በሸዋ በባሌ እና ወለጋ ክፍለሃገራት የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል::
በሸዋ በባሌ እና ወለጋ ክፍለሃገራት የኦሮሞ ተማሪዎች ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል::
#Ethiopia #Oromoprotests #AddisAbabaMasterPlan #MinilikSalsawi #Oromo
በወለጋ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች የታጠቁ የወያኔ ወታደሮች ግቢያችንን ለቀው ይውጡልን ሲሉ ተቃውሞ ያሰሙ ሲሆን ጥያቄያቸውን ተሰሚነት ባለማግኘቱ ተጨማሪ ወታደሮች በግቢው ውስጥ ገብተው ተማሪዎችን ሲያባርሩ ሲደበድቡ እና ሲይዙ ተስተውሏል:: በርካታ ተማሪዎች ክፍኛ መጎዳታቸውን እና አንቡላንሶች ሲመላለሱ ነበር ተማሪዎች የዩንቨርስቲውን ግቢ በመልቀቅ ወደየቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ይገኛሉ:: ተቃውሞ በሚካሄድባቸው አከባቢዎች ኦሮሚኛ ተናጋሪ ያልሆኑ እና ስለ አከባቢው ምንም አይነት እውቀቱ የሌላቸው ወታደሮች በየአከባቢው እየሰፈሩ ይገኛሉ::
እንዲሁም በሰሜን ሸዋ ሂዳቡ አቦቴ ከተማ ተማሪዎች ተቃውሟቸውን እያሰሙ ይገኛሉ::በዚሁ ሰሜን ሸዋ ቱሉ ሚልኪ የወያኔ ወታደሮች የእርዳታ ድርጅቶችን መኪና በመጠቀም ቤት ክለቤት እየዞሩ ወጣቱ በማፈስ ላይ ይገኛሉ::በተጨማሪም በባሌ አጋርፋ ዳግም ተቃውሞ ተቀስቅሷል::በሰበታ መምሕር እና ደራሲ የሆነው ለሚ ግርማ በወያኔ ደህንነቶች የታፈነ ሲሆን ያለበት ቦታ እንደማይታወቅ ቤተሰቦቹ ተናግረዋል::ተቃውሞውን ወያኔ በቁጥጥር ስር አአዋልኩት ቢልም ከቀድሞው በበለጠ ሁኔታ ተፋፍሞ ቀጥሏል::#ምንሊክሳልሳዊ
