Author: VOA Amharic
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 27, 2013
News, Ethiopians in America, Americana, Democracy and Women and Family
በቁጫ ሕይወት የጠየቀ ግጭት መፈጠሩ ተሰማ – ኖቬምበር 27, 2013
Qootcha, Kutcha, Kucha, koocha, Ethiopia, South,SNNPR, clashes
ትብብርና መድረክ – ሁለቱ የተቃውሞው ጎራ ጥምረቶች – ኖቬምበር 27, 2013
Tb’br and Medrek
የሳዑዲ ተመላሾች ቁጥር 37 ሺህ ደረሰ፤ በናሽቪል-ቴኔሲ ሰልፍ ተደረገ – ኖቬምበር 27, 2013
Ethiopian returnees from Saudi Arabia, Nashville, TN demo
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 26, 2013
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 24, 2013
News, Radio Magazine or Mestawot
አሥራ ሦስት ሺህ ኢትዮጵያዊያን ተመልሰዋል፤ ሰልፎቹ እንደቀጠሉ ነው – ኖቬምበር 22, 2013
13 thousand Ethiopians returned from Saudi Arabia.
አሥራ ሦስት ሺህ ኢትዮጵያዊያን ተመልሰዋል፤ ሰልፎቹ እንደቀጠሉ ነው
ወደ አሥራ ሦስት ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን እስከአሁን ከሣዑዲ አረቢያ አዲስ አበባ መግባታቸውን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ተመላሾቹን ለማቋቋም በፌደራል መንግሥቱና በክልል አስተዳደሮች የትብብር ሥራ እንደሚከናወንም መሥሪያ ቤቱ አመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ተፈፅሟል የሚል ዜና ከወጣ ጀምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን እያሰሙ ነው፡፡
ዛሬ፣ ሐሙስ፣ ኀዳር 12 / 2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጅና ጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ውስጥ ደግሞ በሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሰልፎች ተደርገዋል፡፡
ባለፉ ጥቂት ቀናት ውስጥም በእንግሊዝ፣ በጣልያን፣ በአውስትራሊያ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ደግሞ በዳላስ፣…
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 21, 2013
News, Cultural Mosaic, Kebele Lives and Environment or Tech
የአቶ መላኩ ጉዳይ ለሕገመንግሥት ጉባዔ ተመራ – ኖቬምበር 21, 2013
ethiopians, saudi, us, crew, addis ababa, returness
ቪኦኤ የሣዑዲን ተመላሾች አዲስ አበባ ላይ አነጋገረ
ኢትዮጵያዊያን በየአቅጣጫው እየተንቀሣቀሱ ነው፡፡
የአቶ መላኩ ጉዳይ ለሕገመንግሥት ጉባዔ ተመራ
በግንቦት ሰባት ጉዳይ የተከሰሱትም ጉዳይ ችሎት ቀረበ።
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 20, 2013
News, Ethiopians in America, Americana, Democracy and Women and Family
የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኞች ዛሬ አዋሣ ላይ ችሎት ቀረቡ – ኖቬምበር 20, 2013
Ethio-Mihidar Journalists, Hawassa, court
የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኞች ዛሬ ሃዋሣ ላይ ችሎት ቀረቡ
ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመሠረተባቸው ክስ ሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየቀረቡ ያሉት የኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ አዘጋጆች ጉዳያቸው አዲስ አበባ ላይ እንዲታይ ያቀረቡት ጥያቄ ዛሬም ተቀባይነት አላገኘም።
አዘጋጆቹ ወደፍሬ ነገሩ ገብተው እንዲከራከሩ ብይን የሰጠው የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለኅዳር ሃያ አምስት ቀጠሮ ሰጥቷል።
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 19, 2013
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
የመድረክ ሰልፍ ለሃያ ቀናት ተለወጠ – ኖቬምበር 19, 2013
Medrek’s demo deffered
የሙስና ክሥ የፍርድ ቤት ውሎ – ኖቬምበር 19, 2013
corruption, court, melaku …
የሳውዲ አረብያን መንግስት በመቃወም በዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያውያን አደባባይ ወጡ
የሳውዲ አረብያ መንግስት በቅርቡ “የመኖርያ ፈቃድ የላቸውም፤” ያላቸውን በዚያች አገር የሚኖሩ የውጭ አገር ሠራተኞች ለማስወጣት በያዘው ዘመቻ ከፍተኛ ግፍና በደል የደረሰባቸው ወገኖቻቸው ጉዳይ ነው በቁጣ ግልብጥ ያሉት ሠልፈኞች በዛሬው ዕለት ለቅዋሜ አደባባይ የወጡት።
በብዙ መቶዎች የተቆጠሩት ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ከዋሽንግተን ዲሲው የሳውዲ ኤምባሲ ደጃፍ ባካሄዱት በዚህ ሠልፍ፥ የሳውዲ መንግስት ‘ከአገሬ ውጡ!’ ያላቸውን የተለያዩ አገር ዜጎች የሰብዓዊ መብት እንዲያከብር፥ የኃይል እርምጃውን እንዲያስቆምና ተጠያቂ ይሆን ዘንድ ከልዩ-ልዩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች የመጡትን ጨምሮ የተለያዩ የሃይማኖት መሪዎችና የማኅበራት ተጠሪዎች ባሰሙት ጥሪ ጠይቀዋል።
የዘገባውን ዝርዝር ለመስማት የሚቀጥለውን ይጫኑ።
የመድረክ ሰልፍ ለሃያ ቀናት ተለወጠ
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ትናንት ዕሁድ ፤ ኅብር 8 / 2006 ዓ.ም ሊያደርግ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ወደ ኅዳር 29 / 2006 ዓ.ም ለማዛወር መወሰኑን አስታውቋል፡፡
መድረክ ሰላማዊ ሰልፉን ትናንት የሠረዘው የከተማዋ የሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባዎች ዕውቅና ሰጭ አካል ለመድረክ በፃፈው ደብዳቤ በዕለቱ በከተማይቱ የተለያዩ ዓለምአቀፍ ስብሰባዎች እንደሚካሄዱ ገልፆ ለጥበቃ ይሠማሩ የነበሩ የፀጥታ ኃይሎች ዕጥረት ስላለ የግንባሩን ጥያቄ ማስተናገድ እንደማይችል በማስታወቁ መሆኑን የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡
በመጭ ቀናትም በከተማይቱ ውስጥ ተመሣሣይ ክንውኖች ስለሚደረጉ በዚህ ወቅት እንዲህ ዓይነት ጥያቄዎችን ማስናገድ እንደማይቻልም አስተዳደሩ መግለፁን ሊቀመንበሩ አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ…
የሙስና ክሥ የፍርድ ቤት ውሎ
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥራ አምስተኛ የወንጀል ችሎት በአቶ መላኩ ፈንታ፣ አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ እንዲሁም አንዳንድ ተዋቂ ባለሃብቶች ላይ አቃቤ ሕግ የመሠረተውን ክሥ በመደበኛው የሕግ ሥነ-ሥርዓት መሠረት እንደሚመለከተው ወሰነ።
የአንደኛውን ተከሣሽ የአቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይ መመልከት ይችል እንደሆነ ለመወሰን ግን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ለዝርዝሩ የመለስካቸው አምሃን ዘገባ የያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 18, 2013
News, Sports, African Topics and Health
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 17, 2013
News, Radio Magazine or Mestawot
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 16, 2013
News, Call-in show or special interviews and Ye Musica Qana
ዋልያዎቹ ‘ተዘጋጅተናል’ ይላሉ – ኖቬምበር 16, 2013
Ethiopian national soccer team – ready for away match with Nigeria’s counter part
ሃያ ሰዎች የሽብር ክሥ ተከፈተባቸው – ኖቬምበር 16, 2013
Ethiopia, terrorism charges, ginbot 7
የሰማያዊ ሰልፍ በኃይል ተበተነ፤ መድረክ ለፊታችን ዕሁድ ጠርቷል – ኖቬምበር 16, 2013
Semayawi Party, Medrek,Saudi, Ethiopians, demonstrations
የሰማያዊ ሰልፍ በኃይል ተበተነ፤ መድረክ ለፊታችን ዕሁድ ጠርቷል
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ሣዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን ላይ “ተፈፅሟል፣ እየተፈፀመም ነው” ያለውን ግፍ በመቃወም ዕሁድ፤ ኅዳር 8/2006 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡
የሰልፍ ዕውቅና የሚሰጠው ክፍል ግን በቃል አሉታዊ መልስ እንደሰጠው አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ሳዑዲ አረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር በመቃወም የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ፡፡
አዲስ አበባ በሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አቅራቢያ በተሰባሰቡት ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ “ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እሥር ተፈፅሟል” ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ድርጊቱን አውግዟል፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር በበኩሉ ለቪኦኤ በሰጠው ቃል ሰልፉ “ሕገወጥ ነው” ብሏል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ አዘጋጆቹ “ከሚመለከተው ክፍል ፍቃድ…
ዋልያዎቹ ‘ተዘጋጅተናል’ ይላሉ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከፍበኛ መሻሻል ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ፈባጠን አካሄድ አፍሪካን አልፎ በቀሪውም ዓለም መድረክ ሊያሣትፈው የተቃረበ ይመስላል፡፡
ነገ፣ ቅዳሜ ኅዳር 7/2006 ዓ.ም ከናይጀሪያ አቻው ጋር በሚያደርገው የመልስ ግጥሚያ አስፈላጊውን ሁሉ አሟልቶ ካሸነፈ በመጭው ሰኔ ብራዚል በምታስተናግደው የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ አህጉሪቱን ከሚወክሉ አምስት የአፍሪካ ብሔራዊ ቡድኖች አንዱ ይሆናል ማለት ነው፡፡
ለዚህ ወሣኝ ፍልሚያ ቡድኑ “ብቃት ያለው ዝግጅት አድርጌአለሁ” ይላል፡፡
ሰሎሞን ክፍሌ የነገው የመልስ ጨዋታ ወደሚካሄድባት የናይጀሪያ ከተማ ካላባ ደውሎ የቡድኑን ዋና አሠልሐኝ ሰውነት ቢሻውንና ሌሎችም የቡድኑን አባላት አነጋግሯል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
ሃያ ሰዎች የሽብር ክሥ ተከፈተባቸው
ፌደራል አቃቢ ሕግ “የግንቦት ሰባት አባል በመሆን” ና “የሽብር ወንጀል ፈፅመዋል” ሲል በሃያ ሰዎች ላይ ክሥ መሥርቷል፡፡
ሰዎቹ መቼ እንደታሠሩ ግን አልገለፀም፡፡
ጉዳዩ እየታየ ያለው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ሲሆን ተከላካይ ጠበቃ ያቀረበው የክሥ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ውድቅ ሆኗል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የአንዳንድ ተከሣሾች ጉዳይ በሌሉበት መታየት ጀምሯል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የመለስካቸው አምኃ ዘገባ ያዳምጡ፡፡
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 15, 2013
News, Community Heroes or Call-in, Crossfire and African Topics
የዋሽንግተን ኢትዮጵያዊያን ሣዑዲ ስለሚገኙ ወገኖቻቸው ተሰለፉ – ኖቬምበር 15, 2013
Ethiopians demonstrate outside Saudi Embassy in Washington, D.C.
የቁጫ ሕዝብ ጥያቄና የሰሞኑ እሥራቶች – ኖቬምበር 15, 2013
Qootcha people in Ethiopia and arrests
አራት መቶ ተመላሾች ዛሬ ከሣዑዲ አዲስ አበባ ገቡ፤ ሰማያዊ ለዓርብ ሰልፍ ጠርቷል – ኖቬምበር 15, 2013
Ethiopians returning from Saudi Arabia
አራት መቶ ተመላሾች ዛሬ ከሣዑዲ አዲስ አበባ ገቡ፤ ሰማያዊ ለዓርብ ሰልፍ ጠርቷል
በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቹ ወደሀገራቸው እየተመለሱ መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናቱም ከሳዑዲ አቻዎቻቸው ጋር እየተነጋገሩ መሆናቸውን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ አምባሣደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ የተመራ የልዑካን ቡድን ወደ ሪያድ መጓዙ ተገልጿል፡፡
ሰሞኑን መግለጫ እያወጡ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግን መንግሥት ለእርምጃው ዘግይቷል፥ የበለጠ ሥራም ይጠብቀዋል ይላሉ።
በጉዳዩ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ለነገ ጥሪ የበተነው መኢአድ የሌሎች አንዳንድ ሃገሮች ዜጎች መብቶች ከኢትዮጵያዊያኑ በተሻለ ሁኔታ እንደሚጠበቅና በኢትዮጵያዊያን ላይ ግፍ ሲደርስ ግን የአሁኑ የመጀመሪያ አለመሆኑን የድርጅቱ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ አመልክተዋል፡፡
ዛሬ መግለጫ ያወጣው ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ ነገ ዐርብ፣…
የዋሽንግተን ኢትዮጵያዊያን ሣዑዲ ስለሚገኙ ወገኖቻቸው ተሰለፉ
“የወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል መሪ ቃል የተጠራ የኢትዮጵያዊያን ሰልፍ ዛሬ፣ ኅዳር 5 / 2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የሣዑዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ ተካሂዷል፡፡
በሰልፉ ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተገኙ ሲሆን ሣዑዲ አረቢያ ለሚገኙ ወገኖቻቸው ጥበቃ እንዲደረግ፣ ሰብዓዊ መብቶቻቸው እንዲከበሩ፣ በአፋጣኝ ወደ ሃገራቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠይቀዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
የቁጫ ሕዝብ ጥያቄና የሰሞኑ እሥራቶች
በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በቁጫ ወረዳ፥ ከ 20 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ከ 100 በላይ ተማሪዎች፥ መምህራንና አርሶ አደሮች መታሠራቸውም ይነገራል።
ከወረዳው ባለሥልጣናት ጉዳዩን ለማጣራት ባባለፉት ሁለት ቀናት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
መለስካቻው አምሃ ተከታዩን ከአዲስ አበባ ልኳል።
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 13, 2013
News, Ethiopians in America, Americana, Democracy and Women and Family
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 12, 2013
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 11, 2013
News, Sports, African Topics and Health
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 10, 2013
News, Radio Magazine or Mestawot
Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 08, 2013
News, Community Heroes or Call-in, Crossfire and African Topics