ወድቆ በተነሳው ባንዲራ! አትቀልዱብን!!

ተመስገን ደሳለኝ

…ባለመሆንና በመሆን መካከል

ሰው አይሻገረው፣ አለ ትልቅ ገደል።

የማይሆነው ነገር፣ ምን ጊዜም አይሆንም

የሆነውም ነገር ከቶ አይለወጥም።…

‹‹የኮሌጅ ቀን ግጥሞች›› (ተገኝ የተሻወርቅ-1950ዓ.ም) ፐ-እንዴት ያለ ግጥም ነው! ከተፃፈ ከ54 አመት በኋላም ሳይበርድ ሳይነፍስበት የእኝንዘመኑን ገላጭ ነው። ፕሮፓጋንዳውን ገላጭ ነው። የፖለቲካውን ቅጥፈት ገላጭ ነው። የስርዓቱን ጉምነት ገላጭ ነው። በአጠቃላይኢህአዴግን ገላጭ ነው። አጋላጭም ነው።