የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ6 ወራት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጣውን ከ32 ሺ በላይ የኮንዶሚኒየም ቤቶች አሁንም ለእድለኞቹ ማስረከብ አልቻለም።
መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እድለኞቹ በአስተዳደሩ አታላይ ፕሮፖጋንዳ ማዘናቸውን ገልጰዋል። አስተዳደሩ ምርጫ 2007 ተከትሎ ከ32ሺ በላይ ቤቶች ላይ እጣ በመጋቢት ወር 2007 ያወጣ ሲሆን ቤቶቹንም በሳምንታት ጊዜ ውስጥ ከማስረከብ አልፎ ቀጣዩን እጣ በሰኔ ወር 2007 እንደሚያወጣ ቃል ቢገባም አንዱንም መፈጰም ሳይችል ቀርቶአል። አስተዳደሩ የካርታ ስራ እንዳዘገየው ቢናገርም እውነቱ ግን ቤቶቹ …