የኢትዮጵያዉያን ሥደተኞች መከራ

ያለዉ እያስላከ ሲከፍል፥ የሌለዉን አጋቾቹ ይደበድቡ፥ ይደፍሩት ገቡ።ኢትዮጵያዊዉ ዱላ መደፈሩን መቋቋም አቅቶት ሞተ።«ከሞተ በሕዋላ አስከሬኑን እኛን ባሰሩበት ክፍል ዉስጥ ተዉት፥ አስከሬኑ ከበሰበሰ በሕዋላ ትላትሎች ሲወሩት አዉጥተዉ እንድጥለዉ አስገደዱን» ይላል ትረፍ ያለዉ ኤርትራዊ።