የሃበሻ የንግድ ማስተዋወቂያ በጀርመን

ኢትዮጵያንና ኤርትራውያን በብዛት የሚገኙት በታላላቆቹ የጀርመን ከተሞች ነው ። በተለያዩ ከተሞች መፅሄቱን በማከፋፈል ላይ የሚገኘው እዮብ እንደሚለው የኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ቁጥር ከፍተኛ በሆነባቸው ከተሞች የንግድ እንቅስቃሴያቸውም የዚያኑ ያህል ያደገ ነው ።