እንደምታቀርብ ታወቀ -መስፍን ኢንዳስትርያል አዲስ የመኪና መገጣጠምያ ተቛም አስመረቀ የሚሉት ናቸው። …

በኢትዮጵያ የምግብ ዋጋ ለብዚዎቹ የማይቀመስ ሆኗል Read more »

የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ስርጭቱን እንዲያስተካክልና የኢትዮጵያ መንግስትን የሚቃወሙ ድምጾችን እንዲመጥን ከኢህአዴግ አስተዳድር አቤቱታ ቀረበበት። የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮን የሚያስተዳድረው ቦርድ (Broadcasting Board of Governers) በኢትዮጵያ ባደረገው የስራ ጉብኝት ከኮሚውኒኬሽንስ ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምዖንና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ባደረገው ውይይት …

የአሜሪካ ድምጽ የስርጭቱን ይዞታ እስኪያሻሽል ወያኔ ትብብር አላደርግም አለ Read more »

በህክምና ሊረዳ የሚችል የዓይነ-ሥውርነትና የአካል ጉዳት በሽታዎች ህክምና የሚሰጥ የበጎ አድራጎት ተቋም ነው። መስማት ለተሳናቸው የሚሰጥ የህክምና አገልግሎትና በልጅነት ልምሻ ለአካል ጉዳት ለተዳረጉ ወገኖችም በሚሰጠው አገልግሎት ይታወቃል። «ግራር ቤት ተሃድሶ ማኅበር፤» ይባላል። ከ15 ዓመታት በፊት ባቋቋሙት በዚህ ተቋማቸው አማካኝነት፥ በመቶ …

ከዘንድሮው የSEED ተሸላሚዎች አንዱ፤ ዶ/ር ረዳ ተክለሃይማኖት የመልካም ምግባር አረዓያው ሃኪም Read more »

ገዥው የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ በውስጡ ሙስና እየበረታ መምጣቱን አመነ፡፡ በሙስና ላይ የሚያካሂደውን ውጊያ እንደሚያጠናክርም አስታወቀ፡፡ ባለሥልጣናት ጠበቅ ያለ ፍተሻና ክትትል እንደሚደረግባቸው የፓርቲው የሥነ-ሥርዓት ጉዳዮች ምክትል ሊቀመንበር ዉ ዩሊያንግ ዛሬ ገልፀዋል፡፡ ይህ የፓርቲው መግለጫ ከመውጣቱ ቀደም ብሎ ዜጎች በሙስና ውስጥ ተዘፍቀዋል …

የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲና ሙስና Read more »

የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ምክትል ዋና አዘጋጅ ውብሸት ታየ በኢትዮጵያ መንግስት ሃይሎች መታሰሩን የጋዜጠኛው ቤተሰቦችና የስራ ባልደረቦች አስታወቁ። ውብሸት ታየ እሁድለት በጸጥታ ሃይሎች ከመኖሪያ ቤቱ ከተወሰደ ወዲህ ወዳጅ ዘመድ እንዳይጠይቀው መደረጉን የዝግጅት ክፍላችን ተረድቷል። ጋዜጠኛው የታሰረው 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ መሆኑን …

የአውራምባ ታይምስ ጋዜጠኛ በአዲስ አበባ ታሰረ Read more »

ለሁለት ወራት ተስተጓጉሎ የቆየው  የ«ኢሳት፤» ማለትም የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴሌቪዥን ፕሮግራም ባለፈው ሳምንት ከጀመረ በኋላ እንደገና በማግሥቱ መቋረጡ ተገልጿል።   የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን በአምስተርዳም፥ ዋሺንግተን ዲ ሲ እና ለንደን እንዳሉት ከሚገልጻቸው ስቱዲዮዎቹ ሥርጭቱን ማስተላለፍ የጀመረው እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር ከሚያዝያ 2010ዓም …

ኢሳት ቻይናን ወነጀለ Read more »

የኢትዮጵያ ፓርላማ ትናንት ባካሄደው ስብሰባ አምስት ቡድኖችን ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ አልሸባብና አልቃይዳን ሀገሪቱ ላይ በሽብርተኝነት ከባድ ስጋት የደቀኑ ሲል ሰይሟል ። ድርጅቶቹ በተጠቀሰው መንገድ የተሰየሙት በሁለት ሽህ አንድ ዓመተ ምህረት በወጣው የፀረ ሽብርተኛ አዋጅ መነሻነት መሆኑን በፓርላማው የመንግሥት ተጠሪ …

የወያኔ ፓርላማ አምስት ድርጅቶችን በሽብርተኝነት ፈረጀ Read more »

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊና የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂላሪ ክሊንተን በኢትዮጵያ ያለውን የዲሞክራሲ ሁኔታ በተመለከተ የሚደረገው ውይይት እንደሌሎቹ ዘርፎች ሁሉ በሁለቱ ሀገሮች የምክክር ማዕቀፍ ውስጥ እንዲቀጥል መግባባታቸው ተገልጧል። በሌላ በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ትናንት አዲስ አበባ ላይ በአፍሪካ …

የሂላሪ ክሊንተን የአዲስ አበባ ቆይታ Read more »

በየመኑ ፕሬዝዳንት አሊ አብዱላ ሳልህ ታማኝ ኃይሎችና በተቃዋሚ ወገኖች መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት ተባብሶ ቀጥሏል። በመዲናይቱ ሰንዓ በዛሬው ዕለት በተካሄደ ውጊያም የተቃዋሚዎች ይዞታ የሆነ የቴሌቭዥን ጣቢያ መደርመሱ ተዘግዟል። ብሎም የሰንዓው ብጥብጥ ወደ ጎረቤት ከተሞችም እየተዛመተ መሆኑን ዘገባዎች እያመለከቱ ነው። ድንገቱ ቀድሞውንም …

በየመን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እጅግ ለከፋ ሰቆቃ እየተዳረጉ ነው Read more »

የኢትዮጵያ መንግሥት በተወሰኑ መሠረታዊ ሸቀጦች ላይ ጥሎት የነበረው የዋጋ ተመን ከዛሬ ጀምሮ መነሣቱን የንግድ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ አማከል ይማም በስልክ ለአሜሪካ ድምፅ ራድዮ እንደገለፁት ከዘይት ከስኳርና ከስንዴ በስተቀር በሌሎቹ ላይ የተጣለው የዋጋ ተመን ከዛሬ ጀምሮ ተነስቷል። ዘጋቢያችን …

ወያኔ በሸቀጦች ላይ ጥሎት የነበረውን ገደብ ከዘይት ስኳርና ስንዴ በቀር አነሳ Read more »

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማህበረ ቅዱሳን ሂሳቡን እንዲያስመረምርና «የስም ማጥፋት ዘመቻ፤» የተባለውን እንዲያቆም ጠየቀ። «ስም ማጥፋት፤» የተባለውን ያስተባበለው ማኅበር በበኩሉ የማህበሩ ሂሳብም መመርመሩን ብሏል። ዘጋብያችን መለስካቸው አምሃ የሁለቱንም ወግኖች ተወካዮችን አነጋግሮ ከአዲስ አበባ የላከው ዘገባ …

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና የማኅበረ ቅዱሳን ውዝግብ Read more »

ባለፈው ሳምንት ሀሙስ በሶማሊ ክልል የሚንቀሳቀሰው የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በገላልሼ ከተማ አካባቢ ባደረገው ጥቃት በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ላይ ጉዳት ማድረሱንና እስረኞችን ማስፈታቱን አስታውቆ ነበር። የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ አማጺያኑ ለጥቃት ሲዘጋጁ በአካባቢው የፖሊስ ሃይልና ሚሊሻ የደፈጣ ጥቃት ደርሶባቸው …

ኦብነግ ገላልሼ ከተማን ለቅቄ ወጣሁ አለ፣ ነዋሪዎች ቀድሞውንም አልተቆጣጠረም ብለዋል Read more »

ኢህአዲግ የቀድሞውን ወታደራዊ መንግስት አውርዶ የሥልጣኑን መንበር የተረከበበት ግንቦት 20 እነሆ ዛሬ 20 ዓመት ሞላው። ለተከታታይ ዓመታት ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት ዕድገት ማስመዝገቡን ያስታወቀበትን ጨምሮ «የኅዝቡን ህይወት ለማሻሻል ያስቻሉ በርካታ ውጥኖች አሳክቻለሁ፤» ሲል፤ በአንፃሩ በተቃዋሚው ጎራ ተሰልፈው በአገሪቱ የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት …

የወያኔ ሃያ ዓመታት የሥልጣን ዘመን በተቃዋሚ መሪዎች ዓይን ሲቃኝ Read more »

«መንግስት የገባውን ውል አፈረሰ፤» ይላል የፅሁፋቸው ርዕስ። የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው የኢትዮጵያ ተወላጆች በአገር ውስጥ «ሊሰማሩበት አይችሉም፤» መባሉ አነጋጋሪ የሆነበትን አንድ የሥራ መስክ ይመለከታል። ሙልጌታ አረጋዊ አረጋዊ ይባላሉ። ቀደም ሲል በዚህ በዩናይትድ ስቴትስ በጥብቅና ሞያ ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ …

ጥብቅና፥ የውጭ አገር ዜግነት ላላቸው የኢትዮጵያ ተወላጆች ከማይፈቀዱ የሥራ መስኮች አንዱ Read more »

በሶማሊ ክልል የሚንቀሳቀሰው የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በገላልሼና ባቢሌ ከተማ አካባቢ ባደረገው ጥቃት በኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ላይ ጉዳት ማድረሱንና እስረኞችን ማስፈታቱን አስታውቋል። በገላልሼ በሚገኝ እስር ቤት በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን ማስፈታቱን ኦብነግ ገልጾ፤ ከሳምንታት በፊት በኦጋዴን እርዳታ ያደርሱ የነበሩ …

በሶማሊ ክልል ኦብነግና ወያኔ ተጋጭተው ከ30 በላይ ተገደሉ Read more »

ማርክስት ሌኔንስት የትግራይ ሸማቂዎች በኢትዮጵያ ሥልጣን የያዙበት ሃያኛ ዓመት ነገ ሊከበር መስቀል አደባባይ በወዜማዉ ባዶና ጭር ያለ ነዉ። ጥቂት ሰራተኞች ብቻ ነገ ንግግር የሚደረግባቸዉ መድረኮችና የድምጽ ማጉያዎችን ማዘጋጀት ይዘዋል። በ1983 ዓም አምባገነኑ የደርግ መንግስት የተወገደበትንና መሪዉ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪያም ወደ …

ወያኔ ሥልጣን የያዘበትን 20ኛ ዓመት ቅዳሜ ግንቦት 20 ያከብራል Read more »

በአዲስ አበባ ከተማ የተከሰተው የስኳርና ዘይት እጥረት በተለይ በችርቻሮ ሱቆች አካባቢ በግልጽ ይታያል። በየቀበሌው የተቋቋሙት የሸማቾች ማህበራት ስኳርና ዘይት የመሳሰሉ ሸቀጦችን ከመንግስት በመረከብ ሲሸጡ ቆይተዋል፣ ሆኖም ይህም ችግሩ አልፈታም። እጥረቱ የተከሰተው ላለፉት ሁለት ወራት መሆኑንና የሚመቁሙ ቸርቻሪዎች አሰራሩ እነርሱን ያገለለ …

በአዲስ አበባ ከተማ የዘይትና ስኳር እጥረት እያነጋገረ ነው Read more »

ኢትዮጵያ የአለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባል ለመሆን በ1995 ዓ.ም. ማመልከቻ ካስገባች ወዲህ፤ የአለም መንግስታት የገበያ ጉዳያቸውን የሚፈቱበትን የጋራ ማህበር ለመቀላቀል በመጠባበቅ ትገኛለች። ይሄም የሆነው ለዘመናት የሀገር ውስጥ የኢኖኖሚ ተቋሞቿን በተለይ ኢንዱስትሪዎቿል ስታጥናክር የቆየችው ቻይና የWTO አባል በሆነች በሁለት አመት ጊዜ …

የመንግስት እጅ በሚበዛበት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የWTO አባል የመሆን እድሏ Read more »

ህንድ በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት አፍሪካ የልማት ግቦችዋን ታሳካ ዘንድ ለመርዳት አምስት ቢሊዮን ዶላር በብድር ለመስጠት ቃል ገባች ። ኢትዮጲያንና ጅቡቲን የሚያገናኝ አዲስ የባቡር መስመር ለመዘርጋትም ሶስት መቶ ሚሊዮን ዶላር አበድራለሁ ብላለች። ይህን የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞሞሐን ሲንግ  ይፋ ያደረጉት  ዛሬ …

የህንድ እና የአፍሪካ ሁለተኛ የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ Read more »

በኢትዮጵያ በደቡብና በደቡብ ምሥራቅ አካባቢዎች በተከሰተው ድርቅ ሣቢያ የተረጂው ቁጥር 2 ነጥብ 8 ሚሊየን መሆኑን፤ በመላ ሃገሪቱ የምግብ እርዳታ ፈላጊው 3 ነጥብ 2 ሚሊየን እንደሚደርስና የዓለም የምግብ ፕሮግራም የያዛቸውን ተደራቢ የድጋፍ አቅርቦቶችን ጨምሮ በዚህ ዓመት አጠቃላዩ ተረጂ 4 ነጥብ 3 …

የድርቅና የረሃብ ሁኔታ በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ኢትዮጵያ Read more »

የኢትዮጵያ መንግሥት ሜሪሌዎችን በሠላም ወደመጡበት እንዲመልስ አልያ በኃይል እንዲወጡ እንደሚደረግ የኬንያ መንግሥት ማሣወቁም በዚሁ allafrica.com ዌብሣይት ተጠቅሷል። ትዝታ በላቸው ያነጋገረቻቸው አንድ የኬንያ ፓርላማ አባል ግን የጎሣ አባላቱ በአካባቢው ድርቅና የግጦሽ መሬት መመናመን የተጎዱ መሆናቸውን በመጠቆም ጉዳዩ ዘላቂ መፍትሄ ይሻል ይላሉ። …

የኬንያ ፓርላማ አባል የግቤ ግድብ ግንባታ እንዲቆም ጠየቁ Read more »

የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር፥ ኦብነግ ባለፈዉ ሳምንት በኢትዮጵያ መንግስት ሰራዊትና ”ልዩ ፖሊስ” የሚባሉ ያላቸው የክልሉ ኃይሎች በመተባበር በጅምላ ፈጁዋቸዉ ያለዉን የ37 ሰዎች ስም ዝርዝር በትላንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። መግለጫዉ የሰለባዎቹን ጾታ የተገደሉበትን ቀንና ቦታም ለይቶ ይጠቅሳል። የኦብነግ የዉጭ ጉዳይ …

የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር ወያኔን በጅምላ ፍጅት ከሰሰ Read more »

የዓለም የምግብ ድርጅት በሶማሌ ክልል የሚሰጠውን ሰብዓዊ ዕርዳታ በተፈጠረው የደህንነት ሥጋት ሳቢያ ለጊዜው ማቆሙን አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ የድርጅቱ ሰብዓዊ ዕርዳታ መቆሙን በይፋ እንደማያውቅ አመለከቷል። ለዝርዝሩ ከአዲስ አበባ የተጠናቀረውን ዘገባ ያድምጡ፤

ብዙ ሙስሊማን በዩናይትድ ስቴትስ ላይ እንዲያመሩ ካደረጓቸው ምክንያቶች በቁልፍነት የሚጠቀሱት ሦስቱ፥ – የቡሽ አስተዳደር በኢራቅ ላይ ጦርነት ማወጅ፥– የጓንታናሞ ቤይ ኪዩባና አቡ-ግሬይብ እሥር ቤቶች አያያዝና ፖሊሲው፥ እንዲሁም– በፍልሥጤማውያንና እሥራኤል ግጭት ወደ እሥራኤል ያዘነበለ የሚሉት ፖሊሲ ናቸው። ፕሬዘዳንት ኦባማ የዛሬ ሁለት …

ፕሬዘዳንት Obama በመካከለኛው ምሥራቅና ሰሜን አፍሪቃ ሀገሮች ለውጦች ላይ ንግግር አድርጉ Read more »

የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ONLF) “የኢትዮጵያ ኃይሎች በምሥራቃዊ የአገሪቱ ክልል ውስጥ ያካሂዳሉ” ያለውን የግድያ ዘመቻ  የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዲመረምር ጠይቋል። ሸማቂዎቹ ባወጡት መግለጫ “ድርቅ ባጠቃው የኦጋዴን ክልል ባለፈው ዓርብ የኢትዮጵያ መንግሥት ወታደሮች ከዓለም ምግብ ፕሮግራም ሠራተኞች አንዱን ገድለው ሁለት …

የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጭ ግንባር እና ወያኔ ይወነጃጀላሉ Read more »

የሕዳሴ ግድብ ግንባታው እቅድ ድንገት ዱብ ያለው በሰሜን አፍሪካና መካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የተከሰተውን ዓይነት ሕዝባዊ አመፅ ኢትዮጵያም ውስጥ እንዳይከሰት ለመከላከል የተፈጠረ አጀንዳ ነው ሲሉ ተቃዋሚዎች ለሚያቀርቡት ትችት ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ለሚዲያ ምላሽ ሰጥተዋል።የግድቡ ግንባታ ጉዳይ ቀደም ብሎ የታቀደ …

የመንግሥቱ ሚዲያ፥ የሕዳሴ ግድብ እና የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ Read more »

በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ማክሰኞ ግንቦት 9 ቀን 2003 ዓ.ም ይፋ እንደተደረገው አአአ ለ2012 ዓ.ም ለዳይቨርሲቲ ቪዛ (ዲቪ ሎተሪ) አመልክተው ከነበሩ መካከል ዕድሉን አግኝታችኋል ተብለው ዝርዝራቸው ባለፈው ሣምንት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ዌብ ሣይት ላይ የወጣው በሙሉ ተሠርዟል፡፡ …

የዲቪ ውጤት ተሠረዘ Read more »

በአዲስ አበባ ከተማ ተሳፋሪዎችን የሚያመላልሱ (በልማድ ሚኒባስ በመባል የሚታወቁት) ታክሲዎች በተመደበላቸው መስመር ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው የታክሲ አሰራር ሰሞኑን ተግባራዊ ቢደረግም ከቅሬታዎች ነፃ አልሆነም። ሠሞኑን በከተማይቱ ታዬ የሚባለው የተሽከርካሪ እጥረት እያነጋገረ ባለበት፤ ዘጋቢዎቻችን ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች፥ ተሳፋሪውንና አስከርካሪዎችን በማነጋገርና እንዲሁም …

የአዲስ አበባ የታክሲ ቀጠና አሰራር በመዲናይቱ የመጓጓዣ እጥረት ፈጠረ Read more »

ኤርትራውያንና ሶማሊያንውያንን ጨምሮ የሚበዙት ኢትዮጵያውያን የሆኑባቸው 72 ስደተኞች በብጥብጥ በመታመስ ላይ ካለችው ሊቢያ በጀልባ ወደ ጣልያን ወደብ በማቅናት ላይ ሳሉ 61 ያሉቁበትን ዜና መዘገባችን ይታወሳል። በህይወት ተርፈው ከተነሱበት የሊቢያ ባህር ዳርቻ ለመመለስ ከበቁት አስራ አንዱ ሁለቱ መሞታቸው ተመልክቷል። እንዲህ ያለ …

ከ60 በላይ በሊቢያ የነበሩ ኢትዮጵያውያ ስደተኞች እልቂት Read more »

“በኢትዮጵያ ገዢው የሕዝባዊ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ያለፈውን ዓመት ግንቦት ምርጫ ያሸነፈው በማስፈራራት፣ በነፃ የመሰብሰብ ወይም በማኅበር የመደራጀት መብቶችን በመገደብ፣ ሰብዓዊ መብቶችንና የነፃውን ፕሬስ እንቅስቃሴዎች አብዝተው የሚገድቡ ሕጎች ተግባራዊ በሆኑበት፥ የሀገሪቱን የኃብት ምንጮችና ከውጭ የሚገኝ ዕርዳታንና የሥራ ዕድሎችን በስፋት ሕዝቡን …

ኢትዮጵያና ኤርትራ በአምነስቲ ኢንተርናሽናል ተከሰሱ Read more »

የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዛሬ ያጠናቀቁት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸው በአባይ ውኃ መጋራት ጉዳይ ለረጅም ጊዜ የቆየውን ጭቅጭቅ ለመፍታት በራሳቸው ቃል “አዲስ ሁኔታ ከፍቷል” ሲሉ አስታውቀዋል። በዩጋንዳና በኢትዮጵያ ያደረጉትን የሁለት ቀናት ጉብኝት ሲያጠናቅቁ የግብፁ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢሣም ሻራፍ የሙባረክ አስተዳደር የሚገለፅበት በግብፅና በጥቁር …

የግብፅ የተቀየረ አቋም Read more »

www.ethiomuslimglobal.et በሚል አድራሻ የተከፈተው ዌብሣይት በርካታ ዓላማዎች እንዳሉት ተገልጿል፡፡ የዌብሣይቱ ሥራአስኪያጅና የኦፐሬሽን ኃላፊ ያሲን ራጂ በተለይ ማንን መድረስ እንደሚያስቡ ሲናገሩ “ሙስሊሙ ኅብረተሰብ እንደማንኛቸውም ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን መብቱንና ግዴታውን አውቆ ለሃገሩ ልማት፣ መቻቻል፣ ታሪክ፣ ቱሪዝም፣ ኢንቨስትመንት፣ ቅርስ፣ ከመረጃ ምንጮች የተገኙ የሃገራችንን …

ኢትዮሙስሊምግሎባልዶትኢቲ Read more »