ቻርሎት-የዲሞክራቲክ ፓርቲ ጉባኤ

ጉባኤዉ በመጪዉ ጥቅምት ማብቂያ በሚደረገዉ ምርጫ ፕሬዝዳት ባራክ ኦባማ ዲሞክራቲኩን ፓርቲ ወክለዉ ለድጋሚ ዘመነ-ሥልጣን እንዲወዳደሩ እጩነታቸዉን በይፋ ያፀድቃል።ኦባማ ነገ ስታዲዮም ዉስጥ ሊያደርጉት የነበረዉ ንግግር ግን በአየር ጠባይ ለዉጥ ምክንያት አዳራሽ ዉስጥ እንዲደረግ ዛሬ ተወስኗል።