ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተከዜ ወንዝ ጫፍ ላይ የምትኘውና የዋግና የበለሳ ነዋሪዎች መተላለፊያ የሆነችው አርባ ፀጓር ወረዳ ደርግን ለመጣል በተደረገው የትግል ወቅት የኢህአፓና የኢሕዲን መተላለፊያ መስመር የነበረች ሲሆን በወቅቱ የድሮው ኢሕዲን የአሁኑ ብአዴን ታጋዮች የነበሩት ለሕዝቡ የኑሮ ለውጥና ዴሞክራሲያ ስርዓት እንደሚገነቡ ቃል በመግባታቸው ነዋሪው ሸማቂዎቹን በማገዝ ከለላ ይሰጣቸው የነበረ ሲሆን ድል …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ፥ ESFNA በካናዳ የቶሮንቶን ከተማ የ2016 የስፖርት ክብረ በዓል ዓስተናጋጅ እንድትሆን መርጧል። ውሳኔው የተላለፈው፥ በኢትዮ-ስታር ቶሮንቶ የእግር ኳስ ክለብ ዓስተባባሪነት በቶሮንቶ ካናዳ በተዘጋጀው፥ የESFNA ዓመታዊ ጉባኤ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ የክለብ ተዎካዮችና የቦርዱ ዓመራር ዓባላት በተገናኙበት፥ ባሳለፍነው ቅዳሜና እሁድ October 10 እና …

ጥቅምት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኙት የቱርካና ሃይቅና የኦሞ ወንዝ ኢትዮጵያ በምትከተለው የኢንዱስትሪ ዘመቻ ምክንያት የመድረቅ እና የአየር ንብረት መዛባት አደጋን ማስከተሉንና በዚህም ለውጥ ሳቢያ የአካባቢው ነዋሪዎች ስጋት ውስጥ መሆናቸውን ሂውማንራይትስ ወች በጥናት ሪፖርቱ አመልቷል። በሰሜናዊ ምዕራብ ኬንያ በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ የሚገኘው የቱርካና ሃይቅ በዓለማችን በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ከሚገኙት …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚገኙ 8 ሚሊዮን 200 ሺ ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚሹ፣ በከተማ ውስጥ የሚኖሩ 4 ሚሊዮን ተረጅዎች እንዳሉ በመንግስት እና በአለማቀፍ ድርጅቶች ይፋ ከሆነ በሁዋላ፣ የአለማቀፍ ድርጅቶች መንግስት ለልማት በሚል የመደበውን ገንዘብ የዜጎቹን ነፍስ ለመታገድ እንዲያውለው ጠይቀዋል። እስከሚቀጥለው ታህሳስ ወር ድረስ ምግብ ገዝቶ ለማቅረብ የሚያስፈልገው 12 …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው እሁድ ጀምሮ በኢትዮጵያውያንና በሱዳን መንግስት ወታደሮች መካከል የተነሳው ጦርነት መቀጠሉን ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያመለካታሉ።ኢትዮጵያውያን ታጣቂዎች፣ ከዚህ ቀደም ማንነታቸው ያልታወቁ የሱዳን ታጣቂዎች 8 ኢትዮጵያውያንን ለሹፌርነት እንቀጥራችሁዋለን በማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ከመኪና ላይ አውርደው መግደላቸውን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያውያኑ በወሰዱት አጸፋ እርምጃ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የሱዳን ወታደሮችን ገድለዋል። የሱዳን መንግስት ተጨማሪ …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በሲዳማ ዞን በማልጋ ወረዳ ፣ ወታራና ጉጉማ በሚባሉ አካባቢዎች ከ2004 ዓም ጀምሮ በእየአመቱ የሚቀሰቀሰው ግጭት ሰሞኑን አገርሽቶ፣ እስካሁን 2 ሰዎች በከባድ ሁኔታ ተጎድተው አዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሲገቡ፣ መጠኑ ያልታወቀ ንብረትም ወድሟል። በቦንኬ ጎሳና በጉኑፋ ጎሳዎች መካከል የተነሳው ግጭት መንስኤ የአንዱ አካባቢ ተወላጅ ሌላውን ማስተዳደር አይችልም …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሞክሩ በማላ ዊ የድንበር ጠባቂዎች የተያዙ ከ317 በላይ ኢትጵያዊያን ስደተኞች በተለያዩ እስርቤቶች ውስጥ የሚገኙ ሲሆን በእስር ቤት ውስጥ ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው መሆኑን አጃን ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። የማላዊ ፍርድ ቤት በስደተኞች ላይ የእስር ቅጣትና ስድሳ አምስት የአሜሪካን ዶላር መቀጮ የጣለባቸው ሲሆን ፣ አብዛሃኞቹ ከስድስት ወራት …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሰው በ19ኛው ወንጀል ችሎት ነጻ የተባሉት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ሃብታሙ አያሌው፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ል ሰብሳቢ የነበረው የሽዋስ አሰፋ፣ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ም/ል ስብሳቢና የደቡብ ተወካይ የነበረው ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም አብርሃም ሰለሞን ፣ ዛሬ ጠ/ፍርድ ቤት ቀርበው፣ በአቃቢ ህግ የተጠየቀባቸው ይግባኝ …

ጥቅምት ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በፍቼ ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት መስሪያ ቤትስራችንን በአግባቡ ሊያሰራን አልቻለም በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪዎች ከትናንት ጀምረው የስራማቆም አድማ አድርገዋል። የከተማው መንገድ ትራንስፖርት ባጃጅ ለመንዳት የታክሲ አንድ ፈቃድ መያዝ ያስፈልጋል የሚል መመሪያ ያወጣ ሲሆን፣ በሶስተኛ መንጃ ፈቃድ ሲያሽከረክር የተገኘ ሹፌር 2 ሺ 500 ብር ይቀጣል። የቅጣቱን መጠንና …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2 ፣ 2015) የህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሐት ) ማእከላዊ ኮሚቴ ከአመታት በፊት በጡረታ የተገለሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጋዮች በድጋሚ እንዲደራጁ አዘዘ። ባለፈው እሁድ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመቀሌ ከተማ ጉባኤ ያካሄደው የህወሀት ማእከላዊ ኮሚቴ፣ በትጥቅ ትግሉ ወቅት እንዲሁም በጡረታ ሰበብ የተሰናበቱ ታጋዮች ዳግም የማደራጀት ስራ እንዲካሄድ ወስኗል። ከአመታት በፊት በእድሜና በተለያዩ ምክኒያቶች …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2 ፣ 2008 ዓም) በኢትዮጵያና ግብጽ መካከል በአባይ ግድብ ዙሪያ ሊካሄድ የነበረው ድርድር መዘግየትን ተከትሎ፣ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ አልሲሲ ከሱዳን ጋር የሚመክር የልዑካን ቡድን ወደ ሃገሪቱ ላኩ። በሃገሪቱ የመስኖ ልማት ሚኒስትር ሆሳም ሞግሃዚ የተመራው ይኸው ልዩ የልዑካን ቡድን፣ ከፕሬዚዳን አልሲሲ የተላከን ልዩ መልዕክት በመያዝ ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር ለመምከር ካርቱም መግባቱን አል-አህራም …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 2, 2008ዓም) በቅርቡ ወደሶማሊያ የተሰማራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በደቡባዊ የሃገሪቱ ክፍል ለሁለተኛ ሳምንት ከባድ ውጊያ ኣያካሄደ ኣንደሚገኝ የሶማሊያ ወታደራዊ ባለስልጣናት ትናንት ገለጹ። ለሁለተኛ ሳምንት ቀጥሎ የሚገኘው ግጭት ልዩ ስሙ አልዩ ዲዮ በተባለ ደቡባዊ ምዕራብ የሶማሊያ አካባቢ እየተካሄደ እንደሚገኝ እነዚሁ ወታደራዊ ባለስልጣናት ለጋዜጠኞች አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ በአካባቢው እየተካሄደ ባለው ውጊያ፣ የኢትዮጵያ …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስትና አለማቀፍ ድርጅቶች በሰጡት መረጃ መሰረት የተረጂው ጠቅላላ ቁጥር 8 ነጥብ 2 ሚሊየን ደርሷል፡፡ መረጃዎች ግን ከዚህ በላይ መሆኑን ያመለክታሉ። የተጠቀሰው አሃዝ ቀደም ሲል በሴፍቲኔት ፕሮግራም ታቅፈው የሚረዱ ወደ 3 ነጥብ 8 ሚሊየን ኢትዮጵያዊን ወገኖችን ይጨምራል ተብሎአል። ይሁን እንጅ መንግስት ያዘጋጀው እና አለማቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች የሚጠቅሱት ሰነድ …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን አዳ በርጋ ወረዳ 30 ወጣቶች በኦሮምያ ልዩ ሃይሎች በሌሊት ታፍነው መወሰዳቸውን ሂውማን ራይትስ ሊግ ኦፍ ዘ ሆርን ኦፍ አፍሪካ ገለጸ። ድርጅቱ ለኢሳት በላከው መግለጫ አብዛኞቹ የታሰሩት ወጣቶች የናይጀሪያዊው ባለሀብት ንብረት የሆነው የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኞች እና ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብር ወንጀል ተከሶ በእስር ላይ የሚገኘው ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የእስር ቤት አስተዳዳሪዎች በሚያሳድሩበት ጫና ለተጨማሪ ስቃይ እየተዳረገ መሆኑን የሙያ አጋሮቹ ተናግረዋል። የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ አቶ አበበ ውቤ እንደገለጹት፣ እስክንድርን ከሁለት የቅርብ የቤተሰብ አባላት ውጭ ሌሎች ሰዎች እንዳይጥቁት ተከልክለዋል። በሃይማኖት አባቶችም ሆነ በጠበቃ እንደማይጎበኝ የገለጸው …

ጥቅምት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኦህዴድ ላለፉት 2 አመታት ከተማዋን ሲመሩ የነበሩትን አቶ አብርሃም አዱላን ወደ ክልል ቢሮ በማዛወር የሻሸመኔ ከንቲባ የሆኑትን ለከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል። አዲሱ ከንቲባ በሻሸመኔ የሚገኙ ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን በማሰቃት የሚወነጀሉ ሲሆን፣ ለአዳማ የተወሳሰበ ችግር መፍትሄ ያመጣሉ ተብሎ እንደማይታመን ምንጮች ይገልጻሉ። ነባሩ ከንቲባ፣ በደባል ሱሶች በመጠመድ ያለፉትን ሁለት አመታት …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለአመት የዘለቀው የቴፒ ግጭት በአካባቢው ለሰፈረው የፌደራል ፖሊስ እና ለፌደራል ባለስልጣናት እንቆቅልሽ ሆነ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ባለፈው ቅዳሜ ከሌሊቱ 6 ሰአት ከ45 ደቂቃ ላይ ሚሊኒየም ጎዳና ላይ ወይም ሚካኤል አካባቢ ካሳሁን የተባለ የከተማው ፖሊስ አባል ተገድሏል። ፖሊሱ በቅርቡ ለከተማው ተመድቦ የመጣ ነበር። እርምጃውን የወሰዱት ራሳቸውን የቴፒ ወጣቶች …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ቅዳሜ በተነሳው ግጭት ከፖሊስና ከመከላከያ አንዳንድ ወታደሮች ቆስለዋል። የግጭቱ መንስኤ ሁለት የመከላከያ ፖሊስ አባላት በፖሊሶች መደብደባቸው ነው። ከዚህ ቀደም አንድ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ፍቼ አካባቢ ሰፍሮ የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት አባል ከገደለው በሁዋላ፣ በመከላከያና በፖሊስ መካከል ለወራት የዘለቀ ቁርሾ እንዲፈጠር አድርጓል። ባለፈው ቅዳሜ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት …

ጥቅምት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሃገሪቱ ከሚገኙ አምራች አካባቢዎች አንዱ በሆነው በየዓመቱ ከሰኔ እስከ ህዳር ወር ድረስ ከፍተኛ የሰራተኛ ቁጥር የሚያስተናግደው የምዕራብ አርማጮኾ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ ቀበሌዎች የሚገኙ የጤና ተቋማት ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን በጀት የክልሉ መንግስት ባለመመደቡ በየአመቱ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዳልቻሉ የወረዳው የጤና አመራሮችና ባለሙያዎች ተናገረዋል፡፡ በምዕራብ አርማጮኾ ወረዳ ያለው …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 27 ፣ 2008) በዋሺንግተን ዲሲ አቅራቢያ አርሊንግተን በተካሄደው በዚህ የቀብር  ስነ-ስርአትና በአሌክሳንድሪያ ከተማ በተከናወነው የጸሎት ፕሮግራም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ መገኘቱንም ለማየት ተችሏል ። ከአውሮፓ፣ ከካናዳና፣ ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛት የመጡ እንዲሁም በዋሺንግተን ዲሲ ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት የጸሎትና የቀበር  ስነ-ስርአት የአቶ ሙሉጌታ ወዳጆች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። የአንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ እንዲሁም የፖለቲካ ተንታኝ የአቶ …

መስከረም 27, 2008 አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ሃያሲ፣ ደራሲና፣ የፖለቲካ ተንታኝ ሙሉጌታ ሉሌ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው የኢሳት ማኔጅመንት፣ ጋዜጠኞችና፣ መላው የኢሳት ቤተሰብ ከፍተኛ ሃዘን ተሰምቶታል። አቶ ሙሉጌታ ሉሌ በተባ ብዕራቸው ሃገራዊ ፍቅርን፣ አንድነትን፣ ነፃነትንና፣ ፍቅርን የሰብኩ፥ በአንደበታቸው ስለኢትዮጵያ የመሰከሩ፣ እስከመጨረሻ እስትንፋሳቸው ድረስ ኢትዮጵያን ያገለገሉና፣ ኢትዮጵያን ተቀምተው በስደት የቀሩ ሃገራዊ ሃብት ነበሩ። የሙያ አባታችን ሙሉጌታ ሉሌ …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በ በቆጂ ከተማ ከቤት ማፍረስ ጋር በተያያዘ በተነሳ ተቃውሞ ከ20 በላይ ወጣቶች በፖሊሶች ተደብድበው ሆስፒታል የገቡ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ነዋሪዎች ደግሞ ተደብድበዋል። ግጭቱ የተከሰተው የወረዳው ባለስልጣናት ቤት አፍራሽ መኪኖችን በመላክ ህገወጥ ቤቶች ያሉዋቸውን ቤቶች ማፍረስ መጀመራቸውን ተከትሎ ሲሆን፣ ነዋሪዎች ድንጋይ በመወርወር ተቃውሞቸውን ገልጸዋል። …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከጸጥታ እና ከደህንነት ዋስትና ማጣት ጋር በተያያዘ፣ ስራ ያቋረጡት የመንግስት ሰራተኞች፣ ከወረዳው ባለስልጣናት ጋር ተናንት የተወያዩ ቢሆንም፣ መተማመን ላይ ባለመድረሳቸው አብዛኞቹ ዛሬም ስራ ሳይጀምሩ ቀርተዋል። አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች በግዴታ ስራ እንዲጀምሩ ቢደረግም፣ ብዙዎቹ በአድማው ቀጥለውበታል። የሀመር ወረዳ አርብቶአደሮች በየጊዜው በሚሰነዝሩት ጥቃት የፖሊስ፣ የመከላከያና የልዩ ሃይል አባላትን …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የተከሰተውና ከ4 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ለምግብ እጥረት የዳረገው የድርቅ ችግር በቀጣይ ወራትም ሊስፋፋ እንደሚችል ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል። ከብሔራዊ ሚቲሮዎሎጂ ኤጀንሲ የወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከኤልኒኖ ክስተት ጋር ተያይዞ ከቀጣይ ጥቅምት ወር ጀምሮ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚያጋጥም ዓለም አቀፍ ትንበያ መኖሩን በመጥቀስ፣ …

መስከረም ፳፰ (ኅያ ስምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዳንግላ ዙሪያ ነዋሪ የሆነው አቶ ደግአረገ በአካባቢው ያሉ ወጣቶችን በትጥቅ ትግል ለሚታገሉ ሃይሎች እየመለመልክ ትልካለህ በሚል አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተደብድቧል። ማንነታቸውን በውል ለይቶ የማያውቃቸው ሰዎች አይኑን በጨርቅ ሸፍነው ወደ ባህርዳር እንደወሰዱትና በመጨረሻም መረጃ ሲያጡ ፣ አይኑን ሸፍነው እንደለቀቁት ገልጿል።

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በሃመር ወረዳ በዲመካ ከተማ ማክሰኞ የተጀመረው የስራ ማቆም አድማ እስከ ዛሬ የቀጠለ ሲሆን፣ የዞኑ ባለስልጣናት ነዋሪውን ለማነጋገር ስብሰባ ጠርተዋል። የስራ ማቆም አድማው መንስኤ ካለፉት 6 ወራት ጀምሮ በአካባቢው በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት ስራቸውን ለመስራት ስላላስቻላቸው ነው። የመንግስት ሰራተኞች እንደሚሉት ካለፈው ሰኔ ወር ጀምሮ በወረዳው …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሁለት ሳምንት በፊት በሳዑዲ አረቢያ ሚና አካባቢ በሀጂ ስነ-ስርዓት ወቅት በተከሰት ግፊያና መጨናነቅ በደረሰ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያዊያን ቁጥራቸው ከ47 በላይ የበለጠ ቢሆንም ፣ የኢህአዴግ መንግስት ለዚህ ከባድ ሐዘን የሰጠው ትኩረት ማነስ እንዳሳዘናቸው ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው በአዲስአበባ የሚኖሩ ሙስሊሞች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመጅሊሱን ወሬ በመያዝ …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በነሶልያ ሽመልስ የክስ መዝገብ በሽብረተኝነት በተከሰሱት ወጣት ጸሃፍት ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ ዳኞች “አዳማ ስልጠና ላይ ናቸው” በሚል ለ38 ኛ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል። ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ለ5ኛ ጊዜ ቀጠሮ አራዝሟል። በአንድ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል የተወሰኑት መለቀቃቸው፣ ቀሪዎቹም ይለቀቃሉ የሚል ተስፋ አሳድሮ ነበር። ድንበር የለሽ …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሶማሊያ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት አሚሶል ስር ያለውን ንብረነታቸው የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት የሆኑትን ሁለት ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን በደቡባዊ ምዕራብ ሶማሊያ በጌዶ ግዛት በደፈጣ ውጊያ ማውደሙን አልሸባብ አስታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአሊላን መንደር ውስጥ በአልሸባብና በኢትዮጵያ ሰራዊት መሃከል ለሰዓታት የቆየ የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነው። በአርፒጂ የጦር መሳሪያ ተሽከርካሪዎቹ መመታታቸውን የአካባቢው …

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት 4 ቀናት ያለማስጠንቀቂያ የተቋረጠው ኤሌክትሪክ፣ በንግድ ቤቶች እና በነዋሪዎች የእለት ተለት ህይወት ላይ ችግር ማስከተሉን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ የተቋረጠበት መንስኤ ለህዝቡ አለመገለጹንም ተናግረወዋል። ከዚህ በፊት በከተማው በተደጋጋሚ የ ኤሌክትሪክ መቋረጥ የሚከሰት ሲሆን ፣ ያሁኑ ደግሞ የተለየ ነው ሲሉ ነዋሪዎች በምሬት ይገልጻሉ። በከተማው በሳምንት አንድ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስከረም 13 ቀን 2008 ዓም የሃጅ ጸሎት ለማድረስ ወደ አገሪቱ ከተጓዙት ኢትዮጵያውያን መካከል 47 ሙስሊሞች መሞታቸውን የእስልምና ጉዳዮች ጠ/ምክር ቤት አስታውቋል። 24 ጸሎት አድራሽዎች ቆስለው ከሆስፒታል ሲወጡ ፣ 2ቱ አሁንም ተኝተው በመታከም ላይ ናቸው። በእለቱ በደረሰው አደጋ የሳውዲ መንግስት 700 ሰዎች እንደሞቱ ቢናገረም፣ በእየለቱ የሚወጣው አሃዝ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቡድኑ ነገ ሃሙስ ክሳቸው ለ37ተኛ ጊዜ በፍርድ ቤት የሚታየውና በመፃፋቸው ብቻ በአሸባሪነት ክስ ተወንጅለው በእስር ላይ የሚገኙት አራቱ የዞን 9 ጦማሪያን ቡድን አባላት ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ክሳቸው ተቋርጦ በነፃ እንዲለቀቁ ሲል አሳስቧል። ካለፈው ዓመት ጀምሮ በእስር ላይ ከሚገኙት ጋዜጠኞች አጥናፍ ብርሃነ፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣አቤል ዋበላ እና ናትናኤል …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ በማካሄድ ላይ ባለው 11ኛ ጉባኤ በተለያዩ ክልሎች ከ937 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን ገልጿል። ከክልሎች ሁሉ ከፍተኛ ገንዘብ ከስርቆት የዳነው በአማራ ክልል ነው ሲል አክሎ ጠቅሷል። በዚህ ጊዜ እንደተገለጸው ግልጽነት በጎደለው የግዢ ሂደት ሊባክን የነበረ ከ937 ሚሊየን ብር በላይ የህዝብ ገንዘብ ለማዳን ተችሏል። ከሙስና ጋር በተያያዘ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በህገወጥ መንገድ ድንበር አቋርጠው ኬንያ ሲገቡ መንገድ ላይ ያዝኳቸው ያለውን አስራ አራት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የኬንያ ፖሊስ ይዞ ማቻኮስ ፍርድ ቤት አቅርቧቸዋል።ስደተኞቹ የቀረበባቸውን ክስ ያልተቀበሉት ሲሆን የሃያ ሽህ ሽልንግ የገንዘብ ቅጣት ወይም የመቶሰላሳ ቀናቶች የእስር ቅጣት እንደሚበየንባቸውና ቅጣቱን ከከፈሉ በኋላ ወደ አገራቸው እንደሚላኩም ተገልጿል። ስደተኞቹ በናይሮቢ ሞንባሳ …

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎች እንደገለጹት በከተማው ቀበሌ 9 የድሃ ልጆች የሚማሩበትን መዋለ ህጻናት ትምህርት ቤት፣ ምርጫውን ሰበብ ተደርጎ ለፌደራል ፖሊስ በጊዜያዊነት ከተሰጠ በሁዋላ፣ ፖሊስ አለቅም በማለቱ ከነዋሪዎች ጋር ውዝግብ ተፈጥሯል። ፖሊስ በ15 ቀናት ቦታውን እንደሚለቅ ገልጾ፣ ትምህርት ቤቱን ቢረከብም፣ እስካሁን ድረስ ባለመልቀቁ ወላጆች ልጆቻቸውን ማስተማር አልቻሉም። ወላጆች አቤቱታ ለማቅርብ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ ካላካተቱዋቸው የቀድሞ ሚኒስትሮች መካከል የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ ሶፍያን አህመድ፣ የንግድ ሚኒስትሩ ከበደ ጫኔ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አለማየሁ ተገኑ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ አሚን አብዱልቃድር፣ የፕላን ኮምሽን ሚኒስትሩ አቶ መኮንን ማንያዘዋል ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም አቶ ሬድዋን ሁሴንን ከኮምኒኬሽን ሚኒስትርነት አንስተው የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ያደረጉዋቸው ሲሆን፣ የህዝበ ሙስሊሙን …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአመት በላይ ለሆነ ጊዜ በውጥረት ውስጥ የምትገኘዋ የጋምቤላና የደቡብ አዋሳኝ ከተማ ቴፒ፣ ባለፈው አንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ሶስት ዜጎች ተገድለውባታል። ከሳምንት በፊት የፌደራል ፖሊስ አባላት አንድ ሰው ከገደሉ በሁዋላ፣ ማንነታቸው በውል የማይታወቁ ሰዎች በወሰዱት የአጸፋ እርምጃ ደግሞ ከቴፒ 7 ኪሜትር እርቀት ላይ በምትገኝ ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ2008 ዓ.ም በ መንግስት ያዘጋጀውን የፖለቲካ ስልጠና ለመሳተፍ ፈቃደኛ ያልሆኑ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ደሞዛቸው እንዳይከፈል በመታገዱ የምንበላውና የቤት ኪራይ የምንከፍለው አጥተናል ሲሉ ገልጸዋል።በስብሰባው ላይ የተገኙ መምህራን ደሞዝ ሲከፈላቸው በተለያዩ ምክንያቶች ያልተሰበሰቡት መምህራን ደግሞ ደሞዝ እንደማይከፈላቸው ተነግሯቸዋል። በአዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህራን ወደ ውጭ እንዳይወጡ ታግደው ስልጠናውን በግድ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመስተዳድሩ 10 ክፍለ ከተሞችና 116 ወረዳዎች የሚገኙ የኢህአዴግ ካድሬዎች የሹም ሽር እና የሹመት ቦታ ለውጥ መረጃዎች የታወቁ ሲሆን፣ የማዕከል መ/ቤት ቢሮዎችና ሹም ሽር ድልደላ በዚህ ሳምንት የሚጠናቀቅ ሆኖ፣ በወረዳዎችና ክፍለ ከተሞች አጠቃላይ ቁጥራቸው ከ800 የማያንሱ አመራሮች በሙስና፣ከድርጅቱ ጋር ባላቸው ተቃርኖ፣ በአመራር ብቃት ማነስ እንዲሁም በትምህርት ደረጃ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል መንገድ ስራ መስሪያ ቤት ውስጥ የሚታዩ በርካታ የአሰራር ችግሮች ለከፍተኛ ሙስና ሊያጋልጡ እንደሚችሉ በመናገር በየጊዜው እንዲስተካከሉ ሰራተኛው ቢጠየቅም፣ ከዓመት ዓመት አለመቀረፋቸው በስርዓቱና አመራሮች እምነት እንዲያጡ እንዳደደረጋቸው የኦዲት ባለሙያዎች በዓመታዊው የሰራተኞች ስብሰባ ላይ ገልጸዋል፡፡ በባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ስር በሚገኙ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች በተደረገ አጠቃላይ ምርመራ …

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዩኒቨርሳል ቲቪ ጋዜጠኞች የታሰሩት፣ ሁለት የፓርላማ አባላትን ጋብዘው የኢትዮጵያ ጦር በአገሪቱ ውስጥ መቆየት አለበት የለበትም የሚል ክርክር በማድረጋቸው መሆኑን የጣቢያው የዜና ክፍል ሃላፊ የሆነው ጋዜጠኛ አብዱላዚዝ ኢብራሂም ሙሃመድ ተናግሯል። በርካታ የሶማሊያ ዜጎች የኢትዮጵያ ጦር በሶማሊያ መቆየቱን መቃወም ጀምረዋል። ሟቹ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አልሸባብን በ2 ሳምንታት ውስጥ …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ሰራተኞች ላይ ከኢሕአዴግ መንግስት የሚሰነዘረው የፖለቲካ ጠልቃ ገብነትና አፈና ከመቼውም ጊዜ የከፋ ደረጃ ላይ መድረሱን የአዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራን በምሬት ተናግረዋል። የኢሕአዴግ መንግስት “ስልጠና’ በሚል ስም በአገር-አቀፍ ደረጃ ካዘጋጃቸው ስብሰባዎች አንዱ በሆነው ሰብሰባ ጠቅላላውን የአዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሰራተኞች ከሰኞ መስከረም 10 እስከ …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት እና አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ 4 ሚሊዮን 500 ሺ ህዝብ በረሃብ መጠቃታቸውን ይፋ ቢያደርጉም፣ በከተሞች የምግብ እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር ሲጨመር አጠቃላይ የተረጅዎችን ቁጥር ከ8 ሚሊዮን በላይ ሊያደርሰው እንደሚችል መረጃዎች አመልክተዋል። በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ሪፖርት ሲደረግ የቆየው በገጠሩ የሚታየው ችግር ብቻ ነው። ይሁን እንጅ የከተማና …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደቡብና የጋምቤላ አዋሳኝ በሆነቸው ቴፒ ከተማ በየጊዜው የሚታየው የጸጥታ ችግር ሰሞኑን እንደገና አገርሽቶበታል። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ካለፈው አመት ጀምሮ ከፍ ዝቅ እያለ ሲካሄድ የነበረው ግጭት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፣ በህዝብና በመንግስት መካከል ያለው ልዩነትም ሰፍቷል። መስከረም 20 ብርሃኑ የተባለ የዩኒቨርስቲ ጥበቃ የተገደለ ሲሆን፣ ለግድያው እስካሁን ሃላፊነቱን የወሰደ …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በጉንዶ መስቀል ከተማ በሶስት ቀበሌዎች የሚገኙ ከ1 200 በላይ ቤቶች እንዲፈርሱ መወሰኑን ተከትሎ በከተማው ውጥረት ነግሷል። የከተማው ባለስልጣናት ህዝቡን ሰብስበው ቤቶቻችሁን አፍርሱ ብለው ትእዛዝ ሲሰጡ፣ ነዋሪዎቹ ግን አጥብቀው ተቃውመዋል። መስከረም 13 ቀን በከተማው የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በፌደራል ፖሊሶች ቢጨናገፍም፣ ውጥረቱ አሁንም …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዛሬ ጠዋት በሳሸመኔ ተክለሃይማኖት ቤ/ክርስቲያን መቅደስ ውስጥ ካህናትና ዲያቆናት እርስ በርስ በመደባደባቸው ሰዎች ተገድተዋል። የግጭቱ መንስኤ የቆየ መሆኑን የሚናገሩት ምእመናኑ ዛሬ የተፈጠረው ድርጊት ግን ያልተጠበቀ ነው። ካህናቱ ጎራ ለይተው መደባደባቸውን ተከትሎ አካባቢው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎአል። ኢሳት ከገለልተኛ ወገን ለማጣራት ባይችልም፣ በሰአቱ የተኩስ ድምጽም ተሰምቷል። ጥይቱን …

መስከረም ፳፬ (ኅያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች “መልካም ስም ከመቃብር በላይ ዘላለማዊ ሆኖ ይኖራል” በሚል ርዕስ ባወጡት መግለጫ፣ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት እንዲረጋገጥ፤ ብሎም ለአዲሱ የፕሬስ ትውልድ ፈር ቀዳጅ የነበረው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሉሌ ከዚህ አለም በሞት መለየቱ ለብዙዎች የኢትዮጵያ ነጻ-ፕሬስ ጋዜጠኞች እና ቤተሰቦች መሪር ሃዘን ነው ብለዋል። ጋዜጠኛ …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ ነገረ ኢትዮጰያ ሪፖርተር ዘገባ ከአምስቱ እስረኞች መካከል አንዱ የሆነው የአንድነት ፓርቲው አቶ ዳንኤል ሽበሽ ጨለማ ቤት ታስሮ ይገኛል። የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 14/2007 ዓ.ም ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲለቀቁ ወስኖላቸው የነበሩት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ የሽዋስ አሰፋ፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ዳንኤል …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሱዳን ትሪቢዪን እንደዘገበው ፕሬዚዳንት ኡመር ሀሰን አልበሽር ይህን ያረጋገጡት፤ ዛሬ ሀሙስ ከኤርትራው የፋይናንስ ሚኒስቴር ከአቶ ብርሀኔ ሀብተማርያም ጋር ካርቱም ውስጥ ባደረጉት ውይይት ነው። ሰሞኑን ካርቱም በኤርትራ የነበሩ የኢትዮጰያ አማጽያንን ወደ ኢትዮጵያ አሸጋግራለች የሚል መረጃ መውጣቱን ተከትሎ በኤርትራና በሱዳን መካከል ያለው ግንኙነት ሊሻክር እንደሚችል እየተነገረ ባለበት በአሁኑ …

መስከረም ፳፩ (ኅያ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ይህን ያሉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የህዝብ ግንኙነት ዋና የስራ ሂደት መሪ አቶ ስዩም አድማሱ ናቸው። ሀላፊው በ2002 ዓ.ም በታቀደው የመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ በትምህርት ዘርፍ በርካታ ያልተሳኩ የአፈጻጸም ችግሮች መኖራቸውን ሰሞኑን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ባለፉት አምስት ዓመታት በትምህርት ዘርፉ …