ርዕሳነ መምህራን መብታችን አልተከበረልንም አሉ
ሰኔ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ርዕሳነ መምህራን በልዩ ልዩ ምክንያት ከቦታቸው ሲነሱ በአስተማሪነት የሚያገለግሉ ቢሆንም በዲግሪ ሲከፈላቸው የነበረው ደመዎዝ ተቀንሶ በዲፕሎማ ፣በሁለተኛ ዲግሪ የተመርቁ ደግሞ በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሰሩ በመደረጋቸው እንዲሁም በራሳቸው ጥረትና ገንዘብ ዲግሪያቸውን የያዙ መምህራን በተመረቁበት የትምህር ዓይነት ማስተማር ባለመቻላቸው መምህራኑ ዲግሪያቸውን እንደተቀሙ እንደሚቆጥሩት ተናግረዋል፡፡ ቅሬታ አቅራቢ ርዕሳነ መምህራኑና መምህራኑ …