የዓለም ኤኮኖሚና የአዲስ ቀውስ ፍርሃቻ

የዓለም ባንክና የዓለምአቀፉ ምንዛሪ ተቋም የአይ.ኤም.ኤፍ ዓመታዊ የበልግ ጉባዔ የመንግሥታት የዕዳ ችግርና የአዲስ የዓለም ኤኮኖሚ ቀውስ ፍርሃቻ በጋረደው ሁኔታ ባለፈው ዕሑድ ተጠቃሏል። በተቋሙ ጥናት መሠረት የዓለም ኤኮኖሚ ዕድገት በያዝነውና በመጪው ዓመት አቆልቋይ እንደሚሆን ነው የሚጠበቀው።