የዚምባቡዌ ምርጫና የፖለቲከኞቹ ዉዝግብ

በሁለት ሺሕ ስምንቱ የመጀመሪያ ዙር ምርጫ ግን አዲሱ ፖለቲከኛ አሮጌዉን መሪ አሸነፉ።ሰዉዬዉ ተንገዳገዱ ግን አልወደቁም።እንዳይወድቁ መጀመሪያ፥-በፀጥታ አስከባሪዎችና በቻንግራይ ደጋፊዎች መካካል በተደረገዉ ግጭት ከሁለት መቶ ባላይ ሰዉ መገደል፥ ቻንጋራይ ሳይቀሩ በመቶ የሚቆጠሩ መደብደብ፥ መቁሰል፥ መታሰር፥ ብዙ ሺሕ መሰደድ ግድ ነበረበት።