የምርጫ ቦርድ ምክትል ሃላፊ አቶ አዲሱ ገብረግዚአብሄር በፋና ራዲዮ እንዲሁም ሃላፊው ፕሮፌሰር መርጋ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ መኢአድ እና አንድነት ችግር እንዳለባቸው በመገልጽ በስድስት ቀናት ዉስጥ ፓርቲዎቹ “ችግሮቻቸውን” ካልፈቱ ሕጋዊ እርምጃ ይወሰደባቸዋል ሲል አስጠንቅቀዋል። ምርጫ ቦርድ የገዢው ፓርቲ አገልጋይ እንደሆነ ይነገርለታል። የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች በሕጉ መሰረት የሚንቀሳቀሱ ሳይሆን የፖለቲካ ዉሳኔ የሚያስፈጸሙ እንደሆኑ በሚያደርጓቸው ኢሕገ መንግስታዊ እንቅስቃሴዎች […]

አንድነት ፓርቲ የኢህኣዴግን ምንነት ላላመኑ ወገኖች ለማጋለጥ በትጋትና በስሌት ሲሰራ ቆይቷል፡፡እየሰራም ነዉ፤እዚህ ደርሷል፡፡ “የሆደ ሰፊዉን ምርጫ ቦርድ” ሆድ በገሃድ አጋልጧል፡፡በነአሞራዉና ወዲ ቐሺ(በተጋሩ ሁሉ) ትግልና ሞት የሚቀልዱትን በህዝብ ፊት ወጥተዉ ዛሬም እንዲዋሹና ለኢትዮጵያችን የፖለቲካ ታሪክ እነማን ምን እንደሆኑ አንድነት ፓርቲ የበኩሉን ሚና ተጫዉቷል፡፡ ለኔ ከባድመ ዉሳኔና ልህዝቡ በወቅቱ ከተነገረዉ ጋር ይመሳሰላል፤ይጠጋጋል፡፡ ኢህኣዴግ ምርጫዉን እንደማይፈልገዉ፤ከፈለገዉም ለተለመደዉ ቀልዱ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡ በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡ […]

ምርጫ ቦርድ ማንም ይዘዘው ማንም ወይም በግል ተነሳሽነት እያደረገ ያለው ነገር የኢትዮጵያን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከምን ጊዜውም በለይ ወደኋላ ለመመለስ እንደሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊረዳው ይገባል፡፡ ምርጫ ቦርድ ምርጫ እንዲያሰተዳድር በተሰጠው ኃላፊነት የፓርቲዎች አስተዳደሪ ለመሆን እየቃጣው ያለ ተቋም ነው፡፡ ስናከብረው ለመከበር ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ለዚህ ተቋም መጠናክር የበኩላችንን መወጣት አለብን ብለን የተነሳን ፓርቲዎችን ጭምር እየገፉ አለቆቹን […]

* የኮንትራት ሰራተኛዋ አይነ ብርሃኗን ማጣትና የስም የለሿ ሟች እህት መጨረሻ ! * ሰሚ እስኪገኝ እንጮሃለን ! ታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓም ሰኞ በማለዳው ያገኘኋቸው ሁለት መረጃዎች የወጡት በሁለቱ አንጋፋ የሳውዲ ጋዜጦች በአረብ ኒውስ Arab News እና በሳውዲ ጋዜት Saudi Gazette ነው። በአንዱን አይቸ ቢከፋኝ ፣ መፍትሔ ላይገኝ ይህን መርዶ ከንፈር ለማመስመጠጥ ብቻ መረጃ ብየ […]

እንደምታውቁት እሁድ እለት መርህ ይከበር ከሚሉት የወያኔ አፍራሽ ቡድን እኔንም ጠርቶኝ ባለማወቄ በቦታው ተገኝቼ ነበር እኔም በቦታው የተገኘሁት ሲጠሩንኝ የሆነ የእርቅ ኮሚቴ አቋቁመናልና የቡድኑ የኮሚቴ አባል እንድትሆን ነው ብለውኝ ነበር። መቼም እርቅን የሚጠላ የለምና ደስብሎኝ ነበር ነገሩ ግን የእርቅ ኮሚቴ ሳይሆን አንድነት ፓርቲን ለማፍረስ እንደሆነ ነው የገባኝ፤ ሰዎቹ እኛ የምንፍልገው ፓርቲው ፈርሶ ሌላ ፓርቲ ለማቁዋቁዋም […]

የሕወሃቱ ምርጫ ቦርድ፣ አንድነት ፓርቲ እንደገና ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራ ማዘዙን የሚጠቁሙ ፍንጮች ደርሰዉኛል። የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ባላበት፣ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ፣ ምርጫ ቦርድ በወቅቱ እንዲሻሻል የጠየቀው ደንብ ተሻሽሎ የኮረም ቁጥር ማስገባቱ ማለት ነው) ፣ ብሄራዊ ምክር ቤቱ መርጦት የነበረዉን አዲስ አመራር እንደገና አጽድቆ ተለያይቶ ነበር። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ፣ አይ ምርጫ እንደገና በሚስጠር መካሄድ አለበት በሚል […]

በአሁኑ ወቅት በም እራባውያን የተያዘው ድርድር እንደተጠበቀ ሆኖ ስልጣን ክፍፍሉም የምርጫ አዘቦትን ተንተርሶ መካሄዱንም አማክሎ ከውጪ ወደውም ይግቡ አሊያም ነጮቹ አሰልጥነው ይላኳቸው የሆነ ይሁን ባቻ ተቃዋሚዎች ህዝባዊ አጀንዳ የላቸውም ማለት ጉንጭ አልፋ ክርክር ማንሳት ዘመን ያለፈበት ከመሆኑም በላይ የነቃ ሕዝብ እና እልሁን በምርጫ ካርድ ለማሳየት ያደፈጠ ህዝብ መሃል ሆኖ ለመንጠራራት መሞከር ነገን ደብቁኝ ያመጣል:: ምርጫዎች […]

* የኮንትራት ሰራተኛዋ አይነ ብርሃኗን ማጣትና የስም የለሿ ሟች እህት መጨረሻ ! * ሰሚ እስኪገኝ እንጮሃለን ! ታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓም ሰኞ በማለዳው ያገኘኋቸው ሁለት መረጃዎች የወጡት በሁለቱ አንጋፋ የሳውዲ ጋዜጦች በአረብ ኒውስ Arab News እና በሳውዲ ጋዜት Saudi Gazette ነው ። በአንዱን አይቸ ቢከፋኝ ፣ መፍትሔ ላይገኝ ይህን መርዶ ከንፈር ለማመስመጠጥ ብቻ መረጃ […]

የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ፣ አንድነት እና መኢአድ በምርጫ እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ለፋና ራዲዮ ገለጹ። የአንድነት አመራሮች ወደ ምርጫ ቦርድ ሄደው የምርጫ ቦርድን ዉሳኔ በጠየቁ ጊዜ ቦርዱ ነገ ማክሰኞ እንደሚሰበሰብና ቦርዱ እንደሚወስን ቢነገራቸውም፣ ቦርዱ ሳይሰበሰብ ምክትል ሃላፊው፣ ቀደመው በራዲዮ፣ የመኢአድ እና የአንድነት ፓርቲ እንደይሳተፉ መግለጻቸው፣ ከወዲሁ በሕወሃት ማእከላዊ ኮሚቴ የተወሰነና ተግባራዊ የሚሆነው ይሄ ዉሳኔ ይሆናል በሚል እንደሆነ […]

የቴዲ አፍሮ ዝግጅት በፋራንክፈርት ሲደረግ በቦታው ተገኝቼ ነበር ። ብዙ ጊዜ ዘፋኝ ሲመጣ አልገኝም ። ዘንድሮ ግን ወያኔ በእሱ ላይ ያደረገውን ተንኮል መቃወም የሚቻለው በዝግጅቱ በመገኘት በመሆኑ ሰብሰብ ብለን ተገኝተን ነበር። ሰልፉ ሳይጠነክር ቀደም ብለን ለመግባት በጊዜ ነበር የደረስነው። ሰዓቱን ጠብቀን ከፍለን ገባንና ጥግ ላይ ወንበር ፈልገን መጠበቅ ጀመርን ። እሱ ወደ መድረክ እስከሚወጣ በልዩ […]

በርካታ ወጣቶች በፌደራል ፖሊስና በደህነት ሀይሎች በመታሰር ላይ ይገኛሉ! በደብረማርቆስ ስልጠና ላይ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በመንግስት ላይ ጥያቄ ማንሳታቸውን ተከትሎ እየታሰሩ እንደሚገኙ የፍኖተ-ነፃነት ምንጮች አስታወቁ፡፡ ተማሪዎቹ በመንግስት በኩል የሚሰጠውን ስልጠና ማውገዛቸውን እና በመንግስት በኩልም ቤተሰቦቻቸው ኢህአዴግን እንዲመርጡ እንዲያግባቡ መደረጋቸውን የገለፁት ምንጮች ተማሪዎቹ ይህን በመቃወም የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት ላይ የነበሩ ቢሆንም በፖሊስ […]

ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ባደረገው ስብሰባ ለምርጫው የገንዘብ ክፍፍል ቀመር መሰረት ዉይይት አድርጓል። ምርጫ ቦርድ ባቀረበው የገንዘብ ክፍፍል ቀመር መሰረት 10 በመቶ ለሴቶች፣ 10 በመቶ ለሁሉም ፓርቲዎች እኩል፣ 25 በመቶ ፓርቲዎች በሚያቀርቡት እጩ፣ 55 በፓርላማና በክልል ምክር ቤት ባላቸው መቀመጫ እንደሚያከፋፍል በማሳወቅ ነበር ስብሰባው የተጀመረው። ምጫ ቦርድ ባቀረበው ቀምር ላይ ሐሳብ እንዲሰጡ የፖለቲካ […]

(አቶ እያስፔድ ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚና የወጣቶች ክፍል ሃላፊ ናቸው። በቅርቡም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት/ባንክ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ተባረዋል። በነገረ ኢትዮጵያ ብዙ ጊዜ ጽሁፎችን የሚያቀርቡ ወጣት ፖለቲካኛ ናቸው። በጋራ ህዝቡን ማታገል እንደሚገባ በመገልጽ በተለትም ለሰማያዊና ለአንድነት ፓርቲ ጥሩ ያቀረቡበት ጽሁፍን ያንብቡ) ለውጡ ይመጣል! ጥያቄው ግን ተዘጋጅተናል ወይ? ————————————————- ስለ 1966ቱ ለውጥ ብዙ ተብሏል፡፡ በለውጡ ወቅት […]

የአንድነት፣ የሰማያዊና የመኢአድ አባላት ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ! ለጥር 19/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው! በሽብር ክስ ተጠርጥረው የመኢአድ፣ የሰማያዊና የአንድነት አመራሮች በዛሬው እለት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን የአንድነት ፓርቲ ጠበቃ አቶ ገበየሁ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም በነበረው ሰነድ፣ አሻራ እና ቃላቸውን ወስደዋል እንዲሁም አስረላጊ ምርመራም አካሂደዋል፡፡ ተጨማሪ ምንም ምርመራ ያደረጉት ነገር ስላልተገኘ ደምበኞቼን የዋስትና መብታቸው […]

ትናንት በ19/04/07 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ የኮምቦልቻ ጽ/ቤት መከፈቱን ተከትሎ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት የአንድነት አመራሮች መካከል አቶ ተማም መሀመድ በከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ተጠርተው ተጠይቀዋል፡፡ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎቹ ‹‹እናንተ ያለጊዜው የምርጫ ቅስቀሳ እያደረጋችሁ ነው፤ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር እያሰባችሁ ነው፤ሳታሳውቁ ነው የምትሰሩት›› የሚሉ ጥያቄዎች ያቀረቡባቸው ሲሆን፤ አቶ ተማም እኛ ቢሯችንን ስንከፍት ተገቢውን የማሳወቂያ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው […]

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በወህኒ ቤት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው አስታወቁ ‹‹በደምበኞቼ ላይ ዘረፋ ተፈፅሟል›› ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ‹‹በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ›› አቶ ሀብታሙ አያሌው ‹ከፍተኛ በደል ተፈፅሞብኛል›› አቶ ዳንኤል ሺበሺ በእነ ዘላለም ወርቅነህ የክስ መዝገብ የተከሰሱት አራት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ላይ በወህኒ ቤት ውስጥ በመንግስት የደህንነት አባላት ዘረፋ እንደተካሄደባቸው ለፍርድ ቤት ተናገሩ፡፡ በሽብርተኝነት ተወንጅለው ክስ የተመሰረተባቸው […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጥር 3 በባህርዳር ለሚያደርገው ህዝባዊ ሰልፍ የቅድመ ዝግጅት ስራ የሚያከናውኑ ከፍተኛ የፓርቲው ልዑካን ወደ ስፍራው አምርቷል፤ ቀደም ሲል የሰሜን ቀጠና ሀላፊ አቶ አእምሮ አወቀ የሄዱ ሲሆን አሁን ደግሞ አቶ አስራት ጣሴና አቶ ብሩ በርመጅ ወደ ስፍራው አቅንተዋል። የከተማው አስተዳደር ሰልፉን ላለመፍቀድ አሁንም እያንገላገረ ቢሆንም፤ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት የሰልፉን ቦታና ጊዜ አንድነት […]

አንድነት ፓርቲ፣ በወጣቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አማካኝነት በአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ ካፌዎች የሻይ ቡና ውይይት በማካሄድ ፓርቲውን በአዲስ መንገድ ማስተዋወቅ መጀመሩን የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ አቶ እንግዳ ወልደፃዲቅ፣ ለፍኖተ-ነፃነት ገለፁ። “ድምፅ አለኝ ምርጫ አለኝ” በሚል መሪ ቃል ታህሳስ 13 ቀን 2007 ዓ.ም የተጀመረው የሻይ ቡና ውይይት ለአንድ ሳምንት የሚዘልቅ ሲሆን የፕሮግራሙ አላማ “ህብረተሰቡ ስለምርጫው እንዲወያይ […]

የአንድነት ሰሜን አሜሪካ የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ባዘጋጀው የዛሬው ቴሌኮንፈራንስ የቴሌቭዥኝ ፣ የራዲዮ ጣቢያዎች፣ ድህረ ገጾችና ፓልቶክ ክፍሎች ተጋብዘዋል። በዚህ መሰረት ማህደረ አድነት ( አትላንታ)፣ ሕብር ራዲዮ (ላስ ቬጋስ)፣ መለከተ ራዲዮ ( ቫንኮቨር)፣ የአንድነት ድምጽ ራዲዮ ( ዲሲ)፣ የአዲስ ድምጽ ራዲዮ (ዲሲ)፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች አንድነት ድምጽ ራዲዮ፣ አቡጊዳ፣ ሳተናው እና ዘሃበሻ ድህረ ገጾች፣ የቃሌ፣ የከረንት አፌር […]

(አቶ እያስፔድ ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚና የወጣቶች ክፍል ሃላፊ ናቸው። በቅርቡም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት/ባንክ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ተባረዋል። በነገረ ኢትዮጵያ ብዙ ጊዜ ጽሁፎችን የሚያቀርቡ ወጣት ፖለቲካኛ ናቸው። በትብብሩና በአንድነት መካካል ሊኖር ስለሚገባው ግንኙነት የሚከተለዉን ጽሁፍ አቅርበዋል። አንድነት ትብብሩ ውስጥ ለመግባት ያስቀመጣቸው ቅድመሁናዎች ሊሟሉ ይችላሉን? (የሰማያዊ አመራር) የፓርቲዎች መተባበር እና ጋራ መቆም እጅግ በጣም አስፈላጊ […]

የባህር ዳር ህዝብ ይህን ቦታ እጅግ ለረጅም አመታት ለአምልኮ ስንጠቀምበት የነበረ ነው። ለባለ ሀብት መሰጠቱና ለሌላ አገልግሎት እንዲውል መወሰኑ ትክክል አይደለም ብሎ ቅሬታውን ሊያሰማ አደባባይ ወጣ። ይህ ለእምነቱ የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል ቀናዊ የሆነ በአገሬ ጉዳይና በኑሮዬ እሚንት የምታህል መብት አለኝ ብሉ የሚያስብ የየትም አገር ዜጋ ሊያደረገው የሚችል ነው። በእውን ይህን ማድረግ የሚከለከል ወይ ማድረጉስ ወንጀል […]

ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን ወደ እውነት ያመጡ ህጎች በኢትዮጵያ አሉ የሚለው ወያኔ ህዝቦች ግን በተግባር ተጠቃሚ ሲሆኑ አላየንም::ህጎቹ በተግባር ይዋሉ ይህንን ህጎች በመመሪያ በደብዳቤ እና በስልክ የሚቀይሩ የሚደፈጥጡ በጥቅም የሚሸጡ የሚረጋግጡ የሚለውጡ ከየወንበራቸው ተሽቀንጥረው ይጣሉ:: የቀን ተቀን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ሂደት ውስጥ እጃቸውን እያጠለቁ ፍትህን የሚያዛቡ አስተዳደራዊ በደሎችን የሚፈጽሙ ባለስልጣናት የህዝብን ማህበራዊ ህይወቶች ከማፋለሳቸውም […]

በቅርቡ የሚካሄደውን የ2007 ምርጫን አስመልክቶ፣ ኢሕአዴግ፣ አንድነት እና ኢዴፓን የወከሉ ሰዎች በፋና ሬዲዮ ባለፈው እሁድ ውይይት አድርገው ነበር፡፡ መኖሩ ትርጉም ስለአልነበረው ነው እንጂ ሌላም አንድ ፓርቲ ወክያለሁ ያለ ሰው እንደነበር ዘንግቼው አይደለም፡፡ የኢሕአዴጉ ወኪል በመጨረሻ ላይ ያቀረቡትን ሃሳብ ሳደምጥ የኢሕአዴግ ተወካዮች ከላይ የተሞሉትን ወደታች ከማስተጋባት ውጪ አንዳቸውም በራሳቸው መርምረው ሊደርሱበት የሚፈልጉት ሀቅ አለመኖሩ ነው፡፡ በፓርቲው […]

አንድነት የሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ሰጪ ማህበር ከአንድነት ፓርቲ ጋር በመተባበር፤ በፓርቲው እንቅስቃሴዎች እና በምርጫ 2007 ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ አዘጋጅቷል፡፡ በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በውጭ የሚገኙ የቲቪ፤ የሬዲዮ፤ የድህረ ገጽ፤ የፓልቶክ ክፍሎች ተሳታፊ የሚሆኑበት ሲሆን ከአንድነት የፓርቲው ፕሬዘዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ እና ም/ፕሬዘዳንት አቶ ተክሌ በቀለ ይሳተፋሉ። ውይይቱ የሚካሄደው፤ እሁድ ዲሴምበር 28, 2ዐ14 በ 2:00 PM […]

የሳምንቱ የምኒሊክ ሳልሳዊ መልዕክት – ዲሴምበር 26, 2014

1-የዚህ ጽሁፍ ዓላማ፤ የአንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መሪዎች፤ አሁድ ድሴምበር 28 ቀን ከሰአት በኋላ 2pm ላይ፤ በውጭ ለምንገኝ ኢትዮጵያውያን ያዘጋጁትን የስልክ ውይይት ማስተዋወቅ ነው። ይሁን እንጂ ማስታወቂያውን እርቃኑን ባሰፍረው፤ አይማርክም በሚል፤ አንዳንድ ተያያዥ ነገሮችን ላለብሰው ፈቀድኩ። መለመላውን ከሚቀርብ የስልክ ጉባኤ ማስታወቂያ ይልቅ፤ ትንሽ ውዝግብ የለበሰ ማስታወቂያ ቀልብ ይስባል፡፡ 2-አንደኛው ልብስ፡ ሂደት የሚሉት ነገር ነው፡፡ ስለምርጫና […]

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና አደራጅ አቶ አዕምሮ አወቀ በመንግስት የደህንነት ሀይሎች ታፍነው ዝርፊያና ድብደባ እንደተፈፀመባቸው የፓርቲው ድርጅት ጉዳይ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቀ፡፡ አቶ አዕምሮ ዝርፊያና ድብደባው የተፈፀመባቸው በትላንትናው ዕለት በግምት ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል የፓርቲያቸውን ሰነድ እንደያዙ ከአንድ ኢንተርኔት ካፌ ሲወጡ አምስት የመንግስት የደህንነት አባላት ታርጋ በሌለው ሚኒባስ ውስጥ አስገድደው በማስጋት ከባህርዳር ከተማ በግምት የ35 ደቂቃ […]

ሰዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብት አላቸው::የህዝቦችን ነጻነት መጋፋት ጋዜጠኛ አያሰኝም:: ጥፋተኛው የኢሳት ኢዲቶሪያል ሳይሆን የጥቂት ግለሰቦች የማናለብኝነት እና በስሜት የመነዳት ፖለቲካ ነው:: አዎን ምናልባት አንዳንዶች በልቅ የፖለቲካ ስድነት ያሸበረቁ ግለሰቦች ስማቸውን የቀያየሩ ሰውን በየድህረገጹ የሚዘልፉ የኢሳት ጋዜጠኞች ይህ ጽሁፍ ላይመቻቸው ይችላል:: ኢሳት ገና ከጅምሩ ሲመሰረት ህዝባዊ አላማ አንግቦ እና ህዝባዊ ስራዎችን ለመስራት እንደተቋቋመ የማይካድ ሃቅ […]

መታሰር ክፉ ነው፡፡ የታሰረ ሰው ተስፋው ሁሉ ውጪ በቀረው ታጋይ ላይ ነው፡፡ የሀብታሙ አያሌው እና የየሺዋስ አሰፋ ልብ የሚነካ ተማፅኖ አእምሮዬን ሁሉ ተቆጣጥሮታል፡፡ ‹‹እባካችሁ ተባበሩ›› ‹‹እስቲ ቀረብ ብላችሁ ተነጋገሩ›› በየንግግራቸው መሀል እየደጋገሙ የሚያስተላልፉት መልዕክት ነው፡፡ ‹‹እኛ እኮ ከዛሬ ነገ ለውጥ መጥቶ ኑ ውጡ እንባላለን ብለን ነው የምንጠብቀው……በተናጠል ድርጅቶች ያላቸውን አቅም የምናውቀው ነው….እባካችሁ ተባበሩ›› ሀብታሙ አያሌው፡፡ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ምርጫ ቦርድ ነፃና ገለልተኛ እንዳልሆነ የሚገነዘብ ቢሆንም ባለፈው ታህሳስ 12/04/2007 ዓ.ም የተካሄደው የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ በሀገራችን የምርጫ ቦርድ አለ ወይ?! እንዲል አድርጎታል። የታህሳሱ 12/04/2007 ዓ.ም የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ነፃና ገልልተኛ አልነበረም ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የምርጫ ህጉን ተከተሎ ያልተካሄደ ሌላው ይቅርና የራሱ የምርጫ ቦርድ መመሪያን እንኳን ያልተከተለ ከመሆኑ አንፃር ተካሄዷል ብለን […]

እኔ የዓረና-መድረክ ኣባል ከመሆኔ የተነሳ በምርጫ 2007 ዓ/ም ለፌደራል ወይም ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ እንደምሆን የራሴ እቅድ ይዤ ነበር፤ እናንተም በተመሳሳይ ግምት እንደምትጠብቁ እገምታለው። ኣሁን እየሆነ ያለው ግን “…ለምሳ ያሰቡን ለቁርስ ኣደረግናቸው..” ዓይነቱ የጓድ ሊቀ መንበር መንግስቱ ዓይነት ተግባር ህወሓት መራሹ የትግራይ መንግስት እጩ “ሽብርተኛ” ኣድርጎው ኣጭተውኛል። እም በኣቅሚቲ “..የኣሸባሪነት..” ካባ ለብሼ ቅሊንጦ ወይም […]

መኢአድ (የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት) አንጋፋ ድርጅት ነው። ከመስራቹ ከፕሮፌሰር አስራት ጀመሮ የዚህ ድርጅት አባላትና ደጋፊዎች እጅግ ብዙ ዋጋ ከፍለዋል። ብዙዎች ሞተዋል፤ ብዙዎች ታስረዋል። ከማንም ድርጅት ባልተናነሳ ገዢው ሙሸት አማረ በሚመራዉና በአቶ አበባው በሚመራው ቡድን መካከል ያሉ ልዩነቶች በአሁኑ ወቅት መኢአድ ትንች በተጠናከረ መልኩ ወደፊት እንዳይሄድ አድርጎታል። የነዚህ ሁለት ቡድኖች ዉዝግብ ገና አልተፈታም። ሕጋዊዉ የመኢአድ […]

ትግራይ ክልል ላይ የሚፈፀሙትን ጭቆናዎች ሳይታክት አጋልጧል። ዘረኝነትን ፣ አምባገነንነትን ፣ ሙሰኝነትን ፣ ኢ-ፍትሐዊነትን አውግዟል። ሰብአዊነትን በማስቀደም ሰውን በሰውነቱ የሚለካ ምርጥ ኢትዮጵያዊ ነው-አብርሃ ደስታ፡፡ አብርሃ ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የብዙ ሰዎችን ቀልብ ለመሳብ ከመቻሉም በላይ ፤ “ፌስቡክን” ከፌዝ-ቡክነት በመታደግ የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎችን ሲያቀብለን ነበር፡፡ በመግቢያችን ላይ በአጭሩ እንደተገለጸው ይህ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ፣ የአሁኑ የፖለቲካ እስረኛ […]

ጓድ ቆምጬ አምባው በስማቸው የሚነገሩትን ጨዋታዎች በኔ ስም የተፈጠሩ ተረቶች ይሏቸዋል፡፡ ሰውዬውን በቅርበት የሚያውቁት ግን በርሳቸው ስም የተፈጠሩት ጨዋታዎች ከፊል እውነታ እንዳለባቸው ይናገራሉ፡፡ በርካታ ሰዎች ጨዋታዎቹን እያወሱ የሰውዬውን ጅልነት ሊያሳዩ እንደሚፈልጉ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ቆምጬ አምባው ነገር የገባቸው ብልጥ ነበሩ እንጂ በጭራሽ ጅል አይደሉም፡፡ ይህንን ለማሳየት እንዲቻለንም በርሳቸው ስም ከሚነገሩት ጨዋታዎች መካከል ጥቂቶቹን እንጽፍላችኋለን፡፡ ***** በደርግ […]

ገዢው ፓርቲ ሕወሃት/ኢሕአዴግ የእምነት ነጻነትን በመጋፋት ፣ ታቦት ቢወጣበትና የጥቅምት በዓል በሚከበርበት በባህር ዳር የመስቀል አደባባይ “ልማት” በሚል ስም ለባለሃብቶች ቦታዎች ሊሰጥ ማሰቡን ተከትሎ ሕዝቡ ለአስተዳደሩ ብሶቱን በደብዳቤ ለማስገባት፣ በቦታው ሄዱ ለማነጋገር ቢሞክር፣ ለሕዝብ ጥያቄ ደንታ የሌላቸው የሕወሃት/ኢሕአዴግ ባለስልጣናት፣ ቦታውን ለባላሃብቶች ለመስጠት በመወሰናቸው፣ ሕዝቡ የእምነት ነጻነቱን ለማስከበር ባለስልጣናት ዉሳኔያቸዉን እንዲቀለብሱ ለማድረግ፣ በራሱ አነሳሽነት ፣ በሺሆች […]

አምርረህ ልትታገልበት የሚገባ በቂ ምክንያት ካለ አላማው አንድና አንድ “ማሸነፍ” የሆነ ትግል እንጂ የትግል አይነት የሚባል ነገር የለም። አዎ ያለው ትግል ነው። ቢቸግር ነው እንጂ ችግሩ “አይነት” የሚለው ቃል ችግር ሆኖ አይደለም። ትግሉ ላይ ሲሆን አጠቃቀማችንና አረዳዳችን ግን በጣሙኑ ግራ ያጋባል። “ምግብ” ለሚለው ያጋራ መገለጫ ስር ጨጨብሳ፤ ሙዝ ፤ ወተት የመሳሰሉ ምግቦች እንዳሉ ለማሳያት ሳይሆን […]

ካድሬዎቹ በባህር ዳር የተደረገውን ግድያ በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመ ነው ሲሉ ተናግረዋል:: – ባለፈው አርብ በባህር ዳር ሰላማዊ የሆነ ጥያቄ ይዘው አደባባይ በወጡት ንጹሃን ዜጎች ዙሪያ እና በመጭው ምርጫ ዙሪያ በአዲስ አበባ ብአዴን ካድሬዎቹን በመሰብሰብ ያደረገው ውይይት ክለመስማማት መበተኑን ለምንሊክ ሳልሳዊ የውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: እንደ ምንጮቹ ዘገባ ከሆነ ካድሬዎቹ ሕዝብን ማሳመን የማንችልበት ደረጃ ላይ […]

የህዝብ ታዛቢ በመሆን ሊያገለግሉ የሚችሉ ሰዎችን ለመምረጥ በየቀበሌው በተደረገው ታዛቢዎችን የማስመረጥ ሂደት ላይ የገዢው ፓርቲ አባላት በታዛቢነት መመረጣቸውን በምርጫው ሂደት ላይ የነበሩ ተሳታፊዎች ለፍኖተ-ነፃነት ገለፁ፡፡ በዛሬው እለት ታዛቢዎችን በማስመረጥ ሂደት ላይ “የገዢው ፓርቲ አባላት ህዝቡን በማግለል እርስ በእርስ በመመራረጥና የምርጫ ሂደቱን በድብቅ እያካሄዱ” መሆኑን የገለፁት የፍኖተ-ነፃነት ምንጮች “ይህ አካሄድ ህገ-ወጥ እና የምርጫውን ደንብ የጣሰ” መሆኑን […]

.እስክንድር ነጋ እና አንዱዓለም አራጌ ማስታወሻቸው ተወስዶባቸዋል፤ ቃሊቲ እስር ቤት ሙሉ ፍተሻ እንደተደረገበት ዛሬ እኩለ ቀን ላይ እስረኞችን ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ አቅንተው የነበሩ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አመለከቱ፡፡ ከፌደራል ወንጀል ምርመራ እንደመጡ በተነገረላቸው ሰዎች ሙሉ ቃሊቲ እስር ቤት ፍተሻ እንደተደረገበት ከእስረኞች እንደተገለጸላቸው ያመለከቱት ምንጮች እንዳሉት ፍተሻው የእያንዳንዱን የእስረኛ ክፍል ያካተተ ነበር፡፡ በዚህም ወቅት የእስረኞች ማስታወሻዎችና ሌሎች […]

በዛሬዉ እለት የህዝብ ታዛቢ በመሆን ሊያገለግሉ የሚችሉ ሰዎችን ለማስመረጥ በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት/አካላት፤አመራሮችም ጭምር በተለያዩ የምርጫ ጣብያዎች እንደተገኙ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡የታዘቡትን እያካፈሉን ሲሆን እኔም ያየሁትን ላካፍል ወደድኩ፡፡የታዘብኩት የየካ ክ/ከተማ ወረዳ ዘጠኝን ነዉ፡፡መቐለ ከተማ ወረዳ ሓዉልቲ ያለሁ ነበር የመሰለኝ፡፡አስተባበሪዎቹ፤የወረዳዉ ካድሬዎች፤የአንድ ላምስት አስተባባሪዎች፤በሰፈሩ የማዉቃቸዉ ደህንነት ነን ባዮች ወዘተ ከተጠራዉ ህዝብ በቁጥር አያንሱም፡፡የሚሉትን በሙሉ እኔና ታዛቢ አድርጌ የወሰድኩት የማይጨዉ […]

ከኛ በላይ ላሳር ከኛ በላይ አዋቂ የለም የሚል አመለካከት ይዞ ከመክነፍ የህዝብን ጥያቄ መሰረት አድርጎ ተቀራርቦ በመነጋገር እና በመወያየት ሃገራዊ ማኒፌስቶ በማምጣት የጋራ ሃገራዊ አጀንዳ በመቅረጽ ለለውጥ መትጋት ግዴታ ነው::አንድነት ሃይል ነው የሚለው ብሂል ለሃገራዊ አጀንዳ መተግበር ትልቅ አስታውጾ አለው::የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ይህ ሳይታለም የተፈታ እና የሁሉም የነጻነት ፈላጊ ሃይሎች ጥያቄ ነው። ያዳምጡ :: […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) አንድነት – በባህርዳር ከተማ በንፁሀን ዜጎች ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ያደረሱ በህግ ፊት ይቅረቡ! ********************************************************************** ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ *********************************************************************** አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በትናንትናው ዕለት ታህሳስ 10/ 2007 ዓም በባህርዳር ከተማ መንግስት ኃይሎች የጥምቀት ክብረ በዓል ታቦት የሚያርፍበትን ቦታ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የ2ዐዐ7 ዓ.ም አገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍና ለዚህም መተማመኛው ሕዝቡ መሆኑን ገልፀ ‹‹ተደራጅ 2007 ለለውጥ›› በሚል መፈክር አንግቦ አገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትና ኢህአዴግን በቃህ ለማለት ሌት፣ ከቀን በንቃትና በትጋት እየሠራ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ነፃ ሚዲያ በታፈነበትና በተዘጋበት አንድነት የራሱን የማተሚያ ማሽን ገዝቶ በየጊዜው ሆን ተብሎ በሚመስል መልኩ በሚጠፋው የኤሌክትሪክ ችግርን ለማሸነፍ የራሱን […]

-ዶ/ር ዳንኤል ተፈራና ዶ/ር ፀሀይ ለኢሳት ጋዜጠኛ ለአቶ ፋሲል የኔ ዓለም ስለ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ለሰጧቸው መልሶች የቀረበ አስተያየት- ከፈቃዱ በቀለ መግቢያ በቅርቡ ሁለት በአሜሪካን አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ኢኮኖሚስቶችን የኢሳት የቴሊቪዝን ጋዜጠኛ የሆነው አቶ ፋሲል የኔ ዓለም ኢትዮጵያ ከውጭ የምትበደረው ብድር መጠን እያደገ ስለመምጣቱና ስለኢኮኖሚው አጠቃላይ ሁኔታ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ በመጋበዝ በመሰላቸውና በሚታያቸው፣ እንዲሁም ከተማሩት […]