በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም(በተለይ ለዞን 9)በሥራ ላይ አለ የሚባለው በ1987 ዓ.ም. የወጣው ሕገ መንግሥት አንቀጽ 30ና 31 የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረ…

(ክፍል ፫)ጥገኝነትና አውሮፓ!ውዴ ሆይ! በስልኩ ውስጥ እዚህ አገር መረረኝ ልምጣ ማለትሽ ገርሞኛል። ወደ አውሮፓ መምጣት ስለተቻለ ብቻ አይመጣም። መምጣት ያ…

ላለፉት አራት ዓመታት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ቅዳሜ እና እሁድ የሄደ ሰው ወጣቷን ናርዶስን ሳያገኝ አይመለስም፡፡ ናርዶስ ገና የ20 ዓመት ወጣት እና በኪያሜድ የ

(ክፍል ፪)ናፍቆትእስክትመጪ ያልኩሽ ስትመጪ ከምትደናገሪ ቀድመሽ እንድትዘጋጂ ብዬ ነው፡፡አንቺብቻ ሳትሆኚ ማንም ለመሰደድ የሚቋምጥ ሁሉ እስኪሰደድ የስ…

(ክፍል፩)እነዚህ የግል ማስታወሻዎች ናቸው፡፡ለግለሰብ የተጻፉ፡፡ተወዳጅ ባይሆኑም እንኳን አንዳንድ የስደተኛ ታሪኮች አያጡም፡፡ከስደት ጅማሬየአንስቶ

በጌታቸው ሺፈራው በአሁኑ ወቅት የአገራችን ወጣት  ትኩረት የሚሰጠው ነገር እግር ኳስ ሆኗል፡፡  ወጣቱ ለእግር ኳስ ብቻ የሚሰጠውን ትኩረትም አንዳን

በናትናኤል ፈለቀ እና ኤዶም ካሣዬጎረቤት ሀገር ኬንያ እ.አ.አ በ1963 ዓ.ም ነበር ከእንግሊዝ ቀኝ አገዛዝ ነፃ የሆነችው፡፡ በቀጣዩ ዓመት ኬንያ ራስዋን የቻለ

በዳዊት ተ. ዓለሙ*ባለፈው ሳምንት በወጣው የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል የተቃዋሚ ፓርቲዎች የድርድር አቅም ዋና ዋና አላባዎች የተነሱ ሲሆን ተከታዩ እና የ

——————-በዋሲሁን አወቀ——————-አንድ፡- ኢሕአዴግ ሆይ የምትናገረውን የምትተገብር ድርጅት ያድርግህ!!!የፌደራሊዝም ነገርእነሆ ከጥቂት ወራት በኋላ…

እስርቤቶቻችንና ሕገ-መንግሥታዊ መብቶች———————በጌታቸው ሺፈራው———————የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትን እንዲጸድቅ በበላይነት የመሩት አቶ መለስና …

በዳዊት ተ. ዓለሙየፖለቲካ ፓርቲዎች የመደራደር አቅም (Bargaining power) ለዴሞክራሲያዊ ፖለቲካ ስርአት ግንባታም ሆነ በዴሞክራሲያዊ ስርዓቱ ላይ ተመስርቶ ለሚ

በበፍቃዱ ኃይሉወጣቷ ዓለምን የቀን አጋጣሚ ስድስት ኪሎ አካባቢ፣ በዕለተ እሁድ (መጋቢት 8/2005) አንቀዥቅዦ አመጣት፡፡ በዕለቱ የለበሰችው የአዘቦት ቀይ ቲ-

በዳዊት ተሾመኢትዮጵያ፣ ትግራይ እና ህውሓት ምንና ምን ናቸው?በሚል ርዕስ በበፍቃዱ ኃይሉ የቀረበው ጹሑፍ በአሁኑ ወቅት በዋናነት የኢትዮጵያ የውስጥ ፖለ

በበፍቃዱ ኃይሉ“An event has happened, upon which it is difficult to speak, and impossible to be silent.’ ~ Edmund Burke.ሴቶች!ሴቶች ፀጉራቸውን ያሳድጋሉ፡፡ ይህ ዓረፍተ ነገር በስህተት የተደ…

በሶሊያና ሽመልስሴት መሆን መታደል ነው ብዬ ብጀምር  የሚስቅብኝ አይጠፋም! ሴት የመሆን ጉዳቶች ላይ ተደጋጋሚ ነገር ሲነገር ሰምተናል፡፡ የቤት ውስጥ የ…

በማሕሌት ፋንታሁንስለ ቅድመ ምርመራ ስናወራ ሃሳቡን በጠንካራ ሁኔታ ተግባራዊ ያደረገው የደርግ መንግስት ሳይጠቀስ አያልፍም፡፡ ከዚያ በፌት በነበረው ጊ

በናትናኤል ፈለቀለምዕራባዊያኑ የመጨረሻ  ወር በሆነው ዲሴምበር ወር መጀመርያ በሀገረ አሜሪካ ኢትዮጵያዊውን ጦማሪ እና እስክንድርነጋን ለማሰብ የተ

በዘላለም ክብረትየሰው ልጅ ሐሳቡን ለሌላው መግለጽ መጀመሩ ሰዎች የጋራ ባሕርያትን ይዘው ወደ አዲስ ስልጣኔ፤ ወደ አዲስ ሕይወት እንዲወጣ አድርጎታል፡፡

በበፍቃዱ ኃይሉሰሞኑ ‹‹የሕገ-መንግሥቱ›› ይከበር የበይነመረብ ዘመቻ 2ኛ ዙር በአንቀጽ 29 (ሐሳብንና አመለካከትን የመያዝና የመግለጽ መብት) ይከበር ዙሪ

ለተከበሩ አቶ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፤ የኮሙኒኬሽን እና ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ለተከበሩ አቶ በረከት ስምኦን፤ በሚኒስትር ማዕረግ፣ የኮሚኒኬ

በሶልያና ሽመልስ እና በበፍቃዱ ኃይሉ‹‹ፍቅር ማወቅ እና አለማወቅ›› የሚባል ነገር አለ? ‹‹ፍቅር ማወቅ›› የሚባል ነገር ካለስ – ኢትዮጵያውያን ፍቅር

በበፍቃዱ ኃይሉይህ ጽሑፍ ባለፈው ወር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በብሔር ሰበብ በተነሳ ፀብ ላይ ተመስርተው በተከታታይ ድረገጾች ላይ የተጻፉ ጽሑ…

በሶልያና ሽመልስ እና በበፍቃዱ ኃይሉወቅቱ መጽሔቶች እንደአሸን የፈሉበት፣ ጋዜጦች ደግሞ ቁጥራቸው የተመናመነበት ነው፡፡ ብዙዎቹ [የአማርኛ] መጽሔቶች

በፍቅር ለይኩንThere are two things that can bring this planet closer together: love and football.–Iran coach Afshin Ghotbiይህ ለዚህ ጽሑፌ መግቢያ ይሆነኝ ዘንድ የመረጥኩትን ኃይለ ቃል በ1998ቱ…

በበፍቃዱ ኃይሉበ2004 የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ‹‹መጅሊስ ይቀየር›› ጥያቄ መቀስቀሱን ተከትሎ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ዩንቨርስቲዎች በአንዱ ውስጥ …

ትላንት እሁድ (ጥር 12/2005) የርዕዮት ዓለሙ ወዳጆች ልደቷን አስመልክተው እንድንጠይቃት በፌስቡክ ሁሉንም ሰው ጋብዘው ነበር፡፡ እኛም ሰብሰብ ብለን ለመሄድ

በበፍቃዱ ኃይሉየገና ማግስት በቅጡ ሳልዘጋጅ ከቤቴ በመውጣቴ ካሜራ እንደሚያስፈልገኝ የተረዳሁት 200 መቶ ኪሎ ሜትር ከተጓዝኩ በኋላ ነበር – አዋሽን ስንሻገ…

በመስከረም አበራዐፄው ስለትምህርትበሀገራችን ዘመናዊ ትምርት የተጀመረው በዐፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ቢሆንም ከመስፋፋቱ ጋር ስማቸው በታሪክ መዛግብ

–>ዋኤል ጎኔም የግብጽ ደኅንነት ሰዎች ደብድበው የገደሉትን ካሊድ ሰኢድ ለማሰብ ‹‹እኔም ካሌድ ሰኢድ ነኝ›› የተሰኘ የፌስቡክ ገጽ ከፍቶ ለግብጽ አብዮት ያበቃ ሰው ነው፡፡ የመጀመሪያውን የአደባባይ እንውጣ ጥሪ ያቀረበው ይኸው የፌስቡክ ገጽ ነው፡፡ ዋኤል አደባባይ የወጡበትን የመጀመሪያ ቀን (ጃንዋሪ 25) አንድ ዓመት ለማክበር (Revolution 2.0 የተባለ) መጽሐፍ አሳትሟል፡፡ የመጽሐፉ ገቢ በሙሉ በአብዮቱ ለተጎዱ ሰዎች መደጎሚያ እንደሚውልም ተነግሯል፡፡ አሁን እዚህ ልጽፍላችሁ ያሰብኩት ግን ዋኤል ገጹን እና የግል ማንነቱን አስመልክቶ ለሚቀርብለት ጥያቄ ይሰጥ የነበረውን መልስ ነው (መጽሐፉ ላይ እንዳሰፈረው)፤ ዋኤል ኢትዮጵያዊ ቢሆንና የከፈተው ገጽም ኢትዮጵያዊ ቢሆን ኖሮ… በሚል ምናባዊ ምሳሌ፡፡ ስለዚህ ጽሑፉ በዋኤል የተጻፈው በኢትዮጵያኛ ተተርጉሞ ነው ልትሉት ትችላላችሁ፡፡

ስምህ ማነው?
[1]ስሜ ሽብሬ ደሳለኝ ነው፤
[2]ስሜ ዩሱፍ አብደላ ነው፤
[3]ስሜ እስክንድር ነጋ ነው፤
[4]ስሜ ርዕዮት አለሙ ነው፤
[5]ስሜ አሕመዲን ጀበል ነው፤
[6]ስሜ አንዱአለም አራጌ ነው፤
[7]ስሜ በቀለ ገርባ ነው፤
[8]ስሜ ኦልባና ሌሊሳ ነው፤
[9]ስሜ መስፍን ነጋሽ ነው፤
[10]ስሜ አርጋው አሽኔ ነው፤
ስሜ…. ብዙ ነው፡፡
እኔ በጎዳና ላይ የተገደልኩ፣ ያለወንጀሌ የታሰርኩ፣ ያለሀጢያቴ የተገረፍኩ፣ መብቴን በፍርሐት የተነጠቅኩ፣ ከገዛ አገሬ የተሰደድኩ ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡
ዕድሜህ ስንት ነው?
ዕድሜዬ ይህን ያህል ነው አልልም፤ ነገር ግን ከተወለድኩ ጀምሮ ያለው ያው አምባገነን መሪ ነው፤… ሙስናውም ያው ነው፤…. ጭቆናው ያው ነው፤… እናም በአገሬ የገነነው የፖለቲካ ፓርቲ ‹‹ተስፋ የለም›› ይባላል፡፡
ከጠቀስካቸው ሰዎች ጋር ዝምድና አለህ?
እነዚህ ሰዎች የተኛውን ውስጤን ቀስቅሰውታል… ዕድሜ ለነርሱ አሁን ለውጥ ማምጣት እንደምችል ይሰማኛል፤… ታዲያ በራዕይ አልተዛመድንም ማለት ይቻላል?… አንድም ቀን አግኝቻቸው የማላውቃቸው እነዚህ ሰዎች ወንድሞቼ/እህቶቼ ናቸው፡፡
ይህንን የምታደርገው ለምንድን ነው?
ወገኖቼ ላይ የሚደርሰውን በደል ተመልክቼ ወደጥናት ክፍሌ ስገባ እምባዬን መግታት አልችልም፤… ፍርሐት የተጫናቸው ኢትዮጵያውያን ምን ያህል ውርደትን እንደሚታገሱ አየሁ… ከራሴ በመጀመር በፍርሐት የምሠራውን ስህተት ሁሉ ማረም ጀመርኩ፤ እናም ለዛ ነው ይህንን ገጽ የፈጠርኩት፡፡ ለተበደሉ ወገኖቼ ያለቀስኩት ለሞቱ ዘመዶቼ ካለቀስኩት በላይ ነው… በየዕለቱ ፎቷቸውን ስመለከት ድብታ ውስጥ እገባለሁ፤ ኢ-ፍትሐዊነትን እስከመጨረሻው ለመዋጋትም ለራሴ ቃል እገባለሁ፡፡
ማነው በገንዘብ የሚረዳህ?
ፈጣሪ ይመስገን፣ የገንዘብ ምንጮቼ ብዙ ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ንቃተ ሕሊናዬ ነው… ይህ ምንጬ በቀን አራት ሰዓተ ብቻ እንድተኛ እና ጠዋትም ፊቴን ከመታጠቤ በፊት የፌስቡክ ገጼን እንድከፍት ያስገድደኛል፡፡

ሁለተኛው ምንጬ መማሬ ነው፡፡ በመማሬ ደስተኛ ነኝ፤ ዕውቀቴን አገሬን ለማገልገል አውለዋለሁ፡፡
ሦስተኛው ምንጬ የልጆች አባት መሆኔ ነው፡፡ ሁሌም የሚጨንቀኝ ልጆቼ አንድ ቀን ‹‹አባዬ፤ ዜጎች ሲጨቆኑ እያየህ አቅምህ የሚፈቅደውን ለምን አላደረግክም?›› ብለው ይጠይቁኛል ብዬ ነው፡፡
የመጨረሻው ምንጬ የሕዝብ ፍቅር ነው፡፡ አይቶኝ የማያውቅ፤ አይቼው የማላውቀው እና በስም የማንተዋወቀው ሕዝብ ፍቅር… በየዕለቱ የአመሰግናለሁ ማስታወሻ ይደርሰኛል…. የተለያዩ ዲዛይኖች፣ ሎጎዎች፣ ቪዲዮዎች ይልኩልኛል… ገጹ ብዙ ሰዎች ጋር እንዲደርስ ያስተዋውቁልኛል፡፡
ስለዚህ ምንድን ነው የምትፈልገው?
ይህንን ገጽ የፈጠርኩት ራሴን ከአደጋ ለመጠበቅ ብቻ አይደለም.. ነገር ግን አገራችን መልሳ የኛው የሕዝቦቿ እንድትሆን ከመፈለግ በላይ ሌላ ዓላማ የለኝም… አንድ ቀን እንዲህ ይሆናል ብዬ አልማለሁ፡- እርስ በእርስ ዳግም እንዋደዳለን፤ ሁላችንም ኢ-ፍትሐዊነትን እንቃወማለን፤ ከመሐከላችን ማንኛውም ሰው ክፉ ነገር ቢያይ ራሱ ይፈታዋል… እናም የመንግሥት ቅጥረኛ አንድን ዜጋ በጥፊ ከመምታቱ በፊት አንድ ሺሕ ጊዜ ያስብበታል፡፡
አትፈራም?
በጣም እፈራለሁ እንጂ፤… ፍርሐት እኮ የሰው ልጅ ተፈጥሮ ነው… ለተጨቆኑ ዜጎች የሚቆረቆር እንደእኔ እና እናንተ ያለ ሰው ግን ካለ ፍርሐቴ ይከስማል… ዕጣፈንታችንንም የምንወስነው እኛው ራሳችን እንሆናለን… እንዲህ እያልን፡- ‹‹ማንም ያለዕድሜው አይሞትም፣ ማንም ያለወንጀሉ አይታሰርም፣ ማንም አገሩን ለቅቆ አይሰደድም…›› አንድ ዘመዴ በ25 ዓመቱ ሞተ… ቁም ነገር ካልሠራሁበት የኔ ዕድሜ መርዘሙስ ምን ዋጋ አለው?
ብዙ ሰዎች ይህንን ለማመን ይቸገራሉ፤ እውነቱን ለመናገር ቃሉ የወጣው ከልቤ ነው… አገሬን ከልቤ እወዳታለሁ እናም በተሻለ ሁኔታ የምንኖርባት አገር እንድትሆን እፈልጋለሁ፡፡ መፈንቅለ መንግሥት ወይም አብዮት የማቀጣጠል ዓላማ የለኝም… እራሴን እንደፖለቲካዊ መሪም አልቆጥርም… ዋሊያዎችን እና ሉሲዎችን የሚደግፍ፣ ካፌ ደጃፍ ላይ ቁጭ ብሎ ተቆራጭ እየበላ፣ ማኪያቶ እየጠጣ ጋዜጣ የሚያነብ ተራ ዜጋ ነኝ፡፡… የሚከፋኝ ብሔራዊ ቡድናችን በሰው አገር ሲሸነፍ ነው፡፡ … ቁምነገሩ በኢትዮጵያዊነቴ መኩራት እፈልጋለሁ፡፡… ማንም ሰው የዜግነት ክብሩን ተገፍፎ እንዲጨቆን አልፈልግም፡፡ ይኸው ነው ምኞቴ፡፡
—-
[1] – ሽብሬ ደሳለኝ፤ ምርጫ 97ን ተከትሎ በተነሳው ብጥብጥ የመንግሥት ጥይት ሰለባ የሆነች ወጣት ተማሪ፤ [1] – ዩሱፍ አብደላ፤ በተመሳሳይ ወቅት የተገደለ የኮተቤ መምህራን ኮሌጅ ተማሪ፤
[3] – እስክንድር ነጋ፤ በሽብርተኝነት ተከሶ የተፈረደበት ጋዜጠኛ፤
[4] – ርዕዮ ዓለሙ፤ መረጃ ለሽብርተኞች አቀብለሻል በሚል የተፈረደባት ጋዜጠኛ፤
[5] – አሕመዲን ጀበል፤ በሙስሊሞች የመጅሊስ ይቀየር ጉዳይ የታሰረ፣ ጋዜጠኛ እና ደራሲ፤
[6] – አንዱአለም አራጌ፤ ሽብር አሲረሃል በሚል የተፈረደበት የአንድነት ፓርቲ አባል፤
[7] – በቀለ ገርባ፤ ከኦነግ ጋር ግንኙነት አለህ በሚል የተፈረደበት የኦፌዴን ም/ሊቀመንበር፤
[8] – ኦልባና ሌሊሳ፤ ከኦነግ ጋር ግንኙነት አለህ በሚል 8 ዓመት የተፈረደበት የኦብኮ አባል፤
[9] – መስፍን ነጋሽ፤ በሽብርተኝነት አዋጅ/ክስ ምክንያት ከተሰደዱ የቀድሞዋ አዲስ ነገር ጋዜጠኞች አንዱ፤
[10] – አርጋው አሽኔ፤ የመረጃ ምንጩን እንዲሰጥ በመንግሥት ኃይሎች በግዴታ በመጠየቁ የተሰደደ ጋዜጠኛ፤

በዚህ ጦማር ላይ ከጻፍኩ ሰነበትኩ:: ነገር ግን ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁት የጠፋሁት መጻፍ እርም ብዬ ሳይሆን ዞን ዘጠኝ ላይ መጻፍ በመጀመሬ ነው:: ታዲያ ምና

በማሕሌት ፋንታሁንመቼም ተቃዋሚ ስል የትኛው ዓይነቱን ተቃውሞ ለማለት እንደፈለኩ ሳይገባችሁ የቀረ አይመስለኝም፡፡ በሃገራችን በአሁኑ ሰዓት የኢሕአዴ…

በመሐመድ ካሊድበአንድ የግል ጋዜጣ የዘንድውን አወዛጋቢ የመጅሊስ ምርጫ አስመልክቶ የተመረጡትን ሰዎች ፕሮፋይል እየተመለከትኩ ነበር፡፡ ከጎኔ የነበረ…

በበፍቃዱ ኃይሉሃይማኖት ከጊዜ ወደጊዜ ፖለቲካዊ አቅሙን እያጣ የሚሄድ እና በገለልተኛ አስተሳሰብ የሚተካ እንደሆነ ፖለቲከኞች ተስፋ ያደርጋሉ፡፡ ሆኖም …

በበፍቃዱ ኃይሉያጣናቸው ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ግን ቀስ በቀስ ስላጣናቸው አጠፋፋቸው እየቆየ ብቻ ነው የሚገባን፡፡ ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ኢሕአዴግ የመሪነቱን

በናትናኤል ፈለቀ ኅዳር 12 ቀን 2005 ዓ.ም በሥራ ጉዳይ ወደ ጋሞ ጎፋ ዞን ዋና ከተማ አርባ ምንጭ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ለሁለት ቀን ተኩል የሚበቃኝን  ሸክፌ ከመ

በማሕሌት ፋንታሁንአነጋገራችንን፣ አካሄዳችንን፣ አበላላችንን፣ አስተያየታችንን ባጠቃላይ የምናደርገውን ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ቀጥጠኛ አስተዋፅኦ…

በበፍቃዱ ኃይሉለውጥን በምናብ ይወዱታል እንጂ በተግባር አይዳፈሩትም – ሰዎች፡፡ የሥርዓት ለውጥ ሲሆን ደግሞ ፍርሐቱ ያይላል፡፡ የፖለቲካ ሥርዓት ለውጥ

በበፍቃዱ ኃይሉ‹‹ለውጥ የማይለወጥ ሕግ ነው፤›› አሮጌውን በአዲስ መተካት ያስፈልጋል፡፡ ችግሩ የቡድን ሥርዓት ለውጥን ማምጣት ነጠላ ለውጥ እንደማምጣ

በሶልያና ሽመልስሰሞኑን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን የማዳመጥ ፍቃደኝነት ካሳያችሁ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ከሕገ -መንግሥቱ መጽደቅ ጋር ተያይዞ ለአንድ

ጉዳዩ፡- ሕገ መንግሥቱ በመንግሥት እንዲከበር ስለመጠየቅየተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 74 ላይ የጠቅላይ ሚኒስትርን ሥልጣን እና ተግ

ዞን 9 ኢ-መደበኛ የጦማርያን እና አራማጆች ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ማኅበረሰባዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ የተለየ እና ወገናዊ ያልሆነ ተረክ ለመፍጠር እየ

በፍቃዱ ኃይሉየቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከማንኛውም የሕዝብ ወገን (ከወጣቶች፣ ከሴቶች፣ ከነጋዴዎች…) ጋር ሲወያዩ/ሲያወሩም ሆነ ሲያገኙ ብቻ