የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ

ዛሬ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ የተወሰኑ ሐሳቦች ከሌሎች ጎላ ብለው እየተደመጡ ነው። ሁለቱ እጩዎች የሀገሪቱ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ እና ተፎካካሪያቸው ሬፓብሊካዊው ሚት ሮምኒ ባለፉት የምርጫ ዘመቻ ሳምንታት በተለያዩ የሀገሪቱ ግዛቶች ከባድ ፍልሚያ አካሂደዋል። ቨርጂኒያም ከነዚሁ ግዛቶች መካከል አንዷ ነበረች።