የዛምቢያ የአፍሪቃ ዋንጫ ድል

በኤኩዋቶሪያል ጊኒና በጋቡን የጋራ አስተናጋጅነት ለሶሥት ሣምንታት ያህል የተካሄደው የዘንድሮው የአፍሪቃ እግር ኳስ ዋንጫ ፍጻሜ ውድድር ባለፈው ምሽት ሊበርቪል ላይ በዛምቢያና በአይቮሪ ኮስት ግጥሚያ ተፈጽሟል።