ሰኔ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ርዕሳነ መምህራን በልዩ ልዩ ምክንያት ከቦታቸው ሲነሱ በአስተማሪነት የሚያገለግሉ ቢሆንም በዲግሪ ሲከፈላቸው የነበረው ደመዎዝ ተቀንሶ በዲፕሎማ ፣በሁለተኛ ዲግሪ የተመርቁ ደግሞ በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሰሩ በመደረጋቸው እንዲሁም በራሳቸው ጥረትና ገንዘብ ዲግሪያቸውን የያዙ መምህራን በተመረቁበት የትምህር ዓይነት ማስተማር ባለመቻላቸው መምህራኑ ዲግሪያቸውን እንደተቀሙ እንደሚቆጥሩት ተናግረዋል፡፡ ቅሬታ አቅራቢ ርዕሳነ መምህራኑና መምህራኑ …

ሰኔ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየካ ክፍለ ከተማ የግንቦት 16/2007 ዓ.ም የምርጫ ውጤት እንዲሁም የግንቦት 20 በዓልን ለማክበር ግንቦት 292007 ዓ.ም ባዘጋጀው ግብዣ ላይ የኢህአዴግ ካድሬዎች እርስ እርሳቸው መደባደባቸውን ምንጮች ገለጸዋል፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 መሰብሰቢያ አዳራሽ በተደረገው ግብዣ ብዙ ወጭ የፈሰሰበትና በርካታ የኢህአዴግ ካድሬዎች የተገኙበት እንደነበር የገለፁት ምንጮቹ፣ ስጋና ሌሎች ለግብዣው …

ሰኔ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የ1997 ዓም ምርጫ ተከትሎ በአጋዚ ወታደሮችና በፌደራል ፖሊስ አባላት የተገደሉ ኢትዮጵያውያን እየተዘከሩ ነው። በአቶ ማሙሸት አማረ የሚመራው መኢአድ ለሰማአታቱ 10 ሻማዎችን በማብራት ዕለቱን አስቦ የዋለ ሲሆን፣ በእስር ላይ የሚገኙ መሪዎችና አባላቱ እንዲፈቱ ከመጠየቅ በተጨማሪ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ኢትዮጵያውያን የሰማዓታቱን ፎቶ ግራፎች በፌስቡክና በማህበራዊ ድረገጾች በመለጠፍ እየዘከሩዋቸው ነው። …

ሰኔ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጀቱ ለአንድ አመት ሲያካሂድ የነበረውን ጥናት በሚቀጥሉት 2 ሳምንታት ውስጥ ይፋ የሚያደርግ ሲሆን፣ በሪፖርቱ የኤርትራ መንግስትን ይወቀሳል። የኤርትራ ህዝብ ከህግ ይልቅ በፍርሃት ነው የሚገዛው የሚለው ድርጅቱ፣ ከፍርድ ቤቶች እውቅና ውጭ ሰዎች በዘፈቀደ ይገደላሉ ብሎአል። ወጣቶች አገራቸውን ጥለው እንደሚሰደዱና ገደብ ለሌለው ብሄራዊ ውትድርና አግልግሎት እንደሚሰጡ ሪፖርቱን ዋቢ በማድረግ የተለያዩ …

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጋምቤላና ደቡብ ክልል አዋሳኝ ከተማ በሆነቸው ቴፔ ትናንት ሌሊት 11 ሰአት ላይ ለተሻለ ፍትህና ነጻናት እንታገላለን የሚሉ ታጣቂዎች በአንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ በወሰዱት እርምጃ 3 የሌሊት ተረኛ ፖሊሶች ሲገደሉ በርካታ እስረኞችንም አስፈትተዋል። ቁጥራቸው ከ100 እስከ 150 የሚሆኑ በቴፒና አካባቢው የሚታየውን ዘረኝነትና የአስተዳደር በደል እንዋጋለን በማለት ራሳቸውን …

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ያለፉትን 9 ወራት በእስር ሲማቅቁ የቆዩት የሰማያዊ፣ የቀድሞው አንድነትና የመኢኢድ ፓርቲዎች የአመራር አባላት ላይ ክስ መመስረቱን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። በአንደኛ ተከሳሽ ጌታቸው መኮንን መዝገብ 16 ሰዎች በሽብር ወንጀል መከሰሳቸውን ጋዜጣው ዘግቧል። ተከሳሾቹ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን ፣ በላይነህ ሲሳይ፣ አለባቸው ማሞ፣ አወቀ ሞኝሆዴ፣ ዘሪሁን በሬ፣ ወርቅየ …

ግንቦት ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እኩለቀን ላይ ሸራ ተራ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የተነሳው ቃጠሎ በርካታ የንግድ ቤቶችን አውድሟል። የእሳት ማጥፋያ መኪኖች እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረት ቢያደርጉም፣ ይህን ዘገባ እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ከቀኑ 11 ሰአት ድረስ እሳቱ በቁጥጥር ስር አልዋለም። ዘጋቢያችን እንደገለጸው በቃጠሎው ከፍተኛ ንበረት ሳይወድም አልቀረም። የእሳቱ መንስኤ በውል አለመታወቁንም ገልጿል።

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምንጮች እንደገለጹት የሶማሊ ክልል ልዩ ሚሊሺያ አባላትና የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በወሰዱት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አልቀዋል። ሂራን በተባለው አካባቢ ለቀናት በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት መንስኤ በውል አልታወቀም። ዛሬ በማህበራዊ ድረገጾች የተላለፈው አስደንጋጭ ቪዲዮ በርካታ የሞቱ ሲቪሎችንና የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ያሳያል። ቪዲዮውን የለቀቀው የአልጃሲራ …

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግሎባል ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ ባወጣው ልዩ ዘገባ በፈረንጆች አቆጣጠር ከ2008 እስከ 2012 ባለው ጊዜ ውስጥ ከኢትዮጵያ በተለያዩ ህገወጥ መንገዶች ከ70 በሊዮን ብር ወይም ከ3 ቢሊዮን 550 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወደ ውጭ ወጥቷል። በ5 ዓመታት ውስጥ ተሰርቆ የወጣው ገንዘብ ወደ አገሪቱ ከገባው የውጭ የቀጥታ ኢንቨስትመንት መጠን ጋር …

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ የሚታየው ከፍተኛ የዶላር እጥረት መባባሱን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።በአስመጭና ላኪነት ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ስራቸውን መስራት እንዳልቻሉ አቤቱታ በማቅርብ ላይ ናቸው። በርካታ ፋብሪካዎችም በዶላር እጥረት የተነሳ የመለዋወጫ እቃዎችን ማስገባት አለመቻላቸውን እየገለጹ ነው። መንግስት የዶላር ችግር እንደሌለ በተደጋጋሚ ቢናገርም፣ በመሬት ላይ ያለው እውነታ ከዚህ እንደሚለይ ነጋዴዎች ይገልጻሉ። …

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው የግንቦት20 በአልን ለማክበር ጀርመን በርሊን ውስጥ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ ያልተጠበቀ ክስተት መታየቱን ምንጮች ገልጸዋል። በዝግጀቱ ላይ የኢትዮጵያና የጀርመን ከፍተኛ ባለስልጣናት በእንግድነት ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ መዝሙር ያለምንም ችግር የተፈጸመ ቢሆንም፣ የጀርመን ብሄራዊ መዝሙር በሚዘመርበት ጊዜ ግን የጀርመንን ባለስልጣናት ያስደነገጠ መዝሙር ቀርቧል። የኢትዮጵያ ኢምባሲ …

ግንቦት ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ አሊ በኡስታዝ አቡበክር አህመድ መዝገብ ተከሶ የሚገኝ ሲሆን፣ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ፣ በሌሉበት የ15 አመት ጽኑ እስራት ፈርዶባቸዋል። ታህሳስ 23/2005 የዋለው ችሎት አቶ አሊን በነጻ ቢያሰናብታቸውም፣ አቃቢ ህግ ይግባኝ ብሎባቸው ክሱ እንደገና እንዲታይ ተደርጓል። በአቶ አሊ ላይ የተሰጠው ውሳኔ በሌሎች የድምጻችን ይሰማ የመፍትሄ አፈላላጊ …

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዋና ኦዲተር የ2006 ዓ.ም የመንግስት መ/ቤቶች የሂሳብ ሪፖርት ትላንት ለፓርላማው ያቀረበ ሲሆን በዚህ ሪፖርቱ ያለምንም ማስረጃ ገንዘብ ያወጡ 19 መንግስታዊ ተቋማት የተገኙ ሲሆን እነዚህ ተቋማት በድምሩ ከ473 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አውጥተው ተገኝተዋል፡፡ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ ላቅ ያለውን ድርሻ ማለትም 274 ሚሊየን ብር ያወጣው የብሔራዊ መረጃና …

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦጋዴን ነጻ አውጭ ግንባር ለኢሳት በላከው መግለጫ ፣የኦብነግ ሁለቱ ተደራዳሪዎች አቶ ሱሉብ አህመድና አቶ አሊ ሁሴን ፣ እኤአ ሰኔ 1 ቀን 2015 በኢትዮጵያ የደህንነት ባለስልጣን አጃቢነት የኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር ከተማ የሆነችው ሞያሌ ደርሰዋል። ሁለቱ ልኡካኖች ናይሮቢ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተገናኝተዋል። ኦብነግ ተወካዮቹ በኬንያ መንግስት እና በአለማቀፍ …

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምርጫ ቦርድ ትእዛዝ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ የተደረጉት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዝዳንት አቶ ማሙሸት አማረ ፣ ግንቦት 25/2007 ዓም ፍርድ ቤት ከእስር እንዲለቀቁ ቢወስንም ፣ ፖሊስን ግን መልሶ አስሯቸዋል። አቶ ማሙሸት ሚያዚያ 14፣ 2007 በአይ ኤስ የተገደሉ ኢትዮጵያውያንን በማስመልከት ድርጊቱን ለማውገዝና ኢትዮጵያውያኑንም ለመዘከር በተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ …

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የውዝግቡ መነሻ ተማሪዎች የሰኔ ጾምን ለመጾም በመፈለግ ዩኒቨርሲቲው የጾም ምግብ እንዲያዘጋጅላቸው በመጠየቃቸውና ዩኒቨርስቲው ፍቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ ነው፡፡ የዩኒቨርስቲው አስተዳደር ተማሪዎች ላቀረቡት ጥያቄ ዳቦ እየበላችሁ መጾም ትችላላችሁ የሚል መልስ ሰጥቷቸዋል። ዩኒቨርሲቲው ለስጋ የሚወጣውን በጀት ለሽሮ ቢወጣ ይቀንስ እንደሆን እንጂ ተጨማሪ ወጪ አያስከትልበትም ያሉት ተማሪዎቹ በግዳጅ እምነታችንን እንድንተው …

ግንቦት ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት 3 ሳምንታት በአውስትራሊና ኒውዚላንድ የተለያዩ ከተሞች የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ በማድረግ ላይ የሚገኘው አርበኞች ግንቦት 7 ባለፈው ዕሁድ ሜይ 31ቀን በሜልበርን ከተማ የተሳካ የገንዘብ ማሰባሰብ ዝግጅት ማካሄዱን ሃና ጋረደው ከስፍራው ከላከችልን ሪፖርት ለመረዳት ተችሎአል በርካታ የሜልበርንና አካባቢዋ ነዋሪዎች በተገኙበት በዚህ ታላቅ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ የአርበኞች …

ኢሳት ዜና (ግንቦት 25, 2007) በኢትዮጵያና ጎረቤት ሶማሊያ ድንበር አካባቢ የተቀሰቀሰዉን ግጭት ተከትሎ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ወታደራዊ ሃይል ወደስፍራው ማሰማራቷ ተገለፀ። በእስካሁኑ የኢትዮጵያ ልዩ ሃይሎችና በሶማሊያ የጎሳ ታጣቂዎች መካከል በተካሄደዉ ግጭት በትንሹ ከ50 በላይ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን፤ የሶማሊያ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ የፀጥታ ሃይሎች የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈፅመዋል ሲሉ ተቃዉሞ ማሰማታቸውን ሶማሊ ከረትን የተሰኘ ጋዜጣ ዘግቧል። የጋልጋይዱድ ክልል …

ግንቦት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአንድ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ከኬንያ ተጠልፈው ወደ ኢትዮጵያ ተወስደው የነበሩት አቶ ሱሉብ አብዲ አህመድና አቶ አሊ አህመድ ሁሴን ትናንት ምሽት ኬንያ ናይኖቢ መግባታቸውን ለኢሳት ደረሰው መረጃ አመልክቷል። ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮች በምን ሁኔታ ወደ ናይኖቢ እንደተመለሱ የታወቀ ነገር የለም። የድርጅቱ የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አብድረህማን …

ግንቦት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አይ ኤስ የተባለው አሸባሪ ቡድን በኢትዮጵያውያን ላይ የወሰደውን ዘግናኝ እርምጃ ለማውገዝ በተጠራ ሰልፍ ላይ የመንግስትንና የፖሊስን ስም አጥፍተዋል የተባሉ ወጣቶች በእስርና በገንዘብ ተቀጥተዋል። አስማማው ወልዴ፣ የማነ ወርቅነህ፣ ስንታየሁ ታሪኩ፣ ያሲን ቃሲምና ይግረማቸው አበበ ሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓም ጠ/.ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ድምጻቸውን ከፍ …

ግንቦት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግል ድርጅት ሠራተኞች የጡረታ አዋጅን በማሻሻል ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ፕሮቪደንት ፈንድ ሲያጠራቅሙ የቆዩ የግል ሠራተኞችን በጡረታ እንዲታቀፉ በማድረግ ሰበብ ፕሮቪደንት ፈንዳቸውን ለመውረስ የሚያስችል ሕግ ሰሞኑን ለፓርላማ መቅረቡ ከተሰማ ወዲህ በርካታ ሠራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጋር በመነጋገር ገንዘባቸውን ሕጉ ከመተግበሩ በፊት እያወጡ መሆኑን ዘጋቢያችን ገልጿል፡፡ ፓርላማው የቀረበለት የግል ድርጅት …

ግንቦት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጣና ሃይቅ ላይ በቱሪስት ጀልባ ትራንስፖርት የሚያገለግሉ የጀልባ ባለሃብቶችና ካፒቴኖች፣ “የአማራ ክልል ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ‘ህገ ወጥ’ ናችሁ በሚል ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ አስራ ሰባት ጀልባዎችን ከሶስት ወር በላይ በማሰሩ ቤተሰቦቻቸውንና ራሳቸውን ለማስተዳደር መቸገራቸውን ተናግረዋል፡፡ ሶስት መቶ ያህል ቤተሰብ የሚያስተዳድሩት ቅሬታ አቅራቢዎች ፣ ለአመታት በስራው ላይ ሲቆዩ …

ግንቦት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፉት ሁለት ሳምንታት የኢትዮጵያ እና የኬንያ ድንበር የተለያዩ ግጭቶችን አስተናግዷል እንደ አይን ምስክሮች ገለጻ። ዩኒፎርም የለበሱ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ኬንያ በመግባት የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባር አባላትን ለማደን ቢሞክሩም እስካሁን አልተሳካላቸውም። የመንግስት ወታደሮች ወደ ኬንያ ሞያሌ ከተማ በመግባት ቦሩ ሁካ የተባለ የ55 ዓመት የትምህርት ቤት ዘበኛ በጥይት …

ግንቦት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰሜን ጎንደር ዞን ማክሰኝት ከተማ ነዋሪ መሆናቸው የተነገረው አቶ ዘመነ ምህረቱ እና ሌሎች የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሽብርተኝነት ክስ እንደተመሰረታባቸው ሪፖርተር ዘግቧል። አቶ ዘመነ የመኢአድ ምክትል ፕሬዚዳንት መሆናቸው በክሱ የተመለከተ መሆኑን የዘገበው ጋዜጣው፣ መስከረም 18፣ 2007 ዓም በጎንደር በሚገኘው የመኢአድ ጽ/ቤት ውስጥ አባላትን በመሰብሰብ ” የወያኔ መንግስት …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ በዲመካ ከተማ እና አካባቢዋ የሚኖሩ አርብቶአደሮች ” እኛ ድምጽ ሳንሰጥ” እንዴት ኢህአዴግ አሸነፈ ይባላል በሚል ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ሲታኮሱ መቆየታቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አንድ ሻለቃ ጦር እና የፌደራል አባላት ወደ አካባቢው በመንቀሳቀስ በወሰዱት እርምጃ ከፍተኛ ጉዳት …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስከበር በሚያደርገው ቀጣይ ትግል ህብረተሰቡ ከጎኑ እንዲቆምም ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል። የፓርቲው አመራሮች “‹‹ነጻነት በሌለባት ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው!›› በሚል ርእስ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በምርጫው ሂደት በመቆየታቸው የኢህአዴግን አውሬነት ማሳየታቸውን በመጥቀስ፤ ‹‹በኃይል በተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስት በህዝብ ተቀባይነት የለውም››ብለዋል። ‹‹ምርጫው ከዚህ …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባና በክልሎች የኤሌክትሪክ ኃይል በየዕለቱ እየተቆራረጠ ምርታማነት ባሽቆለቆለበት በዚህ ወቅት ሚኒስቴሩ ለጎረቤት ሀገራት ባለፉት 10 ወራት ብቻ 606 ነጥብ 5 ሚሊየን ኪ.ዋ. የኤሌክትሪክ ኢነርጂ በመሸጥ ዳጎስ ያለ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አድርጓል፡፡ በሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግር ከጊዜ ወደጊዜ ተባበሶ በቀን በአማካይ አንድ ጊዜ የሚጠፋበትና …

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቄራ ምድብ ችሎት የቀረበችው ወ/ሮ ንግስት፣ መንግስት በሊቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ በአይ.ኤስ.አይ.ኤስ የሽብር ቡድን የተፈጸመውን የሽብር ድርጊት ለማውገዝ ሚያዝያ 14/2007 ዓ.ም አዲስ አበባ ላይ ጠርቶት በነበረው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳትና ሰላማዊ ሰልፍን በማወክ›› ተጠርጥራ እንደታሰረች ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቱን …

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ የግንቦት15ቱን ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉ ከተገለጸ በሁዋላ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል። ምንጮች እንደገለጹት በርካታ ፊደል ቀመስ አባሎቹ ኢህአዴግ አሸነፍኩ ያለበትን የድምጽ ልዩነት አልተቀበሉትም። ውጤቱን የሚቃወሙ የግንባሩ አባላት ” ህዝቡ ከእንግዲህ በሰላም መንግስት እቀይራለሁ የሚለው እምነቱ ተሟጦ የሃይል አማራጭን ብቻ እንዲመለከት ከማድረጉም በላይ፣ የሃይል አማራጭን የሚከተሉ ሃይሎች …

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ አዲስ ስታንዳርድ ዘገባ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው የባንኩ የቦርድ ስብሰባ ላይ ነው ለፕሬዚዳንትነቱ ሲወዳደሩ ከነበሩት ስምንት ዕጩዎች መካከል የገንዘብ ሚኒስትሩ ሶፊያን አህመድ የሴራውሊዮኗን ሳሞራ ሚሸል ካማራን ተከትለው ሁለተኛው ተሰናባች ሆነዋል። ቦርዱ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር ባለፈው ፌብሩዋሪ 11 ቀን አቢጃን በሚገኘው የባንኩ ዋና ጽህፈት ቤት ባደረገው ስብሰባ ባንኩን …

ኢሳት ዜና ግንቦት 18 2007 በየመን መዉጫ አጥተዉ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን መካከል በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸዉን ጨምሮ ከሁለት እሺ በላይ ሰደተኞችን ከየመን ወደ ኢትዮጵያ ማጓጓዙን አለም አቀፉ የስደተኞች ተቋም ገለጠ። ድርጅቱ የሳዉዲ አረቢያ፥ ሱዳንና፥ ጂቡቲን የድንበር ግዛት በመጠቀም ስደተኞቹን ወደአገራቸዉ መመለስ መቻሉን አስታዉቋል። በየመን መዉጫን አጥተዉ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች መንግስት ዜጎችን ለመታደግ በቂ ጥረት አላደረገም ሲሉ …

ሚያዝያ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ በዲመታ ከተማ እና አካባቢዋ የሚኖሩ አርብቶአደሮች ” እኛ ድምጽ ሳንሰጥ” እንዴት ኢህአዴግ አሸነፈ ይባላል በሚል ከሰኞ ጀምሮ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር መጋጨታቸው ታውቋል። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት ነዋሪዎቹ በምርጫው ማግስት የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ሲጀመሩ በጸጥታ ሃይሎች የተከለከሉ ሲሆን፣ ይህን ተከትሎ አርብቶአደሩ …

ሚያዝያ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወ/ሮ ንግስት በደቡብ ክልል የምርጫ ቅስቀሳ አድርጋ ስትመለስ መታሰሩዋን ባለቤቱዋ ለኢሳት የገለጸ ሲሆን፣ የ3 አመት ህጻን ልጇም አብራ ከታሰረች በሁዋላ እንደመለሱለት አክሏል። ለምርጫ ቅስቀሳ ወጥተው የነበሩ ብዙ ወጣቶች እየተፈለጉ መሆኑን መረጃው እንደደረሳትና እርሱዋም እንደምትታሰር አውቃ ወደ አዲስ አበባ መመለሱዋን ባለቤቱ ገልጿል። በአዲስ አበባ አይ ኤስ ኤስ …

ሚያዝያ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሶስቱ ጋዜጠኞች ግንቦት 19/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ አሉኝ ባላቸው ሲ.ዲዎች እና ቀሪ ምስክሮቹ ላይ ብይን ሰጥቷል፡፡ ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ ምስክሮቹን ለማቅረብ በተደጋጋሚ የሰጠውን እድል ባለመጠቀሙ እና ምስክሮቹን ላለማቅረቡ የሰጠው ምክንያትም በቂ ባለመሆኑ አቃቤ …

ሚያዝያ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው እሁድ ግንቦት15 ፣ 2007 ዓም የተካሄደው ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንደተካሄደ መንግስትና ብቸኛው የውጭ ታዛቢ የአፍሪካ ህብረት ቢገልጽም፣ በምርጫው የተሳተፉ ታዛቢዎችና መራጮች ምርጫው በአሳዛኝ ሁኔታ መካሄዱን መስክርነታቸውን እየሰጡ ነው። በአዲስ አበባ የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢ የነበረው አቶ መሰለ አድማሴ እንደገለጹት እርሳቸው በታዘቡበት የምርጫ ጣቢያ፣ …

ሚያዝያ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት አይ ኦም ኤም፣ የመን ውስጥ በችግር ላይ የነበሩ 2061 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው መመለሱን አስታውቋል። ከተመሰሉት መካከል የቆሰሉ ኢትዮጵያውያንም አሉበት። አይ ኦ ኤም በአዲስ አበባ ጊዚያዊ ማቆያ ጣቢያ ተመላሾችን በማስፈር የትራንስፖርት እና የጤና አገልግሎት መስጠቱን አስታውቋል። ሃድራ የተባለች ተመላሽ በቤት ሰራተኛነት ስትሰራ እንደነበር …

ሚያዝያ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በእስር ላይ በሚገኙ ዞን ዘጠኝ በሚል መጠሪያ ስም በሚታወቁት ወጣት ጸሃፊዎች ላይ ምስክሮች ቀርበው ፣ የክሱን ጭብጥ በደንብ በማያስረዳና ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት የሌላቸውን ነገሮች በመናገር ማሳለፋቸውን ችሎቱን የተከታሉት ታዛቢዎች ገልጸዋል። ችሎቱን ለመከታተል የታደሙ ታዛቢዎች ምስክሮች ሲንተባተቡ እያዩ ችሎት ውስት ይስቁ እንደነበር ታዛቢዎች ገልጸዋል። ወጣት ጸሃፊዎቹ …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ በፓርላማ ተገኝተው ከኢህአዴግ የም/ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸውን ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን በዚህ ምላሻቸውም በስም ያልጠቀሱዋቸውን ተቃዋሚዎች አስጠንቅቀዋል። የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ወደምርጫው የገቡት በግማሽ ልብ መሆኑን ፣ የብጥብጥና የሁከት አማራጭ ከተገኘ ያንን ለማካሄድ የሚያስቡ ናቸው ሲሉ ፈርጀዋቸዋል። ” የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎቹ በአንዳንድ አካባቢዎች ከወዲሁ እኛ አሸንፈናል፣ ከተሸነፍን …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ረዩተርስ ከካይሮ እንደዘገበው በሳውድ አረቢያ የሚመራው የጥምር ሃይል በየመን በአንድ አለማቀፍ የበጎ አድራጎት ጽህፈት ቤት ላይ በወሰደው ጥቃት 5 ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ 10 የሚሆኑት ደግሞ ቆስለዋል። ጥቃቱ የሃውቲ ሚሊሺያዎች ዋና ደጋፊ ተደርጎ በሚቆጠረው ሃጅያ ግዛት ውስጥ በሚገኘው ማይዲ ከተማ ላይ በከባድ መሳሪያና በአየር መፈጸሙን የዜና ድርጅቱ ገልጿል። …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ2005 ዓም ቁጥራቸው ከ20 ሺ ያላነሰ በአብዛኛው ከመስራቅና ምእራብ ጎጃም የመጡ ዜጎች፣ ክልሉን ለቀው እንዲወጡ በመታዘዛቸው ቁጥራቸው በውል ያልተወቁት መንገድ ላይ ሲሞቱ፣ ሌሎች ደግሞ ቤት ንብረታቸውን አጥተዋል። በጊዜው ኢሳትና ሌሎች የመገናኛ ብዙሃን ባደረሱት ተጽኖ መንግስት ተፈናቃዮች እንዲመለሱ ቢያደርግም፣ አጥፊዎችን ለፍርድ የማቅረቡ ጉዳይ ለረጅም ጊዜ ሲጓተት ቆይቶ …

ሚያዝያ ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል፤ አባላትን መልምለዋል፤ ለሽብርተኛ ቡድኑ መረጃ አቀብለዋል፤ እንዲሁም ወደኤርትራ በመኮብለል የሽብር ድርጅቱን ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ተሰናድተው ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ በሚል የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በ7 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመሰርቱን …

ሚያዝያ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢው ፓርቲ ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ ህዝቡን አስተባብረው ህዝባዊ አመጽ ያስነሱ ይሆናል በሚል የሚጠረጥራቸውን ወጣቶች ሁሉ እያፈሰ ከማሰር አልፎ ፣ አንዳንዶች እየተገደሉ ሌሎች ደግሞ አሰቃቂ ድብደባ እየተፈጸመባቸው ነው። በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ የሚማር አንድ የመድረክ አባል እንደሆነ የሚታወቅ የ3ኛ አመት ተማሪ ግቢው ውስጥ ወድቆ ከተገኘ በሁዋላ …

ሚያዝያ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው ግንቦት 12/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት በሃያዎቹ የእድሜ ክልል የሚገኙት ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ እየሩሳሌም ተስፋው ፣ ፍቅረማርያም አስማማው እና ደሴ ካህሳይ ናቸው። ተከሳሾች “ኤርትራ ውስጥ መቀመጫውን ባደረገውና በሽብርተኝነት በተፈረጀው ግንቦት ሰባት ስር አባል ሆነው የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ወስነው …

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከመጪው ምርጫ ጋር በተያያዘ በተለይ በሰሜን የአገሪቱ ክፍል አብዛኛው ህዝብ ረብሻ ይነሳል ብሎ ያምናል። በዚህም የተነሳ ቀድም ብለው ገንዘባቸውን ባንክ ያስቀመጡ ሰዎች ገንዘባቸውን እያወጡ ለምግብ የሚውሉ የእህል ዘሮችን፣ ጨውና ሌሎችንም እቃዎች እየገዙ ነው። ወፍጮ ቤቶች ሰሞኑን ተጨናንቀው ታይተዋል። አቅም ያለው ቤተሰብ ለሶስት …

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በባህርዳር ከተማ በተካሄደው የብአዴን ማእከላዊ የዞን ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች ውይይት በቀጣይ ምን ማድረግ አለብን የሚለውን መመሪያ ለአባላቱ ባስተላለፈው የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት፣ ድርጅቱ በርካታ ችግሮች እንዳሉበት የድርጅቱ ልዩ ልዩ አመራሮች ተናግረዋል፡፡ የብአዴን ማእከላዊ ዞን ጽህፈት ቤቱ ሃላፊ ሲናገሩ የብአዴን አመራሮች በ1990 ዓ.ም ከታየው የጥገኝነት ዝቅጠት አንስቶ …

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ቤተእስራኤላውያን ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ በአገሪቱ ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍንና ዘረና የሆነው ፖሊስ እንዲያዝ ጠይቀዋል። ከሳምንታት በፊት የተካሄደው ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ደም አፋሳሽ ሆኖ ቢጠናቀቅም ፣ የአሁኑ ሰልፍ በሰላም ተጠናቋል። ከ185 ሺ በላይ ቤተእስራኤላውያን በእስራኤል ምድር የሚኖሩ ሲሆን ከዘረኝነት ጋር በተያያዘ የተለያዩ አድሎዎች ይፈጸሙባቸዋል። ከዚህ …

ሚያዝያ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ቴሬንሴ ሊዮንስ በዋሽንግተን ፖስት ላይ “ነጻና ፍትሀዊ ምርጫን ከኢትዮጵያ ጋር ምን አገናኘው?”በሚል ርዕስ ባሰፈሩት ጽሁፍ በመጪው ግንቦት 16 በ ኢትዮጵያ የሚካሄደው ምርጫ የመርሀግብር ማሟያ እንጂ ትርጉም ያለው እንዳልኾነ ገልጸዋል። ሂደቱ ከቅድመ-ምርጫ ጀምሮ ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ እንዳልነበር በስፋት ያብራሩት ጸሃፊው ”ዜጎች አዲስ መንግስት የማይመርጡበት ትርጉም የለሽ ምርጫ”ሲል …

በገዢው የኢህአዴግ መንግስት ላይ የትጥቅ ትግልን እያካሄዱ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ወደ ጥምረት እና ውህደት የሚወስዳቸውን ውይይት መጀመራቸውን ባለፈዉ አርብ ይፋ አደረጉ ። የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፥ የጋምቤላ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፥ የቤኒሻንጉል ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ፥ የአማራ ዴሞክራሲ ሀይል ነቅናቄ፥ እና የአርበኞች ግንቦት ፯ ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ የጥምረት ብሎም የውህደት ዉይይቶችን መጀመራቸውን አስታወቁ ። “ሀገርን እና ህዝብን …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ 22 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖረው የ25 ዓመቱ ሲሳይ ተሾመ በቅጽል ስሙ ገብሬ ያለፉትን 8 ዓመታት በቃሊቲና በዝዋይ እስር ቤቶች እየተመላለሰ አሳልፏል። በተለይ ወደ ዝዋይ እስር ቤት ከተላለፈ በሁዋላ ፣ ሃጎስ የተባለው የእስር ቤቱ ሃላፊ ” አንተ የነፍጠኛ ልጅ እንበቀለሃለን፣ በእኔ እጅ ነው የምትሞተው” እያሉ …

ሚያዝያ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢሳት በናይል ሳት ሲያስተላልፈው የነበረው ስርጭቱ በ2 ሳምንታት ውስጥ የኢህአዴግ አገዛዝ ባሳደረው የዲፕሎማሲ ጫና ከአየር ላይ እንዲወርድ ከተደረገ በሁዋላ፣ በአሞስ ስርጭቱን ቢጀምርም፣ ከአገሪቱ በሚለቀቀው ሞገድ እንደገና በመታፈኑ ከአየር ላይ እንዲወርድ ተደርጓል። ኢሳት ባለፉት 5 አማታት 8 የሳተላይት ጣቢያዎችን እየቀያየረ ስርጭቱን ሲያቀርብ ቆይቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢሳትን …