የኑሮ ውድነትና ወጣቶች

«ሌላው ቢቀር ጎመን እንኳን በጨው ነስንሼ ለመብላት እየተሳነኝ ነው» ሲል የኑሮ ውድነቱን መቋቋም እንዳቃተው ይገልፃል የኦሮሚያው ወጣት የቤተሰብ አስተዳዳሪ። የአዲስ አበባ ነዋሪው ወጣት የቤተሰብ አስተዳዳሪ ደግሞ «አምስት ለአስራ አንድ የአመጋገብ ስልት» የተለመደ ሆኗል ይለናል። ምን ማለቱ ይሆን?