የዘንድሮው የሩሲያ ፓርላማ

በሩሲያ ትናንት በተካሄደው የፓርላማ ምርጫ ፤ የጠ/ሚንስትር ቭላዲሚር ፑቲን ፓርቲ ፣ «የተባበረች ሩሲያ» ብዙ ድምጽ አላገኘም ቢባልም፤ አሁንም በፍጹም ድምፅ ብልጫ ያለተጣማሪ ፓርቲ ማስተዳደር እንደሚችል ተገለጠ።