ግጭት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ
(Deutsche Welle) – ከትናንት ከሰአት በኋላ አንስቶ እስከ ዛሬ ጠዋት በቀጠለው ግጭት ተማሪዎች እንደቆሰሉና በተማሪዎች መኝታ ክፍሎች ላይም ጉዳት መድረሱን የአይን ምስክሮች መናገራቸውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ገልጾልናል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ4 ኪሎ ቅፅር ግቢ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት ተማሪዎች መጎዳታቸውና በግጭቱ የተጠረጠሩም መያዛቸው ተስምቷል ። ከትናንት ከሰአት በኋላ አንስቶ እስከ ዛሬ ጠዋት በቀጠለው ግጭት ተማሪዎች እንደቆሰሉና በተማሪዎች መኝታ ክፍሎች ላይም ጉዳት መድረሱን የአይን ምስክሮች መናገራቸውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ገልጾልናል ። አካባቢውም በፌደራል ፖሊስ ይጠበቅ እንደነበረም ተነግሯል ። ስለ ሁኔታው የአዲስ አበባውን ዘጋቢያችንን ዮሐንስ ገብረ እግዚ አብሔርን በስልክ አነጋግረናል።