ነዳጅ ለሚቀይጡና ለሚቀሽቡ አዋጅ ተዘጋጀ

– በቅርቡ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ይቀርባል

ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡ የነዳጅ ውጤቶችን የሚቀይጡና የሚቀሽቡን የሚቀጣ አዋጅ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ሊቀርብ መሆኑ ታወቀ፡፡