ውሳኔ የሚጠብቀው የኬንያ ምርጫ ውጤት

ራይላ ኦዲንጋ ምርጫው ውድቅ እንዲሆን የጠየቁበትን ምክንያት የሚያስረዳ ወደ 40 ገፅ በሚጠጋ ሰነድ በሂደት የተከሰቱ ማጭበርበሮችን የዘረዘረ ማመልከቻ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት አቅርበዋል ። በማመልከቻቸው የምርጫ ኮሚሽን ፣ የድምፅ አሰጣጡ ስርዓት እንዲቀየር መፍቀዱ ራሱ ህገ ወጥ ነው ሲሉ ተቃውመዋል ።