ሰፊ ህዝባዊ ተቃውሞ በካይሮ

ግብፅ ውስጥ ከዛሬው የዕለተ ዓርብ (ጁምዓ) ጸሎትና ስግደት በኋላ አዲስ የተቃውሞ ማዕበል የተቀሰቀሰ ሲሆን፤ ከካይሮ በስተሰሜን 130 ኪሎሜትር ራቅ ብሎ በሚገኘው ፣ ካፍር ኧል ሼክ በተሰኘው ክፍለ ሀገር፣ በፖሊስና በታጠቁ የሙስሊም ወንድማማች ማኅበር ደጋፊዎች በተደረገ ግጭት 10 ሰዎች ሲሞቱ ከዚያ ቁጥራቸው ከፍ ያለ ቆስለዋል።