ጦርነቱ እንደቀጠለ ነው፡፡ ጦር ሜዳው ሕሊና፣ ጦረኞቹ አማኞች እና ኢ-አማኒዎች ናቸው፡፡ በኔ ጦማር ኢ-አማኒዎች ምክንያተኞች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ለዚህ

በክፍል አንድ ጽሁፌ የፈጣሪ ሕልውናን በተመለከተ መከራከር እና የግል አቋም መያዝ እንጂ መደምደሚያ ላይ መድረስ እንደማይቻልና በሳይንሳዊ ሙግት የፈጣሪን ሕልውና (የቅዱሳን መጽሃፍትን ፍፅምና) ማረጋገጥ እንደማይቻል በጥቂት ነጥቦች መግለፄ ይታወሳል፡፡ ዛሬ ደግሞ ቃል በገባሁት መሰረት ጥቂት ስለዝግመተ ለውጥ እና ኢ-አማኒነት ለመነጋገር …

የሁለት እምነቶች ጦርነት… [ወግ አጥባቂዎች እንዲያነቡት የማይመከር – ክፍል ሁለት] Read more »

ዓለማውያን በምክንያት ሲሟገቱ ኢትዮጵያውያን ግን ገና ‹‹የዘራፍ›› ዘመን ላይ ነን፡፡ ይህንን ለመናገር ያደፋፈረኝ በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ላይ ትችት መሰንዘር – በሃገራችን – ቡጢ የሚያስቀምስ ሃጢያት መሆኑን ስለማውቅ ነው፡፡ እኔ ኢ-አማኒ (atheist) ነኝ፡፡ በርግጥ እንደ ብዙሐኑ ሁሉ እኔም ቤተሰቦቼ በውልደት ያወረሱኝ አምልኮታዊ …

የሁለት እምነቶች ጦርነት… [ወግ አጥባቂዎች እንዲያነቡት የማይመከር] Read more »

ቲፎዞነት የጋርዮሽ ስርዓትን ይመስለኛል፡፡ ሰዎች በቡድን ሆነው አንድን ነገር ብቻ በፍጹም ልቦና ለመደገፍ የመቁርባቸው ነገር – ካሰቡት ያስቃል፡፡ ሰዉ ሁሉ በየፊናው የሚደግፈው የእግር ኳስ ቡድን፣ የፖለቲካ ቡድን፣ የሃይማኖት ቡድን፣ የፆታ ቡድን ራሱ ሳይቀር ያበጃል፡፡ማንቸስተር ዩናይትድ (ብልጫ አወዛጋቢ ቢሆንም) በጨዋታ ብልጫ …

ለመደገፍ መደገፍ፤ ለመቃወም መቃወም Read more »

የብሔር ፖለቲካ በጣም ስስ (sensitive) ነው፡፡ በቀላሉ ተቆስቁሶ ብዙ ሊጓዝ ይችላል፡፡ ኢትዮጵያ በኢሕአዴግ ዘመን፣ በብሔር ፌዴራሊዝም ከተከፋፈለች ወዲህ እንኳን የብሔር ፍላጎቶችና ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ አላገኙም፡፡ የኦሮሞ ብሔረሰብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ ከ34 በመቶ በላይ ድርሻ አለው፡፡ (2007 National Census) ሆኖም የኦሮሞ …

በዻሳ ወይስ badhaasaa? Read more »

ደርግ አንቀጥቅጦ በመግዛት አቻ የለውም፡፡ የሰራዊቱ ግዝፈት እንኳን ተራ ሽፍቶች የተደራጀ ጦር እንኳን የሚደመስሰው አይመስልም ነበር፡፡ የሰራዊት ግዝፈት ለአንድ ስርዓት ዋስትና ሊሆን እንደማይችል የተረጋገጠው በደርግ ውድቀት ነው፡፡ ለደርግ መውደቅ የራሱ የሰራዊቱ አስተዋፅዖ ቢኖርበትም እምነት አጉዳዩ የደህንነት ቢሮ ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡ …

እንኳን ኢሕአዴግ ደርግም ወድቋል Read more »

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምናምን ማለት እየደበረኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ለ20 ዓመታት ሲገዙ የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ የሁሉም ነገር ፈጣሪና ፈላጭ ቆራጭ ናቸው፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ከተባለ እኛንም ስለሚወክል፤ የመለስ ማለትን መርጫለሁ፡፡ “Power corrupts; absolute power corrupts absolutely” (ስልጣን …

የመለስ ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ አበሳ ባሳለፍነው 20 ዓመት Read more »

አምባገነን መንግስታት ከአንድ ባሕር ይቀዳሉ፤ በርካታ የሚመሳሰሉባቸው ባሕርያት አሉዋቸው፡፡ በዚህች መዳፍ በምታክል ገጽ እና በእኔ ቁንፅል እውቀት ሁሉንም ዘርዝሮ መጨረስ ይከብዳል፡፡ ለነገሩ የአምባገነን መሪዎችን የጋራ ባሕርያት እነሱ ራሳቸው በቅጡ አያውቁትም፡፡ ነገር ግን በተለይ ጎልተው የሚለዩባቸውን ባሕርያቶች አንድ፣ ሁለት እያልን እስከአምስት …

የአምባገነን መንግስታት ባሕርያት እና የመለስ እውነታዎች Read more »

በአገራችን ሰው ተመርቆ ሲያበቃ ዝም ማለት የለበትም – ‹‹ከአሜን ይቀራል!›› ይባላል፡፡ አሜን በፀጋ መቀበል፣ ይሁንልኝ፣ ይደረግልኝ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ የዓለማችን ዕውቅ ደራሲዎች ‹አዎንታዊ አስተሳሰብ› ወይም ‹ተስፈኝነት› (optimism) የሚሉት ዓይነት እሳቤ ነው፡፡ ሰሞኑን ‹ተኣምራዊው ኃይል› በሚል የተተረጎመውን የርሆንዳ ባይርኔን መጽሃፍ እያነበብኩ …

ከአሜን ወዲህና ከአሜን ወዲያ ማዶ Read more »

Gene Sharp የአረቡን ዓለም አብዮት አቀጣጥሏል የሚባልለትን From DICTATORSHIP to DEMOCRACY: a Conceptual Framework for Liberation የተሰኘ ጥናት ጸሃፊ ናቸው፡፡ ጥናቱ የአምባገነኖችን ዓይነት ሲዘረዝር ሚሊቴሪ አምባነገን፣ ከአባት ወደልጅ የሚተላለፍ የንግስና ሥርዓት፣ አሃዳዊ የፖለቲካ ፓርቲ የሚመራው እና የውጭ ወራሪዎች ብሎ ይመድባቸዋል፡፡ …

"ድር ቢያብር" ለአምባገነኖች ምናቸው ነው? Read more »

አንዳንድ ደፋሮች ‹‹ኢትዮጵያውያን ምቀኞች ናቸው›› ይሉና አንድ ተረት ይተርታሉ፡፡ እግዚአብሄር አንዱን ኢትዮጵያዊ ‹‹የፈለግከውን ጠይቀኝ እና አደርግልሃለሁ፤ ነገር ግን ላንተ የማደርገውን ነገር በእጥፉ ለጎረቤትህ አደርግለታለሁ›› ብሎ ሲለው ፣ ሰውየው በብርሃን ፍጥነት ‹‹እንግዲያውስ አንድ ዓይኔን አጥፋልኝ›› አለው ይባላል፡፡ የአባይ ግድብ እና የኢትዮጵያውያን …

የአባይ ግድብ፣ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ የባሕር በር እና የወር ደሞዝ Read more »

‹አዳሪ› የሚለውን ቃል የተዋስኩት ከአበባው መላኩ ጣፋጭ የግጥም ስብስብ ውስጥ ነው፡፡ ከግጥሞቹ ስንኞች ጥቂት ቆንጥሬ ጀባ ልበላችሁና ወደጽሁፌ ልንደርደር፡፡ ‹‹… ሴትነቴን ወደው፣ እኔነቴን ንቀው፣ በፍቅሬ ተማርከው ገላዬ ስር ወድቀው፣ ‹እን’ደር› ይሉኛል በስሜት ታውረው፣ እነሱ ቀድመውኝ በወንድነት አድረው፡፡…›› ጽሁፉ ወንደኛና ሴተኛ …

የሚከፈላቸውና የማይከፈላቸው ‹አዳሪዎች› Read more »

ኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ዕርስ በዕርስ ተከባብረው እና ተሳስበው የሚኖሩባት ሃገር ነች፡፡ የኢትዮጵያውያንን ማሕበራዊ ጋርዮሽ የሃይማኖት ልዩነታቸው አላወከውም፡፡ በዚህ ስሌት የሚከተለው የእኔ እምነትም Aክባሪ እንደማያጣ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ በእምነትና በሃይማኖት መካከል የተሰመረ መስመር መኖሩን በእርግጠኝነት መናገር አልችልም፡፡ ሃይማኖት ያለእምነት ምንም ነውና፡፡ ስለዚህ አንድ …

ፅድቅና ኩነኔ Read more »

እንዲያው ለመንደርደር ያህል ‹‹ከለማኝና ከቀማኛ የቱ ይሻላል?›› ተብላችሁ ብትጠየቁ መልሳችሁ ምን ይሆናል? ነገሩ ከሁለት መጥፎ ነገሮች የተሻለ መጥፎ መምረጥ ነው፡፡ (የተሻለ መጥፎ ስንል ጉዳቱ ያልከፋ እንደማለት ነው፡፡) ስገምት፥ ብዙዎቻችሁ ለማኝ የምትመርጡ ይመስለኛል፤ ግን ለማኝ ከቀማኛ በምን ይሻላል? ሁለቱም የሰው ገንዘብ …

ከሠራተኛ፣ ለማኝና ቀማኛ ማነው በላተኛ? Read more »

የእስልምና እምነት ተከታይ አይደለሁም፤ ለነገሩ የክርስትና እምነት ተከታይም አይደለሁም፡፡ ነገር ግን ዛሬ ሙስሊም ሆኜ ሳስበው ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት›› የሚለው ቃል ሳስበው ከፋኝ፡፡ ኢስላም እና ክርስቲያን ተጣጥመው በአንድ ጣሪያ ስር የሚያድሩባት እየተባለች የምትሞገሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ነች›› የሚል …

ኢትዮጵያ የኢስላምም የክርስቲያንም ደሴት ናት Read more »

አማርኛ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ የሚል ማዕረግ ባይኖረውም፣ የፌዴራል መንግስት የስራ ቋንቋ ነው፡፡ ልክ ከ፹ በላይ እንደሆኑት ቋንቋዎቻችን ሁሉ ኢትዮጵዊነት በአማርኛ፣ አማርኛም በኢትዮጵያዊነት ይገለፃሉ፡፡ ኢትዮጵያ ደግሞ በሃይማኖት መቻቻል አንቱ የተሰኘች ሃገር ናት – ‘ተብሏል፣ ብለናል፣ አስብለናል፡፡’ ታዲያ አማርኛስ ምን ያህል የሃይማኖታዊ …

አማርኛ ሃይማኖቱ ምንድን ነው? Read more »

በበፍቃዱ ኃይሉ – “እዚህ ግቢ የሚሸጥ ዕንጀራ አለ” የሚል ፅሁፍ አንድ ግቢ በር ላይ ተፅፎ ባላይ ኖሮ ይህንን ፅሁፍ ለመፃፍ አልነሳሳም ነበር፡፡ ማስታወቂያውን አንብቤ ስጨርስ የሆነ ነገር እንደጎደለው ተሰምቶኝ ደግሜ አስተዋልኩት፡፡ እርግጥ ነው ዕንጀራ የሚለው ቃል ውስጥ ያለችው “ዕ” ለቃሉ …

አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ? Read more »

All you heard about Ethiopia is not true ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ CBC News የተሰኘው የካናዳ መገናኛ ብዙሐን በድረ ዓምባው ‹‹ለጋሽ ሃገራት በኢትዮጵያ ላይ ጫና እንዲያደርጉ›› Human Rights Watch የተሰኘው የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች መጠየቁን የሚያመለክት ዜና ይዞ ወጥቶ ነበር፡፡ በዘገባው ላይ …

5 Myths of Ethiopia Read more »