ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

የቅዳሜ ምሽት የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም በዘንድሮው Grammy Award በስድስት የተለያዩ ከፍሎች ብእጩነት ቀርቦ በአራቱ አሸንፎ 4 ዋንጫዎችን ይዞ እቤቱ የገባውን የ Sam Smithን ሙዚቃዎቸ ያካትታል

 

የመሠረተ ልማት ሕጎች በሀገሮች መካከል የሚፈጠሩ ግንኙነቶችን ከሌሎች ሀገሮች በተሻለ መንገድ እንደሚያስተሳስሩ አንድ ጥናት አመለከተ።

የአፍሪካ ቀንድ ሀገሮችን የሚያስተሳስሩ በርካታ የመሠረተ-ልማት ፕሮጄክቶች ቢቀረፁም ለማስፈፀም እንቅፋት የሚሆን ብርቱ የገንዘብ እጥረት እንዳለም ተጠቁሟል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት ዶክተር ነጋሦ ጊዳዳ ትላንት እዚህ በዩናይትድ ስቴትስ The National Endowment For Democracy የተባለው ዓለምአቀፍ የጥናት ተቋም ባመቻቸላቸው መድረክ ላይ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል።

 

ዶክተር ነጋሦ ባቀረቡት በዚህ ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ ያተኮሩት እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር “ሕገ-መንግሥቱ የሁሉንም ብሄረሰቦች ፍላጎት ማንፀባረቅ ያስፈልገዋል” በሚለው ላይ ነው።

 

በኢትዮጵያ የፊታችን ግንቦት ስለሚካሄደው ምርጫ፥ በሀገሪቱ ስለታየው የረዝም ጊዜ መረጋጋትና ልማትም በጽሁፋቸው ዳሰዋል።

 

ሰሎሞን ክፍሌ በስፍራው ነበር። ተከታዩን አዘጋጅቷል።

 

 

የዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም በአሜሪካ የቢል ቦርድ ሰንጠረዥ ላይ ከመቶዎቹ ምርጥ ዜማዎች መካከል በዚህ ሳምንት ከአንድኛ እስከ አስረኛ ደረጃ የወጡትን ምርጥ ዜማዎች ያካትታል፡፡