ሰኔ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዶ/ር አዲሱ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ቢሆኑም ከህወሃት/ኢህአዴግ ቀጥተኛ መመሪያ በመቀበልና በማስፈጸም ረገድ ቁልፍ ሰው መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በተለይ ተቃዋሚዎች እንዲዳከሙና ትንንሽ ልዩነቶቻቸውን በማጦዝ ፓርቲዎች እንዲናጉና እንዲፈርሱ ከኢህአዴግ ጋር እየተናበቡ የሚሰሩ ሲሆን ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚያቀርቡትንም አቤቱታ በማድበስበስ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ፕ/ር …

ሰኔ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ አቡበክር አህመድ የክስ መዝገብ የተከሰሱት የኮሚቴው አባላት የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል በሚል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሙስሊም ኢትዮጵያዊ በችሎቱ ቢታደምም፣ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የማሰማቱን ሂደት በድጋሜ ወደ ሰኞ አራዝሟል። ችሎቱ የአቃቢ ህግ መስክሮችን ቃል አንብቦ ከጨረሰ በሁዋላ ተከሳሾች ለፖሊስ ሰጡት ያለውን ቃል በንባብ አሰምቷል። የፊታችን ሰኞ የመጨረሻው …

ሰበር ዜና፡- ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር፣ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ፡፡

ዶ/ር አዲሱ የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊቀ መንበር በመሆን ያለፉትን ሁለት አጠቃላይ ምርጫዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ ገዢው ፓርቲና አጋሮቹ 547ቱንም የፓርላማ መቀመጫ ያሸነፉበትን የ2007 ዓ.ም አጠቃላይ ምርጫ በመምራት በሕግ የተፈቀደላቸውን የሥልጣን ዘመን አጠናቀዋል፡፡ 

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የዶ/ር አዲሱን፣ የምክትል ኮሚሽነርና የኮሚሽን አባላት ሹመት በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል፡፡ በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ላለፉት አምስት ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና በዶ/ር አዲሱ ተተክተዋል፡፡

   

በመወያኔ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ አለመግባባቱ ተባብሶ መቀጠሉ ታወቀ በታላቁ አንዋር መሰጂድ ከባድ ተቃውሞ ተደረገ የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የኢትዮጵያ ጉብኝት በዓለም ዙርያ ቁጣ ቀስቅሷል።  አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲፈቱ  ዘመቻ ተጀመረ የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአቶ አንዳርጋቸው አያያዝ ዙሪያ ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ተሰማ በመወያኔ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ አለመግባባቱ ተባብሶ መቀጠሉ ታወቀ በመከላከያ ሰራዊት የሰሜን እዝ አባላት የሆኑት ወታደሮች በአገልግሎት ማብቂያ በሚል […]

ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2007 ዓ.ም ልደታ ፍርድ ቤት 11ኛ ችሎት ቀርበው በቂሊንጦ ታስሮ ሚገኘው ማስተዋል ፈቃዱ ባለመቅረቡ የአቃቢ ህግ ይግባኝ ሳይታይ ቀርቶአል፡፡ ወይንሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬ እና ቤተለሄም አካለወርቅ ትናንት በዛቻ እና ማስፈራራት ክስ ቄራ ምድብ ችሎት ቀርበው በዋስ እንዲወጡ ቢታዘዝም ካሳንቺዝ ስድስተኛ ፖሊስ ግን ታሳሪዎቹን ለመልቀቅ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ጠዋት በልደታ […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሰኔ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ የወንጀል ችሎት በድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት ላይ ሊሰጥ የነበረውን ፍርድ ያራዘመ ሲሆን፣ ፍርዱ ለምን እንደተራዘመ ግን በግልጽ የታወቀ ነገር የለም። በአቶ አቡበከር አህመድ መዝገብ 18 የኮሚቴው አባላት በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሰው የመጨረሻውን ፍርድ ለመስማት ችሎት የተገኙ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ የክሱን …

ሰኔ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመከላከያ ሰራዊት ያወጣው አዲስ የቅጥር ማስታወቂያ ተቀባይነት አለማግኘቱን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። በሰሜን ሸዋ ከሁለት ሳምንት በፊት የወጣውን የቅጥር ማስታወቂያ ተከትሎ ተመዝጋቢ በመጥፋቱ፣ የአካባቢው ባለስልጣናት የሚያደርጉት ጠፍቷቸዋል። በአርባምንጭ ደግሞ የኢህአዴግ ካድሬዎች በመኪና እየዞሩ ወጣቱ ለመከላከያ አባልነት እንዲመዘገብ እየቀሰቀሱ ነው። ይሁን እንጅ ለጥሪው ወጣቱ የሚሰጠው ምላሽ …

ሰኔ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ መንግስት ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ በማንኛውም መልኩ የህግ ትምህርት በግል ተቋማት እንዳይሰጥ የከለከለ ሲሆን፣ የአቶ ደመቀ ከፊል ንብረት የሆነው ሚሸከን ኮሌጅ ግን ተማሪዎችን እያሰተማረ እንደሚገኝ መረጃዎች አመልክተዋል። ተመሳሳይ ድርጊት የፈፀሙ ኮሌጆች ቢዘጉም፣ ለሚሽከን ኮሌጅ ግን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነት ጥራት ኤጀንሲ ከማሰጠንቀቂያ ያለፈ ውሳኔ አልሰጠውም። የሚሽከን ኮሌጅ …

ሰኔ ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰኔ 19 ቀን 2007 ዓም ከጧቱ 1 ሰአት ላይ መድሃኒአለም በሚባል አካባቢ ሁለት መኪኖች ኮንትሮባንድ እቃ ጭነዋል በሚል ምክንያት ሲከተሉዋቸው የነበሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በድንገት ተኩስ በመክፈታቸው አንደኛው መኪና መስመሩን ስቶ ከወጣ በሁዋላ በመገልበጡ 7 ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ሰዎች ደግሞ ተጎድተው ሆስፒታል ገብተዋል። …

በርካታ ድርጅቶች በግል ጡረታ አዋጅ ማሻሻያ ላይ ያላቸውን ቅሬታ ለፓርላማ አቀረቡ

በርካታ የግል ድርጅቶችና የሲቪክ ማኅበራት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ያላቸውን ቅሬታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቀረቡ፡፡ የምክር ቤቱ የማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ማሻሻያውን አስመልክቶ

ባዘጋጀው የሕዝብ አስተያየት መስጫ መድረክ ላይ የተጋበዙ ከ300 በላይ የሚሆኑ የግል ድርጅቶችና ሲቪክ ማኅበራት፣ ማሻሻያውን ያረቀቀው የግል ድርጅት ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ባለድርሻ አካላትን ሳያነጋግር ወይም ሳያወያይ ይህንን ረቂቅ ማሻሻያ ለፓርላማ ማቅረቡ ፍፁም ተገቢ አይደለም ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ 

በዋናነት ከተካተቱት ማሻሻያዎች መካከል በግል ድርጅት ሠራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 715/2003 ቀደም ሲል የፕሮቪደንት ፈንድ ሥርዓት በፈቃደኝነት እንዲቀጥል ቢወሰንም፣ በማሻሻያው ግን ወደ ግል ሠራተኞች ጡረታ ፈንድ ይዞራል የሚለው ይገኝበታል፡፡ 

ይህ ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ከቀረበ በኋላ ግን አርቃቂው አካል የግል ድርጅት ሠራተኞች ማኅበራዊ ኤጀንሲ ማሻሻያውን በድጋሚ በማየት ፕሮቪደንት ፈንዱ በቀጥታ ይዞራል ወይም የተጠራቀመው ገንዘብ ወደ ጡረታ ፈንድ ይገባል የሚለው እንዲስተካከል ማድረጉን የኤጀንሲው የሥራ ኃላፊዎች በውይይቱ መጀመርያ ላይ ተናግረዋል፡፡ 

በውይይቱ እንዲገኙ የተጋበዙት ድርጅቶች በሙሉ ሠራተኞቻቸውን በፕሮቪደንት ፈንድ ዋስትና የሚያስተዳድሩ በመሆናቸው፣ በመጀመርያ እፎይታቸውን ገልጸዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር አረጋ ይርዳው ይገኙበታል፡፡ 

‹‹ይህንን ማሻሻያ በመስማቴ ደስ ብሎኛል፤›› ያሉት ዶ/ር አረጋ መንግሥት ስለ ግል ሠራተኞች ማኅበራዊ ዋስትና ማሰብ ከመጀመሩ በርካታ ዓመታት ቀደም ብሎ፣ የግል አሠሪዎችና ሠራተኞቻቸው ተነጋግረው ፕሮቪደንት ፈንድ ሥርዓትን መፍጠራቸውን አስታውሰዋል፡፡ 

‹‹ስለዚህ ፕሮቪደንት ፈንድ የአሠሪና የሠራተኛው የግላቸው ነው፡፡ ማንም ሌላ ሰው ሊወስንበት አይችልም፤›› ብለዋል፡፡ በዚህም መልክ መወሰኑን ጥሩ ነው ብለዋል፡፡

ሲአርዲኤ የተባለው የሲቪክ ማኅበራት ጥላ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ዶ/ር መሸሻ ሸዋረጋ፣ በተመሳሳይ የማሻሻያ አዋጁ አርቃቂዎች ባለድርሻ አካላትን አወያይተናል በማለት ያቀረቡት ሪፖርት ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ 

በሲአርዲኤ ሥር ከ350 በላይ ሲቪክ ማኅበራት የሚገኙ መሆኑንና ኢትዮጵያ ከዚህ ዘርፍ በዓመት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደምታገኝ አስታውሰው፣ ይህንን ዘርፍ እንደ ባለድርሻ አካል ሳያወያዩ ሪፖርት ማድረግ ተገቢ አለመሆኑን ጠቁመዋል፡፡ 

የአዋጁ አርቃቂዎች ባለድርሻ አካላትን አወያይተናል የሚሉት የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽንና የአሠሪዎች ፌዴሬሽን ነው፡፡ 

‹‹ዛሬ በድፍረት መናገር ያለብኝ ይመስለኛል፡፡ እነዚህ ተቋማት እንደማይወክሉን ታውቃላችሁ፡፡ እንዲያውም ለመንግሥት ነው የሚሠሩት፤›› ሲሉ ዶ/ር አረጋ ይርዳው ተችተዋል፡፡ 

ዶ/ር መሸሻ ፕሮቪደንት ፈንድን በቀጥታ ወደ ጡረታ እንዳይዞር በመጨረሻ መወሰኑን ተቀብለዋል፡፡ ‹‹ይሁን እንጂ ፕሮቪደንት ፈንድ ምንም እንዳልሠራ መቆጠር የለበትም፡፡ በ2003 ዓ.ም. እንደተፈቀደው ሁሉ አሁንም በሠራተኞች ምርጫ ሊቀጥል ይገባል፤›› ብለዋል፡፡ 

የሲቪክ ማኅበራት ፀባይ ከሌሎቹ ስለሚለይ ሠራተኞች የሚቆዩት ፕሮጀክቶች እስካሉ ድረስ ብቻ ስለሆነ፣ ፕሮጀክቶች ሲያበቁ እንደሚሰናበቱ አስታውሰዋል፡፡ 

ዶ/ር መሸሻ ሠራተኞች በሚሰናበቱበት ጊዜ ለሥራ መፈለጊያም ሆነ ቤተሰቦቻቸውን ማስተዳደሪያ ሆኖ የሚያገለግለው ፕሮቪደንት ፈንድ በመሆኑ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡ ምክንያቱም እንደ ሌላው አገር ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ‹ኢምፕሎይመንት ፈንድ› ወይም ሥራ አጥ በሚኮንበት ወቅት የኑሮ ዋስትና አለመኖሩን ጠቅሰዋል፡፡ ‹‹እኛ አገር ይህ ባለመኖሩ ፕሮቪደንት ፈንድን ይዞ መቀጠል ምን ችግር አለው?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ 

የሴንተር ፎር ዲስኤቢሊቲስ ዴቨሎፕመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ የትነበርሽ ንጉሤ በበኩላቸው፣ ‹‹የፕሮቪደንት ፈንድ ሊቀጥል ይገባል፡፡ ምክንያቱም በተለይ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን የሚያበረታታ ነው፤›› ብለዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ወጣቶች እስከ 60 ዓመት ዕድሜያቸው በተቀጣሪነት ቆይተው የጡረታ ተከፋይ እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤትን ወክለው የተገኙት የሕግ ባለሙያው አቶ ዮሐንስ ወልደ ገብርኤል፣ ‹‹የፕሮቪደንት ፈንድ ማኅበራዊ ዋስትና ሥርዓት የራሱ ደካማ ጎኖች አሉት፡፡ እነዚህ ደካማ ጎኖች ግን መንግሥት ለፕሮቪደንት ፈንድ ጥበቃ ለመስጠት ኃላፊነት ባለመውሰዱ የተከሰቱ ችግሮች እንጂ የግሉ ዘርፍ የፈጠረው አይደለም፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹ፕሮቪደንት ፈንድ ለግሉ ዘርፍ ትልቅ ዋስትና ነው፡፡ አሠሪው ለሠራተኛው ዋስትና እንዲኖረው የሚያደርግ ነው፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው፣ ኮንፌዴሬሽኑ ከኤጀንሲው ጋር በተወያየበት ወቅት ፕሮቪደንት ፈንድን በተመለከተ ኮንፌዴሬሽኑ ያቀረበው ሐሳብ የጡረታ ዐቅድ እየሰፋ በሄደ ቁጥር ፕሮቪደንት ፈንድ እየተዋጠ እንደሚሄድ፣ በመሆኑም በራሱ ጊዜ ሊሞት ስለሚችል መነካካት አያስፈልግም የሚል እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ 

አሁንም ቢሆን ፕሮቪደንት ፈንድን የማይፈልጉ ድርጅቶች ብቻ ወደ ጡረታ በምርጫቸው እንዲመጡ መደረግ እንዳለበት ኢሠማኮ እንደሚያምን ተናግረዋል፡፡ ሌሎች በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦችም ፓርላማው ይህንን አዋጅ በዚህ ዓመት ሊያፀድቀው እንደማይገባ ተከራክረዋል፡፡ 

ይህንን ያሉበት ምክንያት የረቂቅ አዋጁ አንቀጽ 19 ላይ የተደረገው ማሻሻያን በመቃወም ነው፡፡ አንቀጹ ‹‹በተቀጠረ ሦስት ዓመት ወይም ከዚህ ባነሰ ጊዜ ውስጥ በጡረታ የሚገለል ሠራተኛ፣ በጡረታ ከሚገለልበት ወር ሦስት ዓመት አስቀድሞ ባለው ወር ሲከፈለው ከነበረው መደበኛ የወር ደመወዝ በ25 በመቶ የሚበልጥ ዓመታዊ አማካይ የደመወዝ ጭማሪ ያገኘ እንደሆነ፣ በየዓመቱ 25 በመቶ ያለው የደመወዝ ጭማሪ ብቻ በደመወዙ ላይ ተደምሮ የሦስት ዓመት አማካይ የወር ደመወዙ ተይዞ ይታሰባል፤›› ይላል፡፡ 

ይህንን የተቃወሙት የድርጅት ተወካዮቹ አገሩን በዝቅተኛ ደመወዝ ሲያገለግሉ የነበሩ የመንግሥት ሠራተኞችን፣ ወታደሮችንና የመሳሰሉትን የሚጎዳ ነው ሲሉ ተቃውመዋል፡፡ በዕድሜው መጨረሻ ላይ የተሻለ ገንዘብ ቢያገኝ ለአገሩ ያበረከተውን በገንዘብ የማይለካ አስተዋጽኦ ወደጎን በመተው፣ 25 በመቶ ጭማሪውን ብቻ ማሰብ ተገቢ አይደለም በማለት ተቃውመዋል፡፡ 

የኤጀንሲው የሕግ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ሲሳይ ፕሮቪደንት ፈንድን በተመለከተ በሰጡት አስተያየት፣ ፕሮቪደንት ፈንድ ዘለቄታዊ ማኅበራዊ ዋስትና መሆን አይችልም ብለዋል፡፡ 

‹‹የፕሮቪደንት ፈንድ ገንዘብን የወሰደ ሠራተኛ ገንዘቡ ካለቀበት አለቀበት ነው፡፡ በማኅበራዊ ዋስትና (በግል ጡረታ) ቢታቀፍ ግን አሥር ዓመት ብቻ አገልግሎ ዕድሜ ልኩን እስከነ ተተኪዎቹ ሚስቱንም ጨምሮ ዕድሜው ስልሳ ዓመት ከደረሰ በኋላ ማግኘት ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ 

አንቀጽ 19 ላይ የተደረገውን ማሻሻያ በተመለከተ በሰጡት አስተያየት፣ አንድ ሠራተኛ በመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ከ25 ዓመት በላይ ያገለግልና በ25/55 የጡረታ መብት መሠረት በአምስት ሺሕ ብር ጡረታውን አስከብሮ፣ ቀሪውን ዕድሜ ማለትም አምስት ዓመቱን በግል ድርጅት በወር እስከ 30 ሺሕ ብር ቢቀጠር አጠቃላይ የጡረታ አበሉ የሚሰላው በ30 ሺሕ ብር ደመወዝ ተመን ነው፡፡ ያላዋጣውን በመብላት ፈንዱን የሚያደርቀው በመሆኑ ገደብ ሊጣልበት የሚገባ ነው ብለዋል፡፡ 

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ገብረ ሚካኤል በበኩላቸው፣ ማኅበራዊ ዋስትናን በተመለከተ በየትም አገር ስምምነት ኖሮ እንደማያውቅ ገልጸዋል፡፡ በኋላ ላይ የኅብረተሰቡን ዋስትና ማስከበር የመንግሥት ኃላፊነት በመሆኑ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ ተናግረዋል፡፡ 

የፓርላማው የማኅበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አበባ ዮሴፍ፣ ከውይይቱ በርካታ ቁም ነገሮችን መገኘታቸውን፣ ለፓርላማ የቀረበ ነገር ሁሉ እንደማይፀድቅ፣ በተደረገው ውይይት ላይ በድጋሚ በመነጋገር ተጨማሪ የሕዝብ ውይይት ካስፈለገም ሊጠራ እንደሚችል አስረድተዋል፡፡ 

 

አዳዲስ የፋይናንስ ድጋፎች በሚጠበቁበት ፎረም የቻይና ባለሥልጣናትና ኩባንያዎች ታድመዋል

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ የቻይናና የኢትዮጵያ መንግሥታት የፋይናንስና የኢኮኖሚ ሚኒስትሮች፣ የዓለም ባንክና የሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎችና ኢንቨስተሮች የተገኙበት ፎረም፣ ቻይና በአፍሪካ

ስለምታካሂደው የኢንቨስትመንትና የንግድ ልውውጥ እየመከረ ነው፡፡ አዳዲስ ስምምነቶችና የፋይናንስ ድጋፎች ይፋ እንደሚደረጉበት ይጠበቃል፡፡ 

‹‹ኢንቨስቲንግ ኢን አፍሪካ ፎረም›› በሚል ስያሜ የመጀመሪያውን ጉባዔ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም እንዳስታወቁት፣ በአፍሪካ ከ2,200 ያላነሱ ኩባንያዎች በተለያዩ መስኮች ኢንቨስት አድርገዋል፡፡ በኢትዮጵያም ኋጂዬን ግሩፕ የተባለው ጫማ አምራች 3,500 ሠራተኞችን በመቅጠር፣ በዓመት ሁለት ሚሊዮን ጫማዎችን በማምረት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ 

ከካቻምና ጀምሮ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ካደረጉ የውጭ ኩባንያዎች የሚገኘው የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት 1.2 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የቱርኩ አይካ አዲስን ጨምሮ የታይዋኑ ጆርጅ ሹ ኩባንያና ሌሎችም ሥራዎችን እያስፋፉ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል፡፡ አዳዲሶቹ ፒቪኤችና ኤችኤንድኤም የተባሉ ትልልቅ ኩባንዎች ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውም፣ በዓመት 13 በመቶ እያደገ ለሚገኘው አምራች ኢንዱስትሪው ትልቅ ተስፋ እንደሆነ አቶ ኃይለ ማርያም ተናግረዋል፡፡ 

የቻይና ምክትል የፋይናንስ ሚኒስትሯ ሊዩ ዢያንሁዋ፣ እንዲሁም የቻይና ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዩዋን ሊ ባደረጉት ንግግር፣ አገራቸው ከአፍሪካ ጋር ያላትን የንግድና የኢንቨስትመንት ትስስር ለማጠናከር እንደምትፈልግ አስታውቀዋል፡፡ በተለይ ዩዋን ሊ እንዳሉት፣ ባንካቸው በ34 የአፍሪካ አገሮች ውስጥ በቻይና-አፍሪካ ልማት ፈንድ በኩል እ.ኤ.አ. በ2006 በ82 ፕሮጀክቶች ላይ ኢንቨስት ካደረገው የ3.15 ቢሊዮን ዶላር ገንዘብ በተጨማሪ፣ 16 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት የማድረግ ሐሳብ አለው፡፡ ይህም ወደ አፍሪካ የሚመጣውን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለማሳደግ፣ የአፍሪካን የወጪ ንግድ በየዓመቱ በሁለት ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ፣ እንዲሁም የታክስ ገቢንም በአንድ ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ እንደሚሠራ ተናግረዋል፡፡ በአንፃሩ እስካሁን በቻይና ኩባንያዎች አፍሪካ ውስጥ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት አማካይነት የተመዘገበው አራት ቢሊዮን ዶላር መሆኑን የገለጹት ምክትል ፕሬዚዳንት ሊ፣ የሁለትዮሽ ንግዱ ግን 222 ቢሊዮን ዶላር ማስመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ አብዛኛው ከቻይና ወደ አፍሪካ የሚገቡ ሸቀጦች የሚሸፍኑት መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ 

በኢትዮጵያ ቻይናውያን ያስመዘገቡት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በሚመለከት የዓለም ባንክ ካቻምና አካሂዶት በነበረው ጥናት መሠረት፣ እ.ኤ.አ. ከ2004 እስከ 2011 ባለው ጊዜ ውስጥ ከቻይና ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣው ኢንቨስትመንት በየዓመቱ በአማካይ የ58 ሚሊዮን ዶላር ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ይህም ቢባል ግን የቻይና ኩባንያዎች በመንግሥት የታክስና ጉምሩክ አስተዳደር የሚታዩ ውጣ ውረዶች፣ በውጭ ምንዛሪ በኩል መንግሥት ግልጽነት አለማሳየቱን፣ በሠራተኛ ሕግ፣ በሠለጠነ የሰው ኃይል አቅርቦትና በመሳሰሉት መስኮች ላይ ችግሮች እያጋጠሟቸው እንደሚገኙ የዓለም ባንክ በጥናቱ አሳይቷል፡፡ 

በሰው ጉልበት ዋጋ መወደድና በማምረቻ ወጪዎች ከፍተኛነት ሳቢያ ከቻይና እየነቀሉ ወደ አፍሪካ የሚመጡ የቻይና ኩባያዎች እንደሚበራከቱ ከሰባት ዓመት በፊት ጀምሮ ሲነገር ነበር፡፡ በዚህ መስክ ኢትዮጵያ መጠቀም አለባት በማለት ደጋግመው ሲናገሩ እንደነበር የሚታወሱት ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ናቸው፡፡ ሆኖም የተገመተውን ያህል ግን በርካታ የቻይና ኩባንያዎች ሳይመጡ ቀርተዋል፡፡ ይህንን በሚመለከት ሪፖርተር ያነጋገራቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ልዩ ረዳት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ አገሪቱ ይህንን ዕድል ለመጠቀም በሚያስችላት ደረጃ ዝግጁ እንዳልነበረች ገልጸዋል፡፡ ይህም ሆኖ በአሁኑ ወቅት በኢንዱስትሪ ፓርኮች አማካይነት የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችንና ሌሎች እንደ ጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ያሉ አገልግሎቶችን በፋብሪካዎቻቸው ደጅ ማግኘት የሚችሉበት ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቅሰዋል፡፡ 

በአፍሪካ ኢንቨስት ስለማድረግ በዝግ እየመከረ የሚገኘው ጉባዔም መሠረታዊ በሚባሉ ችግሮች ላይ ከመነጋገር ባሻገር፣ በአፍሪካ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ረገድ አዳዲስ ስምምነቶች ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሌሎችም የመሠረተ ልማት መስኮች ላይ የቻይና መንግሥት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአፍሪካ አገሮች የሚደረጉ አዳዲስ ብድሮችንና የፋይናንስ ድጋፎችን ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ 

በአፍሪካ የዓለም ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ማክታር ዲዮፕ እንዳስታወቁት፣ በአፍሪካ በየዓመቱ የ90 ቢሊዮን ዶላር የመሠረተ ልማት ግንባታ ፍላጎት ቢኖርም፣ የአፍሪካ አገሮች ኢንቨስት ማድረግ የቻሉት ግን ከ20 ቢሊዮን ዶላር ያልዘለለ ነው፡፡ ይህንን በመንተራስ የቻይና ኩባንያዎች በቋሚ ንብረቶች ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው፣ የቻይና የፋይናንስ ተቋማትም አስፈላጊውን ፋይናንስ ለማቅረብ ፍላጎት እንዳላቸው ታውቋል፡፡ 

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርን ጨምሮ የዓለም ባንክ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) እንዲሁም የቻይና መንግሥት ያዘጋጁት ይህ ፎረም፣ በየዓመቱ በአፍሪካና በቻይና እየተፈራረቀ በቋሚነት እንዲካሄድ ስምምነት መደረጉን የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አህመድ ሺዴ አስታውቀዋል፡፡ 

 

 

  

 

ኤጀንሲው 31 ሺሕ ያህሉ ከፍለው መዋዋላቸውን አስታውቋል

-የተዋዋሉት ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍለዋል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለአሥረኛ ጊዜ ባወጣው የኮንዶሚኒየም ቤት ዕጣ ዕድለኛ ከሆኑ የከተማው ነዋሪዎች መካከል አራት ሺሕ ተመዝጋቢዎች ለክፍያ ይጠበቃሉ፡፡

ክፍያቸውን በሁለት ሳምንት ውስጥ ካላጠናቀቁ ቤቶቹን እንደማያገኙ ተገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ ዕጣ ከወጣላቸው 35 ሺሕ ዕድለኞች ውስጥ 31 ሺሕ ያህሉ ውል መፈጸማቸውን አስታውቋል፡፡

ዕጣው ከደረሳቸው መካከል 31 ሺሕ ያህሉ ውል ተዋውለው መጨረሳቸውንና ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ቅድመ ክፍያ መፈጸሙን አስታውቋል፡፡ ቀሪዎቹ ዕድለኞችም እስከ ሐምሌ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ውላቸውን ፈጽመው መጨረስ እንዳለባቸው አሳስቧል፡፡ ውል የመፈጸሚያ ጊዜው ካለፋቸው ቤቱን እንደማያገኙም አስታውቋል፡፡ 

መክፈል ያልቻሉ ዕጣው የወጣላቸው ዕድለኞች ደግሞ ቅድመ ክፍያ (ሃያ በመቶውን) ለመክፈል ከፍተኛ ችግር ውስጥ መግባታቸውን ይናገራሉ፡፡ ብዙዎቹ በብድርና በተለያዩ ወገኖች ድጋፍ ሊከፍሉ መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡ ከአቅማቸው በላይ የሆነ ኪራይ እየከፈሉ መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ ለደረሳቸው ኮንዶሚኒየምና ለሚኖሩበት የቤት ኪራይ በየወሩ መክፈል ስለማይችሉ፣ ክፍያውን በሁለት ሳምንት አጠናቁ በመባላቸው ከወዲሁ ሥጋት ገብቷቸዋል፡፡ 

አራት ኪሎ፣ ልደታና ለመሀል ከተማው ቀርበው በተሠሩ ኮንዶሚንየም ቤቶች የደረሳቸው ዕድለኞች፣ ኮንዶሚኒየም ቤቱ ባይፀዳ እንኳን ገብተው ለኪራይ የሚከፍሉትን እየከፈሉ እንደሚኖሩ የገለጹት ዕድለኞቹ፣ ከመሀል ከተማው በ10 እና በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የደረሳቸው ግን ግራ እንደተጋቡ ተናግረዋል፡፡ 

ቤቶቹ የተገነቡት አገር ውስጥ በተመረቱ የግንባታ ግብዓቶች በመሆኑ ቅናሽ እንዲደረግላቸው የሚጠይቁት ነዋሪዎቹ፣ የመሠረተ ልማት ባልተሟላባቸው አካባቢዎች ዕጣ የደረሳቸው በኮንዶሚኒየም ቤቶቹ አካባቢ ትምህርት ቤቶች እስከሚከፈቱና ትራንስፖርት ተሟልቶ እስከሚገባ ድረስ፣ የባንክ ክፍያ መጀመሪያው ጊዜ እንዲያራዝምላቸው ጠይቀዋል፡፡ በተለይ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ያለፉና በመሰናዶ ትምህርት ቤት የተመደቡ ልጆቻቸውን እንዴት አጓጉዘው ማስተማር እንደሚችሉ ሥጋት ውስጥ እንደከተታቸው ተናግረዋል፡፡ 

በሌላ በኩል ዕጣ የወጣላቸው የተወሰኑ ዕድለኞች ቅድሚያ ክፍያ የሚከፍሉት አጥተው በየመሥሪያ ቤቱ፣ በካፌ፣ በሬስቶራንትና በመዝናኛ ቦታዎች በመገኘት እውነቱን እየተናገሩ ዕርዳታ እየጠየቁ መሆኑ ታውቋል፡፡ ሪፖርተር ያነጋገራቸው አንዳንዶቹ ዕድለኞች ከአሥር ዓመታት ቆይታ በኋላ የደረሳቸው ዕድል መሆኑን ገልጸው፣ ይህ ዕድል ካመለጣቸው ዳግመኛ ስለማያገኙት ኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸውን ዕርዳታ በመጠየቅ ለማሟላት እየተሯሯጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በልመና ምን ያህሉን መሸፈን እንደሚችሉ አለማወቃቸውን የሚናገሩት ዕድለኞቹ፣ እስከ መጨረሻው ቀን ድረስ የቻሉትን ጥረት አድርገው ካልሞላላቸው ምንም ማድረግ ስለማይችሉ ሳይወዱ በግድ እንደሚተውት ተናግረዋል፡፡

የቤቶች ልማት አስተዳደር ኤጀንሲ ግን ቤቶቹን ለማዋዋል የተቀመጠው ቀነ ገደብ ሐምሌ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ስለሚያበቃ፣ በአስቸኳይ መዋዋሉን እንዲያጠናቅቁ አስታውቋል፡፡ የዕጣ ዕድለኞች የሆኑት አራት ሺሕ ያህል ግለሰቦች በተቀመጠው ቀነ ገደብ ውስጥ የማያጠናቅቁ ከሆነ ቤቶቹን እንደማያገኙ ገልጿል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በተለይ በአሥረኛው ዙር ዕጣ የወጣባቸው ኮንዶሚኒየም ቤቶች ዋጋ በመጋነኑ ምክንያት፣ ልዩ ኮሚቴ አቋቁሞ የዋጋውን ሁኔታ ማጥናት መጀመሩ የታወቀ ቢሆንም፣ አሁን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡   

 

ከአዲስ አበባ እስከ ጂቡቲ ወደብ ድረስ የተዘረጋው የባቡር መስመር ጥቅምት 2008 ዓ.ም. ሥራ የሚጀምር ቢሆንም፣ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያበረክት የሚችለውን ነዳጅ ለማጓጓዝ፣ የሚያስፈልገው የመሠረተ ልማት ቀደም ብሎ አለመጠናቀቁ አለመግባባት ፈጠረ፡፡ 

ኢትዮጵያ የምትጠቀመው አብዛኛው ነዳጅ የሚገባው በጂቡቲ በኩል ሲሆን የሚጫነውም ከሆራይዘን ተርሚናል ነው፡፡ ነገር ግን የተገነባው የባቡር መስመር ቀጥታ ወደ ጂቡቲ ወደብ የሚያመራ ነው፡፡ የአገሪቱ ነዳጅ ወደሚጫንበት ሆራይዘን ተርሚናል የባቡር ሐዲድ አለመገንባቱ አለመግባባት መፍጠሩን የሪፖርተር ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 

ከሆራይዘን ተርሚናል ባቡሩ ነዳጅ ቢጭን እንኳን የተጫነው ነዳጅ ኢትዮጵያ ከደረሰ በኋላ የሚያራግፍበት ዲፖ አለመገንባቱ ሌላ ችግር እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ጉዳዩ ላይ የበለጠ አለመግባባት የፈጠረው የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ የትራንስፖርትና የዕቃ ማጓጓዣ ባቡሮችን እንዲያመርት ከቻይናው ኩባንያ ኖሪንኮ ጋር አስቀድሞ ውል መግባቱ ነው፡፡ ኖሪንኮ በበኩሉ ከአገር በቀሉ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር በገባው ውል መሠረት ከ50 በላይ የሚሆኑ የነዳጅ ማመላለሻ ባቡር ፉርጎዎች ተመርተው ለሥራ ዝግጁ መሆናቸውን እየገለጸ ነው፡፡ 

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የእሳቸው ኩባንያ ከውጭ ነዳጅ ገዝቶ ጂቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ያራግፋል፡፡ ከዚህ በኋላ የነዳጅ ኩባንያዎች በተሽከርካሪዎች ለአገር ውስጥ ገበያ ያቀርባሉ፡፡ ነገር ግን ነዳጅን በባቡር ለማጓጓዝ ወደ ሆራይዘን ተርሚናል የሚጓዝ የባቡር ሐዲድ አልተገነባም፡፡ በአገር ውስጥም ማጠራቀሚያ ዲፖ አልተገነባም፡፡ ‹‹ጉዳዩ በደንብ መታየት ነበረበት፡፡ ትንሽ ክፍተት አለው፤›› በማለት አቶ ታደሰ የጉዳዩን አሳሳቢነት ገልጸዋል፡፡ 

ይህ ጉዳይ ክፍተት እንዳለው ዘግይቶ የተገነዘበው ትራንስፖርት ሚኒስቴር አጀንዳ ቀርጾ መሠረተ ልማት ለማሟላት ውይይት ማካሄድ መጀመሩ ታውቋል፡፡ 

ትራንስፖርት ሚኒስቴር፣ በሥሩ የሚገኘውን ትራንስፖርት ባለሥልጣን፣ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ኢንተርፕራይዝንና አሥሩን ነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች በማሰባሰብ በመፍትሔ ሐሳቦች ላይ እየተነጋገረ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

በዋናነት የቀረበው መፍትሔ ከጂቡቲ ወደብ ወደ ሆራይዘን ተርሚናል የሚወስድ የባቡር ሐዲድ መዘርጋትና በሆራይዘን ተርሚናል ባቡሮቹ ነዳጅ የሚጭኑባቸውን መሣሪያዎች ማሟላት ነው፡፡

በአገር ውስጥ ደግሞ አዲስ አበባ (ሰበታ) አካባቢ በሚገኘው ግዙፍ የባቡር ተርሚናል ውስጥ የነዳጅ ማራገፊያ ዲፖ መገንባት ዋነኛ ጉዳይ ሆኗል፡፡ በአሁኑ ወቅት እነዚህ ጉዳዮች በውይይት ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ ግንባታዎቹን ለማካሄድ የበጀት ጉዳይ ቀጣዩ መነጋገሪያ ይሆናል ተብሏል፡፡ 

ምንጮች እንደገለጹት፣ በጀት ተወስኖ የግንባታ ቦታ ከተዘጋጀ ግንባታው ከሁለት እስከ ሦስት ዓመት የሚፈጅ በመሆኑ፣ በባቡር መሠረተ ልማት ነዳጅ ለማመላለስ ረዥም ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡ ይህ ፕሮግራም ቀድሞ ባለመታሰቡ ብቻ የተገነባው የባቡር መሠረተ ልማት ላልተወሰነ ጊዜ ነዳጅ ከማመላለስ ውጪ ይሆናል፡፡

በጂቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ነዳጅ በተሽከርካሪ የሚያቀርቡ ኩባንያዎች አሥር ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ በወር በ250 ሚሊዮን ዶላር ወጪ በሚያቀርበው ነዳጅ ትልቅ ድርሻ ያላቸው ኖክ፣ ቶታል፣ ኦይል ሊቢያና የተባበሩት ናቸው፡፡ እነዚህና ሌሎች ስድስት ኩባንያዎች በመላው አገሪቱ ባላቸው ከ250 በላይ ነዳጅ ማደያዎች አማካይነት ነዳጅ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ 

ሰበታ አካባቢ የነዳጅ ዲፖ እንደሚገነባ የሚጠበቀው በግል ኩባንያዎቹ ሲሆን፣ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከጂቡቲ ነዳጅ እያጓጓዙ በዲፖው የማራገፍ ኃላፊነት እንዳለበት ይጠበቃል፡፡ ኩባንያዎቹ ደግሞ በተሽከርካሪዎች ወደ ነዳጅ ማደያዎች ያደርሳሉ በሚለው ዕቅድ ላይ ውይይት እየተካሄደ መሆኑም ታውቋል፡፡ 

ከአዲስ አበባ (ሰበታ) እስከ ጂቡቲ ወደብ ድረስ የተዘረጋው የባቡር መስመር 656 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው፡፡ መስመሩ እስከ አዳማ ድረስ ሁለት ባቡሮች በአንዴ የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ከአዳማ እስከ ጂቡቲ ድረስ ደግሞ አንድ መስመር ይኖረዋል፡፡

የባቡር መስመሩ ለመንገደኞችና ለዕቃ አገልግሎት የሚሰጥ በመሆኑ የትራንስፖርት ወጪን በ50 በመቶ ይቀንሳል ተብሏል፡፡ በሁለት የቻይና ኩባንያዎች እየተገነባ ያለው ይህ የባቡር መስመር የሐዲድ ማንጠፍ ሥራው የተጠናቀቀ በመሆኑ፣ በመጪው ጥቅምት አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሏል፡፡ ነዳጅ ለማጓጓዝ በተፈጠረው ክፍተት ላይ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ጌታቸው በኩረ አስተያየት እንዲሰጡ የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡  

 

ከ123 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣበት የአፍሪካ የሰላም ማዕከል በአዲስ አበባ ተገነባ

ለአፍሪካ ሰላምና ደኅንነት እንቅስቃሴዎች ድጋፍ እንዲሰጥ ታስቦ በአዲስ አበባ የተገነባውና ከ123 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣበት የሰላም ማዕከል፣ ሰኔ 20 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመርቆ ተከፈተ፡፡ 

ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ መርቀው የከፈቱት ይኼ የደኅንነት ተቋም፣ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ግጭትን ለመፍታት ለሚደረጉ የሰላም ማስከበር ጥረቶች አስፈላጊ የሥልጠናና የጥናት ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል ታስቦ የተገነባ ነው፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት፣ የተሳካ ሰላም የማስከበር ሥራዎች ለማከናወን ማዕከሉ ትልቁ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ማዕከሉን አስመልክተው ሲናገሩ፣ ‹‹የሰላም ማዕከሉ ወታደራዊና የሰላም አስከባሪ ተቋማት ዓላማቸውን በተሳካ ሁኔታ እንዲወጡ የምርምርና የሥልጠና አገልግሎት በመስጠት የሰላም ማስከበር ሥራዎች ማዕከል ሆኖ ያገለግላል፤›› ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ውጪ ሰላምና ደኅንነት ከማስጠበቅ አንፃር ላደረገው አስተዋጽኦ አድናቆታቸውን ለመከላከያ ሚኒስቴር የቸሩት ፕሬዚዳንት ሙላቱ፣ የአገሪቱ መረጋጋትና የኢኮኖሚ ዕድገት ምክንያት ኢትዮጵያ በአካባቢው የሰላምና የፀጥታ ተምሳሌት መሆን በመቻሏ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡ 

የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ በበኩላቸው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃም ኢትዮጵያ ሰላምን በማስከበር ሥራዎች የማይተካ ሚና እየተጫወተች እንደምትገኝ ገልጸው፣ ማዕከሉ ይህንን ጥረት በዕውቀትና በምርምር ለመደገፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡

በአዲስ አበባ የተገነባው ይኼው የሰላም ማዕከል ግጭትን ለመከላከል፣ ዕርቅ ለመፍጠርና ሰላም ለማስከበር ለአካባቢውና ለመላው አፍሪካ ጥቅም ይውል ዘንድ፣ በተለይ ከአፍሪካ ኅብረትና ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ጋር በትብብር እንደሚሠራ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታ ማጆር ሹም ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስን ጨምሮ፣ በርካታ የመከላከያና የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በክብር እንግድነት ተገኝተዋል፡፡    

 

የአይኤስ አሸባሪ ቡድን ሊቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ በፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ምክንያት መንግሥት በጠራው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ረብሻ በመፍጠር ተከሰው የተፈረደባቸው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት፣

የእስር ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ ከማረሚያ ቤት በራፍ ላይ ተይዘው ከተመሠረተባቸው ክስ በዋስ እንዲለቀቁ ብይን ተሰጠ፡፡

የፓርቲው አባላት ሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም. እያንዳንዳቸው በ5,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቄራ ምድብ ችሎት ብይን የሰጠው በወይንሸት ሞላ፣ በኤርሚያስ ፀጋዬ፣ በዳንኤል ተስፋዬና በቤተልሔም አካለ ወርቅ ላይ ነው፡፡

በተከሳሾቹ ላይ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ፍርድ ተሰጥቶ የነበረው፣ ሰላማዊ ሠልፉን በማወክ የተለያዩ ስድቦችን መንግሥትንና ዜጎችን በመሳደብ፣ ሥርዓቱን በማንጓጠጥና በፖሊስ አባላት ላይ ድንጋይ በመወርወር ወንጀል ተከሰው ነው፡፡

ፍርደኞቹ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፍርድ በቀረቡበት ዕለት ሁለት ወር ከአንድ ቀን በእስር መቆየታቸው በመረጋገጡ፣ በዕለቱ ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆንም ፖሊስ ሌላ ወንጀል መፈጸማቸውን በመግለጽ፣ ሰኔ 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ከእስር ተፈትተው ወደ ቤታቸው ለማምራት ማረሚያ ቤት ደጃፍ ላይ ሲደርሱ ተይዘው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡

ፖሊስ ለፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ፣ ተከሳሾቹ ቀደም ብሎ በተከሰሱበት ወንጀል ላይ በምስክርነት ያቀረባቸውን ማስፈራራታቸውንና መዛታቸውን በመግለጽ ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ክሱን ተቀብሎ ለሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም. መዛታቸውን የሚያስረዱለትን ምስክሮቹን እንዲያቀርብ ቀጠሮ የሰጠ ቢሆንም፣ ፖሊስ ምስክሮቹን በተለያዩ ምክንያቶች ሊያቀርብ አለመቻሉን ገልጾ፣ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል፡፡ 

ተከሳሾቹ ግን ፖሊስ ምስክሮቹን በተሰጠው ቀጠሮ ቀን ማቅረብ እንደነበረበት ገልጸው፣ ፍርድ ቤቱ ዋስትና እንዲፈቅድላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ጥያቄውን ተቀብሎ እያንዳንዳቸው በ5,000 ብር ዋስ እንዲለቀቁ ፈቅዷል፡፡ በሌላ በኩል ተከሳሾቹ ቀደም ብሎ ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ሁለት ወራት ተፈርዶባቸው በነበረውና እስራቸውን ጨርሰው በወጡበት ክስ፣ ዓቃቤ ሕግ ይግባኝ እንዳለባቸውና ሰኔ 24 ቀን 2007 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ ተጠቁሟል፡፡

 

አፍሪካ ከእስያ አገሮች ትልቅ ፉክክር ይጠብቃታል  

የአሜሪካና የአፍሪካ የእርስ በርስ የኢኮኖሚ ግንኙነት ላይ ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበት ላለፉት 15 ዓመታት ሲተገበር የቆየውን ከታሪፍና ከኮታ ነፃ የገበያ ዕድል፣ ለተጨማሪ አሥር ዓመታት ማራዘሙን የአሜሪካ ኮንግረስ ይፋ አደረገ፡፡ 

ከታሪፍና ከኮታ ነፃ የገበያ ዕድል ወይም ‹‹አፍሪካ ግሮውዝ ኤንድ ኦፖርቹኒቲ አክት – አጎዋ›› ሚያዝያ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. በአምባሳደር ማይክል ፍሮማንና አምባሳደር ሱዛን ራይስ በኩል ቀርቦለት ሲመክር የከረመው ሕግ መወሰኛው ምክር ቤት፣ ለመጪዎቹ አሥር ዓመታት እንዲራዘም ይፋ ያደረገው አጎዋ እንደከዚህ በፊቱ ሳይሆን በእስያ አገሮች ዘንድ ፈተና እንደሚገጥመው እየተነገረለት ነው፡፡ አምባሳደር ፍሮማን የአሜሪካ የንግድ ዘርፍ ተወካይ ሲሆኑ፣ የቀድሞዋ የአሜሪካ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር አምባሳደር ሱዛን ራይስ በአሁኑ ወቅት የአሜሪካ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ናቸው፡፡ በአምባሳደሮቹ የቀረበው የአጎዋ ረቂቅ ሕግ ለአሥር ዓመታት የሚራዘም ከሆነ ከ30 በላይ ለሚሆኑ የአፍሪካ አገሮች ትልቅ እፎይታ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በኮንግሬሱ ተቀባይነት አግኝቶ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በፊርማቸው እንዲያፀድቁት መርቶታል፡፡ 

እ.ኤ.አ. በ2009 ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በጋና ተገኝተው አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትስስር የማጠናከር አስፈላጊነት ሲገልጹ፣ ‹‹ለልጆቻችን ማውረስ የምንፈልገውን ዓለም በመቅረፅ ረገድ አፍሪካ የአሜሪካ አጋር ነች፡፡ አጋርነታችንም በጋራ ኃላፊነትና በመከባበር ላይ የተመሠረተ መሆን ይኖርበታል፤›› ብለው ነበር፡፡ ባለፈው ዓመት የአፍሪካና የአሜሪካ የመሪዎች ጉባዔ በተካሄደበት ወቅት፣ ፕሬዚዳንቱ የአፍሪካ የዕድገትና የገበያ ዕድል የሚያበቃበት ጊዜ ማለትም የመጪው ዓመት መስከረም ወር ደርሶ ከመጠናቀቁ በፊት፣ የጊዜ ገደቡ እንዲራዘም ኮንግረሱን መጠየቃቸውም ይታወሳል፡፡ በዚህ መሠረት አጎዋ እንዲራዘም መጠየቅ ብቻ ሳይሆን፣ ማሻሻያዎች ተደርገውበት የበለጠ ውጤታማ የሚሆንበት መንገድ እንዲመቻች ሲጠየቅ እንደቆየ አይዘነጋም፡፡

ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ዕድገትና የገበያ ዕድል ለመፍጠር በሚል መነሻ እ.ኤ.አ. በ2000 ሕግ ሆኖ የፀደቀው አጎዋ፣ በአሜሪካና በአፍሪካ መካከል እያደገ ስለመምጣቱ ለሚነገርለት አጋርነት መጠናከር አስተዋጽኦ ማድረጉን በማስረጃ ደፍገው የሚያቀርቡት የአሜሪካ ባለሥልጣናት ብቻ አይደሉም፡፡ አፍሪካውያንም ይጠቀሳሉ፡፡ በአፍሪካ ወሳኝ የልማትና የዕድገት መርሐ ግብሮች እንዲከናወኑ፣ የተለያዩ የአኅጉሪቱ ቀጣናዎች የኢኮኖሚ ጥምረት እንዲፈጥሩ፣ ኩባንያዎች ተወዳዳሪ እንዲሆኑና የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ለሚያደርገው የካፒታልና የኢንቨስትመንት ፍሰት ምቹነትን በመፍጠር በኩል ሚናው አሌ እንደማይባል የሚገልጹ አሉ፡፡  

በአልባሳት ንግድ ዘርፍ ከተሰማሩ ተቋማት በተገኘ መረጃ መሠረት ከነዳጅ መስክ ውጭ ያለው የወጪ ንግድ፣ መርሐ ግብሩ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ በቀጥታ ወደ 350,000 ለሚቆጠሩ ሰዎች የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር፣ በተዘዋዋሪም ሌሎች በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩትን በማገዝ ዘርፉን በሦስት እጥፍ አሳድጎታል፡፡ 

የአፍሪካን ልማት ከመደገፍ ባሻገር አጎዋ ለአሜሪካ ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎችንም አስገኝቷል፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2000 ጀምሮ አሜሪካ ከሰሃራ በታች ወዳሉት አገሮች የምትልካቸው ሸቀጦች መጠን ይበልጥ እየጨመረ መምጣቱን የሚያመላክቱ ክስተቶች በአፍሪካ እየታዩ ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ያለው የኅብረተሰብ ክፍል እያደገ መጥቶ ከሩብ ቢሊዮን በላይ እንደሚደርስ የኢኮኖሚ ትንበያዎች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም በአሜሪካ የተመረቱ ሸቀጦችን የመሸመት አቅማቸው በማደጉ፣ የሸቀጦች ወጪ ንግድ መጠን በሦስት እጥፍ ሊጨምር ችሏል፡፡ በአፍሪካ የሚገኙ የንግድ ተቋማት የአሜሪካ ግብዓቶች፣ ዕውቀት፣ ክህሎትና አጋርነት አስፈልጓቸዋል፡፡ አሜሪካ በአፍሪካ የምታደርገው የኢንቨስትመንት ፍሰት፣ በአፍሪካም ሆነ በአሜሪካ ለሚገኙ ሠራተኞች የሥራ ዕድሎችን ከመፍጠሩም በላይ፣ ገቢያቸው እንዲያድግ ምክንያት ሆኗል፡፡ 

አሜሪካ በአጎዋ በኩል ከአፍሪካ ጋር የምታደርገውን የንግድ ልውውጥ እንዳፋጠነ የሚነገርለት ቢሆንም፣ አብዛኞቹ የአፍሪካ አገሮች ግን ተጠቃሚ ሳይሆኑበት እንደቀረ ይታወቃል፡፡ በግብርና ውጤቶች፣ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳና የቆዳ ውጤቶች አኳያ ተጠቃሚ መሆን ከሚገባቸው አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ እንደነበረች ይታመናል፡፡ ቢሆንም በአጎዋ በኩል አገሪቱ ከቀረጥና ከኮታ ነፃ ወደ አሜሪካ የላከቻቸው ምርቶች መጠን እጅግ ዝቅተኛ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ 

ኢትዮጵያ ባለፉት አሥራ አምስት ዓመታት ውስጥ በአጎዋ በኩል ከላከቻቸው ምርቶች በአማካይ በዓመት ከ40 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማግኘት አልቻለችም፡፡ ከሪፖርተር ጋር ቆይታ ያደረጉት የአሜሪካ ከፍተኛ የንግድ ባለሙያና በኢትዮጵያ የአሜሪካ የውጭ ንግድ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ታንያ ኮል እንዳስታወቁት፣ አሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ በአጎዋ በኩል ከምትልካቸው ምርቶች ቦይንግ አውሮፕላንን ጨምሮ በዚህ ዓመት ብቻ ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ስታገኝ፣ ኢትዮጵያ ግን ከ225.6 ሚሊዮን ዶላር የዘለለ ገቢ አላገኘችም፡፡ በመሆኑም ምርቶችን በገፍ ማምረትም ሆነ ወደ አሜሪካ መላክ ፈተና ሆኖ ይገኛል፡፡ ለሚቀጥሉት አሥር ዓመታት አጎዋ በመራዘሙ ግን እየተስፋፉ ያሉት የቆዳና የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ትልቅ የገበያ ዕድል እንደሚያገኙ ይጠበቃል፡፡ በአንፃሩ አሜሪካ ከታሪፍና ከኮታ ነፃ የገበያ ዕድል ለእስያ አገሮች ‹‹ትራንስ ፓስፊክ ፓርትነርሺፕ›› በተሰኘው ማዕቀፍ ውስጥ ተመሳሳይ የነፃ ገበያ ዕድል መስጠቷ ግን በርካታ ጨርቃ ጨርቅ አምራቾችን ሥጋት ውስጥ የጣለና የአፍሪካን የተወዳዳሪነት አቅም የሚፈታተን ተብሎለታል፡፡ የሥጋቱ ምክንያት ደግሞ በእስያ አገሮች ውስጥ የማምረቻ ወጪዎች ከአፍሪካ ይልቅ ዝቅተኛ መሆናቸው ነው፡፡ 

 

የዶ/ር አርከበ ዕቁባይ አዲስ መጽሐፍ ለኢትዮጵያ ገበያ ቀረበ

ዋጋው በጣም ውድ ነው ተብሏል

ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ ‹‹ሜድ ኢን አፍሪካ ኢንዱስትሪያል ፖሊሲ ኢን ኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ ያሳተሙት አዲስ መጽሐፍ፣ በኢትዮጵያ ገበያ ቀረበ፡፡

መጽሐፉ በዓለም ገበያ ግንቦት 19 ቀን 2007 ዓ.ም. የቀረበ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በቡክ ወርልድ አማካይነት ገበያውን ተቀላቅሏል፡፡

ዋቢና ኢንዴክስን ጨምሮ 348 ገጽ ያለው ይህ የዶ/ር አርከበ ዕቁባይ መጽሐፍ፣ ከአፍሪካ አጠቃላይ ሁኔታ በመነሳት የኢትዮጵያን ኢንዱስትሪ በጥልቀት ይተነትናል፡፡

ዶ/ር አርከበ ለዚህ መጽሐፍ መነሻ የሆናቸው በለንደን ስኩል ኦፍ ኦርየንታል ኤንድ አፍሪካን ስተዲስ ለተከታተሉት የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ያቀረቡት ጽሑፍ ነው፡፡

ዶ/ር አርከበ በአራት ዓመት የሚጠናቀቀውን ትምህርታቸውን በዩኒቨርሲቲው ባልተለመደ ሁኔታ በ23 ወራት ውስጥ በከፍተኛ ማዕረግ በማጠናቀቃቸው፣ በወቅቱ ከፍተኛ አድናቆትን ተችሯቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡

የተመረቁበትን ዴቨሎፕመንት ስተዲስ የዶክትሬት ዲግሪ የጥናት ጽሑፍ በማስፋት በመጽሐፍ መልክ ያዘጋጁት ሲሆን፣ የተማሩበት ለንደን ስኩል ኦፍ ኦርየንታል ስተዲስ ይኼንን መጽሐፍ እንዲታተም ለኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ልኮታል፡፡

ለዶ/ር አርከበ ቅርበት ያላቸው የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ ዶ/ር አርከበ ይኼንን መጽሐፍ ያዘጋጁት በዘርፉ ጥልቅ ጥናት አካሂደው ነው፡፡

ዶ/ር አርከበ መጽሐፉን ለማዘጋጀት በ150 ኩባንያዎች ላይ ጥልቅ ጥናት ማድረጋቸው፣ ሃምሳ ፋብሪካዎችን በአካል በመገኘት ማጥናታቸው፣ ለዚሁ ጽሑፍ 250 ጥያቄዎችን በማዘጋጀት ከፋብሪካዎች መረጃ እንደሰበሰቡና ከሁለት እስከ አራት ሰዓት የፈጁ 200 ቃለ መጠይቆችን ማድረጋቸው ተሰምቷል፡፡ ለኢንዱስትሪ ልማት ማነቆ ናቸው የተባሉ ችግሮችን ለመለየት በውጭና በአገር ውስጥ የሚገኙ ፋብሪካዎች ላይ ጥናት ማድረጋቸው እንዲሁ ተነግሯል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች ጥናቶች መረጃ ሆነው ያልቀረቡ አንድ ሺሕ ሰነዶችን በማገላበጥ የተሟላ ጥናት ማድረጋቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ይህ አጠቃላይ ጥናት አራት ዓመት የፈጀ መሆኑም ተገልጿል፡፡

ይህ የዶ/ር አርከበ መጽሐፍ የተወሳሰቡ የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ሐሳቦችን በጥልቅ አረዳድ የተነተነ ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ገልጸዋል፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ‹‹ጸሐፊው በንድፈ ሐሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ ልምዳቸውና በፖሊሲ ቀረፃ የረዥም ጊዜ ልምድ ስላላቸው ነው፤›› በማለት የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር ሀ ጁን ቻንግ ለመጽሐፉ ያላቸውን አድናቆት በመጽሐፉ ላይ ገልጸዋል፡፡ 

የቀድሞ የዓለም ባንክ ዋና ኢኮኖሚስት ጀስቲን ይፋ ሊን በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ በልማት ተዓምር እየፈጠረች በመሆኑ ለአፍሪካ አገሮች መነቃቃት፣ በራስ መተማመንና መልካም ተሞክሮ ማካፈል ትችላለች ያሉ ሲሆን፣ ዶ/ር አርከበ ይኼን ለውጥ በመጽሐፉ በግሩም ሁኔታ እንደተረኩት መስክረዋል፡፡ ጃፓን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ለምሥራቅ እስያ አገሮች ምሳሌ እንደሆነችው ሁሉ፣ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አገሮች ተመሳሳይ አስተዋጽኦ ማበርከት ትችላለች ብለዋል፡፡ መጽሐፉ ኢትዮጵያ ዕድገቷን እንዴት እያፋጠነችና ባለሁለት አኃዝ ዕድገት እያስመዘገበች እንደመጣች፣ ጥልቅ ግንዛቤ ይሰጣል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ 

መጽሐፉ በእንግሊዝ ገበያ ውስጥ 55 ፓውንድ ሲሸጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ 1,815 ብር በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡

ከቡክ ወርልድ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፣ የመጽሐፉ ዋጋ መወደዱን ከተለያዩ አቅጣጫዎች አስተያየት እየተሰጠበት ነው፡፡ መጽሐፉ ሊወደድ የቻለው ሐርድ ከቨር ያለውና ደረጃውን ጠብቆ በመታተሙ፣ እንዲሁም በጣም የተለፋበት በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡

መጽሐፉ በዋነኛነት ትኩረት የሚያደርገው በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት መሄድ ባለባቸው አቅጣጫዎች ላይ ነው፡፡ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍን ማሳደግ ለግብርና የላቀ ዕድገት ወሳኝ መሆኑም ተተንትኗል፡፡

ዶ/ር አርከበ በመጽሐፉ መግቢያ ላይ እንደጠቀሱት፣ በመጽሐፉ ያንፀባረቋቸው ምልከታዎች የመንግሥትንም ሆነ አብረዋቸው እየሠሩባቸው ወይም የሠሩባቸው ተቋማትን አይወክሉም፡፡ የመጽሐፉ ዋናው ዓላማ የተለያዩ ምልከታዎች፣ ልምዶችና ተግዳሮቶችን ለማቅረብ ለተጨማሪ ጥናትና ውይይት መጋበዝ መሆኑም ተገልጿል፡፡

 

ሁለት የአላባማ ካውንቲ ፍርድ ቤቶች ውሳኔውን ውድቅ በማድረግ ምንም አይነት የተመሳሳይ ጋብቻ የምስክር ወረቀት የማይሰጡ መሆናቸውን ገልጸው ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ዳግም እንዲያጤነው ጠይቀዋል። ከዚህም በተጨማሪ የቴክሳስ ከፍተኛ አተርኒ ተመሳሳይ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን በግለሰብ ነጻነት ስም ሰዎች ሰብአዊ ክብራቸውን እንዲያዋርዱ መፍቀድ የለብንም የሚሉ አሜሪካውያን በየግዛቱ ተቃውሞ በማሰማት ላይ ናቸው። አንድ ታዋቂ የቤተክርስትያን ፓስተር በበኩላቸው በሚያገለግሉበት […]

ሰኔ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ዲያስፖራውን በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች ለመያዝ ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት መክሸፉን ተከትሎ ፣ የዲያስፖራውን ቀልብ ሊስቡ ይችላሉ ያላቸውን አዳዲስ ዘዴዎች እያሰላሰለ ነው። በቅርቡ በኢትዮጵያ በሚካሄደው የዲያስፖራ ሳምንት ዝግጅት ዙሪያ አስመልክቶ ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዲያስፖራ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በክልልና በፌደራል ደረጃ ከሚገኙ የዲያስፖራ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ሃላፊዎች …

ሰኔ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ወንጀል አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ለመኢአድ አባላት መከላከያ ምስክር መሆን መቻል አለመቻላቸው ላይ ነገ ሰኔ 24፣ 2007 ዓ.ም ብይን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ በግንቦት ሰባት አባልነት የተከሰሱት 5 የመኢአድ አባላት ‹‹በአንዳርጋቸው ፅጌ አሰልጣኝነት የሽብር ተግባር ለመፈፀም ተንቀሳቅሳችኋል፡፡›› በሚል ክስ …

ሰኔ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለሚቀጥለው አምስት አመታት ይተገበራል ተብሎ በተዘጋጀ የሁለተኛ ዙር የ5 አመታት እቅድ ላይ በተዘጋጀ የመወያያ ሰነድ እንደተመለከተው ባለፉት ሶስት አመታት 2 ሺ 995 ፕሮጀክቶች ወደ አገር ውስጥ ገብተው ስኬታማ ሳይሆኑ በመቅረታቸው ተሰርዘዋል። በአማራ ክልል በባህርዳር እንዲሁም በኦሮምያ ክልል አዳማ የተደረገውን የምክክር ጉባኤ አስመልከቶ የተዘጋጀው ሰነድ እንደሚያሳየው፣ በዚህ …

ሰኔ ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ከ2003 እስከ 2005 ዓ.ም ድረስ የሳምባ ምች በሽታ የመጀመሪያው ገዳይ በሽታ የነበረ ሲሆን፣ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ኤች አይ ቪ ኤድስ አንደኛ የአእምሮ ጭንቀት ደግሞ የሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል። ኤ አይ ቪ ኤድስ በኢትዮጵያ እየቀነሰ መምጣቱ ቢነገርም፣ በሽታው አሁንም ቀዳሚ ገዳይ በሽታ ተብሎአል። የአእምሮ ጭንቀት ሁለተኛ ገዳይ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ኢሳት ዜና (ሰኔ 23 2007) ሰሞኑን ፍርድ ቤት ከእስር እንዲፈቱ ወስኖላቸው ፖሊስ በድጋሚ ለእስር በዳረጋቸው አራት የፓርቲ አባላት ላይ አቃቢ ህግ ይግባኝ ጠየቀ። ተከሳሾች የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸው ከውጭ ሆነው ለመከታተል ጥያቄን ቢያቀርቡም ከሳሽ አቃቢ ህግ ተቃውሞን እንዳቀረበ ከሀገር ቤት የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ጉዳዩን ለማየት የተሰየሙት ዳኛ ተከሳሾች እስካሁን ድረስ በእስር ቤት ስለመቆየታቸው የሚያውቁት ነገር …

ለደብሩ ማኅበረ ካህናት፣ ማኅበረ ምእመናንና ለየሰንበት ት/ቤቱ ታላቅ ድል፤ በየአጥቢያው ለተጋጋለው የፀረ ሙስና እና ፀረ ኑፋቄ ንቅናቄ ታላቅ የምሥራች፤ የንቅናቄውን ኃይሎች በነፍስ ግድያ ዛቻዎች ጭምር ለማዳከም ለሚሯሯጡት አማሳኞች ከባድ ድንጋጤ እና መርዶ ኾኗል !!! በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ባለፈው ሳምንት ዓርብ ረፋድ ባሳለፈው የቅጣት ውሳኔ፣ የደብሩ ዋና ሒሳብ ሹም ዲያቆን ተስፋዬ …

ኢሳት ዜና (ሰኔ 22 2007 ዓም) በሚቀጥለው ወር በኢትዮጵያ ጉብኝት የሚያደርጉት የአሜሪካ ፕሬዘዳንትን ጉዞን በመቃወም የፊታችን አርብ በዚህ በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ከተማ በሚገኘው “ ሁዋይት ሀውስ ‘’ የተቃውሞ ሰልፍ መጠራቱን አዘጋጆቹ ገለጹ ። በዋሺንግተን ከተማ ዙሪያ በሚገኘው የወጣቶች ግብረ ሀይል የተዘጋጀው የተቃውሞ ሰልፍ ፕሬዘዳንት ኦባማ የሚያደርጉትን ጉዞ እንዲያስቡበትና እንዲሰርዙት የሚጠይቅ መሆኑ ታውቋል። ፕሬዘዳንቱ በቀጣዩ ወር …

32ኛው በሰሜን አሜሪካ በድምቀት እየተከበረ የሚገኘው የኢትዮጲያዊያን የሰፖርትና የባህል ፌስቲቫል ላይ ከተዘጋጁት ዝግጅቶች መሀከል በጉጉት የሚጠበቁት የሃሙስ እና የዓርብ የሙዚቃ ዝግጅቶች በወጣላቸው ፕሮግራም መሰረት እንደሚደረጉ ተረጋገጠ። ቴዲ አፍሮና ጎሳዬ ተስፋዬ ቪዛቸውን ለማግኘት የአሜሪካ ኤምባሲ የሲስተም መበላሸት ያዘገየው ቢሆንም አሁን ከደቂቃዎች በፊት ኤንባሲው ችግሩን እንዳስተካከለ የሚከተለውን መግለጫ አውጥቷል። U.S. Embassy Addis Ababa በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካን […]

በቱርክ ዋና ከተማ ኢስታንቡል የተሰባሰቡ ግብረሰዶማውያን ሊያደርጉት አቅደው የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ የአገሪቱ መንግስት ህገወጥ ነው ሲል በውሃ መርጫ ካኖን መበተኑ ተሰምቷል። ከሰሞኑ በዓለም ላይ እየተከበረ ያለውን የግብረሰዶማውያን ቀን ለማክበር ወጥተው የነበሩት እነዚህ ሰልፈኞች በታቅሲም አደባባይ አቅራቢያ በመሰባሰብ ላይ እንዳሉ በፖሊሶች እንዲበተኑ መደረጉን በስፍራው የነበረ የሮይተርስ ዘጋቢ ተናግሯል። ፓሊሶች የሰልፉ መሪዎችን ካሰሩ በኋላ ከተማዋ ወደ ቀድሞው […]

ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብአዴን እያስተዳደርኩት ነው በሚለው የአማራ ክልል የጀመራቸው የተለያዩ ተቋማት ውጤት አልባ በመሆናቸው ብዙዎቹ እየፈረሱና ዜጎችን ለችግር እያደረጉ መሆኑን ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል። የክልሉ ቴክኒክ እና ሙያ ኢንተርፕራይዝ እና የክልሉ ጥቃቅን እና አነሰተኛ ቢሮዎች በክልሉ የሚገኙ በሚልዮን የሚቆጠሩ ስራ አጦችን በተለያየ ሙያዎች በማሰልጠን የክልሉን የስራ አጥ ቁጥር …

ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስባ የሆነው መድረክ ባወጣው መግለጫ በ2007 ዓ ም በሀገራችን ተካሄደ የተባለው ምርጫ በሕግና ሥርዓት ያልተመራና በሕገ-መንግሥቱና በምርጫ ሕጎች የተደነገጉትን የነፃ፣ፍትሐዊና ታአማኒነት ያለው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መርሖዎች በኃይል በተጣሱበት ሁኔታ የተፈጸመ በመሆኑ መድረክ የምርጫውን ሂደትም ሆነ ውጤት እንደማይቀበለው ገልጾ፣ ለዚህ አሁን ሀገራችን ለገባችበት አስቸጋሪ ሁኔታ …

ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግል ሠራተኞች የፕሮቪደንት ፈንድ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ያለውን ገንዘብ ወደመንግስት በማስገባት ሠራተኞቹ በጡረታ እንዲታቀፉ በሚያስችል መልኩ የተደነገገው የግል ድርጅቶች የማህበራዊ ዋስትና አዋጅ ማሻሻያ በገጠመው ከባድ ተቃውሞ ምክንያት ለፓርላማው ሳይቀርብ በቋሚ ኮምቴዎች ውሳኔ እንዲሻሻል መደረጉን ዘጋቢያችን ገልጿል። የማሻሻያ ሕጉ ከአንድ ወር በፊት ለፓርላማ ሲቀርብ አሁን በስራ ላይ …

ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከዚህ ቀደም በ1997 ምርጫ ወቅት በቅንጅት መሪዎች፣ በጋዜጠኞችና በሲቪክ ተቋማት መሪዎች ላይ የቀረበው ክስ ፣ 24 ሰአታት አስቂኝ ፊልም የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ነበር። በፍርድ ቤቱ የነበረውን ሁኔታ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የቃሊቲው መንግስት በሚል ርእስ ዘርዝሮ ማቅረቡ ይታወቃል። በቅርቡ አይ ኤስ ኤስ የተባለው አሸባሪ ድርጅት በ30 ኢትዮጵያውያን …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር መንግስት አይ.ኤስ.አይ.ኤስን ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ሰበብ እስር ላይ ቆይተው ሰኔ 15/2007 ዓ.ም በቄራ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት እንዲፈቱ ተወስኖላቸው ሰኔ 16/2007 ዓ.ም ከእስር ቤት ሲወጡ እንደገና በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት ወንይሸት ሞላ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬ፣ ዳንኤል ተስፋዬና ቤትሄልየም አካለወርቅ ዛሬ ሰኔ 22/2007 ልደታ ፍርድ ቤት 11ኛ ምድብ ችሎት ቀርበው ቀደም ሲል ‹‹ሁከትና ብጥብጥ አስነስተዋል›› […]

አይ ኤስን ለመቃወም ከተጠራው ሰልፍ በኋላ ፖሊስና አቃቤ ህግ በየ ችሎቱ ኢህአዴግ ላይ ሰልፍ በመጥራት ስድብ እያዘነቡበት ነው፡፡ በሚያዝያ 14ቱ ሰልፍ ላይ በቦታው ያልነበሩት የሰማያዊ፣ የቀድሞው አንድነትና የቀድሞው መኢአድ አባላትና አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ወጣቶችን ያስሩና እነዚህ ወጣቶች ያላሉትን ክስ ብለው ያቀርባሉ፡፡ ይህ ክስ ደግሞ ለእነሱ የሰልፍ መፈክር መሆኑ ነው፡፡ የስድብ ውርጅብኝ፡፡ በቃ ችሎት የቁጭት መውጫቸው […]

ዛሬ በጥዋት የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ሊሰጥ የተቀጠረውን ውሳኔ ተመልክቼ ለመዘገብ ልደታ በሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አምርቼ ነበር፡፡ 3፡30 ሰዓት ገደባ በታችኛው መግቢያ በር ጋር ስደርስ፣ ቁጥራቸው በዛ ያሉ፣ የሚሊተሪ ልብስ የለበሱ የጸጥታ ሃይሎች እና የአዲስ አበባ ፖሊሶች በፍርድ ቤቴ ቅጥር ግቢ በር ላይ ሆነው ሰዎችን በጥብቅ እየተፈሹ ሲያስገቡ አስተዋልኩ፡፡ በአጋጣሚ ከጠበቃ […]