አፍሪቃ መጪዋ ነብር?

የአፍሪቃ ኤኮኖሚ እያበበ በመሄድ ላይ መሆኑ በየጊዜው ሲነገር የቆየ ጉዳይ ነው። ከሣሃራ በስተደቡብ የሚገኙት ሃገራት ኤኮኖሚ በያመቱ ከአምሥት በመቶ በላይ ዕድገት እያሳየ መሆኑን የአፍሪቃ ልማት ባንክ ያመለክታል።