ትኩረት ለዝዋይ ሐይቅ

የሐሮማያ ባህር በ1970ዎቹ ወደ ስምንት ሜትር ከፍታ ነበረው። ይህ ሐይቅ ለብዙ የአከባቢው አርሶ አደሮችና አሣ እስጋሪዎች የኑሮዋቸው ዋስትና ነበር። ንጹህ የመጠጥ ውሃም ለአከባቢው ከዚው ባህር ይገኝ እንደነበር ይነገራል። ከዚህም አልፎ ለአከባቢው ህዝብና ከሌላ ሥፍራ ለሚመጡም ጎብኚዎች የመዝናኛ ስፍራ ነበረ።