ሂላሪ ክሊንተን ሁሉንም ብለውታል፤ የቀረው ተግባሩ ነው

ታደሰ ብሩ
መለስ ዜናዊን የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ መሪ እንደሆነ አድርጎ በማቅረብ ሥራ ላይ የተሰማሩ የወያኔ ሹማምንትና ካድሬዎች፣ የዩ. ኤስ. አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚስ ሂላሪ ክሊንተን በአዲስ አበባ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ያደረጉትን ንግግር እንዴት እንደሰሙት በአእምሮዬ ሳሰላስል ቆይቻለሁ። እናም የክሊንተንን ንግግር ሳነብ አንዳንድ የማውቃቸው የወያኔ ሹማምንት ንግግራቸውን እንዴት እንደሰሙት በምናቤ እየቃኘሁ ነበር።