ርዕሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ፍራንሲስኩስ ከቫቲካን

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ርዕሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ፍራንሲስኩስ ከቫቲካን ባስተላለፉት የትንሣዔ በዓል የመጀመሪያ መልዕክታቸው በዓለም ላይ ሠላምን ለማስፈን የበለጠ ጥረት እንዲደረግ አሳሰቡ። በቫቲካኑ ቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ በተካሄደው መንፈሣዊ ስነ ስርዓት ላይ 250 ሺህ ግድም ምዕመናን ተገኝተዋል።