በሸዋ በባሌ እና ወለጋ ክፍለሃገራት የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል::

በሸዋ በባሌ እና ወለጋ ክፍለሃገራት የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል::
‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ ‪#‎AddisAbabaMasterPlan‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎Oromo‬

በወለጋ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች የታጠቁ የወያኔ ወታደሮች ግቢያችንን ለቀው ይውጡልን ሲሉ ተቃውሞ ያሰሙ ሲሆን ጥያቄያቸውን ተሰሚነት ባለማግኘቱ ተጨማሪ ወታደሮች በግቢው ውስጥ ገብተው ተማሪዎችን ሲያባርሩ ሲደበድቡ እና ሲይዙ ተስተውሏል:: በርካታ ተማሪዎች ክፍኛ መጎዳታቸውን እና አንቡላንሶች ሲመላለሱ ነበር ተማሪዎች የዩንቨርስቲውን ግቢ በመልቀቅ ወደየቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ይገኛሉ:: ተቃውሞ በሚካሄድባቸው አከባቢዎች ኦሮሚኛ ተናጋሪ ያልሆኑ እና ስለ አከባቢው ምንም አይነት እውቀቱ የሌላቸው ወታደሮች በየአከባቢው እየሰፈሩ ይገኛሉ::

እንዲሁም በሰሜን ሸዋ ሂዳቡ አቦቴ ከተማ ተማሪዎች ተቃውሟቸውን እያሰሙ ይገኛሉ::በዚሁ ሰሜን ሸዋ ቱሉ ሚልኪ የወያኔ ወታደሮች የእርዳታ ድርጅቶችን መኪና በመጠቀም ቤት ክለቤት እየዞሩ ወጣቱ በማፈስ ላይ ይገኛሉ::በተጨማሪም በባሌ አጋርፋ ዳግም ተቃውሞ ተቀስቅሷል::በሰበታ መምሕር እና ደራሲ የሆነው ለሚ ግርማ በወያኔ ደህንነቶች የታፈነ ሲሆን ያለበት ቦታ እንደማይታወቅ ቤተሰቦቹ ተናግረዋል::ተቃውሞውን ወያኔ በቁጥጥር ስር አአዋልኩት ቢልም ከቀድሞው በበለጠ ሁኔታ ተፋፍሞ ቀጥሏል::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

Minilik Salsawi's photo.